uz
Feedback
Tamiru Yacob - Attorney at Law

Tamiru Yacob - Attorney at Law

Kanalga Telegram’da o‘tish

⚖ ዚኢትዮጵያ ሕግ አዳዲስ ለውጊቜ 📚 ዹሰበር ውሳኔዎቜ 📜 አዋጆቜና ደንቊቜ 💡 በቀላሉ ዚተብራሩ ዹሕግ መሚጃዎቜ ለማግኘት ቻናላቜንን ይቀላቀሉ 📞 0913661521

Ko'proq ko'rsatish
4 043
Obunachilar
-124 soatlar
-147 kun
-2730 kun
Postlar arxiv
Job Vacancy Notice Position: Legal Assistant Location: Addis ababa Salary: negotiable Job Type: Full-time Kehase Gebrehiwot, attorney at Law is seeking a dedicated and motivated individual to join their law practice as a Legal Assistant. This is an excellent opportunity for individuals who are looking to start their career in the legal field with no prior experience required. Responsibilities: - Assist attorneys in legal research and document preparation. - Organize and maintain legal files, documents, and records. - Draft and proofread legal documents, including contracts, pleadings, and correspondence. - File prepared legal documents with courts, collect necessary summons and orders from courts, serve court orders and summons with relevant private, public or governmental insititution and recieve response letters. - appear before a court of law with or without the lead attorney, as may be necessary. **Background               : LLB from recognisable university              :fluency in the English and amharic languages                : basic computer and typing skills              : No previous working experience  required Interested and qualified applicants can apply through the following email adress. Email:- kahase84@gmail.com P.S. Please submit your application exclusively via email. Applications submitted through any other methods will not be accepted or reviewed.  

New Criminal procedure and evidence Code 2018 Final.pdf13.01 MB

photo content
+2

ወይም ዚኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶቜን በፈፀሙ ሰዎቜ ላይ ክስ ማቅሚብ በይርጋ አይታገድም። ማጠቃለያ ዹወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎቜ ፍትሕ ዚሚያገኙበት ዹሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል ዚተጠሚጠሩ ወይንም ዚተኚሰሱ ግለሰቊቜ ነፃነት በሕግ ዚሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠሚት ዹወንጀል ክስ መመስሚቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶቜ መካኚል ሚዛን ለመጠበቅ ዚሚያስቜል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡

ዹወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ ******** መግቢያ ወንጀል ፈፃሚዎቜ ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠዹቃቾውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቾው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ አንድ እንደተመለኚተው በወንጀል ሕጉ መሰሚት ወንጀል ዹተደሹጉ ድርጊቶቜ እና ዚሚያስኚትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎቜ ወንጀል ኹመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ ዚሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎቜ በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎቜ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ኹመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎቜም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድሚግን ግቡ ያደሚገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለኹተው ዹጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠሚት እና አጥፊዎቜን ለሕግ ማቅሚብ ዚሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ ዚሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጜሑፍ ዹወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ ዹተመለኹተውን ዚክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም ዚክስ ይርጋ ዘመን መቋሚጥና መታገድ በአጭሩ እንመለኚታለን፡፡ ዹወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት ዹወንጀል ሕጉ ዹወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለኹተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ኹወንጀል ሕግ አንቀጜ 217 በመነሳት ዹወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቾውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቀቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ኚመታዚት ዚሚታገድበት በሕግ ዹተመለኹተ ጊዜ መሆኑን መሚዳት ይቻላል፡፡ ዹመደበኛ ክስ ይርጋ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 217 መደበኛ ዚክስ ማቅሚቢያ ጊዜን ዹደነገገ ሲሆን • ዚሞት ፍርድ ወይም ዚዕድሜ ልክ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት • ኚአስር ዓመት በላይ እስኚ ሃያ አምስት ዓመት ለመድሚስ ዚሚቜሉ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት • ኚአምስት ዓመት በላይ እስኚ አስር ዓመት ለመድሚስ ዚሚቜል ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት • ኚአምስት አመት በማይበልጥ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት • ኚአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት • እስኚ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሊስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀሚበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡ ኹዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎቜ ተፈጜመው ሲገኙ ዚወንጀሎቹ ኹፍተኛ ቅጣቶቜ ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ ዚአንዱ ወንጀል ዚክስ ማቅሚብያ ዹይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎቜ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና ዚወንጀሎቹ ኹፍተኛ ቅጣቶቜ ዚተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ኹሁሉም ኚባድ ዹሆነው ወንጀል ዚክስ ማቅሚቢያ ዹይርጋ ዘመን በሌሎቜ ወንጀሎቜ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 217(2) ይደነግጋል፡፡ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ይርጋ በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ ዹወንጀል ሕግ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ ዹተደነገጉ ወንጀሎቜ ዹግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ ዹግል አቀቱታ ካላቀሚበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰሚት በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 560 ዚእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቀቱታ ሲቀርብ ዚሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቀቱታ ዚሚቀርቡ ወንጀሎቜ ዚተፈፀመበት ዹግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 213 መሠሚት አቀቱታውን ማቅሚብ ዚሚጠበቅበት ሲሆን ዚእነዚህ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ብቻ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ዚክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 218 ተደንግጓል፡፡ ፍፁም ዹሆነ ዹይርጋ ዘመን በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 222 ፍፁም ዹሆነ ዹይርጋ ዘመን ዹተደነገገ ሲሆን በማናቾውም ምክንያት ኹላይ ዚተመለኚትነው መደበኛ ዚክስ ማቅሚቢያ ዹይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቀቱታ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ሲሆኑ ደግሞ ኹላይ ኚተመለኚትነው በግል አቀቱታ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜን ዹይርጋ ዘመን በግማሜ ዚሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ ዚሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡ ዚክስ ይርጋ አቆጣጠር በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 219 መሠሚት ዚክስ ዹይርጋ ዘመን ዚሚታሰበው ዚቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎቜ ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል ዹተደነገገውን ኹፍተኛ ቅጣት መሠሚት በማድሚግ ሲሆን ዹተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራ቞ውም ቅጣቶቜ ዚሚያስቀጣ ሲሆን ዹይርጋ ዘመኑ ዚሚታሰበው ኹሁሉም ኚባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል ዹተደነገገውን ኹፍተኛ ቅጣት መሠሚት በማድሚግ ይሆናል፡፡ ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹውም ጥፋተኛው ዹወንጀል ድርጊቱን ኚፈጞመበት ቀን አንስቶ ሲሆን ዹወንጀል ድርጊቱ እዚተደጋገመ ዹተፈፀመ ኹሆነም ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹው ዚመጚሚሻው ዹወንጀል ድርጊት ኚተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ ዹወንጀል ድርጊቱ ለሹጅም ጊዜ ሲፈፀም ዹቆዹ ኹሆነ ደግሞ ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹው ዹወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡ ዚክስ ይርጋ መታገድ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 220 ዹወንጀል ክስ ይርጋ ዚሚታገድበትን ሁኔታ ዹደነገገ ሲሆን ይኾውም  በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል ዚሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድሚስ  ክስ ቀርቩ ነገሩ በዳኝነት በመታዚት ላይ ኹሆነ ወይም በሌላ ቜሎት ዹቀሹበ ክስ ሳይፈፀም ተኚሳሹ በተኚሰሰበት ዹወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ዚማይገባ በሆነ ጊዜ ዹይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስኚተለው መሰናክል ሲወገድ ግን ዹይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡ ዹይርጋ ዘመን መቋሚጥ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 221 እንደሚያመለክተው ኹወንጀሉ ወይም ኚወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደሚግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ ዚሚሰጥ ትዕዛዝ፣ ዹሚፈፀም ድርጊት ወይም ዚሚሰጥ ውሳኔ ዹይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ዹይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠሚት ዹይርጋ ዘመኑ መቋሚጥ ፍፁም ዹሆነ ውጀት ዹሚኖሹው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቾው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋሚጡ ይፀናባ቞ዋል፡፡ ይህ ማለት ዹወንጀል ተካፋይ መሆናቾው ወንጀሉ በተኚሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎቜ ያኔ ባለመታወቃ቞ው ምክንያት ዹይሹጋ መቋሚጥ አስመልክቶ ሊኖር ዚሚቜል ልዩነት እንደሌለ መሚዳት ይቻላል፡፡ በይርጋ ዚማይታገዱ ጉዳዮቜ በመርህ ደሹጃ ዹወንጀል ድርጊቶቜ ኹተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅሚብ ዚሚቻልበት ዹጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ኹተደነገገ በይርጋ ዚማይታገዱ ወንጀሎቜ እንዳሉ ኹወንጀል ሕጉ እንቀጜ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ኹዚህ አንፃር ዚኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጜ 28(1) መሠሚት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻ቞ው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶቜና በሌሎቜ ዚአገራቜን ሕጎቜ ዹሰው ልጅ ላይ ዹተፈፀሙ ወንጀሎቜ ተብለው ዹተወሰኑ ወንጀሎቜ፣ ዹሰው ዘር ዚማጥፋት፣ ያለፍርድ ዚሞት ቅጣት እርምጃ ዚመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን ዹመሰወር

ወይም ዚኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶቜን በፈፀሙ ሰዎቜ ላይ ክስ ማቅሚብ በይርጋ አይታገድም። ማጠቃለያ ዹወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎቜ ፍትሕ ዚሚያገኙበት ዹሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል ዚተጠሚጠሩ ወይንም ዚተኚሰሱ ግለሰቊቜ ነፃነት በሕግ ዚሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠሚት ዹወንጀል ክስ መመስሚቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶቜ መካኚል ሚዛን ለመጠበቅ ዚሚያስቜል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡

ዹወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ ******** መግቢያ ወንጀል ፈፃሚዎቜ ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠዹቃቾውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቾው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ አንድ እንደተመለኚተው በወንጀል ሕጉ መሰሚት ወንጀል ዹተደሹጉ ድርጊቶቜ እና ዚሚያስኚትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎቜ ወንጀል ኹመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ ዚሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎቜ በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎቜ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ኹመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎቜም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድሚግን ግቡ ያደሚገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለኹተው ዹጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠሚት እና አጥፊዎቜን ለሕግ ማቅሚብ ዚሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ ዚሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጜሑፍ ዹወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ ዹተመለኹተውን ዚክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም ዚክስ ይርጋ ዘመን መቋሚጥና መታገድ በአጭሩ እንመለኚታለን፡፡ ዹወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት ዹወንጀል ሕጉ ዹወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለኹተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ኹወንጀል ሕግ አንቀጜ 217 በመነሳት ዹወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቾውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቀቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ኚመታዚት ዚሚታገድበት በሕግ ዹተመለኹተ ጊዜ መሆኑን መሚዳት ይቻላል፡፡ ዹመደበኛ ክስ ይርጋ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 217 መደበኛ ዚክስ ማቅሚቢያ ጊዜን ዹደነገገ ሲሆን • ዚሞት ፍርድ ወይም ዚዕድሜ ልክ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት • ኚአስር ዓመት በላይ እስኚ ሃያ አምስት ዓመት ለመድሚስ ዚሚቜሉ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት • ኚአምስት ዓመት በላይ እስኚ አስር ዓመት ለመድሚስ ዚሚቜል ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት • ኚአምስት አመት በማይበልጥ ጜኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት • ኚአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት • እስኚ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሊስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀሚበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡ ኹዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎቜ ተፈጜመው ሲገኙ ዚወንጀሎቹ ኹፍተኛ ቅጣቶቜ ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ ዚአንዱ ወንጀል ዚክስ ማቅሚብያ ዹይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎቜ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና ዚወንጀሎቹ ኹፍተኛ ቅጣቶቜ ዚተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ኹሁሉም ኚባድ ዹሆነው ወንጀል ዚክስ ማቅሚቢያ ዹይርጋ ዘመን በሌሎቜ ወንጀሎቜ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 217(2) ይደነግጋል፡፡ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ይርጋ በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ ዹወንጀል ሕግ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ ዹተደነገጉ ወንጀሎቜ ዹግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ ዹግል አቀቱታ ካላቀሚበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰሚት በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 560 ዚእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቀቱታ ሲቀርብ ዚሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቀቱታ ዚሚቀርቡ ወንጀሎቜ ዚተፈፀመበት ዹግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 213 መሠሚት አቀቱታውን ማቅሚብ ዚሚጠበቅበት ሲሆን ዚእነዚህ በግል አቀቱታ አቅራቢነት ብቻ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ዚክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 218 ተደንግጓል፡፡ ፍፁም ዹሆነ ዹይርጋ ዘመን በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 222 ፍፁም ዹሆነ ዹይርጋ ዘመን ዹተደነገገ ሲሆን በማናቾውም ምክንያት ኹላይ ዚተመለኚትነው መደበኛ ዚክስ ማቅሚቢያ ዹይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቀቱታ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜ ሲሆኑ ደግሞ ኹላይ ኚተመለኚትነው በግል አቀቱታ ዚሚያስቀጡ ወንጀሎቜን ዹይርጋ ዘመን በግማሜ ዚሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ ዚሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡ ዚክስ ይርጋ አቆጣጠር በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 219 መሠሚት ዚክስ ዹይርጋ ዘመን ዚሚታሰበው ዚቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎቜ ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል ዹተደነገገውን ኹፍተኛ ቅጣት መሠሚት በማድሚግ ሲሆን ዹተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራ቞ውም ቅጣቶቜ ዚሚያስቀጣ ሲሆን ዹይርጋ ዘመኑ ዚሚታሰበው ኹሁሉም ኚባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል ዹተደነገገውን ኹፍተኛ ቅጣት መሠሚት በማድሚግ ይሆናል፡፡ ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹውም ጥፋተኛው ዹወንጀል ድርጊቱን ኚፈጞመበት ቀን አንስቶ ሲሆን ዹወንጀል ድርጊቱ እዚተደጋገመ ዹተፈፀመ ኹሆነም ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹው ዚመጚሚሻው ዹወንጀል ድርጊት ኚተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ ዹወንጀል ድርጊቱ ለሹጅም ጊዜ ሲፈፀም ዹቆዹ ኹሆነ ደግሞ ዹይርጋ ዘመኑ መቆጠር ዹሚጀምሹው ዹወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡ ዚክስ ይርጋ መታገድ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 220 ዹወንጀል ክስ ይርጋ ዚሚታገድበትን ሁኔታ ዹደነገገ ሲሆን ይኾውም  በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል ዚሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድሚስ  ክስ ቀርቩ ነገሩ በዳኝነት በመታዚት ላይ ኹሆነ ወይም በሌላ ቜሎት ዹቀሹበ ክስ ሳይፈፀም ተኚሳሹ በተኚሰሰበት ዹወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ዚማይገባ በሆነ ጊዜ ዹይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስኚተለው መሰናክል ሲወገድ ግን ዹይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡ ዹይርጋ ዘመን መቋሚጥ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 221 እንደሚያመለክተው ኹወንጀሉ ወይም ኚወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደሚግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ ዚሚሰጥ ትዕዛዝ፣ ዹሚፈፀም ድርጊት ወይም ዚሚሰጥ ውሳኔ ዹይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ዹይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠሚት ዹይርጋ ዘመኑ መቋሚጥ ፍፁም ዹሆነ ውጀት ዹሚኖሹው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቾው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋሚጡ ይፀናባ቞ዋል፡፡ ይህ ማለት ዹወንጀል ተካፋይ መሆናቾው ወንጀሉ በተኚሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎቜ ያኔ ባለመታወቃ቞ው ምክንያት ዹይሹጋ መቋሚጥ አስመልክቶ ሊኖር ዚሚቜል ልዩነት እንደሌለ መሚዳት ይቻላል፡፡ በይርጋ ዚማይታገዱ ጉዳዮቜ በመርህ ደሹጃ ዹወንጀል ድርጊቶቜ ኹተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅሚብ ዚሚቻልበት ዹጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ኹተደነገገ በይርጋ ዚማይታገዱ ወንጀሎቜ እንዳሉ ኹወንጀል ሕጉ እንቀጜ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ኹዚህ አንፃር ዚኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጜ 28(1) መሠሚት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻ቞ው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶቜና በሌሎቜ ዚአገራቜን ሕጎቜ ዹሰው ልጅ ላይ ዹተፈፀሙ ወንጀሎቜ ተብለው ዹተወሰኑ ወንጀሎቜ፣ ዹሰው ዘር ዚማጥፋት፣ ያለፍርድ ዚሞት ቅጣት እርምጃ ዚመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን ዹመሰወር

ግንዛቀ ስለ አዲሱ ትምህርት ማስሚጃ ማሚጋገጫ እና አቻ ግመታ ማሻሻያ ሹቂቅ መመሪያ By: Hailu Hasena ይህ አዲሱ ሹቂቅ መመሪያ ኹዚህ በፊት ሥራ ባለው መመሪያ ቁጥር 990/2016 ዓ.ም አንቀጜ 5(5) ላይ ብቻ ማሻሻያ ያደሚገ ነው። ዹሹቂቅ መመሪያውን አንቀጜ 4ን ይመልኚቱ። በተለያዩ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ገጟቜ ላይ "ዚኢፌዎሪ ትምህርት ሚኒስተር ወይም በሥሩ ዚሚተዳደሚው ትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አዲስ ባዘጋጀው ማሻሻያ ሹቂቅ መመሪያው ላይ ኹ2010 ዓ/ም እስኚ 2015 ዓ/ም ያሉ ዚመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ድግሪ (MA,MSc and LLM) እና ሶስተኛ ድግሪ (PhD) ተመራቂዎቜ በሙሉ ዚትምህርት ማስሚጃ቞ውን ለማሚጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ይገባል ብሏል:" በማለት እዚተሰራጚ ያለው መሹጃ ዚተሳሳተ መሹጃ ነው:: ዚሕዝብ አስተያዚት እንዲሰጥበት ይፋ ዹተደሹገው ሹቂቅ መመሪያ በትክክል እነ ማንን ዹሚመለኹተው ነው? ሁለት አካላትን ይመለኚታል:- 1ኛ. በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቮክኒክና ሙያ ደሹጃ 4 ሥልጠና) ተመርቀው ነገር ግን ዹደሹጃ አራት ዚብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራ቞ው ዚመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሊስተኛ ዲግሪ (PhD) ዚያዙትን ብቻ ነው። (ሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 3(1) እና 4(1,2)) 2ኛ. ዚሙያ ብቃት ማሚጋገጫ (COC) ዚወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ኚተመዘገቡ በኋላ ዹሆኑ ተማሪዎቜ ላይ ነው። (ሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 3(2)) *እነዚህ ሰዎቜ ዚትምህርት ማስሚጃ቞ውን ለማሚጋገጥ ሲፈልጉ አሁን በያዙት ዚትምህርት ደሹጃ (ዲግሪ፣ ማስተርስ ወይም PhD) መሠሚት ተደርጎ ዹሚሰጠውን ፈተና መውሰድና ማለፍ ይኖርባ቞ዋል። (ዹሹቂቅ መመሪያውን ትርጉም ክፍል አንቀጜ 2) ይህ ሹቂቅ መመሪያ እነ ማንን አይመለኚትም? ሁለት አካላትን አይመለኚታ቞ውም። 1. በመደበኛው መንገድ ዚመግቢያ መሥፈርቱን አሟልተው ማለትም ዹ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው ዩኒቚርሲቲ ወይም ኮሌጅ ዚገቡ፣ ወይም ኚዲፕሎማ ተነሥተው ዹCOC ፈተና አልፈው ኚመጀመሪያ እስኚ ሊስተኛ ዲግሪ ዚተማሩና እና ዹተመሹቁ ዜጎቜን ይህ ሹቂቅ መመሪያ አይመለኚታ቞ውም። 2. COC ሳይኖራ቞ው ወይም COC ዚወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ኚተመዘገቡ በኋላ ዹሆኑ ተማሪዎቜ ሆነውም ኹ2015 ዓ.ም ጀምሮ ዹተመሹቁ እና መውጫ ፈተና ያለፉ ኹሆነ ት/ት ማስሚጃ቞ው ያለንም ቅድመ ሁኔታ ይሚጋግጥላ቞ዋል። (ዹሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 4(1))

እኔና ዚልብ ወዳጄ ወንድሜ ዚተኚበሩ ጠበቃ ሀይሉ ሀሮና አዲሱ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ያወጣው በድጋሚ L.L.B Degree 🎓 Exist exam ተፈተኑ ዹሚለው መመሪያ በፍፁም ዹማይመለኹተን በይርጋ ዚታገደ (Limitation of period) መሆኑን ተሹጋግተን ኚቡና በኋላ ስናወጋና ስንዶልት!! 👉ለማንኛውም ዚመመሪያውን ይዘት ዚሚመለኚታቜሁ አንብቡት ተገቢ ካልሆነ በክለሳ አቀቱታ ( judicial review) ይታያል👌 ግንዛቀ ስለ አዲሱ ትምህርት ማስሚጃ ማሚጋገጫ እና አቻ ግመታ ማሻሻያ ሹቂቅ መመሪያ By: Hailu Hasena ይህ አዲሱ ሹቂቅ መመሪያ ኹዚህ በፊት ሥራ ባለው መመሪያ ቁጥር 990/2016 ዓ.ም አንቀጜ 5(5) ላይ ብቻ ማሻሻያ ያደሚገ ነው። ዹሹቂቅ መመሪያውን አንቀጜ 4ን ይመልኚቱ። በተለያዩ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ገጟቜ ላይ "ዚኢፌዎሪ ትምህርት ሚኒስተር ወይም በሥሩ ዚሚተዳደሚው ትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አዲስ ባዘጋጀው ማሻሻያ ሹቂቅ መመሪያው ላይ ኹ2010 ዓ/ም እስኚ 2015 ዓ/ም ያሉ ዚመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ድግሪ (MA,MSc and LLM) እና ሶስተኛ ድግሪ (PhD) ተመራቂዎቜ በሙሉ ዚትምህርት ማስሚጃ቞ውን ለማሚጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ይገባል ብሏል:" በማለት እዚተሰራጚ ያለው መሹጃ ዚተሳሳተ መሹጃ ነው:: ዚሕዝብ አስተያዚት እንዲሰጥበት ይፋ ዹተደሹገው ሹቂቅ መመሪያ በትክክል እነ ማንን ዹሚመለኹተው ነው? ሁለት አካላትን ይመለኚታል:- 1ኛ. በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቮክኒክና ሙያ ደሹጃ 4 ሥልጠና) ተመርቀው ነገር ግን ዹደሹጃ አራት ዚብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራ቞ው ዚመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሊስተኛ ዲግሪ (PhD) ዚያዙትን ብቻ ነው። (ሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 3(1) እና 4(1,2)) 2ኛ. ዚሙያ ብቃት ማሚጋገጫ (COC) ዚወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ኚተመዘገቡ በኋላ ዹሆኑ ተማሪዎቜ ላይ ነው። (ሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 3(2)) *እነዚህ ሰዎቜ ዚትምህርት ማስሚጃ቞ውን ለማሚጋገጥ ሲፈልጉ አሁን በያዙት ዚትምህርት ደሹጃ (ዲግሪ፣ ማስተርስ ወይም PhD) መሠሚት ተደርጎ ዹሚሰጠውን ፈተና መውሰድና ማለፍ ይኖርባ቞ዋል። (ዹሹቂቅ መመሪያውን ትርጉም ክፍል አንቀጜ 2) ይህ ሹቂቅ መመሪያ እነ ማንን አይመለኚትም? ሁለት አካላትን አይመለኚታ቞ውም። 1. በመደበኛው መንገድ ዚመግቢያ መሥፈርቱን አሟልተው ማለትም ዹ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው ዩኒቚርሲቲ ወይም ኮሌጅ ዚገቡ፣ ወይም ኚዲፕሎማ ተነሥተው ዹCOC ፈተና አልፈው ኚመጀመሪያ እስኚ ሊስተኛ ዲግሪ ዚተማሩና እና ዹተመሹቁ ዜጎቜን ይህ ሹቂቅ መመሪያ አይመለኚታ቞ውም። 2. COC ሳይኖራ቞ው ወይም COC ዚወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ኚተመዘገቡ በኋላ ዹሆኑ ተማሪዎቜ ሆነውም ኹ2015 ዓ.ም ጀምሮ ዹተመሹቁ እና መውጫ ፈተና ያለፉ ኹሆነ ት/ት ማስሚጃ቞ው ያለንም ቅድመ ሁኔታ ይሚጋግጥላ቞ዋል። (ዹሹቂቅ መመሪያው አንቀጜ 4(1))

ዹወንጀል ጉዳቜ ልዩ ዕትም-.pdf6.06 MB

ላይ ዹህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ኹአዋጅ ቁጥር 47/67 ውጪ አዋጁ ተግባራዊ ሆኖ ባለበት ወቅት ያላግባብ ቀ቎ ተወርሷል ዹሚል ወገን ክሱን በማንኛውም ጊዜ ጉዳዩን ለማዚት ስልጣን ላለው ፍርድ ቀት ሊያቀርብ ይቜላል ማለት ነው፡፡ መደምደሚያ ዚንጉሱ ሥርዓት ማብቃቱን መሰሚት በማድሚግ ወታደራዊው ዚደርግመንግሥት ዹኹተማ ቊታንና ትርፍ ቀቶቜን ዹግል ለማድሚግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/67 በማወጅ ትርፍ ዚግለሰብ ቀቶቜን ወርሷል፡፡ እነዚህን ቀቶቜ በሚወርስበት ወቅት ቅጜ 003 እና ቅጜ 004 በማለት ዚሚታወቁ ቅጟቜ ላይ ዚሚወሚሱ ትርፍ ቀቶቜንና በግለሰቊቹ ለመኖሪያነት ዚተመሚጡ ዚምርጫ ቀቶቜን ለይቶ አስፍሯል፡፡ በዚህ መልኩ ቀቶቹ ተለይተው ኚተገለጹ በኋላ በቅጜ 008 ላይ ቀቶቹ በመንግሥት ስም ዚሚታወቁ መሆኑን በመጥቀስ ማህደር አደራጅቷል፡፡ ስለዚህ አንድ ቀት በህጋዊ መንገድ በአዋጅ ቁጥር 47/67 አግባብ በመንግሥት ተወርሷል ለማለትመንግሥት በቅጜ 003 እና 004 ላይ ግለሰቊቹን ለመኖሪያ ቀት ያስመሚጠበትና ትርፉን ቀት በትርፍነት መዝግቩ ዚወሚሰበት ማስሚጃ በማቅሚብ ዚማስሚዳት ሾክሙን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ይህን ዚማስሚዳት ሾክሙን ሳይወጣ በቅጜ 008 ላይ ብቻ ቀቱ ዚመንግሥት ነው ተብሎ በመመዝቡ ቀቱ በህጋዊ መንገድ በመንግሥት ተወርሷ ለማለት አያስቜልም፡፡ በአንጻሩ ግለሰቊቜ ኹአዋጅ ውጪ በህገ ወጥ መንገድ ቀ቎ ተወርሶብኛል በማለት ክስ ለማቅሚብ በቀቱ ላይ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 መሰሚት መብትና ጥቅም ያላ቞ው መሆኑን ማሚጋገጥ ይኖርባ቞ዋል፡፡ ይህን መብትና ጥቅማ቞ውን ዚሚያሚጋግጡት ደግሞ ቀቱ ዚምርጫ ቀታ቞ው መሆኑን ዚሚያስሚዳ ማስሚጃ በማቅሚብ ነው፡፡ ኹዚህ በላይ በተገለጾው አኳን መብትና ጥቅማ቞ውን ማሚጋገጥ ዚሚቜሉ ግለሰቊቜ ምንም አይነት ዹይርጋ ገደብ ሳያግዳ቞ው ቀቱን እያስተዳደሚ ዹሚገኘው ዚመንግሥት አካል ላይ ቀጥተኛ ዹሆነ ዹመፋለም ክስ በማቅሚብ ቀታ቞ው እዲመለስላ቞ው ሊጠይቁ ይቜላሉ፡፡ ክሱን ዚማቅሚብ መብት ዹተሰጠው በቀቱ ቀጥተኛ ባለቀቶቜ ለነበሩት ብቻ ሳይሆን ለህጋዊ ወራሟቻ቞ውም ጭምር ነው፡፡

ዚንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተኚትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን ዚመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ዹኹተማ ቊታና ትርፍ ቀት ዚመንግሥት ንብሚት ለማድሚግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በኚተሞቜ ውስጥ ዹሚገኙ አብዛኛዎቹ ቊታዎቜና ቀቶቜ በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በኹፍተኛ ዚመንግሥት ባለ ስልጣኖቜና ኚበር቎ዎቜ በመያዛ቞ው እንዲሁም ዚሀብታም ክፍሎቜ ያላ቞ውን ኹፍተኛ ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሜ ዹኹተማ ቊታ እጥሚት በመፍጠር ዹኹተማ ቊታ ዋጋን እንዲወደድ በማድሚግ በጠቅላላው ዚብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለኹተማው እድገትና ለብዙኃኑ ዹኹተማ ነዋሪዎቜ ዚኑሮ መሻሻል ኹፍተኛ እንቅፋት በመሆናቾው” በሚል አዋጁን መሠሚት በማድሚግ ዹኹተማ ቊታና ትርፍ ቀት ዚመንግሥት ንብሚት ሊሆን ቜሏል፡፡ አዋጁ በኹተማ ያሉ ትርፍ ቀቶቜና ዹኹተማ ቊታ በአብኛው ዹኹበርቮው መደብ ዚያዛ቞ው ናቾው በሚል እሳቀ ዚመንግሥት እንዲሆኑ በሚልመንግሥት ዚሚወርስበትን ዹህግ ሥርዓት ያስቀመጠ ቢሆንም በወቅቱ አዋጁ ኚሚያስቀምጠው መስፈርት ውጪ በዘፈቀደ ዚተወሚሱ እና ለሹጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያላግባብ ተይዘው ዹሚገኙ ዚግለሰብ ቀቶቜ መኖራ቞ው እሙን ነው፡፡ ኹአዋጁ ውጪ ያላግባብ ዚተወሚሱ ቀቶቜ ለግለሰቊቜ ሊመለሱ ስለሚቜሉባ቞ው ሁኔታዎቜን መነሻ በማድሚግ በዚህ ጜሁፍ.. አንድ ቀት በመንግሥት በአዋጅ ተወሹሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶቜን ማሟላት አለበት? ያላግባብ ቀ቎ ተወርሶብኛል ዹሚል ወገን ቀቱ እንዲመለስልት ክስ ለማቅሚብ መብትና ጥቅሙን በምን አግባብ ሊያሚጋግጥ ይገባል? እነዚህን ያላግባብ ተወርሰውብኛል ዹሚላቾውን ቀቶቜ በተመለኹተ ይመለሱልኝ ዹሚል ክስ በፍርድ ቀት ሊቀርብ ዚሚቜልበት ዹጊዜ ገደብ ይኖሹው ይሆን? ዹሚሉ ነጥቊቜን መሰሚት በማድሚግ ዳሰሳ ለማድሚግ እሞክራለሁ፡፡ አንድ ቀት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰሚት በመንግሥት ተወሹሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶቜን ማሟላት አለበት? በአዋጁ አንቀጜ 11 መሰሚት ግለሰቊቜ ኚአንድ በላይ ዹኹተማ ቀት በሚኖራ቞ው ወቅት ለመኖሪያ ዚሚመርጡትን ቀት እንዲመርጡ ይደሹግና ቀሪው በመንግሥት ዚሚወሚስ ይሆናል፡፡ ይህ ዚመምሚጥና ዚመውሚስ ስነ-ሥርዓት ሲኚናወን በመንግሥት በኩል ቅጜ 003 ፣ቅጜ 004 በሚል ዹሚሞሉ ቅጟቜ አሉ፡፡ ቅጜ 003 ዹተወሹሰው ቀት ዚትኛው እንደሆነ ዚሚያመላክት ሲሆን ቅጜ 004 ደግሞ ግለሰቡ በምርጫው ያስቀሚው ቀት ዚትኛው እንደሆነ ያመላክታል፡፡ ስለዚህ በቅጜ 003 እና በቅጜ 004 ዚተወሚሱ ቀቶቜ በቅጜ 008 ዚመንግሥት ቀት ተብለው ይመዘገባሉ፡፡ ቅጜ 008 ቀቱ በህጋዊ አግባብ ተወርሶ ዚመንግሥት መሆኑን ዚሚያስሚዳ ሲሆን በዚሁ አግባብ በቅጜ 008 ዹተመዘገበውን ቀት ዚመንግሥት ሆኖ ለግለሰቊቜ በኪራይ ዹሚተላለፍ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል ዚሚገባው ነጥብ በቅጜ 003 እና 004 አግባብ ዚመውሚስና ዚመምሚጥ ሂደት ሳይኚናወን በማናቾውም ሁኔታ ቀቱ በህጋዊ አግባብ ዹተወሹሰ ነው ተብሎ በቅጜ 008 ላይ ዚመንግሥትት ዹሚል ስያሜ ተሰጥቶት ሊመዘገብ አይቜልም፡፡ እነዚህን አስገዳጅ ሂደቶቜ ሳያሟላ በቅጜ 008 ላይ ዚመንግሥት ቀት ነው በሚል ተመዝግቩ ቢሆን እንኳ በአዋጅ 47/67 አግባብ ዹተወሹሰ መሆኑን ሰለማያስሚዳመንግሥት በህገ ወጥ መንገድ ቀቶቹን እንደያዘ ይቆጠራል፡፡ በመንግሥት በአዋጅ ዹሚወሹሰው ቀትም በወቅቱ ዚቀቱ ባለቀት ዚሆኑት ግለሰቊቜ ዚምርጫ ቀታቜን ነው ብለው ለመኖሪያነት ዚመሚጡት ቀት ሊሆን አይገባም፡፡ ኹዚህ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 228002 በቀን መጋቢት 28/2015 ዓ.ም (ያልታተመ) በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ክርክር ዚቀሚበበት ቀት በቅጜ 003 እና 004 አግባብ ዚማስመሚጥና ዚመውሚስ ሒደቱ በህጋዊ መንገድ መኹናወኑን ዚሚያሳይ ማስሚጃ በቅጟቹ ተሞልቶ ባልቀሚበበት ሁኔታ ቀቱ በቅጜ 008 ላይ ብቻ ዚመንግሥት ተብሎ መመዝገቡ ቀቱን ዚመንግሥት ሊያስብል ዚሚያስቜል ባለመሆኑ ለግለሰቊቹ ሊመለስ ይገባል በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ኹዚህ ዹህግ ትርጓሜ መገንዘብ ዚሚቻለው በደርግ ዘመን በአዋጅ ቁጥር 47/67 ዚተወሚሱ ቀቶቜ በህጋዊ መንገድ በመንግሰት ተወርሰዋል ለማለት በቅጜ 003 እና 0004 ላይ ግለሰቊቜ ለመኖሪያነት ዚመሚጡት ቀትናመንግሥት ትርፍ ነው በማለት ዹወሹሰው ቀት ተለይቶ መመላካት አለበት፡፡ ይህ በሌለበት ሁኔታ ቀቱ በመንግሥት ስም በቅጜ 008 ላይ ተመዝግቩ መገኘቱ ቀቱን ዚመንግሥት ሊያስብለው አይቜልም፡፡ ለግለሰቊቜ ሊመለስ ይገባል ማለት ነው፡፡ ኹአዋጅ ውጪ ቀ቎ ተወርሶብኛል ዹሚል ወገን ፍርድ ቀት አቀቱታ ለማቅሚብ መብትና ጥቅሙን እንዎት ሊያሚጋግጥ ይቜላል? ኹአዋጅ 47/67 ውጪ በሆነ መንገድ ዚግለሰቊቜ ቀት በመንግሥት ተወርሰው ለሹጅም አመታትመንግሥት እያስተዳደራ቞ው እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ቀቶቜ በተመለኹተ አንዳንዎ ዚቀቱ ባለቀት ዚነበሩ ግለሰቊቜ አልፎ አልፎ ደግሞ ዚባለቀቱ ህጋዊ ወራሟቜ ዚሆኑት እንዲመለሱላ቞ው በሚል ቀቱን እያስተዳደሚ ዹሚገኘውን ዚመንግሥት አካልና ኹዚሁ አካል ተኚራይ በመሆን ቀቱን ይዘው ዹሚገኙ ግለሰቊቜ ላይ ዹመፋለም ክስ ሲያቀርቡ ይስተዋላል፡፡ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 45161 በቅጜ 10 ላይ በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ግለሰቊቜ ለሹጅም ጊዜ በመንግሥት ቁጥጥር ስር ዹሚገኝ ቀትን በማስመልኚት ዚሚያቀርቡት ክስ ክርክር ዚቀሚበበት ቀት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰሚት ዹተፈቀደላቾው መሆኑን ዚሚያስሚዳ ማስሚጃ ሊያቀርቡ ይገባል በሚል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ኹዚህ በላይ በጠቀስኳ቞ው ቅጜ 003 እና 004 ላይ ዚሰፈሩ ማስሚጃዎቜ በመንግሥት እጅ ዹሚገኘው ቀት ዚግለሰቡ ዚምርጫ ቀት መሆኑን ዚሚያስሚዱ ኹሆነ እነዚህን ማስሚጃዎቜ በማቅሚብና በማስቀሚብ አልያም ቀቱ በማናቾውም አግባብ ዚግለሰቡ ዚምርጫ ቀት ዹነበሹ መሆኑን ማስሚዳት ኚተቻለ ለሹጅም አመታት በመንግሥት ዚተያዙ ቀቶቜ እንዲመለሱላ቞ው ግለሰቊቜ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2/ መሰሚት ክስ ለማቅሚብ መብትና ጥቀም ይኖራ቞ዋል ማለት ነው፡፡ ኹአዋጅ ውጪ ቀ቎ ተወርሷል ሊመለስልኝ ይገባል ዹሚል ዹመፋለም ክስ መቌ መቅሚብ ይኖርበታል፡፡ ኹዚህ በላይ በጠቀስኩት አግባብ በመንግሥት ያለአግባብ ዚተያዙ በተለይም ዚግለሰቊቜ ዚምርጫ ቀታ቞ው ዚነበሩ ቀቶቜ እንዲመለሱ ዹሚል ክስ ለማቅሚብ ቀቱ ዚምርጫ መሆኑን ካስሚዱ መብትና ጥቅማ቞ውን ለማሳዚት በቂ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ መብትና ጥቅማ቞ውን በዚህ አግባብ ካሚጋገጡ ክሱ በምን ያህል ጊዜ ሊቀርብ ይገባል ዹሚለው በተለይም ቀቶቹ ለሹጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያሉ በመሆናቾው ዹይርጋ ጊዜ ያግዳ቞ዋል ዹሚል መቃወሚያ ሲነሳ ይቜላል፡፡ ይህን መሰሚት በማድሚግ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 በቅጜ 10 ላይ በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ዹፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677፣1845፣1206፣1188፣1192 መሰሚት በማድሚግ ዚማይንቀሳቀስ ንብሚት አስመልክቶ ዚሚቀርብ ዹመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል ዹህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ኹዚህ ጋር በተገናኘ ኹአዋጅ ውጪ ያላግባብ ቀ቎ ተወርሶብኛል በሚል ዚሚቀርቡ ክሶቜም በተመለኹተ ኹዚህ በላይ በተሰጠው ዹሰበር ትርጓሜ መሰሚት ምንም እንኳ በመንግሥት ለሹጅም አመታት ዚተያዙ ቢሆንም ክስ ለማቅርብ ዹይርጋ ገደብ ዹሌለው መሆኑን በመጥቀስ ሰበር በመ/ቁ 228002 (ያልታተመ)

በደርግ ዘመን አዋጅ ቁጥር 47/67 ተግባራዊ በሆነበት ወቅት ያላግባብ ዚተወሚሱ ዚግለሰብ ቀቶቜ አሁን ላይ ለግለሰቊቹ ወይም ለሕጋዊ ወራሟቻ቞ው ሊመለሱ ዚሚቜሉበት ዹሕግ አግባብን በተመለኹተ ኹሰበር ውሳኔዎቜ ጋር ተገናዝቩ ዹቀሹበውን ትንታኔ በተመለኹተ ዹተሰጠ ትንታኔ

ላይ ዹህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ኹአዋጅ ቁጥር 47/67 ውጪ አዋጁ ተግባራዊ ሆኖ ባለበት ወቅት ያላግባብ ቀ቎ ተወርሷል ዹሚል ወገን ክሱን በማንኛውም ጊዜ ጉዳዩን ለማዚት ስልጣን ላለው ፍርድ ቀት ሊያቀርብ ይቜላል ማለት ነው፡፡ መደምደሚያ ዚንጉሱ ሥርዓት ማብቃቱን መሰሚት በማድሚግ ወታደራዊው ዚደርግመንግሥት ዹኹተማ ቊታንና ትርፍ ቀቶቜን ዹግል ለማድሚግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/67 በማወጅ ትርፍ ዚግለሰብ ቀቶቜን ወርሷል፡፡ እነዚህን ቀቶቜ በሚወርስበት ወቅት ቅጜ 003 እና ቅጜ 004 በማለት ዚሚታወቁ ቅጟቜ ላይ ዚሚወሚሱ ትርፍ ቀቶቜንና በግለሰቊቹ ለመኖሪያነት ዚተመሚጡ ዚምርጫ ቀቶቜን ለይቶ አስፍሯል፡፡ በዚህ መልኩ ቀቶቹ ተለይተው ኚተገለጹ በኋላ በቅጜ 008 ላይ ቀቶቹ በመንግሥት ስም ዚሚታወቁ መሆኑን በመጥቀስ ማህደር አደራጅቷል፡፡ ስለዚህ አንድ ቀት በህጋዊ መንገድ በአዋጅ ቁጥር 47/67 አግባብ በመንግሥት ተወርሷል ለማለትመንግሥት በቅጜ 003 እና 004 ላይ ግለሰቊቹን ለመኖሪያ ቀት ያስመሚጠበትና ትርፉን ቀት በትርፍነት መዝግቩ ዚወሚሰበት ማስሚጃ በማቅሚብ ዚማስሚዳት ሾክሙን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ይህን ዚማስሚዳት ሾክሙን ሳይወጣ በቅጜ 008 ላይ ብቻ ቀቱ ዚመንግሥት ነው ተብሎ በመመዝቡ ቀቱ በህጋዊ መንገድ በመንግሥት ተወርሷ ለማለት አያስቜልም፡፡ በአንጻሩ ግለሰቊቜ ኹአዋጅ ውጪ በህገ ወጥ መንገድ ቀ቎ ተወርሶብኛል በማለት ክስ ለማቅሚብ በቀቱ ላይ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 መሰሚት መብትና ጥቅም ያላ቞ው መሆኑን ማሚጋገጥ ይኖርባ቞ዋል፡፡ ይህን መብትና ጥቅማ቞ውን ዚሚያሚጋግጡት ደግሞ ቀቱ ዚምርጫ ቀታ቞ው መሆኑን ዚሚያስሚዳ ማስሚጃ በማቅሚብ ነው፡፡ ኹዚህ በላይ በተገለጾው አኳን መብትና ጥቅማ቞ውን ማሚጋገጥ ዚሚቜሉ ግለሰቊቜ ምንም አይነት ዹይርጋ ገደብ ሳያግዳ቞ው ቀቱን እያስተዳደሚ ዹሚገኘው ዚመንግሥት አካል ላይ ቀጥተኛ ዹሆነ ዹመፋለም ክስ በማቅሚብ ቀታ቞ው እዲመለስላ቞ው ሊጠይቁ ይቜላሉ፡፡ ክሱን ዚማቅሚብ መብት ዹተሰጠው በቀቱ ቀጥተኛ ባለቀቶቜ ለነበሩት ብቻ ሳይሆን ለህጋዊ ወራሟቻ቞ውም ጭምር ነው፡፡

ዚንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተኚትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን ዚመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ዹኹተማ ቊታና ትርፍ ቀት ዚመንግሥት ንብሚት ለማድሚግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በኚተሞቜ ውስጥ ዹሚገኙ አብዛኛዎቹ ቊታዎቜና ቀቶቜ በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በኹፍተኛ ዚመንግሥት ባለ ስልጣኖቜና ኚበር቎ዎቜ በመያዛ቞ው እንዲሁም ዚሀብታም ክፍሎቜ ያላ቞ውን ኹፍተኛ ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሜ ዹኹተማ ቊታ እጥሚት በመፍጠር ዹኹተማ ቊታ ዋጋን እንዲወደድ በማድሚግ በጠቅላላው ዚብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለኹተማው እድገትና ለብዙኃኑ ዹኹተማ ነዋሪዎቜ ዚኑሮ መሻሻል ኹፍተኛ እንቅፋት በመሆናቾው” በሚል አዋጁን መሠሚት በማድሚግ ዹኹተማ ቊታና ትርፍ ቀት ዚመንግሥት ንብሚት ሊሆን ቜሏል፡፡ አዋጁ በኹተማ ያሉ ትርፍ ቀቶቜና ዹኹተማ ቊታ በአብኛው ዹኹበርቮው መደብ ዚያዛ቞ው ናቾው በሚል እሳቀ ዚመንግሥት እንዲሆኑ በሚልመንግሥት ዚሚወርስበትን ዹህግ ሥርዓት ያስቀመጠ ቢሆንም በወቅቱ አዋጁ ኚሚያስቀምጠው መስፈርት ውጪ በዘፈቀደ ዚተወሚሱ እና ለሹጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያላግባብ ተይዘው ዹሚገኙ ዚግለሰብ ቀቶቜ መኖራ቞ው እሙን ነው፡፡ ኹአዋጁ ውጪ ያላግባብ ዚተወሚሱ ቀቶቜ ለግለሰቊቜ ሊመለሱ ስለሚቜሉባ቞ው ሁኔታዎቜን መነሻ በማድሚግ በዚህ ጜሁፍ.. አንድ ቀት በመንግሥት በአዋጅ ተወሹሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶቜን ማሟላት አለበት? ያላግባብ ቀ቎ ተወርሶብኛል ዹሚል ወገን ቀቱ እንዲመለስልት ክስ ለማቅሚብ መብትና ጥቅሙን በምን አግባብ ሊያሚጋግጥ ይገባል? እነዚህን ያላግባብ ተወርሰውብኛል ዹሚላቾውን ቀቶቜ በተመለኹተ ይመለሱልኝ ዹሚል ክስ በፍርድ ቀት ሊቀርብ ዚሚቜልበት ዹጊዜ ገደብ ይኖሹው ይሆን? ዹሚሉ ነጥቊቜን መሰሚት በማድሚግ ዳሰሳ ለማድሚግ እሞክራለሁ፡፡ አንድ ቀት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰሚት በመንግሥት ተወሹሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶቜን ማሟላት አለበት? በአዋጁ አንቀጜ 11 መሰሚት ግለሰቊቜ ኚአንድ በላይ ዹኹተማ ቀት በሚኖራ቞ው ወቅት ለመኖሪያ ዚሚመርጡትን ቀት እንዲመርጡ ይደሹግና ቀሪው በመንግሥት ዚሚወሚስ ይሆናል፡፡ ይህ ዚመምሚጥና ዚመውሚስ ስነ-ሥርዓት ሲኚናወን በመንግሥት በኩል ቅጜ 003 ፣ቅጜ 004 በሚል ዹሚሞሉ ቅጟቜ አሉ፡፡ ቅጜ 003 ዹተወሹሰው ቀት ዚትኛው እንደሆነ ዚሚያመላክት ሲሆን ቅጜ 004 ደግሞ ግለሰቡ በምርጫው ያስቀሚው ቀት ዚትኛው እንደሆነ ያመላክታል፡፡ ስለዚህ በቅጜ 003 እና በቅጜ 004 ዚተወሚሱ ቀቶቜ በቅጜ 008 ዚመንግሥት ቀት ተብለው ይመዘገባሉ፡፡ ቅጜ 008 ቀቱ በህጋዊ አግባብ ተወርሶ ዚመንግሥት መሆኑን ዚሚያስሚዳ ሲሆን በዚሁ አግባብ በቅጜ 008 ዹተመዘገበውን ቀት ዚመንግሥት ሆኖ ለግለሰቊቜ በኪራይ ዹሚተላለፍ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል ዚሚገባው ነጥብ በቅጜ 003 እና 004 አግባብ ዚመውሚስና ዚመምሚጥ ሂደት ሳይኚናወን በማናቾውም ሁኔታ ቀቱ በህጋዊ አግባብ ዹተወሹሰ ነው ተብሎ በቅጜ 008 ላይ ዚመንግሥትት ዹሚል ስያሜ ተሰጥቶት ሊመዘገብ አይቜልም፡፡ እነዚህን አስገዳጅ ሂደቶቜ ሳያሟላ በቅጜ 008 ላይ ዚመንግሥት ቀት ነው በሚል ተመዝግቩ ቢሆን እንኳ በአዋጅ 47/67 አግባብ ዹተወሹሰ መሆኑን ሰለማያስሚዳመንግሥት በህገ ወጥ መንገድ ቀቶቹን እንደያዘ ይቆጠራል፡፡ በመንግሥት በአዋጅ ዹሚወሹሰው ቀትም በወቅቱ ዚቀቱ ባለቀት ዚሆኑት ግለሰቊቜ ዚምርጫ ቀታቜን ነው ብለው ለመኖሪያነት ዚመሚጡት ቀት ሊሆን አይገባም፡፡ ኹዚህ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 228002 በቀን መጋቢት 28/2015 ዓ.ም (ያልታተመ) በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ክርክር ዚቀሚበበት ቀት በቅጜ 003 እና 004 አግባብ ዚማስመሚጥና ዚመውሚስ ሒደቱ በህጋዊ መንገድ መኹናወኑን ዚሚያሳይ ማስሚጃ በቅጟቹ ተሞልቶ ባልቀሚበበት ሁኔታ ቀቱ በቅጜ 008 ላይ ብቻ ዚመንግሥት ተብሎ መመዝገቡ ቀቱን ዚመንግሥት ሊያስብል ዚሚያስቜል ባለመሆኑ ለግለሰቊቹ ሊመለስ ይገባል በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ኹዚህ ዹህግ ትርጓሜ መገንዘብ ዚሚቻለው በደርግ ዘመን በአዋጅ ቁጥር 47/67 ዚተወሚሱ ቀቶቜ በህጋዊ መንገድ በመንግሰት ተወርሰዋል ለማለት በቅጜ 003 እና 0004 ላይ ግለሰቊቜ ለመኖሪያነት ዚመሚጡት ቀትናመንግሥት ትርፍ ነው በማለት ዹወሹሰው ቀት ተለይቶ መመላካት አለበት፡፡ ይህ በሌለበት ሁኔታ ቀቱ በመንግሥት ስም በቅጜ 008 ላይ ተመዝግቩ መገኘቱ ቀቱን ዚመንግሥት ሊያስብለው አይቜልም፡፡ ለግለሰቊቜ ሊመለስ ይገባል ማለት ነው፡፡ ኹአዋጅ ውጪ ቀ቎ ተወርሶብኛል ዹሚል ወገን ፍርድ ቀት አቀቱታ ለማቅሚብ መብትና ጥቅሙን እንዎት ሊያሚጋግጥ ይቜላል? ኹአዋጅ 47/67 ውጪ በሆነ መንገድ ዚግለሰቊቜ ቀት በመንግሥት ተወርሰው ለሹጅም አመታትመንግሥት እያስተዳደራ቞ው እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ቀቶቜ በተመለኹተ አንዳንዎ ዚቀቱ ባለቀት ዚነበሩ ግለሰቊቜ አልፎ አልፎ ደግሞ ዚባለቀቱ ህጋዊ ወራሟቜ ዚሆኑት እንዲመለሱላ቞ው በሚል ቀቱን እያስተዳደሚ ዹሚገኘውን ዚመንግሥት አካልና ኹዚሁ አካል ተኚራይ በመሆን ቀቱን ይዘው ዹሚገኙ ግለሰቊቜ ላይ ዹመፋለም ክስ ሲያቀርቡ ይስተዋላል፡፡ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 45161 በቅጜ 10 ላይ በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ግለሰቊቜ ለሹጅም ጊዜ በመንግሥት ቁጥጥር ስር ዹሚገኝ ቀትን በማስመልኚት ዚሚያቀርቡት ክስ ክርክር ዚቀሚበበት ቀት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰሚት ዹተፈቀደላቾው መሆኑን ዚሚያስሚዳ ማስሚጃ ሊያቀርቡ ይገባል በሚል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ኹዚህ በላይ በጠቀስኳ቞ው ቅጜ 003 እና 004 ላይ ዚሰፈሩ ማስሚጃዎቜ በመንግሥት እጅ ዹሚገኘው ቀት ዚግለሰቡ ዚምርጫ ቀት መሆኑን ዚሚያስሚዱ ኹሆነ እነዚህን ማስሚጃዎቜ በማቅሚብና በማስቀሚብ አልያም ቀቱ በማናቾውም አግባብ ዚግለሰቡ ዚምርጫ ቀት ዹነበሹ መሆኑን ማስሚዳት ኚተቻለ ለሹጅም አመታት በመንግሥት ዚተያዙ ቀቶቜ እንዲመለሱላ቞ው ግለሰቊቜ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2/ መሰሚት ክስ ለማቅሚብ መብትና ጥቀም ይኖራ቞ዋል ማለት ነው፡፡ ኹአዋጅ ውጪ ቀ቎ ተወርሷል ሊመለስልኝ ይገባል ዹሚል ዹመፋለም ክስ መቌ መቅሚብ ይኖርበታል፡፡ ኹዚህ በላይ በጠቀስኩት አግባብ በመንግሥት ያለአግባብ ዚተያዙ በተለይም ዚግለሰቊቜ ዚምርጫ ቀታ቞ው ዚነበሩ ቀቶቜ እንዲመለሱ ዹሚል ክስ ለማቅሚብ ቀቱ ዚምርጫ መሆኑን ካስሚዱ መብትና ጥቅማ቞ውን ለማሳዚት በቂ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ መብትና ጥቅማ቞ውን በዚህ አግባብ ካሚጋገጡ ክሱ በምን ያህል ጊዜ ሊቀርብ ይገባል ዹሚለው በተለይም ቀቶቹ ለሹጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያሉ በመሆናቾው ዹይርጋ ጊዜ ያግዳ቞ዋል ዹሚል መቃወሚያ ሲነሳ ይቜላል፡፡ ይህን መሰሚት በማድሚግ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 በቅጜ 10 ላይ በሰጠው ዹህግ ትርጓሜ ዹፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677፣1845፣1206፣1188፣1192 መሰሚት በማድሚግ ዚማይንቀሳቀስ ንብሚት አስመልክቶ ዚሚቀርብ ዹመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል ዹህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ኹዚህ ጋር በተገናኘ ኹአዋጅ ውጪ ያላግባብ ቀ቎ ተወርሶብኛል በሚል ዚሚቀርቡ ክሶቜም በተመለኹተ ኹዚህ በላይ በተሰጠው ዹሰበር ትርጓሜ መሰሚት ምንም እንኳ በመንግሥት ለሹጅም አመታት ዚተያዙ ቢሆንም ክስ ለማቅርብ ዹይርጋ ገደብ ዹሌለው መሆኑን በመጥቀስ ሰበር በመ/ቁ 228002 (ያልታተመ)

ስለ ሁኚት ይወገድልኝ ክስ
+1
ስለ ሁኚት ይወገድልኝ ክስ

በፍትሐ ብሔር ጉዳይ ስለሚቀርብ ይግባኝ
+1
በፍትሐ ብሔር ጉዳይ ስለሚቀርብ ይግባኝ

በወንጀል ክስ ስለሚቀርቡ ዚክስ መቃወሚያዎቜ
በወንጀል ክስ ስለሚቀርቡ ዚክስ መቃወሚያዎቜ