HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 280
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+77 kunlar
+3930 kunlar
Postlar arxiv
◈ ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ዕለት ነው!
◈ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም፡፡ የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡
◈ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡
◈ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡
◈ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ (ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3)
◈ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰግደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ…›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡
◈ ያች ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ (ሉቃ 1፡35)
◈ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡
◈ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡
◈ ሥሉስ ቅዱስን በምግባር በሃይማኖት ሆነን እናገለግል ዘንድ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን! 🙏🏽 🙏🏽 🙏🏽
(ምንጭ #ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ እና #ከገድላት_አንደበት)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
በጸጋ እግዚአብሔር ዙሪያ የሚታዩ ሕልሞች ሰውና ሕልም በፀጋ ዙሪያ የምታዩ ሕልሞች || ቀሲስ ሄኖክ ወልደማርያም መምህር ግርማ #ethiopia 🔥🚩💥😭
https://youtu.be/4z-GlbYYmYM
መምህር ግርማን ለምን ይቃወሙታል? ጸሎት እያቋረጥኩ ተቸገርኩ ለምትሉ የአጋንንት ስውር ወጥመድን መጠንቀቅ || መጽሐፍ ቅዱስና የአጋንንት ውጊያ 💥🚩🔥 https://youtu.be/uZ417_HcLao
«በቃልኪዳን መጎናጸፊያ ለተጠቀለለ የስምሽ መታሰቢያ ሰላምታ ይገባል፤ የጥራቱ ህብር ለሚያበራም ጸጉርሽ ሠላምታ ይገባል። ትዕግስትን የተሸለምሽ፥ ድልንም የተጎናጸፍሽ፤ ቅድስት አርሴማ ሆይ ረቂቅ የሚሆን የኃይልሽ ትርጓሜ መሸከሚያና በአንደበቴና በቃሌ ላይ ይጻፍ።» /መልክአ ቅድስት አርሴማ/
አምላከ ቅደስት አርሴማ
ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቀን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«አስተውሉ! ሰይጣን አንድን ኃጢአት ሊያሠራን ሲፈልግ ቀድሞ ስለ እግዚአብሔር መሐሪነት በሰፊው ይሰብከናል። ያን ኃጢአት ከፈጸምን በኋላ ደግሞ ስለ እውነተኛ ፈራጅነቱና ምንም ቢሆን ከቁጣው የማናመልጥ መሆኑን ከቀድሞው ይልቅ እየጮኸ ይነግረናል። በመጀመሪያው ስብከቱ ኃጢአትን እንዳንቃወም ሰነፎች ያደርገናል። በሁለተኛው ስብከቱ ደግሞ ንስሐ እንዳንገባ ተስፋ ያስቆርጠናል። ይህ የተገለባበጠ ስብከት "የሰይጣን" ነው። ሰው በኃጢአት ከመውደቁ በፊት ሊያስብ የሚገባው የእግዚአብሔርን ፈታሒነት (ፈራጅነት) ሲሆን በኃጢአት ከወደቀ በኋላ ግን ማሰብ ያለበት የእግዚአብሔርን መሐሪነት ነው።»
ፈታሒነቱ ኃጢአትን እንዳንሠራ ይጠብቀናል፤
መሐሪነቱ ንስሐ እንድንገባ ያቀርበናል፤
መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
5ቱ የሳጥናኤል ሰራዊት የወደቀበት ቦታዎች || እየቀደሱ አለመቀደስ አያሳዝንም || የሦስት ሰዓት ንስሐ | ሕይወት የሌለው ክርስትና || መምህር ግርማ 💥🔥🚩🙏 https://youtu.be/2KeN7-L2qE4
◈ በምድር ላይ እንደ እንስሳ መኖር ስትመርጥ እና እንደ ሰው ለመኖር አቅም ስታጣ እንደ መላዕክት የኖሩ አበው መነኮሳተት በፀጋቸውና በተጋድሎአቸው በፍፁምም አፍቃሪነታቸው ከመላዕክት ይበልጣሉ የተባሉ እነ ቅዱስ ጳውሎስን የመሰሉ ትጉሀን ፍፁም ታዛዦች መኖራቸውን አስታውስ።
◈ ወንድሜ አንዳንድ ጊዜ መንገዳገዳችን ወይንም በእግዚአብሔር ቤት ጸንተን አለመቆማችን ወደ መውደቅ እንጂ ወደ መቆም ሊመራን የማይችል እስኪመስለን ድረስ ተስፋ እንቆርጣለን፤ ይህ እኔ ላይ ብቻ የሆነ ነው ብለህ እንዳታስብ ማንኛውም በመንፈሳዊ እድገት ላይ ያለ ሰው በዚህ ይፈተናል፤ እግዚአብሔርን ያዝ አትጠራጠር፤ እግዚአብሔር ውድቀታችንን የማይሻ አምላክ መሆኑን በመፅሐፍ ብቻ የነገረን አይደለም "አይተንማል።"
◈ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እና በቅዱሳን አባቶቻችን መንፈሳዊ መመሪያዎች ውስጥ ግልፅ የማይሆኑልን ወይንም በንባብ የማንረዳቸው፣ በማሰላሰል የማንደርስባቸው አሳቦች የገባንን ጥቂት የወንጌል ቃል ስንኖረው የምንረዳቸው ናቸው።
"ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!" (ታላቁ ቅዱስ ጎሮጎርዮስ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።"
መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን! በርቱ፣ ጠንክሩ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«በተከለከለ ነገር የሚማረክ»
◈ ብዙ ጊዜ በsocial midea ይሁን በብዙኃን መገናኛ በስፋት የሚታዩና ትልቅ ተደራሽነት የሚኖራቸው ነገሮች በማኅበረሰቡ ዘንድ የተከለከሉ እና ተቀባይነት የሌላቸው ድርጊቶች ናቸው፤ እነዚያን ጉዳዮች በማውገዝም ይሁን "ጉድ እኮ ነው" በሚል አግራሞት ለሌሎች የሚያጋራቸውና አስተያየት የሚሰጥባቸው ተመልካች ቁጥር ጥቂት የማይባል ነው። ይህ ግርግር በራሱ ሙሉ በሙሉም ባይሆን በከፊል ግን በውስጣችን ያለውን "በተከለከለ ነገር የሚማረክ" ማንነታችንን በደንብ ያሳያል (ይህ ሁኔታ በሥነ ልቡናው "forbidden fruit effect" በመባል ይታወቃል)
=> አይሆንም ተብለን እየተከለከልን በገባንበት ሱስ፣ ወዳጅነት፣ ፍቅር፣ ትዳር የምንሰቃይ ስንቶቻችን እንሆን?
◈ ለመንፈሳዊ ሕይወታችንም ትልቅ እንቅፋት የሚሆንብን ይህ የተከለከለውን የሚያሳድድ ክፉ አመላችን ነው፤ ፈጣሪያችን "አታድርጉ" ሲለን እኛን ለመጠበቅ ሳይሆን የእኛን ዓለም ለማጥበብ ሲል ያሰረን ያህል ይሰማናል፤ የተሰጡንን ሕግጋት ካልጣስንም ነጻነታችንን ተግባራዊ ያደረግን አይመስለንም፤ የተፈቀደልንን አናደርግም፣ ያልተፈቀደልን ያንንም ሳናደርግ አንውልም፤ እኛ እንዲህ ነን ቀኝ ሲጠብቁን በግራ፣ በግራ ሲያስሱን በቀኝ ብቅ የምንል ጉራማይሌ ነን። ከሁሉ የሚያስደንቀው ደግሞ በዚህ ጠባያችን "የሰይጣን ነጻ አውጪ" እስከ መሆን መድረሳችን ነው፤ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው መድኃኒታችን ክርስቶስ ለዘመናት ባሪያ ያደረገንንና ሲረግጠን የኖረውን ሰይጣን በመስቀሉ ጠርቆ (አስሮ) ከመንገድ አስወግዶልናል። (ቆላ 2፥14)
◈ እኛን ከእርሱ ጋር በትንሣኤው ሲያስነሣን ያን ዕቡይ ጠላታችንን ግን እንሳለቅበት ዘንድ ከእግራችን ስር ጥሎልናል፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሰይጣን ጌታ ከተሰቀለባት እለተ አርብ በኋላ በብረት ሳጥን እንደ ታሰረ ውሻ ሆኗል ይለናል፤ ስለዚህ እንደ ፈቃዱ ሊፈነጭና ማንም ላይ ሊሰለጥን አይችልም ማለት ነው፤ ነገር ግን ሰው በፍላጎቱ ወደ ታሰረው ሰይጣን በሄደና መዝጊያውን በከፈተለት ጊዜ ለታሠረው ሰይጣን ነጻነት ይሰብካል፤ በክፋት ጥርሶቹ ነካክሶ ያደማው ዘንድ በገዛ እጁ በራሱ ላይ ያነግሠዋል፤ በዚህም ሰው የተፈቀደለትን ንግሥና ትቶ የተከለከለውን የዲያብሎስ ባርያነት ኑሮን ይገፋል። አባ መቃርስ እንዳለው "የሚወደውን ባለጠጋ እግዚአብሔርን ጠልቶ የሚጠላውን ደሃ ሰይጣንን ወድዶ የሚከተል" ሰው ምን ያህል ሞኝ ነው?
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33)
(በዲያቆን አቤል ካሳሁን)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
በዝሙት ፊልም የገባ የሉሲፈር አጋንንት የአምልኮት ስግደት ለምን አይቋረጥም? የማዕድ ጸሎትና ምስጋና ጥቅሙ | የቡዳ ዛር እያለብን ትደር ስንይዝ 🚩💥
https://youtu.be/-EAYokco7nQ
"እንኳን ለሐዋርያት (የሰኔ) ጾም ፍቺ፤ እንዲሁም ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ"
#የቅዱሳኑ_እረፍታቸው
◈ የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም እንዲህ ኾነ፤ በዘመኑ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረው የሮም ንጉሥ ወደ አካይያ ዘምቶ ድል አድርጎ በደስታ ወደ ሮሜ ሲመለስ መኳንንቱን ለማስደሰት፤ ጣዖታቱንም ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ትጥቁን ለውጦ ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡ በዚህ ጊዜ "አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?" ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም "ልሰቀል ወደ ሮም እሔዳለሁ" አለው። "ዳግመኛ ትሰቀላለህን?" ባለው ጊዜም "አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ" ሲል መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም "ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድ ነበር። ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል፤" (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡
◈ በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
◈ እንደ ሥርዓታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን "እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ" አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ሐምሌ ፭ ቀን ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ በመስቀል ላይ ሳለም ተከታዮቹን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ ካዘዛቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ ሥጋውንም መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ሽቱ ቀብቶ፣ በነጭ ሐር ገንዞ ዛሬ ቫቲካን በምትባለዋ ስፍራ በክብር ቀብሮታል፡፡
◈ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ከእዚያም እግዚአብሔር በሞቱ እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም አደባባይ በጨካኙ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት ቁልቁል (እንደ አምላኬ አልሰቀልም ብሎ) በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
◈ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለ 2 ዓመት ከ6 ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት አንገቱን በሠይፍ ተሠይፎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይክፈለን፤ አሜን፡፡
#አቢያተ_ክርስቲያናቱ፤
#ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ-ወጳውሎስ፤ ከፒያሳ ወደ አስኮ በሚወስደው መስመር መንገድ ላይ የሚገኝ፡፡
#ሰዋስወ_ብርሃን_ቅዱስ-ጳውሎስ_ገዳም፤ ከ3ቱ መንፈሳውያኝ ኮሌጆች አንዱና ዋነኛው የሚገኝበት፡፡ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ 18ት ማዞሪያ ብላችሁ ስትሄዱ የሚገኝ፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የቡዳ መንፈስ ያለባችሁ ይሄንን አዳምጡ || ሸክላ ሰሪዎችና የተሳሳተው ንግግራችን || የዘወትር አምልኮትና ስግደት || በጸሎት ሰዓት አሳበ ይበታተናል 💥🔥🚩🔥 https://youtu.be/Fm_a4fHpN7I
◈ አንድ ዓይነ ሥውር በእጁ ደማቅ ብርሃን ያለው ፋኖስ ይዞ በጨለማ በመንደር ውስጥ እየሔደ ነው:: አንድ ሰው ድንገት ሲያልፍ አየውና ፋኖሱን ሲያይ ተገርሞ ጠየቀው:: "ይቅርታ ወንድሜ:: በእጅህ ፋኖስ አብርተህ ይዘሃል:: እንዳትደናቀፍ ነው እንዳልል እንደማይህ ዓይነ ሥውር ነህ:: የማታይ ከሆነ የፋኖሱ ብርሃን ምን ይጠቅምሃል?" አለው:: "ልክ ነህ የፋኖሱን ብርሃን አላይም:: የምይዘው እኔ በጨለማ ውስጥ ስሔድ እንዳልደናቀፍ አይደለም:: ሆኖም በጨለማ ውስጥ ብርሃን ሳልይዝ ከሔድኩ ሰዎች እኔን ስለማያዩኝ ከእኔ ጋር እንዳይጋጩ ወይንም እንዳይደናቀፉ ነው። ፋኖሴንን ከያዝሁ በብርሃኑ እኔን ያዩኛል" ብሎ መለሰለት።
◈ ወዳጄ በዚህች ጨለማ ዓለም ስትሔድ የልብህ ዓይን በመታወሩ ምክንያት የማታያቸው ብዙ እንቅፋቶች አሉ:: "ኸረ እኔ ዕውር አይደለሁም" ካልክ "ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም፡ የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ" ነው። (ራእ 3:17)
◈ በጨለማው ዓለም ስትሔድ ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ማሰብ ትገደዳለህ:: እውነተኛውን ፋና ክርስቶስን በጉያህ ከያዝክ ሰዎች እሱን አይተው በአንተ ከመሰናከል ይድናሉ:: አለዚያ ግን በአንተ ምክንያት የሚደናቀፈው ሰው ብዙ ነው። "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።" (ማቴ 5፡16)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«የጀማሪ ጠባይ»
◈ መንፈሳዊ ሕይወትን ገና ስትጀምረው ለፍጹምነት ጥቂት የቀረህ ያህል ይሰማሃል፤ አንተ ጋር ያለው ደስታ እና ሰላም ሌሎች ጋር የሌለ ይመስልሃል። በዚህች ሁከት በሞላባት ዓለም አንተ ብቻ ክርስቶስን እንዳገኘኸው ታስባለህ፤ የቀረው ሕዝበ አዳም እንዲሁ በከንቱ ሲርመሰመስ የሚውል ባካና ሆኖ ይታይሃል፤ ታዝንለታለህ፣ አይይይ ይህ ኃጢአተኛ ሕዝብ ምን ይሻለዋል? ትላለህ።
◈ የእውነተኛ መንፈሳዊ እድገት መገለጫ ግን ይህ አይደለም፤ ሰው ወደ እግዚአብሔር እየቀረበ ሲመጣ ከሌላው ሰው ይልቅ የራሱ ጉድለት ይታየዋል፤ መንፈሳዊነት የሚገልጥልህ ሰዎችን ተመልክተህ የምትፈርድበትን ውጫዊ ዓይንህን ሳይሆን ራስህን አይተህ የምትወቅስበት የውስጥ ዓይንህን ነው፤ መንፈሳዊ ሕይወትህ ሲጎመራ "አይ ሰው" ሳይሆን "አይ እኔ!" ያሰኝሃል። አባ ማቴዎስም እንዲህ ይላል "ሰው የበለጠ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርብ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆኑ እየታየው ይመጣል፤ ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ካየ በኋላ ከንፈሮቼ የረከሱብኝና የጠፋሁ ሰው ነኝ እንዳለ።"
◈ ከብቃት ደርሰህ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ቢታዩህ እንኳን ሁሉ እንዳንተ ስለሚመስልህ እንደ ዮሐንስ ሐጺር "ሚካኤል ይበልጣል ወይስ ገብርኤል?" እያልህ ከአጠገብህ የቆመውን ትጠይቃለህ እንጂ "አይይ አንተ እንኳን ገና አልበቃህም፤ ብዙ ይቀርሃል" ብለህ ወዳጅህን አታናንቅም ይልቅ "ለእኔ ብቻ ገልጦ ለሌላው እንዲሰውር የሚያደርገው ምንም ቁም ነገር የለኝም" በማለት ከወንድምህ የተሻልህ እንዳልሆንክ በፍጹም ልብህ ታምናለህ።
◈ ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስትሆን ገና ጥቂት ጸልየህ፣ ጥቂት ጾመህ፣ ጥቂት መጽውተህ ሳለ ግን ሩጫህን ወደ መጨረሱ የተቃረብህ ይመስልሃል፤ ጉዞህን በግማሽ እርምጃ ከመጀመርህ ከፍጻሜው ላይ የደረስህ ያህል ይሰማሃል "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምርሃል፤ ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብትሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው፤ ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ?" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው።
ጌታ ሆይ መንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ፤ እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።
(በዲያቆን አቤል ካሳሁን)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
በትዳር ተፈተንኩ ለምትሉ! እራሳችሁን በንጽሕና ጠብቁ! የአዛዝኤል አጋንንት በፋሽኑ ዓለም | ስትጸልዩ ዲያብሎስ ይሰቃያል | የዛር መንፈስ ስብሳቢ ነው 🚩 https://youtu.be/sBdvO8QRjP0
የቄስ ልጅ ነኝ ሰይጣን አይነካኝም || ዕድላችንን የወሰደ የእድሳት መተት || የእድሳት መተት ምንድነው? || በልጅነት የተዋረስነው መንፈስ #ebs #ንቁ 🔥💥 https://youtu.be/AP7vntNAXoo
የመምህር ተስፋዬ መልዕክት ለምስቶች || ቁረቡ እንቢ፣ ስገዱ እንቢ፣ ጸልዩ እንቢ አልን || የማንቆርበው ለምንድነው? ንስሐ ምንድነው? #ebs #eotc 💥🚩😭 https://youtu.be/vXzO2ouZu_E
"ጸሎትን የምንጸልየው እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር ኖሮ ለመንገር ወይም የረሳው ነገር ኖሮ ለማስታወስ አይደለም፤ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ቀርበን ወዳጆቹ እንድንኾን፣ ዘወትር እንዲረዳን፣ ራሳችንን ዝቅ ለማድረግ፣ ኃጢአታችንንም እንድናሰብ ነው እንጂ፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
