cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

መዝሙር ግጥሞች ቤት

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ሥርዓትን የምንማማርበት Channel ነው !  ወደ ቻናላችን በመቀላቀል 👇 ➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መፅሐፍትን በPDF ➲ስንክሳር ትምህርቶች ➲ መዝሙራትን በግጥሞች ➲ ኪነ-ጥበብ ➲ ጥያቄዎችን በሐይማኖት ብትኖሩ እራሳችሁን መርምሩ"   ( 2ኛቆሮ -13 ፥ 5)👇 Group ገጽ👇👇 https://t.me/Orthodoxs_Tewahdo_menfeswi_group

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
16 268
Obunachilar
+6324 soatlar
+7167 kunlar
+2 44230 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
•➢ ጾመ ሐዋርያት መች ይገባል እና ዓርብ ረቡዕን የምንጾምበት ምክንያትና ሌሎች ጥያቄዎችን መልስ ያገኙበታል 👇👇👇
Hammasini ko'rsatish...
አሁኑኑ ይቀላቀሉ 📍
🎚JOIN 🔐
" ጥያቄ " ------------- ➪ ዔሳው ለወንድሙ ያዕቆብ ብኩርናውን በምን ሸጠ ?
Hammasini ko'rsatish...
ሀ. በ30 ዲናር
ለ. በ2 መክሊት
ሐ. ሀ/ እና ለ/
መ. በምስር ወጥ
Photo unavailableShow in Telegram
🕊  💖  ▬▬    †    ▬▬  💖  🕊 [ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ [  ❝  ባሕርዩን ሳይለቅ ሰው ሆነ !  ❞  ] 🕊 ❝ መድኃኒታችን በሥጋ ያደረገውን ተዋሕዶ አምናለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቃል በአካሉ በባሕርዩ ጸንቶ ኖሯልና ፤ ሰውን ያድሰው ዘንድ ሳይለወጥ ፤ ባሕርዩን ሳይለቅ ሰው ሆነ፡፡ ከእግዚአብሔር አብ በተወለደው በቀዳማዊ ልደቱ የእግዚአብሔር አብ ልጅ ነው፡፡ ከድንግል በተወለደው በደኃራዊ ልደቱ የሰው ልጅ ሆነ፡፡ [ገላ.፬፥፬] እርሱ አንዱ በመለኮት ከአብ ጋር  አንድ የሚሆን የሚተካከል ፍጹም አምላክ ነው ፤  እርሱ ብቻ ከድንግል በተወለደው ልደት በሥጋ ከሰው ጋር አንድ የሚሆን ፍጹም ሰው ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ሥጋን ይዞ እንደመጣ የሚናገር ወይም ጌታችን የተዋሐደው ሥጋ በቅድምና በመኖር ከአብ ጋር ትክክል ነው የሚል ቢኖር የተወገዘ የተለየ ይሁን፡፡ ጌታችን የተዋሐደው ሥጋ ከድንግል እንደተገኘ ከእኛም ጋር አንድ እንደሆነ የማያምን ቢኖር የተወገዘ የተለየ ይሁን፡፡ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ነሥቶ ሰው ስለሆነ ስለ ጌታችን ስለ መድኃኒታችን ሥጋው ነፍስ የሌለው ነው ፣ ምትሐት ነው ወይም የማይናገር ነው የሚል ሰው ቢኖር የተወገዘ የተለየ ይሁን። ክርስቶስ በሥጋ ስለ እኛ የታመመ የሚለውን የመጽሐፍን ቃል ትቶ ደፍሮ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ያይደለ በመለኮት ታመመ የሚል ቢኖር የተወገዘ የተለየ ይሁን። ❞ [      ቅዱስ ናጣሊስ      ] ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። †                       †                         † 💖                    🕊                     💖
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?👇👇👇
Hammasini ko'rsatish...
🎤 ሊቀ መዘምራን . ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ሐይሌ
🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
🎤 ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
🎤 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
📌 የሁሉንም ዘማሪዎች መዝሙር 🔐
📌ትክክለኛውን ቁልፍ በመጫን ይምረጡ👇🔐 ---------------------------------------------------------- ➠ የቅዱስ ጳውሎስ የቀድሞው ስሙ ማን ነበር ?
Hammasini ko'rsatish...
🔐 ሳኦል
🔐 ሳውል
🕊 †  እንኩዋን ለሐዲስ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ  † 🕊  †  ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ  †  🕊 ሰማዕቱ የተወለደው በምድረ ግብጽ አሕዛብ [ተንባላት] በሰለጠኑበት የመጀመሪያው ዘመን ነበር:: በተለይ ተንባላቱ ግብፅና ሶርያን ከያዙ በሁዋላ ባልተጠበቀ ፍጥነት በኃይልም በሰውም ተደራጅተው ነበር:: ቅዱስ ጊዮርጊስ [ልብ በሉልኝ ሊቀ ሰማዕታት አይደለም] የተወለደው በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር:: እናቱ የተመሠከረላት ክርስቲያን ብትሆንም እንዳለመታደል አባቱ ተንባላታዊ [አሕዛብ] ነበር:: ስሙንም መዛሕዝም ይሉታል:: ሕጻኑ እንደተወለደ ያወጡለት ስም አሕዛባዊ ከመሆኑ ባለፈ በሰዓቱ መጠመቅ አልቻለም:: የወቅቱ ሕግ ከወላጆቹ አንዱ አሕዛባዊ ከሆነና አጠምቃለሁ ቢባል የሚከተለው ሰይፍ ነበር:: በዚሕ ምክንያት ሳይጠመቅ ፯ [7] ዓመት ሞላው:: እናቱ ግን ሕጻን ቢሆንም ፍቅረ ክርስትናን ታስተምረው ነበር:: ባይጠመቅም ጸበሉን: እመቱን ትቀባው ነበር:: ደብቃ ቅዳሴ ታሰማውም ነበር:: አንድ ቀን ግን ሕጻናት ሲቆርቡ አይቶ ካልቆረብኩ ብሎ አለቀሰ:: ምን ታድርገው? ወደ ውጪ አውጥታ ከአውሎግያ [የሰንበት በረከት] አበላችው:: "ጌታየ! ልጄን እርዳው" አለች:: ልክ በአፉ ሲቀምሳት መዓዛ መንፈስ ቅዱስ አደረበትና ፍጹም ተደሰተ:: ትንሽ ከፍ ሲል ለምን እንደማይጠመቅና እንደማይቆርብ እናቱን ጠየቃት:: "ልጄ ሆይ! ይገድሉሃል" አለችው:: ከዚህች ቀን ጀምሮ የሚጠመቅበትን ዘዴ ይፈልግ ጀመር:: አስቀድሞ ትምሕርተ ክርስትናን ተማረ:: ለአካለ መጠን ሲደርስ አፈላልጐ ጠንካራ ክርስቲያን የሆነች ሴት አገባ:: ጥቂት ጊዜ ከቆየ በሁዋላ ሚስቱን ስለ መጠመቅ አማከራት:: "ሌላ ሃገር ሒደህ ተጠመቅ" አለችው:: ከግብፅ ተነስቶ ሶርያ ገባ:: አባቶችን አፈላልጎ ተጠመቀ:: ቀጥሎም መንገዱን ወደ ልዳ አደረገ:: ወደ ደብሩ ተጠግቶ አባቶችን "ስም አውጡልኝ" ቢላቸው መንፈስ ቅዱስ አናግሯቸው "ጊዮርጊስ" አሉት:: እሱም ደስ እያለው: ባጭር ታጥቆ የልዳውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያገለግለው ገባ:: ትንሽ ቆይቶ ሁከት መንፈሳዊ ተሰማው:: ማለትም ስለ ሃይማኖቱ ደሙን ማፍሰስ ፈለገና ወደ ግብፅ ተመለሰ:: በዚያ ያሉ አሕዛብ በክርስትና ስም: ልብስና ሞገስ ሲመለከቱት ተበሳጩ:: ዕለቱኑ አሠሩት:: ሌሊት እናቱና ሚስቱ መጥተው አሉት:- "አደራ! ፍቅረ ዓለም እንዳያታልልህ:: ሰማዕት ብትሆን ላንተም ክብር: ለእኛም ሞገስ ነው" ብለውም አጽናኑት:: [ እንዲሕ ያሉ እናትና ሚስት ማግኘትም ታላቅ እድል ነው!!! ] ሐዲስ ጊዮርጊስም ጸና:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ደበደቡት: አካሉን ቆራረጡት: ደሙንም መሬት ላይ አንጠፈጠፉት:: በየመንገዱ እየጎተቱ ተሳለቁበት:: እርሱ ግን ክርስቶስን ወዷልና ሁሉን ታገሰ:: ሌሊት በሆነ ጊዜም ጌታችን ተገልጦ "ከሰማዕታት ተቆጠርህ" አለው:: በማግስቱ በአደባባይ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡት:: ክፋታቸው የጸና ነውና ሥጋውን በእሳት አቃጠሉት:: ወደ ባሕርም ጣሉት:: እናቱ ከባሕር ስታወጣው ግን ምንም አላገኘውም ነበር:: በዚሕች ቀን እናቱና ሚስቱ በክብር ቀብረውታል:: ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ ጽናትን: ትእግስትን: ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: 🕊 † ሰኔ ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ ሰማዕት ፪. አባ ብሶይ አኖብ ሰማዕት [ በአንበሳ ጀርባ ላይ የተቀመጠ አባት ] ፫. ቅዱሳን ፭ቱ "5ቱ" ጭፍሮች [ በብዙ ስቃይ ሰማዕት የሆኑ ባልንጀሮች ] ፬. አባቶቻችን የደብረ ቁዋዐት ጻድቃን [ †  ወርሐዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት ፫. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ ፬. አቡነ ስነ ኢየሱስ ፭. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም " ስለዚሕ ወንድሞቼ ሆይ ! ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ:: ልባሞች እንደመሆናችሁ እላለሁ:: በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ:: የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን ? . . . እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ  ነን:: ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና:: " [፩ቆሮ.፲፥፲፬-፲፰] (10:14-18) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.