uz
Feedback
ኡስታዝ አክመል ኑራቶ ሙሳ (Ustaz Akmel Nurato Mosa) قناة أستاذ أكمل بن نوراتو بن موسى

ኡስታዝ አክመል ኑራቶ ሙሳ (Ustaz Akmel Nurato Mosa) قناة أستاذ أكمل بن نوراتو بن موسى

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በኡስታዝ አክመል ኑራቶ ሙሳ የሚሰጡ ደርሶች፣ ሙሃደራዎች እንዲሁም ጠቃሚ መልዕክቶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናሉን ሊንክ በመንካት ቤተሰብ ይሁኑ t.me/DaruNurChannel 🌐قناة تهتم بنشر دروس ومحاضرات وفوائد الأخ أكمل نوراتو موسى سدده الله ጥያቄና አስተያየት ካልዎት በዚህ ማስፈንጠርያ ይላኩ  @malekitmeqebya333

Ko'proq ko'rsatish
1 150
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+27 kunlar
+830 kunlar
Postlar arxiv
وقد قيل قديما نصف السلامة في التغاضي عن الناس ونصف الأدب في عدم التدخل فيما لا يعنيك ونصف الحكمة في الصمت ​የሰላም ግማሹ ሰውን ከመከታተል መቆጠብ ነው የአደብ ግማሹ በማያገባህ አለመግባት ሲሆን የጥበብ ግማሹ ዝምታ ነው ወደ አረብኛ ቀይረው

ማሳሰቢያ ለወላጆችመርከዝ አስ-ሱና (አሸዋ ቢላል መስጂድ) ​መርከዛችን በየዓመቱ አዳዲስ ተማሪዎችን በነዘርና በሂፍዝ (በሁለቱም ጾታዎች) ተቀብሎ እንደሚያስተምር ይታወቃል። ​በአሁኑ ሰዓት የምዝገባ ማስታወቂያ ሳይወጣና ትክክለኛው ጊዜ ሳይደርስ ልጆቻቸውን ለማስመዝገብ በአካልና በስልክ የሚወተውቱ ወላጆች በብዛት እየጠየቁ ይገኛሉ (ዛሬ ብቻ ከ5 በላይ ጥያቄዎችን አስተናግጃለሁ) ​ስለሆነም ይህ የሰኔ ወር አልቆ በሐምሌ ወር ውስጥ በማስታወቂያ እስከሚነገር ድረስ ወላጆች በትዕግሥት  እንድትጠባበቁ ባረከሏሁ ፊኩም። ልጆቻችሁ የመግቢያ ፈተናውን አልፈው መስፈርቱን ካሟሉ በመርከዙ እንደ አቅሙ የሚስተናገዱ ይሆናል ኢንሻ አላህ።

«የጀማዓ ሰላት ስታመልጠን የማይሰማን የልብ ሞት» قال حاتم الأصم رحمه الله تعالى مصيبة الدين أعظم من مصيبة الدنيا ولقد ماتت لي بنت فعزاني أكثر من عشرة آلاف، وفاتتني صلاة الجماعة فلم يعزني أحد  مفتاح التأهب لدار القرار: ( 30 ) 📜 ትርጉም፦ ​ታላቁ ዓሊም ሐቲም አል-አሰም (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦ ​በዲን (በመንፈሳዊ ሕይወት) ላይ የሚደርስ መከራ በዱንያ (በምድራዊ ሕይወት) ላይ ከሚደርስ መከራ እጅግ የላቀና የከበደ ነው ይኸውላችሁ አንዲት ሴት ልጄ በሞተች ጊዜ ከዐስር ሺህ በላይ ሰዎች መጥተው አጽናኑኝ  ነገር ግን አንዲት የጀማዓ ሰላት አምልጦኝ በነበረበት ወቅት አንድም ሰው መጥቶ ያጽናናኝ ወይም ሐዘን የገለጸልኝ አልነበረም።" ​ልብ የሚነካ ማጠቃለያ ​ይህ ንግግር በጀማዓ ሰላት ላይ ሊኖረን የሚገባውን ንቃትና ጥንቃቄ በብርቱ ያስታውሰናል የቅርብ ሰው በሞት ሲለይ በምድራዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ስብራት ሆኖ ይታየናል፤ ሰዎችም በዙሪያችን ከበው ያጽናኑናል ነገር ግን ከዚያ በላይ ትልቅ ዋጋና ምንዳ ያላት የጀማዓ ሰላት ስታመልጠን በነፍሳችን ላይ ምን ያህል ታላቅ መከራና ኪሳራ እየደረሰባት እንደሆነ ልብ አንለውም።

قَالَ يَحْيَى بْنُ مُعَاذٍ دَوَاءُ القَلْبِ خَمْسَةُ أشْيَاءَ قِرَاءَةُ القُرْآنِ بِالتَّفَكُّرِ وَخَلَاءُ البَطْنِ وَقِيَامُ اللَّيْلِ وَالتَّضَرُّعُ عِندَ السَّحَرِ، وَمُجَالَسَةُ الصَّالِحِينَ حلية الأولياء وطبقات الأصفياء" للحافظ أبي نعيم الأصبهاني (في ترجمة يحيى بن معاذ الرازي).

መርከዝ አስ-ሱና (አሸዋ ቢላል መስጂድ) ​ለነዘርና ለሂፍዝ የተቀበላቸውን ተማሪዎች የትምህርት ዘመን ማጠናቀቂያን አስመልክቶ ለመጨረሻው ፈተና ብቁ ለማድረግ፤ ከሁለት ወር በላይ በተከታታይ ሲሰጥ ከነበረው ፈተና የተቀነጨበ።  

የትዳር ህይወትን በከፍተኛ ሁኔታ ከሚጎዱ ነገሮች ውስጥ አንዱ የሌላውን ቤተሰብ ማራቅ ነው። #ለምሳሌ ሚስት የራሷ ቤተሰቦች ሲመጡ ጠብ እርግፍ ብላ በደስታ እያስተናገደች፣ የባሏ ቤተሰቦች ሲመጡ ግን የሚደብራት ከሆነ በትዳራቸው ውስጥ የማይጠገን ስንጥቃት ይፈጥራል። ስለዚህ ሰላማዊ ግንኙነት ይኖረን ዘንድ በራሳችን ላይ እንዲሆን የማንፈልገውን ነገር በሌሎች ላይ ልናደርግ አይገባም። ኢብን ሙነወር

የሰሞኑ የድሬደዋ ሙቀት ጥፉ ጥፉ ያስብላል አላህ ሆይ እንቅልፋችን ጤናችን ታውከዋል አንተህ ድረስልን

የዛሬው የጁምዓ ኹጥባችን ለአኺራው ሲል ዱንያውን ስለሸጠው ወጣት፣ ስለ መጀመሪያው የእስልምና አምባሳደር ሙስዐብ ቢን ዑመይር ( رضي الله عنه) ታሪክና መስዋዕትነት የሚዳስስ ይሆናል  

የአንዳንድ ክልል ፕሬዝዳንቶች ነገር እጅግ አጃኢብ ነው ለበቀል ብሔርን ከብሔር ሃይማኖትን ከሃይማኖት ሊያባሉ በስልጣን ወንበር የተቀመጡ ይመስላል ስራቸው ደግሞ የመንግስት ጋርድ ይመስል ከመንግስት ጀርባ መገተር ውስጣቸው ነው ወይ ማስተዳደር አይችሉ ወይ ንግግራቸው አያምር የህዝባቸው ስቃይና መከራ ምንም የማይመስላቸው ክፉ ናቸው። ​በሚያስተዳድሩት ክልል ውስጥ የሆነ አስከፊ ነገር ሲከሰት እንኳ ተሳስተው መግለጫና ማብራሪያ የማይሰጡ እንዲህ አይነት መሰሪና ክፉ አስተዳዳሪዎች እያሉ እንዴት ሰላም ይገኛል?"

«ከፈጣሪ ጋር የተደረገ የሌሊት ሹክሹክታ» صَلَّى الْإِمَامُ أَبُو حَنِيفَةَ النُّعْمَانُ -رَحِمَهُ اللَّهُ- صَلَاةَ الْعِشَاءِ يَوْمًا خَلْفَ مُؤَذِّنِ الْمَسْجِدِ، فَقَرَأَ الْمُؤَذِّنُ سُورَةَ الزَّلْزَلَةِ، فَلَمَّا قُضِيَتِ الصَّلَاةُ وَخَرَجَ النَّاسُ مِنَ الْمَسْجِدِ، لَمْ يَبْقَ غَيْرُ الْإِمَامِ أَبِي حَنِيفَةَ وَالْمُؤَذِّنِ. ​يَقُولُ الْمُؤَذِّنُ: فَنَظَرْتُ لِأَبِي حَنِيفَةَ وَهُوَ جَالِسٌ يَتَفَكَّرُ وَيَتَنَفَّسُ، فَقُلْتُ فِي نَفْسِي: أَقُومُ لَا يَنْشَغِلُ قَلْبُهُ بِي، فَخَرَجْتُ مِنَ الْمَسْجِدِ وَتَرَكْتُ الْقِنْدِيلَ وَلَيْسَ فِيهِ إِلَّا زَيْتٌ قَلِيلٌ. ​ثُمَّ جِئْتُ وَقَدْ طَلَعَ الْفَجْرُ وَهُوَ لَا يَزَالُ فِي مَجْلِسِهِ يَقُولُ: «يَا مَنْ يَجْزِي بِمِثْقَالِ ذَرَّةٍ خَيْرٍ خَيْرًا، وَيَا مَنْ يَجْزِي بِمِثْقَالِ ذَرَّةٍ شَرٍّ شَرًّا، أَجِرْ عَبْدَكَ مِنَ النَّارِ، وَأَدْخِلْهُ فِي سَعَةِ رَحْمَتِكَ». ​قَالَ الْمُؤَذِّنُ: فَدَخَلْتُ فَإِذَا الْقِنْدِيلُ مَا زَالَ يَزْدَهِرُ (يَشْتَعِلُ)، فَقَالَ الْإِمَامُ أَبُو حَنِيفَةَ: «تُرِيدُ أَنْ تَأْخُذَ الْقِنْدِيلَ؟» -وَهُوَ يَظُنُّ أَنَّهُ لَا يَزَالُ فِي وَقْتِ الْعِشَاءِ- فَقُلْتُ: لَقَدْ طَلَعَ الْفَجْرُ يَا إِمَامُ! ​فَقَالَ أَبُو حَنِيفَةَ: «اكْتُمْ عَنِّي مَا رَأَيْتَ»، وَرَكَعَ رَكْعَتَيْنِ، وَجَلَسَ لِيُصَلِّيَ الْفَجْرَ مَعَنَا بِوُضُوءِ الْعِشَاءِ، وَلَمْ أَتَحَدَّثْ بِالْقِصَّةِ لِأَحَدٍ حَتَّى مَاتَ الْإِمَامُ. ​(تَارِيخُ بَغْدَادَ 13/355) ትርጉም ​የኢማም አቡ ሐኒፋ ልብ የሚነካ ምሽት! ​አንድ ቀን ኢማም አቡ ሐኒፋ (አላህ ይዘንላቸውና) ከመስጂዱ ሙአዚን ጀርባ የዒሻእ (የማታ) ሶላትን ሰገዱ ሙአዚኑም በሶላቱ ላይ አዝ-ዘልዘላ (ምድር በኃይል ስለምትንቀጠቀጥበት ዕለት የሚያወሳውን) ሱራ ቀራ ሶላቱ ተጠናቆ ሰዎች ሁሉ ከመስጂዱ ወጥተው ሲሄዱ ከኢማሙ እና ከሙአዚኑ በስተቀር ማንም አልቀረም ነበር። ​ሙአዚኑ ታሪኩን እንዲህ ሲል ያስታውሳል ​ወደ ኢማም አቡ ሐኒፋ ተመለከትኩ እርሳቸውም ተቀምጠው በጥልቅ እያስተነተኑና በሐዘን እየተነፈሱ  ነበር በውስጤ እኔ እዚህ ከቆምኩኝ ሐሳባቸውን እበታትነዋለሁ ብዬ አሰብኩና ከመስጂዱ ወጣሁ ስወጣም በውስጡ ጥቂት ዘይት ብቻ የቀረውን ቀንዲል (ኩራዝ) እንደበራ ትቼው ሄድኩ   ​በኋላ ላይ ተመልሼ ስመጣ የፈጅር (የንጋት) ወቅት ደርሶ ነበር እርሳቸው ግን አሁንም በዚያው በተቀመጡበት ቦታ ላይ ነበሩ እንዲህ እያሉ አላህን ይማጸኑ ነበር ​የአንዲት ቅንጣት ያህል በጎ ለሠራ ሰው በጎ ዋጋን የምትከፍል የቅንጣት ያህል ክፉ ለሠራ ሰውም ተገቢውን ቅጣት የምትሰጥ ጌታ ሆይ ባሪያህን ከእሳት  ጠብቀው በሰፊው እዝነትህም ውስጥ አስገባው።'"   ​ወደ መስጂዱ ስገባ ያ ቀንዲል (ኩራዝ) አሁንም እንደበራና ብርሃን እየሰጠ ነበር ኢማሙም እኔን ሲያዩኝ አሁንም በዒሻእ ክፍለ ጊዜ ውስጥ ያሉ መስሏቸው መብራቱን ልትወስደው መጣህ እንዴ አሉኝ ​እኔም ኢማም ሆይ እኮ ፈጅር ደርሷል አልኳቸው ​ኢማሙም ያየኸውን ነገር ለማንም እንዳትናገር (ደብቅልኝ) አሉ ከዚያም የፈጅርን ሁለት ረከዓ ሱና ሰገዱና በዚያው በዒሻእ ሶላት ባደረጉት ውዱእ ከእኛ ጋር የፈጅርን  ሶላት ሰገዱ ኢማሙ እስኪሞቱ ድረስም ይህንን ድንቅ ገጠመኝ ለአንድም ሰው አልተናገርኩም ነበር ​(ታሪኩ የተወሰደው ከታሪኽ ባግዳድ ቅፅ 13/355)  

የዛሬው ኹጥባ ርዕስ فِي أَيَّامِ التَّشْرِيقِ وَشُكْرِ النِّعَمِ وَالْحَذَرِ مِنَ الْغَفْلَةِ وَالْمَعَاصِي በአያሙ-ተሽሪቅ ቀናት ውስጥ ስለ መገኘት፣ ጸጋዎችን ስለ ማመስገን እንዲሁም ከመዘንጋት እና ከወንጀሎች ስለ መጠንቀቅ።

بمناسبة عيد الأضحى المبارك أتقدم إليكم بأصدق والتهاني وأطيب الأماني سائلًا المولى عز وجل أن يتقبل طاعتكم، ويجعل أيامكم كلها أفراحًا ومسرات. عيدكم مبارك وسعيد! እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-አድሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በዓሉ የሰላም የጤና እና የደስታ ይሁንላችሁ ዒድ ሙባረክ

እንደ ሸሪዓ ብይን (حكم) የአክሱም ሙስሊሞች በሶስት አይነት ሊታይ ይችላል ሁለቱን ማድረግ እስከቻሉ ሶስተኛውን ከመረጡ ከባድነው