Tamiru Yacob - Attorney at Law
Kanalga Telegram’da o‘tish
Legal service/Lawyer የሕግ አማካሪ /ጠበቃ የጥብቅና አገልግሎት ከፈለጉ በዚህ ስልክ ይደውሉ Tel:- 0913661521 ታምሩ ያዕቆብ
Ko'proq ko'rsatish4 065
Obunachilar
+124 soatlar
-27 kunlar
-2930 kunlar
Postlar arxiv
ወይም የኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም።
ማጠቃለያ
የወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎች ፍትሕ የሚያገኙበት የሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል የተጠረጠሩ ወይንም የተከሰሱ ግለሰቦች ነፃነት በሕግ የሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠረት የወንጀል ክስ መመስረቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶች መካከል ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ
********
መግቢያ
ወንጀል ፈፃሚዎች ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠየቃቸውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቸው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ አንድ እንደተመለከተው በወንጀል ሕጉ መሰረት ወንጀል የተደረጉ ድርጊቶች እና የሚያስከትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎች ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎች በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎችም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠረት እና አጥፊዎችን ለሕግ ማቅረብ የሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ የተመለከተውን የክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም የክስ ይርጋ ዘመን መቋረጥና መታገድ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት
የወንጀል ሕጉ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለከተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 217 በመነሳት የወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቸውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቤቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ከመታየት የሚታገድበት በሕግ የተመለከተ ጊዜ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
የመደበኛ ክስ ይርጋ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217 መደበኛ የክስ ማቅረቢያ ጊዜን የደነገገ ሲሆን
• የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት
• ከአስር ዓመት በላይ እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችሉ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት
• ከአምስት ዓመት በላይ እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት
• ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት
• ከአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት
• እስከ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሦስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈጽመው ሲገኙ የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ የአንዱ ወንጀል የክስ ማቅረብያ የይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች የተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከሁሉም ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217(2) ይደነግጋል፡፡
በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚያስቀጡ ወንጀሎች ይርጋ
በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ የወንጀል ሕግ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ የተደነገጉ ወንጀሎች የግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የግል አቤቱታ ካላቀረበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰረት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 560 የእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቤቱታ ሲቀርብ የሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቤቱታ የሚቀርቡ ወንጀሎች የተፈፀመበት የግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 213 መሠረት አቤቱታውን ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን የእነዚህ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ የሚያስቀጡ ወንጀሎች የክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 218 ተደንግጓል፡፡
ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 222 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የተደነገገ ሲሆን በማናቸውም ምክንያት ከላይ የተመለከትነው መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎች ሲሆኑ ደግሞ ከላይ ከተመለከትነው በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ አቆጣጠር
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 219 መሠረት የክስ የይርጋ ዘመን የሚታሰበው የቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ሲሆን የተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራቸውም ቅጣቶች የሚያስቀጣ ሲሆን የይርጋ ዘመኑ የሚታሰበው ከሁሉም ከባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡
የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረውም ጥፋተኛው የወንጀል ድርጊቱን ከፈጸመበት ቀን አንስቶ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ እየተደጋገመ የተፈፀመ ከሆነም የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው የወንጀል ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ የወንጀል ድርጊቱ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆየ ከሆነ ደግሞ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ መታገድ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 220 የወንጀል ክስ ይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ የደነገገ ሲሆን ይኸውም
በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል የሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድረስ
ክስ ቀርቦ ነገሩ በዳኝነት በመታየት ላይ ከሆነ ወይም በሌላ ችሎት የቀረበ ክስ ሳይፈፀም ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ በሆነ ጊዜ
የይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስከተለው መሰናክል ሲወገድ ግን የይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡
የይርጋ ዘመን መቋረጥ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 221 እንደሚያመለክተው ከወንጀሉ ወይም ከወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደረግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ የሚሰጥ ትዕዛዝ፣ የሚፈፀም ድርጊት ወይም የሚሰጥ ውሳኔ የይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ የይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠረት የይርጋ ዘመኑ መቋረጥ ፍፁም የሆነ ውጤት የሚኖረው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቸው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋረጡ ይፀናባቸዋል፡፡ ይህ ማለት የወንጀል ተካፋይ መሆናቸው ወንጀሉ በተከሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎች ያኔ ባለመታወቃቸው ምክንያት የይረጋ መቋረጥ አስመልክቶ ሊኖር የሚችል ልዩነት እንደሌለ መረዳት ይቻላል፡፡
በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች
በመርህ ደረጃ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅረብ የሚቻልበት የጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ከተደነገገ በይርጋ የማይታገዱ ወንጀሎች እንዳሉ ከወንጀል ሕጉ እንቀጽ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28(1) መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የአገራችን ሕጎች የሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑ ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር
ወይም የኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም።
ማጠቃለያ
የወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎች ፍትሕ የሚያገኙበት የሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል የተጠረጠሩ ወይንም የተከሰሱ ግለሰቦች ነፃነት በሕግ የሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠረት የወንጀል ክስ መመስረቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶች መካከል ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ
********
መግቢያ
ወንጀል ፈፃሚዎች ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠየቃቸውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቸው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ አንድ እንደተመለከተው በወንጀል ሕጉ መሰረት ወንጀል የተደረጉ ድርጊቶች እና የሚያስከትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎች ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎች በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎችም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠረት እና አጥፊዎችን ለሕግ ማቅረብ የሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ የተመለከተውን የክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም የክስ ይርጋ ዘመን መቋረጥና መታገድ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት
የወንጀል ሕጉ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለከተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 217 በመነሳት የወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቸውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቤቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ከመታየት የሚታገድበት በሕግ የተመለከተ ጊዜ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
የመደበኛ ክስ ይርጋ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217 መደበኛ የክስ ማቅረቢያ ጊዜን የደነገገ ሲሆን
• የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት
• ከአስር ዓመት በላይ እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችሉ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት
• ከአምስት ዓመት በላይ እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት
• ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት
• ከአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት
• እስከ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሦስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈጽመው ሲገኙ የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ የአንዱ ወንጀል የክስ ማቅረብያ የይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች የተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከሁሉም ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217(2) ይደነግጋል፡፡
በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚያስቀጡ ወንጀሎች ይርጋ
በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ የወንጀል ሕግ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ የተደነገጉ ወንጀሎች የግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የግል አቤቱታ ካላቀረበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰረት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 560 የእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቤቱታ ሲቀርብ የሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቤቱታ የሚቀርቡ ወንጀሎች የተፈፀመበት የግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 213 መሠረት አቤቱታውን ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን የእነዚህ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ የሚያስቀጡ ወንጀሎች የክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 218 ተደንግጓል፡፡
ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 222 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የተደነገገ ሲሆን በማናቸውም ምክንያት ከላይ የተመለከትነው መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎች ሲሆኑ ደግሞ ከላይ ከተመለከትነው በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ አቆጣጠር
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 219 መሠረት የክስ የይርጋ ዘመን የሚታሰበው የቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ሲሆን የተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራቸውም ቅጣቶች የሚያስቀጣ ሲሆን የይርጋ ዘመኑ የሚታሰበው ከሁሉም ከባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡
የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረውም ጥፋተኛው የወንጀል ድርጊቱን ከፈጸመበት ቀን አንስቶ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ እየተደጋገመ የተፈፀመ ከሆነም የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው የወንጀል ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ የወንጀል ድርጊቱ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆየ ከሆነ ደግሞ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ መታገድ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 220 የወንጀል ክስ ይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ የደነገገ ሲሆን ይኸውም
በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል የሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድረስ
ክስ ቀርቦ ነገሩ በዳኝነት በመታየት ላይ ከሆነ ወይም በሌላ ችሎት የቀረበ ክስ ሳይፈፀም ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ በሆነ ጊዜ
የይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስከተለው መሰናክል ሲወገድ ግን የይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡
የይርጋ ዘመን መቋረጥ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 221 እንደሚያመለክተው ከወንጀሉ ወይም ከወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደረግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ የሚሰጥ ትዕዛዝ፣ የሚፈፀም ድርጊት ወይም የሚሰጥ ውሳኔ የይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ የይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠረት የይርጋ ዘመኑ መቋረጥ ፍፁም የሆነ ውጤት የሚኖረው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቸው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋረጡ ይፀናባቸዋል፡፡ ይህ ማለት የወንጀል ተካፋይ መሆናቸው ወንጀሉ በተከሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎች ያኔ ባለመታወቃቸው ምክንያት የይረጋ መቋረጥ አስመልክቶ ሊኖር የሚችል ልዩነት እንደሌለ መረዳት ይቻላል፡፡
በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች
በመርህ ደረጃ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅረብ የሚቻልበት የጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ከተደነገገ በይርጋ የማይታገዱ ወንጀሎች እንዳሉ ከወንጀል ሕጉ እንቀጽ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28(1) መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የአገራችን ሕጎች የሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑ ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር
ግንዛቤ ስለ አዲሱ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ ማሻሻያ ረቂቅ መመሪያ
By: Hailu Hasena
ይህ አዲሱ ረቂቅ መመሪያ ከዚህ በፊት ሥራ ባለው መመሪያ ቁጥር 990/2016 ዓ.ም አንቀጽ 5(5) ላይ ብቻ ማሻሻያ ያደረገ ነው። የረቂቅ መመሪያውን አንቀጽ 4ን ይመልከቱ።
በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ
"የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስተር ወይም በሥሩ የሚተዳደረው ትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አዲስ ባዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ መመሪያው ላይ ከ2010 ዓ/ም እስከ 2015 ዓ/ም ያሉ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ድግሪ (MA,MSc and LLM) እና ሶስተኛ ድግሪ (PhD) ተመራቂዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ይገባል ብሏል:" በማለት እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ መረጃ ነው::
የሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥበት ይፋ የተደረገው ረቂቅ መመሪያ በትክክል እነ ማንን የሚመለከተው ነው?
ሁለት አካላትን ይመለከታል:-
1ኛ. በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቴክኒክና ሙያ ደረጃ 4 ሥልጠና) ተመርቀው ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) የያዙትን ብቻ ነው።
(ረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 3(1) እና 4(1,2))
2ኛ. የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ላይ ነው። (ረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 3(2))
*እነዚህ ሰዎች የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ሲፈልጉ አሁን በያዙት የትምህርት ደረጃ (ዲግሪ፣ ማስተርስ ወይም PhD) መሠረት ተደርጎ የሚሰጠውን ፈተና መውሰድና ማለፍ ይኖርባቸዋል።
(የረቂቅ መመሪያውን ትርጉም ክፍል አንቀጽ 2)
ይህ ረቂቅ መመሪያ እነ ማንን አይመለከትም?
ሁለት አካላትን አይመለከታቸውም።
1. በመደበኛው መንገድ የመግቢያ መሥፈርቱን አሟልተው ማለትም የ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው ዩኒቨርሲቲ ወይም ኮሌጅ የገቡ፣ ወይም ከዲፕሎማ ተነሥተው የCOC ፈተና አልፈው ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ የተማሩና እና የተመረቁ ዜጎችን ይህ ረቂቅ መመሪያ አይመለከታቸውም።
2. COC ሳይኖራቸው ወይም COC የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ሆነውም ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ እና መውጫ ፈተና ያለፉ ከሆነ ት/ት ማስረጃቸው ያለንም ቅድመ ሁኔታ ይረጋግጥላቸዋል። (የረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 4(1))
እኔና የልብ ወዳጄ ወንድሜ የተከበሩ ጠበቃ ሀይሉ ሀሴና አዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው በድጋሚ L.L.B Degree 🎓 Exist exam ተፈተኑ የሚለው መመሪያ በፍፁም የማይመለከተን በይርጋ የታገደ (Limitation of period) መሆኑን ተረጋግተን ከቡና በኋላ ስናወጋና ስንዶልት!!
👉ለማንኛውም የመመሪያውን ይዘት የሚመለከታችሁ አንብቡት ተገቢ ካልሆነ በክለሳ አቤቱታ ( judicial review) ይታያል👌
ግንዛቤ ስለ አዲሱ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ ማሻሻያ ረቂቅ መመሪያ
By: Hailu Hasena
ይህ አዲሱ ረቂቅ መመሪያ ከዚህ በፊት ሥራ ባለው መመሪያ ቁጥር 990/2016 ዓ.ም አንቀጽ 5(5) ላይ ብቻ ማሻሻያ ያደረገ ነው። የረቂቅ መመሪያውን አንቀጽ 4ን ይመልከቱ።
በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ
"የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስተር ወይም በሥሩ የሚተዳደረው ትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አዲስ ባዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ መመሪያው ላይ ከ2010 ዓ/ም እስከ 2015 ዓ/ም ያሉ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ድግሪ (MA,MSc and LLM) እና ሶስተኛ ድግሪ (PhD) ተመራቂዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ይገባል ብሏል:" በማለት እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ መረጃ ነው::
የሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥበት ይፋ የተደረገው ረቂቅ መመሪያ በትክክል እነ ማንን የሚመለከተው ነው?
ሁለት አካላትን ይመለከታል:-
1ኛ. በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቴክኒክና ሙያ ደረጃ 4 ሥልጠና) ተመርቀው ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) የያዙትን ብቻ ነው።
(ረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 3(1) እና 4(1,2))
2ኛ. የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ላይ ነው። (ረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 3(2))
*እነዚህ ሰዎች የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ሲፈልጉ አሁን በያዙት የትምህርት ደረጃ (ዲግሪ፣ ማስተርስ ወይም PhD) መሠረት ተደርጎ የሚሰጠውን ፈተና መውሰድና ማለፍ ይኖርባቸዋል።
(የረቂቅ መመሪያውን ትርጉም ክፍል አንቀጽ 2)
ይህ ረቂቅ መመሪያ እነ ማንን አይመለከትም?
ሁለት አካላትን አይመለከታቸውም።
1. በመደበኛው መንገድ የመግቢያ መሥፈርቱን አሟልተው ማለትም የ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው ዩኒቨርሲቲ ወይም ኮሌጅ የገቡ፣ ወይም ከዲፕሎማ ተነሥተው የCOC ፈተና አልፈው ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ የተማሩና እና የተመረቁ ዜጎችን ይህ ረቂቅ መመሪያ አይመለከታቸውም።
2. COC ሳይኖራቸው ወይም COC የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ሆነውም ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ እና መውጫ ፈተና ያለፉ ከሆነ ት/ት ማስረጃቸው ያለንም ቅድመ ሁኔታ ይረጋግጥላቸዋል። (የረቂቅ መመሪያው አንቀጽ 4(1))
ላይ የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡
ስለዚህ ከአዋጅ ቁጥር 47/67 ውጪ አዋጁ ተግባራዊ ሆኖ ባለበት ወቅት ያላግባብ ቤቴ ተወርሷል የሚል ወገን ክሱን በማንኛውም ጊዜ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል ማለት ነው፡፡
መደምደሚያ
የንጉሱ ሥርዓት ማብቃቱን መሰረት በማድረግ ወታደራዊው የደርግመንግሥት የከተማ ቦታንና ትርፍ ቤቶችን የግል ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/67 በማወጅ ትርፍ የግለሰብ ቤቶችን ወርሷል፡፡ እነዚህን ቤቶች በሚወርስበት ወቅት ቅጽ 003 እና ቅጽ 004 በማለት የሚታወቁ ቅጾች ላይ የሚወረሱ ትርፍ ቤቶችንና በግለሰቦቹ ለመኖሪያነት የተመረጡ የምርጫ ቤቶችን ለይቶ አስፍሯል፡፡ በዚህ መልኩ ቤቶቹ ተለይተው ከተገለጹ በኋላ በቅጽ 008 ላይ ቤቶቹ በመንግሥት ስም የሚታወቁ መሆኑን በመጥቀስ ማህደር አደራጅቷል፡፡ ስለዚህ አንድ ቤት በህጋዊ መንገድ በአዋጅ ቁጥር 47/67 አግባብ በመንግሥት ተወርሷል ለማለትመንግሥት በቅጽ 003 እና 004 ላይ ግለሰቦቹን ለመኖሪያ ቤት ያስመረጠበትና ትርፉን ቤት በትርፍነት መዝግቦ የወረሰበት ማስረጃ በማቅረብ የማስረዳት ሸክሙን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ይህን የማስረዳት ሸክሙን ሳይወጣ በቅጽ 008 ላይ ብቻ ቤቱ የመንግሥት ነው ተብሎ በመመዝቡ ቤቱ በህጋዊ መንገድ በመንግሥት ተወርሷ ለማለት አያስችልም፡፡
በአንጻሩ ግለሰቦች ከአዋጅ ውጪ በህገ ወጥ መንገድ ቤቴ ተወርሶብኛል በማለት ክስ ለማቅረብ በቤቱ ላይ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 መሰረት መብትና ጥቅም ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን መብትና ጥቅማቸውን የሚያረጋግጡት ደግሞ ቤቱ የምርጫ ቤታቸው መሆኑን የሚያስረዳ ማስረጃ በማቅረብ ነው፡፡
ከዚህ በላይ በተገለጸው አኳን መብትና ጥቅማቸውን ማረጋገጥ የሚችሉ ግለሰቦች ምንም አይነት የይርጋ ገደብ ሳያግዳቸው ቤቱን እያስተዳደረ የሚገኘው የመንግሥት አካል ላይ ቀጥተኛ የሆነ የመፋለም ክስ በማቅረብ ቤታቸው እዲመለስላቸው ሊጠይቁ ይችላሉ፡፡ ክሱን የማቅረብ መብት የተሰጠው በቤቱ ቀጥተኛ ባለቤቶች ለነበሩት ብቻ ሳይሆን ለህጋዊ ወራሾቻቸውም ጭምር ነው፡፡
የንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተከትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን የመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በከተሞች ውስጥ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ቦታዎችና ቤቶች በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በከፍተኛ የመንግሥት ባለ ስልጣኖችና ከበርቴዎች በመያዛቸው እንዲሁም የሀብታም ክፍሎች ያላቸውን ከፍተኛ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሽ የከተማ ቦታ እጥረት በመፍጠር የከተማ ቦታ ዋጋን እንዲወደድ በማድረግ በጠቅላላው የብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለከተማው እድገትና ለብዙኃኑ የከተማ ነዋሪዎች የኑሮ መሻሻል ከፍተኛ እንቅፋት በመሆናቸው” በሚል አዋጁን መሠረት በማድረግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ሊሆን ችሏል፡፡
አዋጁ በከተማ ያሉ ትርፍ ቤቶችና የከተማ ቦታ በአብኛው የከበርቴው መደብ የያዛቸው ናቸው በሚል እሳቤ የመንግሥት እንዲሆኑ በሚልመንግሥት የሚወርስበትን የህግ ሥርዓት ያስቀመጠ ቢሆንም በወቅቱ አዋጁ ከሚያስቀምጠው መስፈርት ውጪ በዘፈቀደ የተወረሱ እና ለረጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያላግባብ ተይዘው የሚገኙ የግለሰብ ቤቶች መኖራቸው እሙን ነው፡፡ ከአዋጁ ውጪ ያላግባብ የተወረሱ ቤቶች ለግለሰቦች ሊመለሱ ስለሚችሉባቸው ሁኔታዎችን መነሻ በማድረግ በዚህ ጽሁፍ.. አንድ ቤት በመንግሥት በአዋጅ ተወረሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት አለበት? ያላግባብ ቤቴ ተወርሶብኛል የሚል ወገን ቤቱ እንዲመለስልት ክስ ለማቅረብ መብትና ጥቅሙን በምን አግባብ ሊያረጋግጥ ይገባል? እነዚህን ያላግባብ ተወርሰውብኛል የሚላቸውን ቤቶች በተመለከተ ይመለሱልኝ የሚል ክስ በፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚችልበት የጊዜ ገደብ ይኖረው ይሆን? የሚሉ ነጥቦችን መሰረት በማድረግ ዳሰሳ ለማድረግ እሞክራለሁ፡፡
አንድ ቤት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰረት በመንግሥት ተወረሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት አለበት?
በአዋጁ አንቀጽ 11 መሰረት ግለሰቦች ከአንድ በላይ የከተማ ቤት በሚኖራቸው ወቅት ለመኖሪያ የሚመርጡትን ቤት እንዲመርጡ ይደረግና ቀሪው በመንግሥት የሚወረስ ይሆናል፡፡ ይህ የመምረጥና የመውረስ ስነ-ሥርዓት ሲከናወን በመንግሥት በኩል ቅጽ 003 ፣ቅጽ 004 በሚል የሚሞሉ ቅጾች አሉ፡፡ ቅጽ 003 የተወረሰው ቤት የትኛው እንደሆነ የሚያመላክት ሲሆን ቅጽ 004 ደግሞ ግለሰቡ በምርጫው ያስቀረው ቤት የትኛው እንደሆነ ያመላክታል፡፡ ስለዚህ በቅጽ 003 እና በቅጽ 004 የተወረሱ ቤቶች በቅጽ 008 የመንግሥት ቤት ተብለው ይመዘገባሉ፡፡ ቅጽ 008 ቤቱ በህጋዊ አግባብ ተወርሶ የመንግሥት መሆኑን የሚያስረዳ ሲሆን በዚሁ አግባብ በቅጽ 008 የተመዘገበውን ቤት የመንግሥት ሆኖ ለግለሰቦች በኪራይ የሚተላለፍ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ በቅጽ 003 እና 004 አግባብ የመውረስና የመምረጥ ሂደት ሳይከናወን በማናቸውም ሁኔታ ቤቱ በህጋዊ አግባብ የተወረሰ ነው ተብሎ በቅጽ 008 ላይ የመንግሥትት የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ሊመዘገብ አይችልም፡፡ እነዚህን አስገዳጅ ሂደቶች ሳያሟላ በቅጽ 008 ላይ የመንግሥት ቤት ነው በሚል ተመዝግቦ ቢሆን እንኳ በአዋጅ 47/67 አግባብ የተወረሰ መሆኑን ሰለማያስረዳመንግሥት በህገ ወጥ መንገድ ቤቶቹን እንደያዘ ይቆጠራል፡፡ በመንግሥት በአዋጅ የሚወረሰው ቤትም በወቅቱ የቤቱ ባለቤት የሆኑት ግለሰቦች የምርጫ ቤታችን ነው ብለው ለመኖሪያነት የመረጡት ቤት ሊሆን አይገባም፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ በቅርቡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 228002 በቀን መጋቢት 28/2015 ዓ.ም (ያልታተመ) በሰጠው የህግ ትርጓሜ ክርክር የቀረበበት ቤት በቅጽ 003 እና 004 አግባብ የማስመረጥና የመውረስ ሒደቱ በህጋዊ መንገድ መከናወኑን የሚያሳይ ማስረጃ በቅጾቹ ተሞልቶ ባልቀረበበት ሁኔታ ቤቱ በቅጽ 008 ላይ ብቻ የመንግሥት ተብሎ መመዝገቡ ቤቱን የመንግሥት ሊያስብል የሚያስችል ባለመሆኑ ለግለሰቦቹ ሊመለስ ይገባል በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ከዚህ የህግ ትርጓሜ መገንዘብ የሚቻለው በደርግ ዘመን በአዋጅ ቁጥር 47/67 የተወረሱ ቤቶች በህጋዊ መንገድ በመንግሰት ተወርሰዋል ለማለት በቅጽ 003 እና 0004 ላይ ግለሰቦች ለመኖሪያነት የመረጡት ቤትናመንግሥት ትርፍ ነው በማለት የወረሰው ቤት ተለይቶ መመላካት አለበት፡፡ ይህ በሌለበት ሁኔታ ቤቱ በመንግሥት ስም በቅጽ 008 ላይ ተመዝግቦ መገኘቱ ቤቱን የመንግሥት ሊያስብለው አይችልም፡፡ ለግለሰቦች ሊመለስ ይገባል ማለት ነው፡፡
ከአዋጅ ውጪ ቤቴ ተወርሶብኛል የሚል ወገን ፍርድ ቤት አቤቱታ ለማቅረብ መብትና ጥቅሙን እንዴት ሊያረጋግጥ ይችላል?
ከአዋጅ 47/67 ውጪ በሆነ መንገድ የግለሰቦች ቤት በመንግሥት ተወርሰው ለረጅም አመታትመንግሥት እያስተዳደራቸው እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ቤቶች በተመለከተ አንዳንዴ የቤቱ ባለቤት የነበሩ ግለሰቦች አልፎ አልፎ ደግሞ የባለቤቱ ህጋዊ ወራሾች የሆኑት እንዲመለሱላቸው በሚል ቤቱን እያስተዳደረ የሚገኘውን የመንግሥት አካልና ከዚሁ አካል ተከራይ በመሆን ቤቱን ይዘው የሚገኙ ግለሰቦች ላይ የመፋለም ክስ ሲያቀርቡ ይስተዋላል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 45161 በቅጽ 10 ላይ በሰጠው የህግ ትርጓሜ ግለሰቦች ለረጅም ጊዜ በመንግሥት ቁጥጥር ስር የሚገኝ ቤትን በማስመልከት የሚያቀርቡት ክስ ክርክር የቀረበበት ቤት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰረት የተፈቀደላቸው መሆኑን የሚያስረዳ ማስረጃ ሊያቀርቡ ይገባል በሚል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በጠቀስኳቸው ቅጽ 003 እና 004 ላይ የሰፈሩ ማስረጃዎች በመንግሥት እጅ የሚገኘው ቤት የግለሰቡ የምርጫ ቤት መሆኑን የሚያስረዱ ከሆነ እነዚህን ማስረጃዎች በማቅረብና በማስቀረብ አልያም ቤቱ በማናቸውም አግባብ የግለሰቡ የምርጫ ቤት የነበረ መሆኑን ማስረዳት ከተቻለ ለረጅም አመታት በመንግሥት የተያዙ ቤቶች እንዲመለሱላቸው ግለሰቦች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2/ መሰረት ክስ ለማቅረብ መብትና ጥቀም ይኖራቸዋል ማለት ነው፡፡
ከአዋጅ ውጪ ቤቴ ተወርሷል ሊመለስልኝ ይገባል የሚል የመፋለም ክስ መቼ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ከዚህ በላይ በጠቀስኩት አግባብ በመንግሥት ያለአግባብ የተያዙ በተለይም የግለሰቦች የምርጫ ቤታቸው የነበሩ ቤቶች እንዲመለሱ የሚል ክስ ለማቅረብ ቤቱ የምርጫ መሆኑን ካስረዱ መብትና ጥቅማቸውን ለማሳየት በቂ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ መብትና ጥቅማቸውን በዚህ አግባብ ካረጋገጡ ክሱ በምን ያህል ጊዜ ሊቀርብ ይገባል የሚለው በተለይም ቤቶቹ ለረጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያሉ በመሆናቸው የይርጋ ጊዜ ያግዳቸዋል የሚል መቃወሚያ ሲነሳ ይችላል፡፡ ይህን መሰረት በማድረግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 በቅጽ 10 ላይ በሰጠው የህግ ትርጓሜ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677፣1845፣1206፣1188፣1192 መሰረት በማድረግ የማይንቀሳቀስ ንብረት አስመልክቶ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተገናኘ ከአዋጅ ውጪ ያላግባብ ቤቴ ተወርሶብኛል በሚል የሚቀርቡ ክሶችም በተመለከተ ከዚህ በላይ በተሰጠው የሰበር ትርጓሜ መሰረት ምንም እንኳ በመንግሥት ለረጅም አመታት የተያዙ ቢሆንም ክስ ለማቅርብ የይርጋ ገደብ የሌለው መሆኑን በመጥቀስ ሰበር በመ/ቁ 228002 (ያልታተመ)
በደርግ ዘመን አዋጅ ቁጥር 47/67 ተግባራዊ በሆነበት ወቅት ያላግባብ የተወረሱ የግለሰብ ቤቶች አሁን ላይ ለግለሰቦቹ ወይም ለሕጋዊ ወራሾቻቸው ሊመለሱ የሚችሉበት የሕግ አግባብን በተመለከተ ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበውን ትንታኔ በተመለከተ የተሰጠ ትንታኔ
ላይ የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡
ስለዚህ ከአዋጅ ቁጥር 47/67 ውጪ አዋጁ ተግባራዊ ሆኖ ባለበት ወቅት ያላግባብ ቤቴ ተወርሷል የሚል ወገን ክሱን በማንኛውም ጊዜ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል ማለት ነው፡፡
መደምደሚያ
የንጉሱ ሥርዓት ማብቃቱን መሰረት በማድረግ ወታደራዊው የደርግመንግሥት የከተማ ቦታንና ትርፍ ቤቶችን የግል ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/67 በማወጅ ትርፍ የግለሰብ ቤቶችን ወርሷል፡፡ እነዚህን ቤቶች በሚወርስበት ወቅት ቅጽ 003 እና ቅጽ 004 በማለት የሚታወቁ ቅጾች ላይ የሚወረሱ ትርፍ ቤቶችንና በግለሰቦቹ ለመኖሪያነት የተመረጡ የምርጫ ቤቶችን ለይቶ አስፍሯል፡፡ በዚህ መልኩ ቤቶቹ ተለይተው ከተገለጹ በኋላ በቅጽ 008 ላይ ቤቶቹ በመንግሥት ስም የሚታወቁ መሆኑን በመጥቀስ ማህደር አደራጅቷል፡፡ ስለዚህ አንድ ቤት በህጋዊ መንገድ በአዋጅ ቁጥር 47/67 አግባብ በመንግሥት ተወርሷል ለማለትመንግሥት በቅጽ 003 እና 004 ላይ ግለሰቦቹን ለመኖሪያ ቤት ያስመረጠበትና ትርፉን ቤት በትርፍነት መዝግቦ የወረሰበት ማስረጃ በማቅረብ የማስረዳት ሸክሙን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ይህን የማስረዳት ሸክሙን ሳይወጣ በቅጽ 008 ላይ ብቻ ቤቱ የመንግሥት ነው ተብሎ በመመዝቡ ቤቱ በህጋዊ መንገድ በመንግሥት ተወርሷ ለማለት አያስችልም፡፡
በአንጻሩ ግለሰቦች ከአዋጅ ውጪ በህገ ወጥ መንገድ ቤቴ ተወርሶብኛል በማለት ክስ ለማቅረብ በቤቱ ላይ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 መሰረት መብትና ጥቅም ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን መብትና ጥቅማቸውን የሚያረጋግጡት ደግሞ ቤቱ የምርጫ ቤታቸው መሆኑን የሚያስረዳ ማስረጃ በማቅረብ ነው፡፡
ከዚህ በላይ በተገለጸው አኳን መብትና ጥቅማቸውን ማረጋገጥ የሚችሉ ግለሰቦች ምንም አይነት የይርጋ ገደብ ሳያግዳቸው ቤቱን እያስተዳደረ የሚገኘው የመንግሥት አካል ላይ ቀጥተኛ የሆነ የመፋለም ክስ በማቅረብ ቤታቸው እዲመለስላቸው ሊጠይቁ ይችላሉ፡፡ ክሱን የማቅረብ መብት የተሰጠው በቤቱ ቀጥተኛ ባለቤቶች ለነበሩት ብቻ ሳይሆን ለህጋዊ ወራሾቻቸውም ጭምር ነው፡፡
የንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተከትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን የመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በከተሞች ውስጥ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ቦታዎችና ቤቶች በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በከፍተኛ የመንግሥት ባለ ስልጣኖችና ከበርቴዎች በመያዛቸው እንዲሁም የሀብታም ክፍሎች ያላቸውን ከፍተኛ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሽ የከተማ ቦታ እጥረት በመፍጠር የከተማ ቦታ ዋጋን እንዲወደድ በማድረግ በጠቅላላው የብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለከተማው እድገትና ለብዙኃኑ የከተማ ነዋሪዎች የኑሮ መሻሻል ከፍተኛ እንቅፋት በመሆናቸው” በሚል አዋጁን መሠረት በማድረግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ሊሆን ችሏል፡፡
አዋጁ በከተማ ያሉ ትርፍ ቤቶችና የከተማ ቦታ በአብኛው የከበርቴው መደብ የያዛቸው ናቸው በሚል እሳቤ የመንግሥት እንዲሆኑ በሚልመንግሥት የሚወርስበትን የህግ ሥርዓት ያስቀመጠ ቢሆንም በወቅቱ አዋጁ ከሚያስቀምጠው መስፈርት ውጪ በዘፈቀደ የተወረሱ እና ለረጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያላግባብ ተይዘው የሚገኙ የግለሰብ ቤቶች መኖራቸው እሙን ነው፡፡ ከአዋጁ ውጪ ያላግባብ የተወረሱ ቤቶች ለግለሰቦች ሊመለሱ ስለሚችሉባቸው ሁኔታዎችን መነሻ በማድረግ በዚህ ጽሁፍ.. አንድ ቤት በመንግሥት በአዋጅ ተወረሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት አለበት? ያላግባብ ቤቴ ተወርሶብኛል የሚል ወገን ቤቱ እንዲመለስልት ክስ ለማቅረብ መብትና ጥቅሙን በምን አግባብ ሊያረጋግጥ ይገባል? እነዚህን ያላግባብ ተወርሰውብኛል የሚላቸውን ቤቶች በተመለከተ ይመለሱልኝ የሚል ክስ በፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚችልበት የጊዜ ገደብ ይኖረው ይሆን? የሚሉ ነጥቦችን መሰረት በማድረግ ዳሰሳ ለማድረግ እሞክራለሁ፡፡
አንድ ቤት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰረት በመንግሥት ተወረሰ ለማለት ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት አለበት?
በአዋጁ አንቀጽ 11 መሰረት ግለሰቦች ከአንድ በላይ የከተማ ቤት በሚኖራቸው ወቅት ለመኖሪያ የሚመርጡትን ቤት እንዲመርጡ ይደረግና ቀሪው በመንግሥት የሚወረስ ይሆናል፡፡ ይህ የመምረጥና የመውረስ ስነ-ሥርዓት ሲከናወን በመንግሥት በኩል ቅጽ 003 ፣ቅጽ 004 በሚል የሚሞሉ ቅጾች አሉ፡፡ ቅጽ 003 የተወረሰው ቤት የትኛው እንደሆነ የሚያመላክት ሲሆን ቅጽ 004 ደግሞ ግለሰቡ በምርጫው ያስቀረው ቤት የትኛው እንደሆነ ያመላክታል፡፡ ስለዚህ በቅጽ 003 እና በቅጽ 004 የተወረሱ ቤቶች በቅጽ 008 የመንግሥት ቤት ተብለው ይመዘገባሉ፡፡ ቅጽ 008 ቤቱ በህጋዊ አግባብ ተወርሶ የመንግሥት መሆኑን የሚያስረዳ ሲሆን በዚሁ አግባብ በቅጽ 008 የተመዘገበውን ቤት የመንግሥት ሆኖ ለግለሰቦች በኪራይ የሚተላለፍ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ በቅጽ 003 እና 004 አግባብ የመውረስና የመምረጥ ሂደት ሳይከናወን በማናቸውም ሁኔታ ቤቱ በህጋዊ አግባብ የተወረሰ ነው ተብሎ በቅጽ 008 ላይ የመንግሥትት የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ሊመዘገብ አይችልም፡፡ እነዚህን አስገዳጅ ሂደቶች ሳያሟላ በቅጽ 008 ላይ የመንግሥት ቤት ነው በሚል ተመዝግቦ ቢሆን እንኳ በአዋጅ 47/67 አግባብ የተወረሰ መሆኑን ሰለማያስረዳመንግሥት በህገ ወጥ መንገድ ቤቶቹን እንደያዘ ይቆጠራል፡፡ በመንግሥት በአዋጅ የሚወረሰው ቤትም በወቅቱ የቤቱ ባለቤት የሆኑት ግለሰቦች የምርጫ ቤታችን ነው ብለው ለመኖሪያነት የመረጡት ቤት ሊሆን አይገባም፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ በቅርቡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 228002 በቀን መጋቢት 28/2015 ዓ.ም (ያልታተመ) በሰጠው የህግ ትርጓሜ ክርክር የቀረበበት ቤት በቅጽ 003 እና 004 አግባብ የማስመረጥና የመውረስ ሒደቱ በህጋዊ መንገድ መከናወኑን የሚያሳይ ማስረጃ በቅጾቹ ተሞልቶ ባልቀረበበት ሁኔታ ቤቱ በቅጽ 008 ላይ ብቻ የመንግሥት ተብሎ መመዝገቡ ቤቱን የመንግሥት ሊያስብል የሚያስችል ባለመሆኑ ለግለሰቦቹ ሊመለስ ይገባል በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ከዚህ የህግ ትርጓሜ መገንዘብ የሚቻለው በደርግ ዘመን በአዋጅ ቁጥር 47/67 የተወረሱ ቤቶች በህጋዊ መንገድ በመንግሰት ተወርሰዋል ለማለት በቅጽ 003 እና 0004 ላይ ግለሰቦች ለመኖሪያነት የመረጡት ቤትናመንግሥት ትርፍ ነው በማለት የወረሰው ቤት ተለይቶ መመላካት አለበት፡፡ ይህ በሌለበት ሁኔታ ቤቱ በመንግሥት ስም በቅጽ 008 ላይ ተመዝግቦ መገኘቱ ቤቱን የመንግሥት ሊያስብለው አይችልም፡፡ ለግለሰቦች ሊመለስ ይገባል ማለት ነው፡፡
ከአዋጅ ውጪ ቤቴ ተወርሶብኛል የሚል ወገን ፍርድ ቤት አቤቱታ ለማቅረብ መብትና ጥቅሙን እንዴት ሊያረጋግጥ ይችላል?
ከአዋጅ 47/67 ውጪ በሆነ መንገድ የግለሰቦች ቤት በመንግሥት ተወርሰው ለረጅም አመታትመንግሥት እያስተዳደራቸው እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ቤቶች በተመለከተ አንዳንዴ የቤቱ ባለቤት የነበሩ ግለሰቦች አልፎ አልፎ ደግሞ የባለቤቱ ህጋዊ ወራሾች የሆኑት እንዲመለሱላቸው በሚል ቤቱን እያስተዳደረ የሚገኘውን የመንግሥት አካልና ከዚሁ አካል ተከራይ በመሆን ቤቱን ይዘው የሚገኙ ግለሰቦች ላይ የመፋለም ክስ ሲያቀርቡ ይስተዋላል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 45161 በቅጽ 10 ላይ በሰጠው የህግ ትርጓሜ ግለሰቦች ለረጅም ጊዜ በመንግሥት ቁጥጥር ስር የሚገኝ ቤትን በማስመልከት የሚያቀርቡት ክስ ክርክር የቀረበበት ቤት በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሰረት የተፈቀደላቸው መሆኑን የሚያስረዳ ማስረጃ ሊያቀርቡ ይገባል በሚል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በጠቀስኳቸው ቅጽ 003 እና 004 ላይ የሰፈሩ ማስረጃዎች በመንግሥት እጅ የሚገኘው ቤት የግለሰቡ የምርጫ ቤት መሆኑን የሚያስረዱ ከሆነ እነዚህን ማስረጃዎች በማቅረብና በማስቀረብ አልያም ቤቱ በማናቸውም አግባብ የግለሰቡ የምርጫ ቤት የነበረ መሆኑን ማስረዳት ከተቻለ ለረጅም አመታት በመንግሥት የተያዙ ቤቶች እንዲመለሱላቸው ግለሰቦች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2/ መሰረት ክስ ለማቅረብ መብትና ጥቀም ይኖራቸዋል ማለት ነው፡፡
ከአዋጅ ውጪ ቤቴ ተወርሷል ሊመለስልኝ ይገባል የሚል የመፋለም ክስ መቼ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ከዚህ በላይ በጠቀስኩት አግባብ በመንግሥት ያለአግባብ የተያዙ በተለይም የግለሰቦች የምርጫ ቤታቸው የነበሩ ቤቶች እንዲመለሱ የሚል ክስ ለማቅረብ ቤቱ የምርጫ መሆኑን ካስረዱ መብትና ጥቅማቸውን ለማሳየት በቂ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ መብትና ጥቅማቸውን በዚህ አግባብ ካረጋገጡ ክሱ በምን ያህል ጊዜ ሊቀርብ ይገባል የሚለው በተለይም ቤቶቹ ለረጅም አመታት በመንግሥት እጅ ያሉ በመሆናቸው የይርጋ ጊዜ ያግዳቸዋል የሚል መቃወሚያ ሲነሳ ይችላል፡፡ ይህን መሰረት በማድረግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 በቅጽ 10 ላይ በሰጠው የህግ ትርጓሜ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677፣1845፣1206፣1188፣1192 መሰረት በማድረግ የማይንቀሳቀስ ንብረት አስመልክቶ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተገናኘ ከአዋጅ ውጪ ያላግባብ ቤቴ ተወርሶብኛል በሚል የሚቀርቡ ክሶችም በተመለከተ ከዚህ በላይ በተሰጠው የሰበር ትርጓሜ መሰረት ምንም እንኳ በመንግሥት ለረጅም አመታት የተያዙ ቢሆንም ክስ ለማቅርብ የይርጋ ገደብ የሌለው መሆኑን በመጥቀስ ሰበር በመ/ቁ 228002 (ያልታተመ)
