uz
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Ko'proq ko'rsatish
638
Obunachilar
-224 soatlar
-57 kunlar
-1130 kunlar
Postlar arxiv
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ግንቦት ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ጻድቅ_ለታላቋ_ለሰላም እናት #ለቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ ዲያብሎስን ማርልኝ ብላ ለጠየከችበት፤ #ከቅዱስ_ሚካኤል ጋር ከሲዖል #ዐሥር_ሺህ_ነፍሳት ለአወጡበት በዓልና ለልደቷ በዓል፣ #ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ለሥጋቸው ፍልሰት ካዐረፉ ከ57 (56) ዓመት በኋላ ከደብረ አስቦ ወደ ገዳማቸው ደብረ ሊባኖስ ለፈለሰበትና በአባታችን ተክለ ሃይማኖት መንበር ለተሾሙ መምህራን ዐሥራ ሰባተኛ ቁጥር ለሆነው ለደብረ ሊባኖስ መምህር ለአባ አብርሃም ለዕረፍት፡ በሰላም አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ ክርስቶስ ሠምራ የአምላክ አገልጋይ ይበራል ስምሽ ዛሬም በምድር ላይ መመረጥ በእግዚአብሔር እንደ በትረ ማርያም ለሰው ልጅ ጸልዪ እስከ ዘለዓለም አዝ............................................ በትረ ማርያም ብሎ ክርስቶስ ሠምራ ስሟን ለወጠላት ክርስቶስ ሠምራ ሚካኤል ቀኝ እጅ ረዳት ቢያደርግላት ዐሥር ሺህ ነፍሳት ክርስቶስ ሠምራ ማረከች ከሲኦል ክርስቶስ ሠምራ ባዶ ሆነ ቤቱ አፈረ ሳጥናኤል የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ መዝሙር። ስንኙ ይቀጥላል                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ፦ በሸዋ ከፍለ አገር በቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌዬ የተባለች አገር ነበረች ይህችም የእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ አገሯ ናት። በዚህም አገር በወርቅና በብር በሐር እና በልዩ ልዩ ልብስ በወንድና በሴት አገልጋዮች በፈረስና በበቅሎ የከበረ አንድ ስሙ የታወቀ ሰው ነበር። የዚህ ሰው ስሙ ቅዱስ ደረሳኒ ሲሆን የሚስቱም ስም ቅድስት ዕሌኒ ይባላል ሁለቱም ባልና ሚስቱ እግዚአብሔር የሚፈሩ ደጋግ ሰዎች ስለነበሩ በጎ ሥራቸው በዓለም ሁሉ የታወቀ ነበር። እሊህም ሰዎች በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠችና የከበረችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ግንቦት 12 ቀን ወልደው በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ አሳደጓት ከዚያም የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓቶችንም ሁሉ አስተማሯት። ባደገችና ለአቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ የንጉሥ ባለሟል የሆነ ትውልዱ፤ ነገዱ ከአባ ፃሠርጓ ወገን የሆነ ለኢየሱስ ሞዓ ልጅ ለሠምረ ጊዮርጊስ በሕግ አጋቧት። እሱም በዚህ ዓለም ገንዘብ በጣም የከበረ ከመሆኑም በላይ በይበልጥ መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ነበረ። ከደም ግባቷ የተነሣ ሙሽራይቱ ማለት እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን እጅግ አድርጎ ወደዳት። አሟቷ ኢየሱስ ሞዐም ይህች ብላቴና "በታላቅ ቁም ነገር የተመረጠች ነች" በማለት ትንቢት ይናገርላታል ስለዚህ እንደ እመቤቱ አድርጐ ያከብራት ነበር። ከዚህም በኋላም ለሕጋዊ ባሏ ለሠምረ ጊዮርጊስ ዓሥራ አንድ ልጆች ወለደችለት ከነዚህም መካከል ዘጠኙ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ። ልጆችዋንም ሕገ እግዚአብሔርን እያስተማረች በክብር በሥርዓት አሳደገቻቸው። ❤ በዚያን ዘመን የእግዚአብሔር ባለሟል የሚሆን ዓፄ ገብረ መስቀል የሚባል የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበር። እርሱም ዝናዋን ሰምቶ ሥነ ምግባሯን ተመልክቶ ይልቁንም በሷ ላይ ያደረውን ኃይለ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ስለገለጸለት እጅግ አድርጐ ይወዳትና ያከብራት ነበር። ከዕለታት ባንድ ቀን በጸሎትሽ አስቢኝ በማለት በራሱ በንጉሡ ቤተ መንግሥት ከሚያገለግሉ አገልጋዮች ወይም ሠራተኞች መካከል እንዲያገለግሏት 174 አገልጋዮች ላካላት። ዳግመኛም ፈረስና በቅሎ ከነሥራታቸው እንደዚሁም ለነሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማ ላከላት። ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ለዓላማዊ ዕንቅፋት ወይም ከንቱ ውዳሴ ይሆንብኛል በዚያውስ ወርቁ ጌጡ ልብሱ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ለቤተ ክርስቲያን መባዕ ይሰጣል እኒህን አገልጋዮች ግን ምን አደርጋቸዋለሁ በማለት ወደ እግዚአብሔር እያመለከተች ቆየች። ❤ ከአገልጋዮችዋ መካከል ምግባሯ የከፋ የምታናድዳትና የምታበሳጫት አገልጋይ ነበረች። ከዕለታት በአንድኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ በጣም ተበሳጨችና በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት። ያም እሳት ትንታግ በአገልጋይዋ ጉረሮ ድረስ ዘለቀና ገደላት። በዚህን ጊዜ ቤተሰቦችዋ መጥተው የአገልጋይቱን አስከሬን ወደሌላ ክፍል ወሰዱት። ብፅዕት ክርስቶስ ሠምራም ደንግጣ ካለችበት ቤት ውስጥ ወደ ሌላው ክፍል ገባችና ወደ ሰማይ አቅንታ "ወይኔ ወዮልኝ ወዮታ አለብኝ የካህን ሚስት ስሆን ነፍስ ገዳይ ሆኛለሁና። ሰውስ ምን ይለኛል ለነፍሴስ ምን እመልስላታለሁ ከእግዲህ ከክርስቲያን ወገን ልቆጠር አይገባኝም በደሌንስ እንደምን አድርጌ ልሸሸሽጋት እችላለሁ" እያለች አለቀሰች። ❤ ከዚህ በኋላ እንዲህ ስትል ለእግዚአብሔር ብፅዓት አደረገች "አቤቱ ይህችን በእኔ እጅ የሞተችውን አገልጋይ ነፍስዋን ከሥጋዋ አዋህደህ ብታሥነሣልኝ ልጆቼን ቤቴን ንብረቴን ትቼ ባለ ዘመኔ ሁሉ አንተን እከተላለሁ። አንተን ከመከተል ከቶ ወደኋላ አልልም። ለሰውነቴ ጌጥ ወይም ግርማ ሞገስ የሚሆናት ወይም የሚሞቃት ልብስ ከቶ አልለብስም ሥጋዬን የሚያረካ ምግብም አልመገብም። አቤቱ ጌታዬ ሆይ ጸሎቴን ስማኝ ልመናዬም በፊትህ ፈጥኖ ይድረስ አቤቱ ፊትህን ከኔ ከባሪያህ አትመልስ"። እንዲህ እንዲህ እያለች በልቅሶና በኀዘን ለብዙ ሰዓት ከጸለየች በኋላ ድካም ተሰማትና ዕረፍት አደረገች። ከዚህ በኋላ ቤተሰቦችዋ እስዋ ወዳለችበት ክፍል መጥተው "እመቤታችን ሆይ ሙታ የነበረችው አገልጋይሽ በእግዚአብሔር ኃይልና በአንቺ ጸሎት ተነሥታለችና ደስ ይበልሽ" አሏት። በዚህ ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ደስ እያላት ሙታ የነበረችው አገልጋይ ካለችበት ቦታ ደረሰችና ሕይወት አገኘቻት ከዚያም ቃሏን ከፍ አድርጋ "ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከኔ ከባሪያው ያላራቀ ፈጣሪ ይክበር ይመስገን" ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔር አመሰገነች። ❤ ከዚህ በኋላ አስቀድሞ ከአፏ የወጣውን ከአንደበቷ የተነገረውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኵስናዋን ማለት ቆቧን ቀሚሷን አጽፏን መታጠቂያዋን አዘጋጀች። ቤተሰቦቿና አገልጋዮቿም "እመቤታችን ሆይ ይህ የምታዘጋጂው የምናኔ ልብስ ለምንሽ ነው ወይስ ለማን ነው የምታዘጋጂው" አሏት። እርሷም "ሃይማኖት ያስተማሩኝ አባቴ ልብስ አልቆባቸዋል ሲሉ ሰምቼ ለሳቸው ነው የማዘጋጀው" አለቻቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ከዕለታት ባንደኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ አገልጋዮቿን ወደ ቤተ ክርስቲያን እንሄድ ዘንድ ተዘጋጁ አለቻቸውና እነሱም አሺ በጎ ብለው አጅበዋት ወደቤተ ክርስቲያን ሄዱ። ከዚያም እንደደረሱ "በሉ እንዲህ እኔ ከዚህ ጥቂት እቆያለሁና እናንተ ወደ ቤታችሁ ተመለሱ ለኔ ይህች አንድዲት አገልጋይና ይህ ሕፃን ልጅ ብቻ ይበቁኛል አለቻቸው። በዚያኑ ጊዜ አገልጋዮቿ እጅ እየሱ ወይም እየተሰናበቱ ወደቤታቸው ተመለሱ። ከዚያም ከዳዊት መዝሙር "ልቤ ጽኑ ነው አቤቱ ልቤ ጽኑ ነው እግዚአብሔርን ፈጽሜ አመሰግነዋለሁ እግዚአብሔር የደህንነቴ መብራት ስለሆነ ምን ያስደነግጠኛል እግዚአብሔር የሕይወቴ መተማመኛ ነው ምንስ ያስፈራኛል የሚለውን እየጸለየች የሚያልፈን ዓለም በማያልፈው ዓለም ለመተካት ወይም ለመለወጥ አውጭኝ እግሬ ብላ ገሠገሠች። ያ በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግር ከመንገዱ ብዛት እንደዚሁም ከቅርቅፍቱና ከእንቅፋቱ የተነሣ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሙ እንደጒርፍ ውሃ ይወርድ ነበር።

❤ ከዚህም በኋላ እስከ ማግሥት ከወህኒ ቤት ጨምራትና በማግሥቱ ወደ ሸንጎ አውጧት እርሱም "ለአማልክት ሠዊ" አላት። ቅድስት ኤፎምያም ሣቅ ብላ "እኔስ ለማይናገሩ ደንጊያዎች አልሠዋም" አለችው። አንቲሂጳጦስም ሰምቶ ሥጋዋን ይገፉ ዘንድ መቃጥን ያላቸው አራት ደንጊያዎችን እንዲያመጡ አዘዘ። ሁለተኛም አራዊት ከአሉበት ኵሬ ውስጥ እንዲጨምሩዋት አዝዞ ከዚያ ወረወሩዋት። አራዊት ግን ተሸክመው አውጥተው ከውኃው ዳር አቆሙዋት። ደግሞ ስለታሞች ደንጊያዎችንና ሰይፎችን በመሬት ውስጥ እንዲተክሉ ተቆራርጣ ትሞት ዘንድ በላያቸው እንዲያስሮጡዋት አዘዘ ሩጣም ተሻገረች ምንም የነካት የለም። ደግሞም በግለቱ ታር ዘንድ ደብድበው ከብረት ምጣድ ውስጥ እንዲጨምሩዋት አዘዘ ግን ምንም ምን አልነካትም። ❤ ከዚህ በኋላም አራዊትን ሁሉ ድባትንም ሰበሰበ። በላይዋም ወሰዱዋቸው አንበሶችም እግርዋን ሳሙ አንዲትም አውሬ ተሸብራ እግርዋን ነከሰቻት ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ "የተመሰገንሽ ኤፎምያ  ወጥተሽ ወደ ከበረ ቦታ ነዪ" እንዲህም ገድሏን ምስክርነቷን ግንቦት11 ቀን ፈጽመች እናትና አባቷም መጥተው ገንዘው በአዲስ መቃብር ውስጥ ቀበሩዋት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቷ ቅድስት ኤፎምያ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት11 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለበፍኑትዮስ_ዘአሕረመ አፈ። ከመ ኢይብላዕ ብሱለ እንበለ ሐመልማል ዘልፈ። ፍትወተ ዓለም ፍጹም እስከ እምልቡ ገደፈ። በመዋዕለ ክብሩ ኢለወጠ ዐጽፈ። እምነ ይለብስ ወትረ ሠቀ ፀጉር ገዚፈ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_11።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት፲፩ (11) ቀን። ❤እንኳን #ለባሌ_መምህር_ለአባ_አሴር ሰማዕትነት ለተቀበሉት ለዕረፍታቸው በዓል፣ #ለቅዱስ_ዮስጦስ_ለሚስቱ_ቅድስት_ታውክልያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ በዲዮቅልጥያኖስ መንግሥት ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበለች #ለታላቋ_ሰማዕት_ለቅድስት_ኤፎምያ ለዕረፍቷ በዓል፣ ለከበረ ኤጲስቆጶስ #ለአባ_በፍኑትዮስ ለዕረፍት በዓልና #ለቅድስት_አናሲማ ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከኤስድሮስ_እናት_ከቅድስት_ሶፍያና_ከእኅቱ_ኤፎምያ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከአባ_በኪሞስና_ከአብላዲን ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የባሌ_መምህር_አባ_አሴር፦ ይኸውም በንጉሥ ወናግ ሰገድ ዘመን ወደ ኢየሩሳሌም ወርዶ ሳለ መጀመሪያ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡ። በኋላም የጌታችን እግር በቆመበት በኢየሩሳሌም መግቢያ በእሳት አቃጠሉት። የባሌ መምህር አባ አሴር በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ዮስጦስና_ሚስቱ_ቅድስት_ታውክልያ፦ በየካቲት ዐሥር እንደ ተጻፈ የእስክንድር ገዢ እርስበርሳቸው ከአለያያቸው በኋላ ቅድስት ታውክልያን ወደ አገረ ፃ ወሰዱዋት። በአገረ ፃ መኰንንም ፊት የመኰንነ እስክንድርያን መልእክት በአነበቡ ጊዜ "መንግሥታቸውን ትተው እንዴት ከመንግሥታቸው ሞትን መረጡ" ብሎ አደነቀ። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሸነገላት ብዙ ታላላቅ ቃል ኪዳኖችንም ገባላት። የከበረች ታውክልያም "እኔ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር መንግሥቴን ተውኩ ከልጅነት ባሌም ተለየሁ በልጆቼም አልተጽናናሁም ለመሆኑ አንተ የምትሰጠኝ ስጦታ ምን ያህል ነው" ብላ መለሰችለት። ይህንንም ሰምቶ ታላቅ ግርፋት እንዲገር ፉዋት አዘዘ የሥጋዋም ቊርበት እስከሚቆራረጥ ገረፋዋት። ከዚህ በኋላም ከእሥር ቤት አስገቡዋት የእግዚአብሔርም መልአክ ተገለጠላትና ቊስሎቿን አዳናት። አሥረኞችም አይተው አደነቁ ብዙዎቹም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ዐረፉ። ❤ የምስክርነቷ ፋጻሜ በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ለከበረች ታውክልያ ተገልጦላት አጽናናት ከክብር ባለቤት ጌታችንም የተሰጡዋትን ቃል ኪዳኖች ነገራት። በዚያን ጊዜም ራስዋን ግንቦት11 ቀን ይቆርጡ ዘንድ መኰንኑ አዘዘ የሕይወት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች። ምዕመናን ሰዎች መጥተው ለወታደሮች ብር ሰጥተው የቅድስቲቱ ሥጋ ወሰዱ በመልካም መግነዝም ገንዘው የስደቱ ወራት እስኪፈጸም በሣጥን ውስጥ አኖሩዋት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_በፍኑትዮስ፦ ይህም ከታናሽነቱ በአባ መቃርስ ደብር በአስቄጥስ ገዳም መነኰሰ ታላቅ ተጋድሎንም በመጋደል ብዙ ትሩፋትን ሠራ። አዘውትሮ ይጾም ነበረ ቅጠላቅጠልን ይባላል እንጂ በእሳት የበሰለ አይበላም በገዳም ውስጥም መጻሕፍትንና የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ተምሮ ቅስና ተሾመ በዚያም ሠላሳ አምስት ዓመት ኖረ። እነሆ ትሩፋቱና ጽድቁም በሁሉ ዘንድ ታወቀ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊላታዎስ ልኮ ወደ እርሱ አስመጥቶ ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾመው። ኤጲስቆጶስነትም ከተሾመ በኋላ ቅዳሴ በሚቀድስ ጊዜ ከልሆነ በቀር ከቶ ልብሱን አልለወጠም ቅዳሴውንም ሲፈጸም ከጠጒር የተሠራውን ማቅ ይለብሳል። ❤ እንዲህም የሚጋደልና የሚጸና የሚጸመድ ሁኖ ኖረ በዚህ ሁሉ ዘመንም ከመነኰሳት ጋራ ያገለግል ነበር በታመመ ጊዜም እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው። "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ኤጲስቆጶስነት ስለተሾምኩ ጸጋህን በውኑ ከእኔ ታርቃለህን?" ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም ወደርሱ መጥቶ "አስተውል ዕወቅ አንተ በገዳም ሳለህ በታመምክ ጊዜ የሚጐበኝህ የለም ወይም የሚአገለግልህና ለደዌህ መድኃኒትን የሚሰጥህ አታገኝም ነበር። ስለዚህ እግዚአብሔር የሚረዳህና ደዌውንም ከአንተ የሚያርቅልህ ሆነ። ዛሬ ግን እንሆ አንተ በዓለም ውስጥ ነህ በአንተ ዘንድ የሚጐበኝህና የሚአገለግልህ አለ ለደዌህም መድኃኒትን የምትሻውንም ምግብ ታገኛለህ" አለው። ❤ ይህም አባት በኤጲስቆጶስነት ሹመት ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ የሚያርፍበትም በቀረበ ጊዜ ካህናቱንና ዲያቆናቱን መምህራኑን ጠራቸው። የአብያተ ክርስቲያንናትንም ንዋየ ቅዱሳታቸውንና ገንዘባቸውንም ሁሉ ሰጣቸው እንዲህም አላቸው "ዕወቁ እኔ ወደ እግዚአብሔር እሔዳለሁና እንደሚገባም በመካከላችሁ እንደኖርኩ እናንተ ታውቃላችሁ። ለኤጲስቆጶስነት ሹመቴም እጅ መንሻ ከሚአመጡልኝ እንኳ አንድ ብር አላድ እንዳልሠወርኩ በፊቱ ልቆም ያለኝ የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በእኔ ላይ ምስክርን ይሁን አላቸው። ይህንም ሰምተው አለቀሱ ተሳለሙትም እንዲባርካቸውና በክብር ባለቤት ጌታችንም ዘንድ መራዳቱን እንዳይረሳ ለመኑት እርሱም ባረካቸው። "እግዚአብሔርም ያክብራችሁ እስከ መጨረሻዪቱም ሕቅታ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ያጽናችሁ" ይህንንም ብሎ ግንቦት11 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በፍኑትዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ትድረሰን አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_አናሲማ፦ ይቺም ቅድስት በደናግል ገዳም መንኵሳ ራስዋን እብድ አስመስላ ኖረች። በሌሊትም በጾምና በጸሎት ሥጋዋን በመቅጣት ራሷን ታሠቃያለች ሰዎችም በሚያዩዋት ጊዜ ራስዋን አእምሮዋን እንደሳተች ታስመስላለች መበለቶችም ይስድቧታል። ❤ እግዚአብሔርም ገድሏን ለአባ ዳንኤል ገለጠ። እርሱም ከደናግል ገዳም ሔዶ ትሩፋቷንና ገድሏን ሁሉ ለእመ ምኔቷ ነገራት እርሷም ለእኅቶች መነኰሳይት ነገራቻቸው በዚያችም ዕለት ወዲህ አከበሩዋት። እርሷም ስለ አዋረዱዋትና ስለአጐሳቈሉዋት እኅቶችን እያመሰገነች ደብዳቤ ጽፋ ትታ ከንቱ ውዳሴን በመጥላቷ ተሠውራ በሌሊት ወጥታ ወደ ዱር ሸሽች በዚያም ግንቦት11 ቀን በሰላም ዐረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።                              + + + ❤ #ሰማዕቷ_ቅድስት_ኤፎምያ፦ የዚችም የእናቷ ስም ቴዎድርስያኒ ነው እርሷም የክብር ባለቤት ክርስቶስን የምታምንና የምትፈራው ናት። ሰይጣንም ክርስቲያኖችን በማስገደድ ለጣዖት  እንዲሰግድ አንቲሂጳጦስም በአነሣሣው ጊዜ ይቺ ቅድስት ኤፎምያን ከብዙ ክርስቲያኖች  ጋራ አሥረው አመጡዋት። አንቲሂጳጦስም "ለአማልክት ሠዊ" አላት። እርሷም እኔ ከክብር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አልሠዋም የአባቶቼን ተስፋ ለማግኘት ልቤ የጸና ነውና" አለችው። ያን ጊዜ አንቲሃጳጦስ ተቆጥቶ ዐጥንቷ እንዲሰበር ሕዋሳቷ ሁሉ እንዲለያይ ከሠረገላ መንኰራኵር ውስጥ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ። የእግዚአብሔርም መልአክ አዳናት ሁለተኛም ነበልባሉ አርባ አምስት ክንድ ከፍ ከፍ እስከሚል እሳትን አንድደው ከውስጡ ይወረውሩዋት ዘንድ አዘዘ። በእሳቱ መካከልም ቁማ ጸለየች እየጸለየችም በደኅና ወጣች ብዙዎችም በጌታ አምነው በሰማዕትነት ዐረፋ።

❤ ንዑድ ክብር ቅዱስ ያሬድም ስውር ዋሻ ውስጥ ገብቶ ፈጣሪውን እግዚአብሔር እንዲህ በማለት ለመነው "መታሰቢያዬን የመምህሬን የጌድዮንን መታሰቢያ የሁላችንንም አባት የአዳምን መታሰቢያ ያደረገው እንግዲህ ዋጋው ምንድን ነው?" አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው "የክብር መቀውጫ አስቀምጠው ዘንድ በመንግሥቴ ማልኩልኽ በፍርድ ቀን ማለትም በዕለተ ምጽዋት ያለ ሐፍረት በግልጥ ከአንተ ጋራ ይለፍ" አለው። መታሰቢያህን ያደረገ የገድልኽንም መጽሐፍ የጻፈ ወይም ያጻፈ ንዑድ ምስጉን ክብር ነው፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጠዋለኹ፤ የክብር ዙፋንም አወርሰዋለኹ" አለው። ይህንንም ቃል ኪዳን ጌታችን ከሰጠው በኋላ በስሜን ከሚገኝ አንድ ገዳም በኅቡእ (በስውር) እስከ ዕለተ ምጽአት ይኖል ዕረፍቱ ይህ ነው። ከቅዱስ ያሬድ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎቱም ይማረን!። ምንጭ፦ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን ቅዱስ ያሬድና የቅዱስ ያሬድ ታሪክ ከሚሉት መጻሕፍት።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለይትፈሣሕ ልብ ዘየኀሦ ለእግዚአብሔር። ኅሥዎ ለእግዚአብሔር ወትፀንዑ። ወኅሡ ገጾ በኲሉ ጊዜ"። መዝ 104፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥7-17።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "መድኃኔ ገጽየ እግዚአብሔር ተወክፈኒ። እሴብሕ ለስመ አምላኪየ በማኅሌት። ወአዐብዮ በስብሐት"።  መዝ 68፥29-30። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 5፥15-21፣ ያዕ 5፥12-14 እና የሐዋ ሥራ 26፥24-30። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥1-7። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው ወይም የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ያሬድ ከሞት የተሰወረበት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ለሁላችንም ይሁንልን።

ተቀምጦ ዝማሬ መዋሥዕት የተባለውን መጽሐፍ ለሦስት ዓመት ከሦስት ወር ስላስተማረበት ይህም ቦታ ገዳም እስከ ዛሬ ድረስ የዝማሬና የመዋሥዕት ምስክር ቦታ ሆኖ ይኖራል። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ከአኵሱም ወደ ማይኪራህ አምርቶ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን በአካለ ነፍስ ከሶርያ አባ ሕርያቆስ ከብሕንሳ አምጥታ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ንባቡን እየነገሩት በዜማ እንዲደርስላት አድርጋለች። ከዚህም አያይዞ ለሥጋ ወደሙ ጸሎት የሚያገለግሉትን ንባቡ የሌሎች ሊቃውንት ድርሰት የሆኑትን ዐሥራ አራቱን ቅዳሴዎች በዜማ አዘጋጀ። ❤ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ጸለምት ሔዶ ምዕራፍ የተባለውን ድርሰቱን ደረሰ። ከዚህ በኋላ አገው፣ ፎገራ እና ወደ ሌሎችም ቦታዎች እየዞረ አስተማረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ በአኵሱም ወንበር ዘርግቶ፣ ጉባኤ አስፍቶ ደቀ መዛሙርቱን እያስተማረ ሲኖር በጾመ ፵ ሱባኤ ላይ ሳለ አንድ ቀን በምኵራብ ሰሞን ስለምናኔው እያስታወሰ በተመስጦ ሲዘምር የዜማው ጣዕም እንኳን ሌላውን ራሱን እጅግ ይመሥጠው ነበር። በጣዕመ ዝማሬው ተመሥጦ ሲያዳምጥ የነበረው ኢትዮጵያዊው ንጉሥ የዐፄ ገብረ መስቀል ዐይን ዐይኑን እየተመለከተ ሳይታወቀው በመስቀል ስላጢኑ (በበትረ መንግሥቱ ዘንግ) ጫፍ የቅዱስ ያሬድን እግር ወጋው። ቅዱስ ያሬድ ግን ከሰማያት የተገኘች ቃለ ማሕሌቱን እስኪፈጽም ድረስ ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ሕመሙ ሳይታወቀው ቀጠለ፤ ደሙም ያለማቋረጥ ፈሰሰ። ❤ ቅዱስ ያሬድ የጀመረውን በፈጸመ ጊዜ ንጉሡ ደንግጦ በትሩን ከቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ቢነቅለው ደሙ በኃይል ይፈስ ጀመር። ያን ጊዜ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል የቅዱስ ያሬድን ትዕግሥት ባለ ጊዜ በመደነቅ፣ በመገረምና በመደንገጥ ዝም በማለት አፉን ይዞ ቆመና ምድራዊ ዋጋ የሚፈልግ መስሎት "ካህን ያሬድ ሆይ የምትፈልገውን ዋጋ ጠይቀኝ" አለው። ቅዱስ ያሬድ መልሶ "የፈለግኹትን እንዳትከለክለኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ" አለው። ንጉሡም የጸና ቃል ኪዳን ለቅዱስ ያሬድ ገባለት። ቅዱስ ያሬድም "ከዚህ ሐላፊ ዓለም ክብር ተለይቼ መናኝ ሆኜ እንድኖር ተወኝ አሰናብተኝ" ብሎ አሳብን ገለጸለት። ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ያሬድ ካህን የጠየቀውን እንዳይከለክለው ከአፉ የወጣውን መሐላ አስቦ በምናኔ አሰናበተው እንጂ ሊከለክለው አልቻለም። ❤ ቅዱስ ያሬድ ካህንም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ታቦት ወዳለችበት ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ሁለት እጆቹን በታቦተ ጽዮን ላይ አኑሮ "ቅድስት ወብፅዕት፣ ስብሕት ወቡርክት፣ክብር ወልዕልት አንቀጸ ብርሃን መዓርገ ሕይወት" ብሎ በደረሰው አንቀጸ ብርሃን ጸሎት እመቤታችንን አመሰገ። በዚህ ጊዜ እጁ በታቦተ ጽዮን ላይ ረቦ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ ስለነበር ከመሬት አንድ ክንድ ከፍ ከፍ ብሎ ይታይ ነበር። እስከመጨረሻው በከፍተኛ ቃል በዕዝል ዜማ እየዘመረ እግዚአብሔር እና እመቤታችንን ከአመሰገነ በኋላ እመቤታችን የቀና መንገድ እንድትመራውና እስከ ፍጻሜ ገድሉ ትረዳው ዘንድ በጸሎት ለመናት። እመቤታችንም መልሳ "ሰማያዊት ጽዮን ያደረግኻት መቅደሴን፣ በመዝሙር በማሕሌት ምስጋና የኪሩቤልና የሱራፌል ወገን ሰማያውያን ያደረግኻቸው ልጆቼ ካህናትን እንዴት ትተህ ትሔዳለህ" ብላ ቃል በቃል አነጋገረችው። የመንገዱን ስንብት እስክትፈቅድለት ድረስ በለቅሶና በእንባ ዳግመኛ ለመናት እርሷም እንዲሔድ ፈቀደችለት። ❤ የቅዱስ ያሬድ ምናኔ፦ ወደ ገዳም ሊሆድ ተዘጋጀ በዚህ ጊዜ የሚወዱት ካህናት፣ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ተከትለውት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት። ከእርሱ በሚለዩበትም ጊዜ "ሰላመ ነሳእነ ወሰላም ኃደግነ ለክሙ ወሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኩልክሙ፤ ሰላምን ከእናንተ ተቀበልን ለእናንተም ሰላምን ተውንላችሁ የእግዚአብሔር ሰላምም ከሁላችሁ ጋራ ይኹን" ብሎ በዜማ ተሰናበታቸው። ዳግመኛ "ወሰላም እግዚአብሔር እንተ ኵሉ ባቲ ተሀሉ ወትረ ምስለ ኵልክሙ፤ ፍቅርና ስምምነት ሁሉ ያለበት የእግዚአብሔር ሰላምታ ሁል ጊዜ ከሁላችሁ ጋራ ትኑር" ብሎ በጣዕ ዜማው መረቃቸው። ካህናቱም ይህን ሰምተው አለቀሱ። እርሱም ከእርሱ ጋራ አለቀሰ። በዚሁ ጣዕመ ዜማው የመጨረሻ ቡራኬውን ሰጣቸውና እርስ በእርሳቸው ተሳስመው ተነሰነባብተው ከእርሱ በመለየታቸው እያዘኑና እየተከዙ ወደ አገራቸው አኵሱም ተመለሱ። እርሱ ግን የተከዜን ወንዝ ተሻገረ። የወንዙ ፏፏቴና ጎርፍ እንሚጮህ አንበሳ ሲጮህ በሰማ ጊዜ "አኅለፍኮሙ በእግር እንተ የብስ ማእከለ ባሕር ተከዜ...፤ በተከዜ ባሕር መካከል በእግር እንደሚሻገር በደረቅ አሻገርካቸው..." እያለ በረቀቀ ምስጢር እግዚአብሔርን በማመስገን እየዘመረ ሲሒድ አንዲት ሴት ውሃ ቀድታ ወደ ቤቶ ስትመለስ ድምፁን ሰምታ ወይ ቃል! ወይ ቃል! እንዴት አንጀት ይበላል! ምንኛስ ያሳዝናል! ብላ ደጋግማ ስለተናገረች ቅዱስ ያሬድ ቆሞ የዘመረባት ቦታ "ወይ ቃል" ተብላ ተጠራች። ዛሬ ይህች ቦታ ጎንደር ክፍለ አገር ደባርቅ አካባቢ "ወይ ቃል" ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራለች። ❤ ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ሔዶ ጸለምት ወጥቶ ብርድ በጸናበት በረዶ በተከማቸበት ሳኔር ተብሎ በሚጠራ በሐዊ ዐምባ ጽሞና ይዞ ተቀመጠ። በዚያም በብዙ ትጋት በጾምና በጸሎት ይልቁንም በስብሐት እግዚአብሔር ብቻ ተወስኖ ጉባኤ ዘርግቶ፣ ትምህርት አስፍቶ ከሱራፌል መላእክት እንደተማረው አድርጎ ከጸለምት፣ ከስሜን፣ ከአገውና ከሌላ አገር ወደ እርሱ የሚመጡትን ሰዎች ሁሉ ማሕሌተ እግዚአብሔር እያስተማረ ኖረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ከትውልድ አገሩ አኵሱም መንኖ ከወጣ በኋላ ትዕግሥቱን እያዘወተረ ወደ እርሱ የመጡትን ሁሉ በማስተማር በገዳመ ስሜን ኖረ። ቅዱስ ቍርባን ለመቀበልና ቅዱሳት ገዳማትን ለመሳለም በፈለገ ጊዜ በሠረገላ ብርሃን ተጭኖ አኵሱም ደርሶ ቅዱስ ቍርባን ተቀብሎ ሌሎች ገዳማትንም ይሳለም ነበር። ❤ በመጨረሻ ቅዱስ ያሬድ ካህን ዘመኑን ሁሉ በመላእክት ማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገልና ይህን ማኅሌት ለሚከተሉት ደቀ መዛሙርት በማስተማር ዘመኑን ፈጽሞ ለሃያ ሁለት ዓመታት በላይ በምናኔ ታግሦ በገድሉና በጣዕመ ዜማው ፀላኤ ሠናያትን ድል አድርጎ ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ የሚያርፍበት፣ የሚሰወርበት ቀንና ሰዓት መድረሱን በጸጋ በዐወቀ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ "ይቤ ጳውሎስ ኃላፊ ንብረቱ ለዝንቱ ዓለም አኃውየ አስተፋጥኑ ገቢረ ሠናየ አነሰ በድረየኒ ፈጸምኩ ወሃይማኖትየኒ ሠለጥኩ እንከሰ ጽኑሕ ሊተ አክሊል ዘየዓሥየኒ መኰንነ ጽድቅ" 2ጢሞ4፥7-8 እያለ በሚያራራ ቃል ምክሩን ሰጥቶ ተሰናበታቸው። እነርሱም ምክሩን ተቀብለው "አባ አቡነ፣ አባ መምህርነ አይቴ ተሐውር ወለመኑ ተኀድገነ፤ አባታችን መምህራችን ወደ የት ትሔዳለኽ? ለማንስ ትተወናለኽ? እያሉ ሲያዝኑ ሲያለቅሱ በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቶ ግንቦት11 ቀን በ571ዓ.ም ተሰወረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ከመሰወሩ በፊት በእግዚአብሔር አምነው በእርሱ ቃል ኪዳን ለተማፀኑ፣ በስሙ ቤተ ክርስቲያን ላሳነጹና ላነጹ፣ መጽሐፈ ገድሉን ለጻፈና ላጻፈ፣ ዕጣን ቋጥረው ጧፋና ጥላ ገዝተው መገብሪያ ሰፍረው፣ መጋረጃና ሌሎችንም ንዋያተ ቅዱሳት ገዝተው አምጥተው በስሙ ለታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ላበረከቱት ሁሉ የማየሠልፈውን ርስት መንግሥተ ሰማያት እንደሚያወርስለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገብቶለታል።

❤ በዚያም ቅዱሳን መላእክት የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠረ እግዚአብሔር በቅኔና በከፍተኛ ደምፅ ያለማቋረጥ በመንበሩ ዙሪያ ኾነው ሲያመሰግኑ እንዲሁም የእንዚራ፣ የበገና የመሰንቆ ድምፅ በሰማ ጊዜ ካለበት ሥፍራ እነርሱ ወዳሉበት ሊገባ ወደደ ነገር ግን አልተቻለውም። በመጨረሻም እነዚያ አዕዋፍ ወደ እርሱ ተመልሰው መጡ። "ያሬድ ሆይ፤ የሰማኸውን አስተውለኸዋል?" ብለው ጠየቁት እርሱም "አላስተዋልኸም" ብሎ መለሰላቸው። እንግዲያውስ አዲሱን የእግዚአብሔር ምስጋና ጥራ፤ እርሱም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው። ከእግዚአብሔር መዘምራን ከቅዱሳን መላእክት በየዐይነቱ ዜማ ያለውን ማሕሌት ትማራለኽ፤ ታጠናለኽ" አሉት። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ማሕሌቱን በየዓይነቱ አውጥቶ "መልካምን ነገር ልቤ ተናገረ" እያለ ከቅዱሳን መላእክት ተማረ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም "ሌሎችን አገልጋዮች ሰዎች ይሾሟቸዋል፤ አንተን ግን እኔ ሢመተ ክህነት (ቅስና) ሾሜኻለሁ" አለው። ❤ ቅዱስ ያሬድም የመላእክት ሥርዓታቸው ዐይቶ፤ ማሕሌታቸውን አጥንቶ ኅዳር 6 ቀን 527 ዓ.ም በጠዋት ሦስት ሰዓት ወደ ቀድሞ ቦታው ተመልሷል። ከዚያም ኾኖ ፊቱን ታቦተ ጽዮን ወዳለችበት ወደ ምሥራቅ አዙሮ እጆቹን ዘርግቶ እንዲህ ብሎ ሰማያዊ ዜማን ለመጀመርያ ጊዜ በአኵሱም አደባባይ (ዐውደ ምሕረት) ዘመረ። ❤ "ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብር ግብራ ለደብተራ"። ብሎ በዓራራይ ዜማ አዜመ። ይህም ማለት ዓለም ሳይፈጠር ለነበረ ዓለምን አሳልፎ ለዘለዓለም ለሚኖር አሁንም ላለ ለአብ ምስጋና ይገባል፤ ለወልድም ምስጋና ይገባል፤ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፤ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ፤ ዳግመኛም ደብተራ ኦሪትን እንዴት አድርጎ መሥራት እንዳለበት ለሙሴ አሳየው ማለት ነው። ስለምን በዓራራይ ዜማ ጀመረ ቢሉ ቋንቋን የሚያናግር ምስጢር የሚያስተረጉም መንፈስ ቅዱስ የገለጠልኝ ዜማ ነው ሲል ነው። ምክንያቱም ዓራራይ ዜማ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነውና። ❤ ከሰማይ እንደተመለሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ጣዕመ ዜማውን ያሰማበት ቦታ "ሙራደ ቃል" (የቃል መውረጃ) እየተባለ ይጠራል። ይኸውም ዜማው ከሰማይ የወረደ ለመኾኑ እውነተኛ ማስረጃ ነው። ይህችንም ዜማ "አርያም" አላት። ይህም ማለት ከመላእክት ወይም ከሰማይ የተገኘች ማለት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ከብሉይና ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት መጻሕፍትም ከነ አትናቴዎስ፣ ቄርሎስ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የተስማሙትን ቃላት እየመረጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጸደይና በክረምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ። የመጽሐፉ የድርሰቱ ስም ድጓ ተባለ። ድጓ ማለትም በትግርኛ ደጉዓ ማለት መዝሙረ ኃዘን፥ የኃዘን ዜማ፥ ማለት ነው፤ ሙሾ የዜማውን ዓይነት በሦስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል። እነርሱም ግእዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ። ግእዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ የተገኘ ማለት ነው ፤ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ከግእዙ ጋር ተደርቦ፣ ተጨምሮ ፣ታዝሎ የሚነገር ማለት ነው። ዓራራይ ማለትም ሦስተኛ ተጨማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ፣ አሳዛኝ ልብን የሚመስጥና ደስ የሚያሰኝ ማለት ነው። ይህን ድርሰቱን ያዘጋጀበት ዘመን ከ540 ዓ.ም ሲሆን በአፄ ገብረ መስቀል መንግሥት ነው። ❤ አፄ ገብረ መስቀልና አባ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሦስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪከ ነገሥቱና ገድለ አረጋዊ ይገልጽልናል። አቡነ አረጋዊ የደብረ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላቸው፣ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጸልዩበት ፈቀደላቸው። እርሳቸውም ይህንን ተራራ ከተረከቡ በኋላ በተራራው ላይ የጸሎት ቤት ስለሌለ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልን አንድ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራላቸው ለመኑት። ንጉሡም ቤተክርስቲያን ልሠራ የምችልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ ብሎ ነገራቸው አቡነ አረጋዊም ተነሥተው ዞረው ቦታውን መርጠው አሳዩት። ❤ ከዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጨቱ እየተሰበሰበ በከብትና በሠረገላ እየተጋዘ ተሰበሰበና ከታች ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ። ባለቀም ጊዜ የቤተክርስቲያኑ ሥራ ተመልካቾች አስደነቀ። ለዚህም ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ የሆኑ አልባሳት፣ የብርና የወርቅ የተደጎሱና የተከፈፉ መጻሕፍትን አበረከቱ። ከማኅበረ በኩር የመጣውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጽላት አግብተው አቡነ አረጋዊ ባርከውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆረቡ። ከዚያም አፄ ገብረ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ። ❤ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ፥ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቤተክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ከተራራው ሥር ሲደርስ የአቡነ አረጋዊን ደቀመዛሙርት ማትያስና ዮሴፍ የሚባሉትን ከወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ "ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ ፤ ይህ አረጋዊ አባታችሁ ደህና ነው" ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም ደኅንነታቸውን ነገሩት። ከዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ከአቡነ አረጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቤተ ክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ከተሳለመ በኋላ የሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ከፍ ባለ የዜማ ድምፅ እያጉረመረመ እንዲህ ሲል ዘመረ። "ይሔውጽዋ መላእክት እንተ በሰማያት ይሔውጽዋ መላእክት እስመ ማኅደረ መለኮት ይእቲ ዖድክዋ ዖድክዋ ዖድክዋ ወርኢኩ ሥነ ሕንፄሃ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ምስአል ወምስጋድ ወምስተስርዬ ኃጢአት ይእቲ ቅድስት ደብተራ፤ በሰማያት ያሉ መላእክት ይጎበኟታል፤ የመለኮት ማደሪያ ናትና መላእክት ይጎበኟታል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ዞርኋት፣ ዞርኋት፣ ዞርኋት የሕንፃዋን ማማር ዐየኹ፤ እርሷ መጸለያ፣ መስገጃና የኃጢያት ማስተሰረያ ቅድስት ማደርያ ናትና"። እያለ ስለዘመረ ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሎ ተጠራ። ደብረ ዳሞ የሚለው ስያሜ በኋላ የወጣ ስም እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ይናገራሉ። ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ገዳም ስምንት ቀን ያህል ከአቡነ አረጋዊ ጋር ሰንብቶ ወደ አክሱም ተመለሰ። ❤ ከዚህ በኋላ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ ከቅዱስ ያሬድ ጋር አብረው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ። ከዚያም በጣና በአንዱ ደሴት ላይ የቅዱስ ቂርቆስን ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ። በዚያም ቦታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማረ። እርሱ እራሱ ጻፈው የሚባል ድጓ ምልክት የሌለው ዛሬ በዚሁ ደሴት በጣና ቂርቆስ ይገኛል። ❤ ከዚህም ደሴት ከጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ። በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባቸው ሲጨነቁ አንድ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ አቡነ አረጋዊን "ዑድ አባ መንገለ ምሥራቅ ወዑዳ ለዛቲ ደብር፤ ዙር አባ ወደ እርስዋም ትወጣ ዘንድ በምሥራቅ በኩል ዙር" አላቸው ወደ ምስራቅ ሲዞሩ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነጭ ሐረግ ዘረጋላቸው እርሱን ይዘው ወደ ተራራው ላይ ወጡ። በዚሁ ተራራ ላይ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠሩ። የተራራውም ስም እስከ ዛሬ ድረስ ዙር አምባ ተብሎ ይጠራል። በዚህ ገዳም ምሥራቃዊ አቅጣጫ ቅዱስ ያሬድን የምትዘክር "ከርሞ አይደርቅ" የምትባል ዛፍ አለች። ቅዱስ ያሬድ በዚች ዛፍ ሥር

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን ለማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን #ለቅዱሳን_ሱራፌል አምሳላቸው ለሆነ #ለኢትዮጵያዊው_ለታላቁ_ማኅሌታይ_ለካህኑ_ቅዱስ_ያሬድ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወረበት ቀን ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #ማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን_ታላቁ_ማኅሌታይ_ካህኑ_ቅዱስ_ያሬድ፦ የስሙ ትርጓሜ ያሬድ ማለት ርደት፣ ወሪድ፣ ማለትም መውረድ ማለት ነው። ከአዳም ስድስተኛ በሆነው በመላልኤል ልጅ በያሬድ ጊዜ ደቂቅ ሴት ከደብር ቅዱስ ወደ ደቂቀ ቃየን ወደ ምድረ ፍዳ ስለወረዱ ያንን ለማስታወስ አባቱ መላልኤል ያሬድ ብሎታል። ኩፍ 5፥21-22 ❤ በኢትዮጽያም ዳግማዊ ያሬድ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ተነስቶ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ የሚያወርድ ነውና ይህንን ለመግለጽ እግዚአብሔር አምላክ በእናቱ እና በአባቱ ላይ አድሮ ያሬድ እንዲባል አድርጓል። ምስጢሩ ልዩ ጣዕመ ዜማን ከሰማይ የሚወርድ መሆኑን ያሳያል። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት ንብ ማለት ነው። ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከቅዱሳት መጻሕፍት የማይጠቅሰው የለምና። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት ረአዬ ምስጢር ነጻሬ ኅቡአት "ምስጢር ተመልካች ምስጢር ገላጭ ማለት ነው። ምስጢር ገላጭ መባሉ የመላእክት ምስጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፤ " ዋይ ዜማ ዘሰማዕኩ በሰማይ እመላእክት ቅዱሳን፤ ከቅዱሳን መላእክት በሰማይ የሰማኹት ዜማ ምን ይረቅ! ምን ይጠልቅ!" እንዲል። ምስጢር ተመልካች መባሉ ደግሞ ኅቡእ (ስውር) የኾነ የነቢያት፣ የሐዋርያትን፣የሰማዕታትና የጻድቃን ገድል አምልቶ አስፍቶ ስለሚናገር ነው። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው። እነዚህ በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ፤ የቅዱስ ያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክት ፣ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና። ❤ ታላቁ ማኅሌታይ ካህኑ ቅዱስ ያሬድ፦ ከእናቱም ቅድስት ክርስቲና (ታውክልያ) ከአባቱ ከቅዱስ አብዩድ (ይስሐቅ) በአኵስም (አክሱም) በ505ዓ.ም ሚያዝያ5 ቀን ተወለደ። አባቱ የአክሱም ጽዮን ቄሰ ገበዝ ነበር። በዚያን ጊዜ የብሉያትና የሐዲሳት መምህራንና ተማሪዎች የሚገኙት አክሱም ጽዮን ነውና የአኵሱም ቤተ ቀጢን (ቤተ ጉባኤ) መምህር የነበረው የእናቱ ወንድም አጎቱ መምህር ጌዴዎን ይባል ነበር። ❤ ቅዱስ ያሬድ የሰባት ዓመት ሕጻን በኾነ ጊዜ አባቱ ስለ ሞተ ትምህርት ቤት ከመግባቱ በፊት በዚያ ዘመን አጠራር ለጌታው ዐደረ። ጌታውም የዐፄ ገብረ መስቀል ቢትወድድ አዛዥ ዜና ገብርኤል ይባላል። ያሬድን ዐቅሙ ለጉልበት ሥራ እንዳነሰ አይቶት "አንተ ልጅ ጋሻ ቢያስይዙህ አትችል፤ ሾተል ቢያሸክሙህ አይሆንልህ ለምን ከዚህ መጣህ?" ብሎ መለሰለት። ከዚያ በኋላ ከአጎቱ ዘንድ ሔደ። መምህሩም "ከዚህ የመጣህበት ምክንያት ምንድ ነው?" አለው። እርሱም "መጽሐፍት እማራለኹ ብዬ ነው የመጣኹት" አለው። መምህር ጌድዎንም ዐቅሙንና ዕውቀቱን በመገመት ለተማሪዎች "በሉ ፊደል አስቆጥሩት" አላቸውና ትምህርቱን ጀመረ። ኾኖም ቃለ እግዚአብሔርን የመቀበል ችሎታው ደካማ ስለነበር አብረው የሚማሩትም ሕፃናት "ሰነፍ ያሬድ ዕንጨት ስበር ውሃ ቅዳ" እያሉ አፌዙበት፤ ቀለዱበት። አጎቱ ጌዴዎንም ከትምህርቱ ድክመት የተነሣ በጨንገር (በአለንጋ) ቢገርፈው ሕፃኑ ያሬድም በዚህ ተበሳጭቶና ተስፋ ቆርጦ ከአክሱም ከተማ ወጥቶ ወደ እናቱ መንደር ወደ መደባይ ወለል ደረሰ። ለጥሙ ከምንጭ ውሃ ጠጥቶ ለድካሙ ከዛፋ ጥላ አረፈ። በምን ምክንያት ከጓደኞቹ በታች እንደኾነ ሲያስብና ሲያሰላስ ሳያዝንና ሲተክዝከቆየ በኋላ እግዚአብሔር አንድ የሚያጽናና ምልክት አሳየው። ይኸውም አንድ ትል የዛፏን ፍሬ ለመመገብ ፈልጎ ወደ ላይ እየወጣና እየወደቀ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሰባተኛው ጊዜ ወደ ዛፋ ወጥቶ ፍሬዋን ሲመገብ ተመለከተ ተማሪ ያሬድም ከዚህ ትል ትዕግሥትን፣ ጽናትን፣ ጥረትን፣ ስኬትን ትምህርት ወስዶ እኔም እኮ ተስፋ ሳይቆርጥ ብዙ ጥረት ካደረግኹ እግዚአብሔር ያሳካልኛል ብሎ በተስፋ ተጽናንቶ እንደገና ወደ መምህሩ በመመለስ ትምህርቱን ለመቀጠል ወሰነ። ወደ መደባይ ያደረገው የነበረውን ጉዞ ሠርዞ ወደ አክሱም ከተማ ወደ መምህሩ ጌድዬን ጉባኤ ቤት ተመለሰ። በመጸጸት አጎቱን "አባቴ ስለተቆጣኸኝና ስለገረፍከኝ ተበሳጭቼ ሔጄ ነበር ፤ ነገር ግን በመንገድ ላይ እግዚአብሔር ስላስተማረኝ ተጸጽቼ መጥቻለኹ። ከእንግዲህስ ወዲህ እየተቆጣኽና እየገሠጽህ አስተምረኝ" ሲል አሳቡን ሳይደብቅ ገለጸለት። ❤ አጎቱም ያሬድ ተጸጽቶ በመመለሱ በጣም ተደስቶ ዐይነ ልቡናውን ያበራለት ዘንድ ፈጣሪውን እያለቀሰ በለመነለት ጊዜ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ለያሬድ ዕውቀትን ገለጸለት። የያሬድ ኅሊናው ተከፍቶለት መዝሙረ ዳዊትን፣ ውዳሴ ማርያምን፣ መሓልየ ነቢያት፣ መሐልየ ሰሎሞንን፣ መጻሕፍተ ብሉያትንና ሐዲሳትን ንባባቸውን እስከ አገባባቸው አወቀ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃሉ ይዞ ሲያስተምር ሳለ የትምህርቱን ጥራት፣ የሃይማኖት ጽናት፣ ደግነቱንና ትዕግስቱን፣ ትሕትናውና ተልኮውን በመምህሩና በካህናቱ ተመስክሮለት የአክሱም ጳጳሱ አባ ዮሐንስ ሢመተ ዲቁና ሾመው። ቅዱስ ያሬድ የታላቋ የአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አጋልጋይ ዲያቆን ኾነ። ❤ ትምህርቱን በስፋት ስለቀጠለበት የመጻሕፍት ብሉያትና ሐዲሳት፣ የመጻሕፍት ሊቃውንት ትርጓሜ ሊቅ ኾነ። ቅዱስ ሬድም ለመንፈሳዊ አገልግሎት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት ከዘጠኙ ቅዱሳን ጋራ በቤተ ቀንጢን ጉባኤ ቤት ይውል ስለነበር ገዳማዊ ሕይወት ከእነርሱ በመማር እንደ እነ አቡነ አረጋዊ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጰንጠሌዎን በድንግልና ተወስኖ በንጽሕና ሲያገለግል ቆይቷል። ❤ ለቅዱስ ያሬድ ሰማያዊ ዜማ መገለጽ፦ ኅዳር 5 ቀን 527 ዓ.ም ከጠዋቱ በሦስት ሰዓት እግዚአብሔር ከኤዶም ገነት ሦስት አዕዋፍን (መላእክት በአዕዋፍ ተመስለው) እርሱ ወዳለበት ላከለት። እነርሱም ያሬድ ባለበት ቦታ አንጻር በአየር ላይ ረብበው በግእዝ ቋንቋ "ብፁዕ ያሬድ ብፅዕት ከርሥ እንተ ጾረተከ ወብፁዕት አጥባት እለ ሐፀናከ (የተመሰገንክና የተባረክ ያሬድ ሆይ፤ አንተን የተሸከመች ማሕፀን የተመሰገነች ናት፤ አንተን ያሳደጉ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸው") ብለው አወደሱት። ቅዱስ ያሬድም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ወደ ሰማይ አንጋጦ ሦስቱን አዕዋፍ አየና "እናንተ በሰው አንደበት የምትናገሩ ከወዴት መጣችኹ" አላቸው። ከሦስቱ አዕዋፍ አንዷም "ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ማሕሌትን ሰምተኽ እንድታዜም የተመረጥኽ መኾኑን እነግርህና እናበሥርህ ዘንድ ወደ አንተ ተልከን መጥተናል" አለችው። ከዚያም ቅዱሳን መላእክት በዜማወደሚያመሰግኑባት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በአካል ተነጠቀ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ከደቡባዊ_ግብጽ ከታችኛው ምድር አውራጃ ከንሒሳ ከተማ ለሆነ ለታላቁ ለሰማዕቱና ለጻድቁ አባት #ለአባ_ኖብ_ቅዱስ_ሚካኤል ከሞት ላስነሳበት ዓመታዊ በዓልና ከእርሱ ጋር በሰማዕትነት ለዐረፉ #ለስምንት_መቶ_ሃምሳ ሰዎች ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የግንቦት_ዐሥር_ቀን_የአባ_ኖብ_የተጋድሎውን መጽሐፍ፦ ቅዱስ አባታችን አባ ኖብም ተጋድሎልን ከፈጸመ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወረደ የብረቱንም ሹል ሰበረው የቅዱስ አባታችንንም ሥጋ እርስ በርሱ ሁለት ክፍል አደረገው ዐይኖቹንም እንደ ቀደመው መልሶ አገባለትና ያለ ጥፋት አስነሣው እንዲህም አለው "አባ ኖብ ሆይ ጽና በርታ እኔም ከአንተ ጋራ እኖራለሁ የክብር አክሊልን እስከምትቀዳጅ ይህም ሁሉ ሕዝብ በትምህርትህ እስከሚ ያምን ድረስ አጸናሃለሁ" አለው። ቅዱስ አባታችን አባ ኖብም ሕዝቡ ሁሉ እያዩት ያለ ምንም ጥፋት በእግዚአብሔር ኃይል ድኖ ተጽናንቶ በክብር ተነሣ። ❤ ከዚህም በኋላ በአትሪብ ሀገር የተሰበሰቡ ሕዝቡ ሁሉ "በንሒሳው ሰው በአባ ኖብ አምላክ አመን እኛ በግልጥ ክርስቲያኖች ነን" እያሉ አሰምተው ተናገሩ። የሳምኑድ ሀገረ ገዥም ተነሥቶ እጁን በልብሱ ውስጥ አግብቶ ቀደደው ከእግሩም ጫማውን አውልቆ የጭፍሮች አለቃ የቅብርያንን ራስ መታው ቅብርያንም "ከአባታቸው ከዲያብሎስ ተንኮል የተነሣ ዐይናቸውን ያሳወረ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰማዕታቶቹ የሚሰጠውን ክብርና ድንቅ ተአምራት ኀይላትን አታይምን እኔ ክርስቲያናዊ ነኝ እኮ ሁሉም ጭፍራዎቼ ከእኔ ጋራ ይበተናሉ አጵሎንንም የሚያመልኩት ሁሉ ይበተናሉ" አለ፡፡ ❤ ሀገረ ገዥውም በሀገሩ የሆነውን ሁካታ ባየ ጊዜ ሰይፋቸውን መዘው በክርስቶስ ያመኑትን ሁሉ አንገታቸውን ይቆርጧቸው ዘንድ ጭፍራዎችን አዘዘ ከጠዋትም ጀምሮ እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ ገደሏቸው የተገደሉትም ቍጥራቸው ስምንት መቶ ሃምሳ ስምንት ሰዎች ሆኑ። ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስም ደማቸውን ያፈሰሱ ቍጥራቸው በዛ በግንቦት ዐሥር ቀንም ገድላቸውን ፈጸሙ። የእነዚህም ቅዱሳን ልመናቸውና በረከታቸው የአባ ኖብም በረከቱ በእግዚአብሔር አብ ፍቅር አንድነት ለሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ይደረግልን አሜን። ❤ የጭፍሮች ገዥ አውሕያስም ከንሒሳ የተገኘ የንሒሳውን ጻድቅ አባታችን አባ ኖብን "ይህ አንተ የምታስበው ሁሉ በአንተ በኵል መልካም ነውን? በአንተ ምክንያት የፈሰሰውን ይህን ሁሉ ደም አሁን አይተሃልና ይልቁንም የጭፍሮቹንና የብርቅያንን ዛቻና ነገር ተውና እንደ ጌታዬ እንደ ንጉሡ እንደ ዲዮቅልጥያኖስ ትእዛዝ ናና ለአጵሎን ስገድ" አለው። ቅዱስ አባታችን አባ ኖብም "አንተ ውሻ ሰነፍ ዲዮቅልጥያኖስ ለአንተ ጌታህ ቢሆን ለእኔ ጌታዬ አይደለም፤ የኔስ ጌታዬ የሰማይና የምድር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እንጂ ትዕቢተኞችን አባትህ ዲያብሎስን ከአንተ ጋራ ያሉትንም ሁሉ ያጐሰቍላቸዋል" አለው። በዚያም ሰዓት ሁለት አፍ ያለው የተሳለ መጥረቢያ አመጡ ቅዱስ አባታችን አባ ኖብንም በደረቱ እንዲያስተኙት አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላ ከትከሻው ላይ ክንዱን ቆርጠው ትተውት ሄዱ። ሀገረ ገዥውም "በእውነት አምላክ አጵሎን ታላቁ ያውቃል እነሆ በእሱ ላይ ዐመጽህ በእዚች ሰዓት ገሊላዊው ኢየሱስ እስቲ መጥቶ ከእጄ ያድንህ እንደሆነ አያለሁ ያለ አርዳሚስና ያለ አጵሎን ሌላ አምላክ የለኝምና" ብሎ አሰምቶ ተናገረ። የሀገሩም ሰዎች ሁሉ ቅዱስ አባታችንን መከራ ባጸኑበት ቦታ ተገድሎ ወድቆ ባዩት ጊዜ በዚች ሰዓት እነሆ ሞተ እያሉ ፈጽመው ስለ እሱ ልባቸው ተጨነቀ። ሀገረ ገዥውም በአንድ ጊዜ በልተው እንዲጨርሱት የቅዱስ አባታችን ሥጋ ባለበት ቦታ ላይ የሀገሩን ውሾች ሁሉ እንዲሰበስቡ አዘዘ። በሀገሩ ውስጥም ካለ ከአባ አባሲና ከራሱ ከሕፃን ከአባ ኖብ በቀር እርሱን መልአክ እንዲጠብቀው አንድም ሰው አላወቀም ነበር። በዚችም ሰዓት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱሳን ሱራፌልና ኪሩቤል ከእሱ ጋራ ሆነው ሊያጽናነት ከሰማይ ወረዱ የቅዱስ አባታችን የአባ ኖብንም ሰውነቱን ራስ በራሱ ሰብስበው በጻድቁ በአባታችን በአባ ኖብ ፊት እፍ አለበት እሱም ያለምንም ጥፋት ተነሣ፡፡ ❤ ቅዱሳን ሱራፌልም "መልካም ተጋዳይ የጸናህ አካል ሆይ ይህን ከዳተኛ ንጉሡንና አማልክቶቹን እስከምታሳፍራቸው ድረስ እናጸናህ ዘንድ እኛ ከአንተ ጋር እንኖራለንና ጽና፤ እነሆ እስክንድርያ ሀገር ይወስዱሃል በዚያም መከራ ያጸኑብሃል ወደ አንተም መጥተን እናድንሀለን ገድልህንም ትፈጽማለህ። ከዚህም በኋላ በዚያ ቦታ ራስህን ይቆርጡሃል ከአቅፋሐስ ያለው ዮልዮስም ሥጋህን ገንዞ ወደ ሀገርህ ይወስድሃል ፈውስ ይደረጋል ሥጋህንም በእጅህም ለብዙ ሰዎች ብዙ የሚያኖሩበት ቦታው ይቀደስ ዘንድ እስከ ዘለዓለም ድረስ ይባረካል" አለው። ❤ እኒህም ቅዱሳን ሚካኤልና ሱራፌል ኪሩቤልና ዑራኤል ቅዱስ አባታችን አባ ኖብን ይህን ካሉት በኋላ በክብር ወደ ሰማይ ዐረጉ። ከአባታችን ከአባ ኖብና ከሰማዕታቱ አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አባ ኖብ።

❤ ቅዱስ አብርሃምም ወደ ሰማዕቱ ቴዎድሮስ ቤተ ክርሰቲያን ሄዶ ከጸለየ በኋላ ወደ መኰንኑ ዘንድ በመሄድ ስለ ጌታችን መመስከሩን ቀጠለ፡፡ በዚህም ምክንያት በግንድ አሥረው አሠቃዩት፡፡ ጌታችንም ተገልጦለት አበረታው፡፡ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ መኰንኑ ራሱን ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ በትእዛዙም መሠረት ግንቦት 10 የቅዱስ አብርሃም ራስ በሰይፍ በቆረጡት ጊዜ ራሱ ለብቻ እየተንከባለለች "እኔ ክርስቲያን ነኝ" እያለች መሰከረች፡፡ ሆዱን ሰንጥቀው ባሩድና ሙጫ መልተው ከእሳት ውስጥ ጣሉት፡፡ እሳቱም እንዳልጎዳው ቢያዩ ሰውነቱን ከታትፈው ብዙ ቦታ ቆራርጠው በእንቅብ አድርገው ከባሕር ውስጥ ጣሉት፡፡ የተቆራረጠው ሰውነቱም በተአምራት ከጭንቅላቱ ጋር ተጋጥሞ ቀድሞ እስና በትምባል ሀገር በባሕሩ ወደብ ላይ ተገኘ፡፡ ምእመናንም ወስደው በታላቅ ክብር ቀበሩት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሰማዕት በቅዱስ አብርሃም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ሚካኤል፦ የዚህም ቅዱስ ክርስቲያን ባለጸጎች ናቸው ልጅ ባጡ ጊዜም የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ክርስቲያንር ለመኑ እርሱም ይህን የተቀደሰ ልጅ ሰጣቸው የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማሩት። ወላጆቹም በሞቱ ጊዜ የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ ገንዘቡን አስጠበቀለት ዐሥራ ሁለት ዓመትም ሲሆነው የዚህን ዓለም ኃላፊነት አስቦ ወደ አባ ይስሐቅ ገዳም ሒዶ የምንኩስና ልብስ እንዲያለብሰው ፈለገ። እርሱም ከፈተነውና ብርታቱን ከአየ በኋላ አለበሰው የእግዚአብሔርም ጸጋ አደረበት የፊቱ መልክ ተለውጦ እንደ ደረቅ እንጨት እስኪሆን በጾምና በጸሎት ሰውነቱን አስጨነቀ። ❤ በአንዲት ዕለትም አባቱ አባ ይስሐቅ ወደ አባ ሚካኤል በዓት ሔደ መልኩ እንደ ሞተ ሰው ሆኖ አይቶት አለቀሰ። "ልጄ ሆይ እንዴት እንዲህ ሥጋህ ተጎዳ" አለው እርሱም "አባቴ ሆይ አታልቅስ እግዚአብሔር አልተወኝምና ለመቆምም ኃይሌ አልደከመምና ነገር ግን በሕልሜ ያየሁትን ልንገርህ እኔን የሚፈልጉ የንጉሥ መልክተኞች ከእስክንድርያ ወደ አንተ ሲመጡ እኔን አትከልክላቸው አንተን እንዳይወቅሱ። በሁለተኛውም ዓመት ታላቅ ረኃብ ይመጣል ምድርንም ያጠፋታልና ለልጆችህ ምግባቸውን አዘጋጅ" ብሎ መለሰለት። ❤ ከወራትም በኋላ በንጉሥ ጭፍራ አምሳል ሰዎች አባ ሚካኤልን አየፈለጉ መጥተው አባ ይስሐቅን ያዙት ሚካኤልም በአገኙትና በአወቁት ጊዜ ከእርሳቸው ጋራ ወሰዱት መነኮሳቱም እያዘኑ ቀሩ። ረኃብም በሆነ ጊዜ አገረ ገዥው በዚያ ገዳም እህል እንዳለ ሰምቶ ሊከባቸው ፈለገ። አባ ይስሐቅም ሊማልድ ወደ መኰንኑ መጣ ያንጊዜም ብዙ ጭፍሮች ከሰይፎች ጋራ ከዚያ ገዳም ወጥተው መኰንኑ እያደነቀ አባ ይስሐቅን ወሰዱት። ከዚህም በኋላ አባ ሚካኤል መጥቶ ራሱን ገለጠለት እነዚያ የወሰዱት ሰዎች የሰማይ ሠራዊት እርሱን የወሰዱበት አገርም ኢየሩሳሌም ሰማያዊት እንደሆነች ነገረው። ❤ ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶስ በአስጠበቀለት ገንዘቡ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራለት አዘዘው በዚያች በበዓቱ ላይ ሠራለትና በዚች ዕለት አከበሩዋት። ደግሞም አባ ሚካኤል ለአባ ይስሐቅ ተገልጾ በመጪው ዓመት እንደሚሞት ነገረው እንደቃሉም ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሚካኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ የግንቦት 10 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአባ_ሚካኤል እምነ መምህሩ ዘአፍለሶ። እንተ ነሥእዎ መላእክት ሶበ ንጉሦሙ ኀሠሦ። ወበተመይጦቱ ደኀሪ መንገለ አቡሁ ገይሦ። ዜነወ ወአይድዐ ዘከመ ይኄድፍ ነፍሶ። እግዚአብሔር ውስተ ዛኅን ወመርሶ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_10።                            + + + ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መሐሪ እግዚአብሔር ወጻድቅ። ወአምላክነሂ መስተሣህል። የዐቅብ ሕፃናተ እግዚአብሔር። መዝ 114፥5-6 ወይም 65፥12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 19፥13-16 ወይም 18፥19-23።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወአፅዐንከ ሰብአ ዲበ አርእስቲነ። አኅለፍከነ ማእከለ እሳት ወማይ። ወአውጻእከነ ውስተ ዕረፍት"። መዝ 65፥12። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥17-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥19-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ  ቅዳሴ ነው። መልካም የሠለስቱ ደቂቅ የዕረፍት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን ለከበሩ ጻድቃን #ለሠለስቱ_ደቂቅ_ለቅዱሳን_ለአናንያ_አዛርያና_ሚሳኤል ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል፣ ለፀራቢ #ለቅዱስ_አብርሃም_ሰማዕነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል መታሰቢያና #ለአባ_ሚካኤል ለመታሰቢያውና ቤተ ክርስቲያኑ ለከበረችበት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦  ከፖትርያርክ #ከአባ_ዮሐንስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ሠለስቱ_ደቂቅ፦ እሊህም ለይሁዳ ንጉሥ ለኢዩአቄም ልጆች ናቸው ነቢዩ ዳንኤል የእኅታቸው ልጅ ነው። በምርኮ ጊዜም ከእስራኤል ልጆች ጋራ ተማርከው ወደ ባቢሎን ወረዱ። ከእስራኤል ልጆች ምርኮ ውስጥ በመብልና በመጠጥ እያስተማረ አሳድጎ በሠራዊቱ መካከል ጭፍሮቹ ያደርጋቸውን ወጣቶች ንጉሥ መረጠ። እሊህም ከተመረጡት ውስጥ የተቆጠሩ ሆኑ። የእኅታቸው ልጅ ነቢዩ ዳንኤልም። ምግባቸውን በሚሰጡአቸው ጊዜ አረማውያን ከአረዱአቸው ውስጥ መብላትን አልወደዱም ከንጉሥ ማዕድም ከሚመጣ ከሥጋው እንዳያበላቸውና እንዳያጠጣቸው አለቃውን ለመኑት። እግዚአብሔር በባለማሎች አለቃ ፊት ቸርነትን አደረገላቸው። ❤ የባለሟሎች አለቃም "ንጉሡ ጌታዬን እፈራዋለሁ የምትበሉትንና የምትጠጡትን ምግባችሁን ስለ አዘዘ ከባልንጀሮቻችሁ እናንተን ከስታችሁ ቢያያችሁ ንጉሥ ራሴን ይቀጣኛል" አላቸው። በእነርሱ ላይ የተሾመ አሚሳድን እንዲህ አሉት "እኛን ባሮችን ዐሥር ቀን ፈትነን ከምድር ዘር ሽምብራን ይስጡን እንበላ ዘንድ ውኃንም እንጠጣ ዘንድ"። ቃላቸውንም ሰምቶ ዐሥር ቀን ፈተናቸው ዐሥር ቀንም ከአለፈ በኋላ የንጉሥን ማዕድ ከሚመገቡ ከእነዚያ ልጆች ይልቅ ሰውነታቸው ወፍሮ መልካቸውም አምሮ ታየ። ❤ ከዚህ በኋላ አሚሳድ የሚበሉትን ምግብ የሚጠጡትን ወይን እየወሰደ ለአራቱ ሁሉ ልጆች ሽምብራ ይሰጣቸው ነበር። እግዚአብሔር ዕውቀትንና ጥበብን መጻሕፍትን በማንበብ ሁሉ ማስተዋልን ሰጣቸው። ❤ ከዚህ በኋላ ንጉሥ ያዘዘው ቀን በተፈጸመ ጊዜ ወደርሱ አመጡአቸው የባለሟሎችም አለቃ ወደ ንጉሡ ወደ ናቡከደነጾር አገባቸው። ንጉሡም ጠየቃቸው በሰው ሁሉ ዘንድ እንደ አናንያና እንደ ዳንኤል፣ እንደ ሚሳኤልና እንደ አዛርያ ያለ አልተገኘም በንጉሡም ፊት ቆሙ። ንጉሡም የፈለገውን የምክርና ጥበብን ነገር ሁሉ በግዛቱ ካሉ ጠንቋዮችና አስማተኞች ሰዎች ሁሉ ይልቅ በነሳቸው ዘንድ ዐሥር እጥፍ አገኘ። ንጉሡም እጅግ ወደዳቸው በባቢሎን አገር ሁሉ ላይ ገዢዎች አድርጎ ሾማቸው። ❤ ንጉሥም ጣዖትን ከወርቅ ባሠራ ጊዜ ሰዎች ሁሉ እንዲሰግዱለት አዘዛቸው። ሦስቱ ልጆችም ለዚያ ጣዖት ባልሰገዱ ጊዜ የሚቀኑባቸው ወደ ንጉሥ ነገር ሠርተው በንጉሥ ፊት አቀረቧቸው ስለ አልሰገዱለትም ጠየቃቸው እነርሱም "እኛስ ለሠራኸው ለወርቅ ምስል አንሰግድም" አሉት። ንጉሥም ተቆጥቶ ከምትነድ የእሳት ምድጃ ውስጥ ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ። እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ የእሳቱን ነበልባል አጠፋው በጥዋት ጊዜ እንደሚቀዘቅዝ በእሊህ ሦስት ልጆች ዘንድ እንደ ጥዋት ውኃ ቀዝቃዛ አደረገላቸው። ከዚያም የእሳቱ ነበልባል አርባ ዘጠኝ ክንድ ያህል ከፍ ከፍ ብሎ በውጪ ያሉትን አቃጠላቸው እሊህን ሠለስቱ ደቂቅን ግን ምንም አልነካቸውም። ንጉሥም ይህን ድንቅ ሥራ አይቶ በፊታቸው ሰገደ። የሰማይና የምድር ፈጣሪ እግዚአብሔርንም አመነ ለእሊህም ልጆች ሹመታቸውን ከፍ ከፍ አድርጎ ክብርን ጨመረላቸው። ❤ ከዚህም ዓለም የሚወጡበት ጊዜ ሲደርስ በበዐታቸው እየጸለዩ ሳለ ሰግደው ነፍሳቸውን ግንቦት10 ቀን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። ወዲያውኑ ታላቅ ንውጽውጽታ በባቢሎን አገር ሆነ። ንጉሡም ፈርቶ "ስለ ምን ይህ ታላቅ ንውጽውታ ሆነ?" ብሎ ነቢዩ ዳንኤልን ጠየቀው ነቢይ ዳንኤልም "ይህ ሦስቱ ልጆች ስለ አረፉ ከዓለም ለመውጣታቸው ምልክት ነው" ብሎ ነገረው። ንጉሡም ወደርሳቸው ሦስት ሣጥኖችን እንዲሠሩላቸው በሐር በግምጃ ልብሶች ገንዘው ቅዱሳኑን በሣጥኑ ውስጥ እንዲያኖሩአቸው አዘወ ንጉሡ እንዳዘዛቸውም አደረጉ። ሁለተኛም የወርቅ ሣጥን ሠርተው እርሱ በሚሞት ጊዜ ሥጋውን በውስጡ አድርገው በከበሩ ሠለስቱ ደቂቅ መካከል እንዲያኖሩት አዘዘ እንዲሁም አደረጉለት። ❤ ከዚህ በኋላ የከበረ አባት አባ ቴዎፍሎስ በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና በተሾመበት ወራት በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ሠራ ሥጋቸውን ወደዚያች ቤተ ክርስቲያን ሊያመጣ ወዶ ሥጋቸውን እንዲያመጣለት አባ ዮሐንስ ሐፂርን ወደ እርሳቸው አገር ባቢሎን ላከው። ወደ ባቢሎን አገርም በደረሰ ጊዜ ወንዞቿን አየ በውስጧም ከቶ ሰው አልነበረም የወርቁ ምስልም በዚያ አለ። ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም የቅዱሳን ሥጋ ወደአለበት አደረሰው የንጉሡም ሥጋ በመካከላቸው ነበር። ሥጋቸው በአለበትም ቦታ ሰገደ። እንዲህም ብሎ በማልቀስ ጸለየ "የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ የከበረ አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ በስማችሁ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ሥጋችሁን በውስጧ ሊያኖር እኔን ልኮኛልና ከእኔ ጋራ ትሔዱ ዘንድ ፈቃዳችሁ ይሁን"። በዚያን ጊዜ እንዲህ የሚል ቃል ከሥጋቸው ወጣ "ለሃይማኖት አባት ለአባ ቴዎፍሎስ እንዲህ በለው የድካምህን ዋጋ እግዚአብሔር ይስጥህ ነገር ግን እኛን እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ሥጋዎቻችን ከንጉሡ እንዳይለዩ እግዚአብሔር ስለአዘዘን ከዚህ አንወጣም ድካሙንም ከንቱ አናደርግም። ቤተ ክርስቲያኒቱ በምትከብርበት ዕለት በሌሊት መብራቶችን ይሰቅሉ ዘንድ እንዲአዝ በውስጣቸውም ዘይትና ፈትል እንዲያደርጉ በእሳት ግን አይለኩሱአቸው። እኛም ከዚያ ደርሰን በእኛ የእግዚአብሔር ኃይል በዚያ ይገለጣል ብለህ ንገለው" አሉት። ❤ አባ ዮሐንስ ሐፂርም ተመልሶ እንደነገሩት እንዴትም እንዳዘዙት ሁሉንም ለአባ ቴዎፍሎስ ነገረው እርሱም ሠለስቱ ደቂቅ እንዳዘዙ አደረገ። በዚችም በግንቦት ወር በዐሥር ቀን ቤተ ክስቲያኒቱ በምትከብር ሌሊት የከበሩ ሠለስቱ ደቂቅ ተገለጡ ያለ እሳትም መብራቶችን አበሩ ሊቀ ጳጳሳቱና ለዚህ ጸጋ የታደሉ ሁሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ እርከን ላይ ሲዞሩ ሠለስቱ ደቂቅን አዩአቸው በየአይነቱ በሆነ ደዌ የታመሙ ብዙ በሽተኞችም ከቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ መገለጥ የተነሣ ያን ጊዜ ተፈወሱ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሠለስቱ ደቂቅ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።                                + + + ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_አብርሃም_ፀራቢ፦ ይህም ከሰማዕቱ ቴዎድሮስ ገዳም ከመርቅያስ አገር ሰዎች የተገኘ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ የቤተክርስቲያንን ትምህርት እየተማረ አድጎ በታላቅ ገድል መኖር ጀመረ፡፡ ዕድሜውም ዘጠኝ ዓመት በሆነ ጊዜ ከድንጋይ የሚሠራ የውኃ መሄጃ መጥረብን ተማረና እርሱን ሠርቶ እየሸጠ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች ይመጸውት ነበር፡፡ በሌሊትም ሲጸልይ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ ይሞት ዘንድ ሁልጊዜ ይለምን ነበር፡፡ ከጸሎቱም በኋላ አንድ ቀን የታዘዘ መልአክ ተገልጦለት የሰማዕትነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለትንሣኤ_ስድስተኛ_ሳምንት እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፫ "#ፋሲካ_ዛቲ_ዕለት_ቅድስት_ይእቲ፤ አዝ፣ ዛቲ ዕለት ንትፈሣሕ ባቲ፤ አዝ፣ ንትፈሣሕ ባቲ ወንትሐሠይ ባቲ፤ ዛቲ ዕለት ናኅይ ወዕረፍት፤ አዝ፣ ሰማይ ወምድር ይትፌሥሑ ባቲ፤ አዝ፣ #ፋሲካ_ፋሲካ_ተዝካረ_ትንሣኤሁ_ለመድኀኒነ። ትርጉም፦ ይህቺ ዕለት የተለየች #የደስታ_ቀን_ናት፤ በዚች ዕለት እንደሰትባት፤ ፈጽመን ሐሤት እናድርግባት፤ ይህቺ ዕለት የዕረፍትና የእፎይታ ዕለት ናትና፤ ሰማይና ምድር ይደሰቱባታል፤ ይህቺውም #የመድኀኒታችን_የትንሣኤው_መታሰቢያ_ፋሲካ_ናት። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"በልዑ ወጸግቡ ጥቀ። ወወሀቦሙ ለፍትወቶሙ። ወኢያኅጥዖሙ እምዘፈቀዱ"። መዝ 106፥16-17 ወይም 77፥29-30። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 4፥14-ፍ.ም ወይም ሮሜ 6፥1-15፣ ራዕ 20፥1-ፍ.ም ወይም 1ኛ ጴጥ 4፥4-12 እና የሐዋ ሥራ 10፥39-44 ወይም 23፥15-22። የሚነበቡው ወንጌል ዮሐ 21፥1-14 ወይም 21፥15-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም ዕለተ ሰንበትና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ። ሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ለዘጠኝ ዓመት በዓባይ ባሕር ውስጥ በራሳቸው ተዘቅዝቀው በመቆም ስለ ኢትዮጵያውያ ሕዝብ ለጸለዩ ለታላቅ አባት #ለአቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ_በቅዱስ_ኤልያስ_ሠረገላ ወደ ሰማይ ተነጥቀው ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት በመላእክት እጅ ላዐረጉበት በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በፍቅር አደረሰን።                           ✝️ ✝️ ✝️                   ❤ #የአባታችን_አቡነ_እስትንፋ_ክርስቶስ_ተአምር ይህ ነው ጸሎቱና በረከቱ ከእኛ ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፦ከዕለታት በአንዲት ቀን በግንቦት  ወር አባታችን አብነ እስትንፋሰ ክርስቶስ  በብርሃን ሠረገላ ወደ ሰማይ ሲያርግ አንድ ዓይኑ የጠፋ እግሮቹ ልምሾ የሆኑ ሰው አባቴ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ በጸሎትህ ፈውሰኝ ብሎ ተማጸነው፡፡ አባታችንም ያንን ሰው በአየ ጊዜ አዝኖለት በእጁ ያለውን መሐረብ ወረወረለት በዚያን ጊዜ ልምሾ የነበሩ እግሮቹ ዳኑ ዓይኑም በራለት አባታችን እስከ ዕለተ ሞትህ ለሰው አትናገር አለው፡፡ ❤ ከዚህ በኋላ አባታችን በነፋስ ሠረገላ ሄዶ የሕያዋን ጻድቃን መኖሪያ ወደ ምትሆን ሰማያዊት እየሩሳሌም ደረሰ ከዚህ በኋላም ወደ ጽርሐ አርያም ደርሰ ከዚህ በኋላ ወደ ጽርሐ አርያም ደርሶ እንደ አስለመደው ከሃያ አራቱ ቅዱሳን ጓደኞቹ ጋር የጌታን መንበር አጠነ በዚያ ጊዜ ሰማያዊ ኅብስት ከነፃህሉ ወይኑ ከነጽዋው ቀርቦለት ዚያ ቦታ በቀደሰ ጊዜ ጣቶቹ በክርስቶስ ደም ታለሉ ሁለንተናውም እንደ እሳት ተንቦገቦ በዚያ ሥጋ ወደሙን ተቀበለ፡፡ ❤ ጌታችንም ለእሱና በዓሉን ለአከበሩ መንፈሳዊውያን ልጆቹ የሰጠውን ሰማያዊ ቤትንም አየ( ተረከበ) ይህንን ሁሉ አስተካክሎ መላእክት እየተከተሉት ወደ ቦታው በሰላም ተመለሰ፡፡ በጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ከማኅበር ልጆች ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ ይደረግን። ይህን ያደረገበት ግንቦት 9 ቀን ከአባታችን አበይት እና ዓመታዊ በዓል አንዱ ሆና ታስቦ ይውላል፡፡ ምንጭ፦  ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ተአምር።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ለጻድቁ_ንጉሥ_ለቈስጠንጢኖስ_እናት የጌታችን መስቀል ከተቀበረበት ላገኘችው #ለንግሥት_ቅድስት_እሌኒ ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪም በዚች ከሚታሰቡት፦ ከበይደርና ስልዋኖስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝️ ✝️ ✝️                       ❤ #ንግሥት_ቅድስት_ዕሌኒ፦ ይቺም ቅድስት በፊት የአንድ ነጋዴ ሰው ሚስት ነበረች እርሱም በነገረ ሠሪ ንጽሕት ሁና ሳለች ወደ ባሕር ጣላት። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ፈቃድም ሮሐ ከሚባል አገር ደርሳ የበራጥያ ንጉሥ ቊንስጣ አገኛት። ውበቷንና ደምግባቷንም አይቶ አገባት። ለክርስቲያን ነገሥታት መጀመርያቸው የሆነውን ቈስጠንጢኖስን ወለደችው ምግባርንና ሃይማኖትን በማስተማር በመልካም አሳደገችው። ❤ ልጇም በነገሠ ጊዜ "ወደ ኢየሩሳሌም ሔደሽ የክብር ባለቤት የሆነ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ግለጪ የከበሩ ቦታዎችንም ሥሪ" የሚላትን በሕልሟ አይታ እንዴት እንዳየች ይህን ለልጇ ነገረችው እርሱም ከብዙ ሠራዊቱ ጋራ ሰደዳት። በደረሰችም ጊዜ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን መስቀል መረመች አዳኝ የሆነ መስቀሉንም ሁለት ወንበዴዎች ከተሰቀሉባቸው መስቀሎች ጋራ አገኘችው። የክብር ባለቤት የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የትኛው እንደሆነ ታውቅ ዘንድ በወደደች ጊዜ ከራሱ በላይ "ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው" የሚል በእንጨት የተቀረጸበት ጽሑፍ ያለው እንደሆነ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ቅዱስ መቃርስ ነገራት። ❤ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ምልክት ታይ ዘንድ ፈለገች የሞተ ሰውም አግኝታ መስቀሎችን በበድኑ ላይ አኖረች አልተነሣም። ከዚህ በኋላ ሦስተኛውን መስቀል በላዩ አኖረች። ያን ጊዜ ያ ምውት ተነሣ ሃይማኖቷም ጸና ደስታዋም በዛ። ❤ ከዚህ በኋላ ዜናቸው በመስከረም ወር በዐሥራ ሰባት የተጻፈ በከበሩ ቦታዎች ውስጥ አብያተ ክርስቲያናትን ትሠራ ዘንድ ጀመረች። ለአባ መቃርስም በከበሩ ቦታዎች ሁሉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲሠራ ብዙ ገንዘብ ሰጠችው። ❤ ከዚህ በኋላ ወደ ልጇ ተመልሳ የሆነውን ሁሉ ነገረችው የከበረ መስቀል በመገኘቱ እጅግ ደስ አለው። ይቺም ቅድስት በጎ ገድላሏን ከፈጸመችና እግዚአብሔርንም ከአገለገለች በኋላ ስለ ካህናትም ልብስና ቀለብ ለአብያተ ክርስቲያናትና ለገዳማት ብዙ ጉልቶችና ርስቶችን ለድኆችና ለምስኪኖችም እንዲሁ ከሠራችና ከተከለች በኋላ ግንቦት9 ቀን በሰላም ዐረፈች መላ ዕድሜዋም ሰማንያ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ዕለኔ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ የግንቦት 9 ስንክሳር።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ አንተ ፈጠርከ ኵልያትየ እግዚኦ። ወተወከፍከኒ ከመ አእምር። እገኒ ለከ እግዚኦ እስመ ግሩመ ተሰባሕከ"። መዝ 138፥13-14 ወይም መዝ 59፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ማር 14፥26-32 ወይም ዮሐ 16፥15-22።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ኤርትራ አገር ሁለት ታላላቅ ገዳማት ለመሰረቱ፤ #ቅዱስ_አብሃርም_ቅድስት_ሥላሴ በአንድነትና በሦስትነት ለተገለጹላቸው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ብፁዕ_አምላክ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ብፁዕ_አምላክ፦ እኚህ ጻድቅ የአባታቸው ስም ቅዱስ አፍቅረነ እግዚእ ሲሆን የእናታቸው ስም ደግሞ ቅድስት ማርያም ዘመዳ ሲባሉ በ1425 ዓ.ም መስከረም 1 ቀን ትግራይ ክልል ልዩ ስሙ መከዳ በተባለ ቦታ ተወለዱ። እስከ ሰባት ዓመታቸው በእናትና አባታቸው ቤት ከኖሩ በኋላ በስምንት ዓመታቸው ወደ ደብረ ቢዘን ገዳም ገብተው የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሲማሩ በገዳማዊ ኑሮ ሲያገለግሩ ቆይ እስከ 25 ዓመታቸው ከቆዩ በኋላ በዛው በደብረ ቢዘን በ25 ዓመታቸው መነኵሰዋል። ❤ ከዚያም ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገብተው ለ 5 ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በድጋሚ በእግዚአብሔር ፈቃድ ወደ ኤርትራ አገር ወደ መጀመርያ ወደ መሰረቱ ገዳም ደብረ ኰዳዱ ሔደው በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብተው የጌታችን ሕማማተ መስቀልን በማሰብ በ1000 ችንካሮች እራሳቸው ቸክረው ለ30 ዓመታት ሲጋደዱ ኖሩ በዛው ሳሉ አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ለአብሃም እንደተገጹ ለእርሳቸውም በአንድነትና በሦስትነት ታኅሣሥ 1 ቀን ተገለጡላቸው እርሳቸው ቅድስት ሥላሴ መሆናቸው ለማረጋገጥ የቆሙበት ድንጋይ ለሦስት ቦታ ተከፈለ  እንደ ገና ደግሞ ተመልሶ ወደ አንድ ተለወጠ በዚህ የተገለጡላቸው ቅድስት ሥላሴ እንደሆኑ አረጋገጡ ቃል ኪዳን ከገቡላቸው በኋላ። ❤ መጨረሻ የሚያርፉበት ቦታ ነግረዋቸው ተሰወሩ ከዚያም ወደ ሁለተኛ ወደ መሰረቱት ገዳም ደብረ ምዕዋን ገብተው ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ግንቦት 9 ቀን 1500 ዓ.ም በ75 ዓመታቸው ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ተቀብለው ዐርፈዋል። አጽማቸውም እስካሁን በዛው በደብረ ምዕዋን ይገኛል። ከአባታችን አቡነ ብፁዕ አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገዳሙ የተገኘ ማስታወሻ።