Our Side of the Story
Kanalga Telegram’da o‘tish
"To those who hurt and hunger” Since Oct 14, 2019 Here to help @DebbieTesfaye
Ko'proq ko'rsatish1 687
Obunachilar
+724 soatlar
+247 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
From a buffet of topics to write and wail about “በእንጨትም አልነካው ኧረ” የምል የሚመስለኝ is romantic love፣ እንዲያ እንደ ጅል ቀን ሌት ጉሮሮህ ድምፅህ ጠጉርህ ምናምን እያልኩ እንዳላላዘንኩ ምፅ!
The things we outgrow are so bizarre. I was having a conversation about it with someone and mid conversation I realised that experiencing life’s different shades intensely besides romantic love lessened it’s significance for me. It’s not that I hate it (I hope so lol), just that I’d rather be more excited and inspired by literally anything else.
ምናልባት ደግሞ it’s the need to be in control. All the days I wrote about love, I witnessed my control slowly ebbing away in my words and I was a walking open wound liable for more damage. Random thoughts I can tailor however I want to, I shape and carve them however I want them to sound. ያኛው ሶዬ ግን፣ the words immediately go “sorry debs, boss is here” and turn their backs to tell on me. ፅፌ ካበቃሁ ኋላ ነው the deep water I’m in የሚታወቀኝ። Yeppp maybe that’s it. As usual psychoanalysis አይፈቀድም ቴንክስ :).
Repost from Brown Empire
Day 4
መስታወት መስታወቴ…
መስታወቴ ፊት ስቆም ሶስት ነገር አስባለሁ።
አንድ
እህቶቼ የምላቸውን የአክስቴን ልጆች። ትንሽ ሆነን ቃል የተገባባነውን “ሳገባ ሚዜዎቼ እናንተ ናችሁ’ን” የምርም አግብቼ ሚዜዎቼ እስኪሆኑ የቆዩትን።
መስታወቴ የነሱ ትዝታ አለው። (መስታወቴ የነሱ ነበር።) መኖር ያዘናጋኝና፣ ናፍቆት ብልጭ ያደረገልኝ ሰሞን እንደትልቅ እህት የወደቅኩ ይመስለኛል።
አለ አይደል መቼም የምንራራቅ፣ ብንራራቅም የማንጠፋፋ ይመስለኝ ነበር። እዚህኛው የህይወቴ ክፍል ውስጥ ያሉት ሰዎች ማናቸው ደግሞ ዱቼ እና ቀጮ ሲሉኝ የሆነ ግማሽ ህይወቴ ቻው ሳይለኝ እንደሞተ ያህል ይሰማኛል። ቢሆንም አሁንም ባዶ ቦታ ትቶ እንደመቀመጥ ያህል “ሰው አለ” ብዬ የተውኩላቸው በኋላ የምንሞላው ቦታ ያስቀመጥኩላቸው ናቸው። የማልተዋቸው በመኖሬ ውስጥ ትርጉም ሳፈላልግ አንድ ብዬ የምቆጥራቸው ናቸው።
እናወራለን እኮ፣ የቻት ግሩፕ አለን፣ ርቀት ያፈዘዘው። ምን እየሰሩ ይሆን በዚች ቅፅበት የሚለውን ማወቅ የነበረብኝ ግን የማላውቀው ነገር ልብ ልቤን ሀላፊነቴን በአለመወጣት ይገርፈኛል። ያኔ የተራራቅንባቸውን ዘጠኝ አመታት እንደመስስና እንደአዲስ ካችአፕ እንደራረጋለን።
ከልጆቼ በፊት ልጆቼ፣ ከእህቶቼ በፊት እህቶቼ ፣ከጏደኞቼ በፊት ጏደኞቼ ነበሩ።
ደግሞ እኮ ሁለት በምንም በምንም የምስማማቸው my partner in crime’s ነበሩ። መስታወቴ እና የለጠፍንበት ስቲከሮች እነሱን ያስናፍቀኛል።
*
ሁለት
ፊቴን አየዋለሁ። የሰላሳ ቤቱ ፊቴ ደስ ይለኛል። ቆንጆ ነበርኩ ግን I wasn’t always this beautiful. Millennials understand this glow። ዘመን እና እድሜን የምወደው ለዚህ ነው። ለራስ ብዙ ያውቃል።
beauty is often a fragile illusion, a delicate arrangement of creams, oils, potions, and routines. ቢሆንም ፊቴን ብዙ ጣጣ አላበዛበትም። አለ አይደል ሳልቀባባ እንዳልደነግጥ። ቤት ቤት ሰውዬ፣ ውጪ እመቤት ከመሆን መሀል መሆንን እፈልጋለሁ። በጣም ተቀባብቼ ከአማረብኝ አንዱን መቀባት የምጠርግ፣ ጆሮጌጥ ወይ የአንገት ጌጥ የምመርጥ ለዘብተኛ አጊያጭ ነኝ።
ከውበት ጋ እሰጥ አገባ አልፈልግም። ስንት ችግር በፈላበት ግዜ ከመልክ ጋ አታካራ “የአለ ምንም ምክንያት ነው ድንገት ተነስታ ራሷን የሰዋችውን” ያመጣል። በውበት በኩል የተጫነብንን ቀምበር እንደፆታ የምናውቀው እውነታ ነው።
የእውነት ቆንጆ የሆንኩ የሚመስለኝ ከወንድሜ ሚስት ፍሬ እና ከጏደኛዬ ሰሚራ ጋ ስሆን ነው።
ቁንጅናን ሲገልጡ ከእኔ ፊቸር ይዋሳሉ። እኔም እንደጥኡም ልብወለድ ፈገግ ብዬ ልቤም ስኪፕ እያደረገች እንሰማቸዋለን።
“አፍንጫዋ እንዳንቺ ስልክክ ያለ፣ ከለሯ እንዳንቺ ንፅት ያለ፣ ጠይምምም ፣ ፀጉሯ እንዳንቺ ጫካ… “ምናምን ይሉኛል ሰልሆነች አንዷ ቆንጆ ሲያወሩ። ሳል’ዋሽ ውበቴ የሚነገረኝ በነሱ አፍ ይመስለኛል።
ምርምር እንደሚሻ ሁሉ “ለካ ቆንጆ ነሽ” “ግን እኮ ታምሪያለሽ” ምናምን ሳልባል ስለውበቴ የሰማሁት ከነሱ ነዉ ወይንም ያመንኩት እነሱን ነው። እንደአፍሮዳይት የውበት መለኪያም ስለሚያደርጉኝ፣ መስታወቴ ፊት ስቆም አይኔን ከነሱ እዋሳለሁ።
*
ሶስት
የእድሜ መስመሮች
ማበብና ማማርም እንዳለ ሆኖ የህይወት ቀጣይ የምእራፍ ዳናዋም የሚጀምረው ሰላሳዎቹ ውስጥ እንደሆነ ይሰማኛል። ጆዉ ላይናችን ሞር ዲፋይንድ ይሆናል፣ ጉንጫችን ስር ያለው የሳቅ መስመር ደመቅ ይላል፣ አይናችን ስር በስሱ መነስነስ የጀመሩ የሪንክል ጉዝጏዞዎች ትናንት እንደነበሩ ሁሉ በዝምታ ቦታ ይይዛሉ … አለአይደል እንደኔ ከአላተኮራችሁባቸው የማታይዋቸው አይነት ሆነው።
የአርባዎቼ ጠዋት ላይ ላለመደንገጥ፣ ህይወት በኋላ ልታደምቃቸው ዛሬ በስሱ ንድፍ ያወጣችበትን ፊቴን እዳስሰዋለሁ።
Thirties are quietly magnificent, People might call this the polite excuse we whisper to avoid naming the inevitability of aging. I have friends who extremely glorifies reality, that don’t let me mascara my gray hair on my forehead which makes me more age conscious, and make me want to punch their throats lol and yes, sometimes I feel the pangs, ከመሬት ተነስቼ. But more often, I glide past it, letting the thought pass like a cloud across a sky I do not own.
“what’s a habesha? I’m a visual learner”
It was a random TikTok post, of course I went through the comments. I found so many pretty girls. My heart was suddenly so full እያየኋቸው…most of them are diasporas. እንጃ እኔ ምን የሚሉት የሀገር ፍቅር እንዳፈነኝ…this የሀገር ልጅ መሆን ሌላውም ይሰማው ይሆን ወይስ እኛ ብቻ የተሰጠን ነው?
ቢልልን እና ፀድ ኑሮ ቢኖረን ሞላችንም ቤታችን ብንኖር፣ ድህነት አይኑ በጠፋ፣ የሞቱላት ሀገሪት መልኳን ባወቅነው፣ የሀገር ስሜት እና ሽታው ትዝታ ውስጥ ብቻ ባልቀረ፣ አሁንም እማዬ ታደርግ እንደነበረው random የቸገረው መንገደኛ ቤቴ አምጥቼ አኑሬ ሰርቶ ያጠራቀማትን ይዞ ሲሄድ “በል ይቅናህ” ብቻ ብዬ without asking anything in return እንደ ውለታ ሳልቆጥር ብሸኝ፣ to go back in time and have the chance to play ሰፈር ውስጥ ወጥቼ፣ ህይወት ተፈራ vivid description ውስጥ መኖር፣ እነ ሀይሉ መርጊያ የገባቸው የሀገር እና nostalgia ሚስጥር ቢገባኝ፣ ኧረ ኤድያ ብቻ ብዙ ተመኘሁ።
My issue with contemporary love songs is they’re blatantly focused on convincing everyone the entire purpose of being alive is to be approved/loved by someone else. Don’t even get me started on the painful lyrics.
እና ደግሞ the best you can do to spite people who thrive on riling you up is being unbothered like you’re blind and deaf.
Repost from Wonder Soul 💭
born to pole vault to conclusions but forced to understand where you are coming from
Repost from Inner Peace
Have you ever struggled with accessing mental health support?”
Take a moment to check in—share your thoughts in our quick questionnaire below.
"Nurturing Minds" 💬💚
Click Here
#MentalHealth #MentalWellness #FindYourPath #SupportLocal #EthiopiaMentalHealth #Wellbeing #SelfCare #ClarifyYourMind
Telegram | Instagram | TikTok | LinkedIn
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
