Construction Contractors Association of Ethiopia
Ko'proq ko'rsatish
1 932
Obunachilar
+324 soatlar
+357 kunlar
+2230 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም
Photo unavailableShow in Telegram
6ተኛ ዙር የኮንስትራክሽን የሙያ ደህነትና ጤንነት ስልጠና ምዝገባ ተጀምራል!
አሁኑኑ ፈጥነው ይመዝገቡ!
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም
Photo unavailableShow in Telegram
6ተኛ ዙር የኮንስትራክሽን የሙያ ደህነትና ጤንነት ስልጠና ምዝገባ ተጀምራል!
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም
በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ስፋት እና ይዘቱ አዲስ ከተማን የመገንባት ላይ ሲሆን በውስጡ ከላይ የምትመለከቱትን ይመስላል።
(ከፅ/ቤት)
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም
በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ስፋት እና ይዘቱ አዲስ ከተማን የመገንባት ያህል ሲሆን በውስጡ ከላይ የምትመለከቱትን ይመስላል።
(ከፅ/ቤት)
“የኮንስተራክሽን ኢንዱስትሪው በሙያ ደህንነትና ጤና ዙሪያ በአቅም ግንባታ ስልጠና እየታገዘ ነው"
🚧የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር በ2016ዓ/ም በጀት ዓመት ታህሳስ ወር ላይ ከኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት እንዲሁም ከከኮንስትራክሽን ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሦስትዮሽ የመግባቢያ ሰነድ ከተፈራረመ በኋላ ስራ ተቋራጮች አስገዳጅ ሆነው በሚወጡ ህጎች ሳቢያ የብቃት ማረጋገጫ ምዝገባ ላይ እክል እንዳይገጥማቸው የሚወጡ ረቂቅ ህጎች ላይ ግብረ መልስ ከመስጠት በተጨማሪ የማኅበሩ አባላትን በተለያዩ ዘርፎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን አንዲወስዱ የራሱን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
🚧በዚህ መሰረትም ከየካቲት 28 እስከ ሚያዚያ 11 ቀን 2016 ዓ/ም በተለያዩ አምስት ዙሮች ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር የሁለት ሙሉ ቀናት ስልጠና በ Health and Safety in Construction ዙሪያ እንዲሰጥ አድርጓል፡፡
🚧በዚህም የመጀመሪያ ክፍል አምስት ዙሮች ላይ 194 ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን የድርጅት ባለቤቶች፣ስራ አስኪያጆች እና በድርጅቶቹ የተወከሉ መሐንዲሶች ተሳትፈዋል፡፡
🚧የምስክር ወረቀት የመስጠት ስነ-ሥርዓቱም ማክሰኞ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በተገኙበት ተከናውኗል፡፡
🚧ክብርት ሚኒስተሯ መንግስት በአካባቢ ብክለት እንዲሁም በሙያ ደህንነት እና ጤንነት ዙሪያ መንግስት አስገዳጅ የሆነ ፖሊሲና የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ወደ ስራ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
🚧አሰገዳጅ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን የሚወስዱ ስራ ተቋራጮች መንግስት በዘረጋቸው ሰፋፊ ፕሮጀክቶች ላይ የስራ እድል በውደድር የሚያገኙበት ሁኔታ ቢመቻች ተብለው ከተሰታፊ ስራ ተቋራጮች የተጠየቁት ክብርት ሚኒስተሯ በጎ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
🚧የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማኅበር ጋር በሚወጡ ህጎች ዙሪያ በቅርበት እየሰራን ነው ካሉ በኋላ ስራ ተቋራጮች ራሳቸውን በአቅም በማሳደግ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡
🚧የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ታምራት ሙሉ፤ ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትን አቅም ማጎልበት ላይ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ይህ በ Health and Safety in Construction ዙሪያ ለሥራ ተቋራጮች የተሰጠው ስልጠና የዚሁ አካል ነው ብለዋል፡፡
🚧የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ግርማ ኃብተማሪያም የኮንስትራክሽን የሙያ ደህንነትና ጤንነት በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ እንዲውል እየተደረገ ባለው የሙያ ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ላይ እንደ አንድ አስገዳጅነት ያለው መሥፈርት ሆኖ በመቀመጡ የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጭ ድርጅቶች ሙያተኞቻቸውን ለሥልጠና እንዲሊኩ እና ለተግባራዊነቱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ አድረጓቸዋል ብለዋል፡፡
🚧የሙያ ደህንነትና ጤንነት ስልጠና እና ሰርተፍኬት ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ አስገዳጅ ስለሚሆን ከዚህ በፊት ላልሰለጠኑ ሥራ ተቋራጮች ስለጠናውን በማኅበሩ አማካኝነት በመመዝገብ እንዲወስዱ ጥሪ ቀርቧል፡፡
🚧ማኅበሩ የ2017ዓ/ም በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆኑ የተለያዩ የስልጠና ፓኬጆችን የነደፈ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነውን የHealth and Safety in Construction ስልጠና ስድስተኛ ዙርን ከሐምሌ ጀምሮ ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
🚧ባለፉት አምስት ዙሮች ስልጠናውን ያልወሰዳችሁ ድርጅቶች የድርጅታችሁን ስም እንዲሁም የሰልጣኝ ስም እና ስልክ ቁጥር በማድረግ ምዝገባውን በዚሁ ቻናል ወይንም በስልክ ቁጥር 0941808788 መልዕክት በመላክ ማከናወን እንደሚቻል ማኅበሩ አሳስቧል፡፡
Po'stilar arxiv
Boshqa reja tanlang
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.