uz
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Kanalga Telegram’da o‘tish

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Ko'proq ko'rsatish
2 277
Obunachilar
+224 soatlar
+97 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
"ራስን ማየት => አንድ ወቅት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ አንድ በእድሜ ጠና ያሉ በመልካም ትዳር ያለፉ አንድ አዛውንት ነበሩ፤ እርሳቸውም ሆነ ባለቤታቸው ያላቸው መንፈሳዊ እውቀት የተራራቀ አልነበረም፤ አንድ ነው ቢባል ይቀላል። => ከእለታት በአንድ ቀን አዛውንቱ ጠዋት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገስግሰው ኪዳኑን አድርሰው እንደጨረሱ ዕለቱ ረቡዕ ነበረና፤ የግል ጸሎታቸውን ለማድረግ ወደ መጠለያ ገቡ፤ በዚያው መጠለያ ሌሎች የግል ጸሎታቸውን የሚያደርሱ በእጅ የሚቆጠሩ ሰዎች ነበሩ። => እርሳቸውም "በስመ አብ . . ." ብለው ጸሎታቸውን ጀመሩ፤ በጸሎታቸው መካከል ሁለት ከባድ ገጠመኝ ገጥሟቸው ኖሮ፤ እየተበሰጫጩ ወደ ቤታቸው አቀኑ። => ከቤታቸውም ደርሰው ምርር ብለው ለባለቤታቸው እንዲህ ሲሉ ገጠመኛቸውን መንገር ጀመሩ "ይገርምሻል! እኔ ምን አይነት ዘመን እንደመጣብን አላውቅም?"፤ ባለቤትም መልሰው "ምን ሆነህ ነው?" ብለው ጠየቁ፤ እርሳቸውም መልሰው "ቤተ ክርስቲያን ከመጠለያው ተገኝቼ 'በስመ አብ. . .'ብዬ ጸሎቴን ከመጀመሬ፤ በስተ ቀኜ ቆሞ የጸሎት መጽሐፉን ይዞ የሚጸልይ አንድ ጎልማሳ፤ ጸሎቱን አቋርጦ ድምጽ አሰምቶ ወደ መቅደስ እያዘገመ የነበረ ባልንጀራውን ጠርቶ፤ ስለ ዕቁብ ጉዳይ አንስቶ የባጡን የቆጡን ሲነጋገሩ፤ ቀና ብዬ እያየኋቸው 'እኔ እንዲህ ያዘንኩኝ ፈጣሪ ምን ያህል ያዝን ይሆን?' በማለት ከልቤ እያዘንኹኝ ሳለ፤ ይህ አላንስ ብሎኝ ፊት ለፊቴ የነበሩ እንደ አንቺ ዕድሜ የጠገቡ ሁለት እናቶች፤ የቤታቸውን ጉዳይ አንድም ሳያስቀሩ ያወጋሉ፤ ሰሞኑን ውኃ እንደሚጠፋ ጭምር ሲነጋገሩ ሰምቻለሁ፤ እኔም ነገራቸው አስገርሞኝ፤ ምን አለ ከሚያወሩ ጥቂት ቢጸልዩ እያልኩኝ ጨጓራዬን ስልጥ ቆይቼ 'ይህን ያሳየኽኝ አደራህን ሰላም አውለኝ' ብዬ ወደ ቤቴ መጣሁ እልሻለሁ፤ እንደው አይገርምሽም ጉድ እኮ ነው?" ብለው ንግግራቸውን በመጠይቅ አሳረፉ። => ሚስትየውም በአግራሞት ቀጠል አድርገው "እውነት ነው ይገርማል! እኔ ግን የገረመኝ ይህን ሁሉ ጉድ በዐይንዎ አይተው በጆሮዎስ ሰምተው ነው?" በማለት ይጠይቃሉ፤ ከንዴት በረድ ያሉት አባወራ ቀጠል አድርገው "በዐይኔ ሳላይ በጆሮዬ ሳልሰማ ከየት አምጥቼ አወራለሁ?"፤ ሚስትየውም መልሰው "ታዲያ እርስዎስ ከሰዎቹ በምን ተሻሉ፤ ይህን ሁሉ የሰው ጉድ ሲመለከቱ እርስዎስ ምኑን ጸሎት አደረጉት፤ በሰው ከሚናደዱ በራስዎ ነው ሊናደዱ የሚገባው፤ ሌላው ሲሠራ መጥፎ የተባለ ለእርስዎ ጥሩ ሊሆን፤ ለሌላው ሬት የሆነ ለእርስዎ ማር ሊሆን አይችልም" ብለው ገሰጿቸው። "ጭብጥ ለሌሎች ስናስተምር ራሳችንን እንዳንጥል፤ በነቀፌታ ውስጥ እንዳንገኝ ልንጠነቀቅ ይገባል፤ የጨው ዕቃ ሌላውን ሲያጣፍጥ ለራሱ መጣፈጥ የለውም፤ እንደዚያ እንዳንሆን ራሳችንን ቆም ብለን ማየት ይገባናል። => "ነገር ግን ሌሎች ከሰበክኹ በኋላ ለራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛለሁ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ። (1ኛ ቆሮ 9፥27) አባ ጴሜንም ሌሎችን እያስተማረ እርሱ የማይኖርበትን ሰው እንዲህ በማለት ይገልጸዋል => "የሚያስተምር ነገር ግን የሚያስተምረውን የማይፈጽም ሰው ማለት ለብዙዎች ለጥማቸው ማርኪያ፤ ለንጽሕናቸውም ምንጭ እንደሚሆን ነገር ግን ራሱን እንደማያጠራ ምንጭ ማለት ነው።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

=> የማይዘነጋ ነው፦ "አዳም መራራ ሕይወትን የምታመጣበትን ዕፀ በለስን የበላበት አፉ በደል አለበት። ለዚህ ካሳ ይከፍል ዘንድ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ መራራ ሐሞትን ጠጣ።" የዕለተ ዓርብን
=> የማይዘነጋ ነው፦ "አዳም መራራ ሕይወትን የምታመጣበትን ዕፀ በለስን የበላበት አፉ በደል አለበት። ለዚህ ካሳ ይከፍል ዘንድ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ መራራ ሐሞትን ጠጣ።" የዕለተ ዓርብን የጌታችንን ውለታ እንዘነጋ ዘንድ እንዴት ይሆናል? የማይዘነጋ ነውና። እንኳን አደረሳችሁ ለመድኃኔዓለም ወረሃዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ከእንግዳዬ ጋር የነበረኝ ቆይታ #ክፍል_1 || አጋንንቱ ጨርቃችንን አስጥለውን ነበር || ስግደት አይከለክለኝም ጸሎት እንጂ #ethiopia #ebstv 😱🚩🔥💥 https://youtu.be/dbrqK0LxwYU

የማይጋለጡና የማይያዙ ክፉ መናፍስቶች ጸበል ስንሄድ እቤት የሚቀሩ አጋንንቶች መምህር ተስፋዬ አበራ | ግርማ ወንድሙ #ethiopia #ebstv 🔥🚩😭 https://youtu.be/H2tS02A0qD4?si=J_6Ux0rxVTjrA9UA

🙏 (26) የጻድቁ አባታችን አቡነ ሃብተ ማሪያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። የአባታችን ቃልኪዳናቸው ከሥጋ በሽታ፣ ከቸነፈር፣ ከወርሽኝ፣ ከነፍስ ቁስል (ከኃጢአት) ይሠውረን። 🙏🙏
🙏 (26) የጻድቁ አባታችን አቡነ ሃብተ ማሪያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። የአባታችን ቃልኪዳናቸው ከሥጋ በሽታ፣ ከቸነፈር፣ ከወርሽኝ፣ ከነፍስ ቁስል (ከኃጢአት) ይሠውረን። 🙏🙏

=> እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወርሃዊ መታሰቢያ አደረሳችሁ፣ አደረሰን። የሰማዕቱ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። ቃልኪዳኑ ተራዳኢነቱ አማላጅነቱ አይለየን። (ነሐሴ 25) አሜን 🙏🙏
=> እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወርሃዊ መታሰቢያ አደረሳችሁ፣ አደረሰን። የሰማዕቱ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። ቃልኪዳኑ ተራዳኢነቱ አማላጅነቱ አይለየን። (ነሐሴ 25) አሜን 🙏🙏🙏

በስዕለ አድህኖ የተደገመ ድግምት ያመጣው መከራ || በመስቀል እንዴት ድግምት ይሰ'ራል? | ካሲናዬን ፊልም ለተቻችሁ! አዲስ ፊልም መምህር ተስፋዬ አበራ 😱🚩💥 https://youtu.be/a8QqN3VH2o8

እኛን ማስተካከል ለምን አቃተን? | እስማዚያ አደገኛው መንፈስ | እስማዚያ የክህደትና የፍልስፍና መንፈስ ልዩ መገለጫዎች | የሰውን የክፋት ጥግ ተመልከቱ 🔥😱 https://youtu.be/CENsBeRA7pg?si=tnvLpQ-tZXGm2ZDc

ተጠንቀቁ! በፎቶና በጫት የተደገመ ድግምትና ጣጣው | የዲያቆኑ ግብረ ሰዶማዊነት ሲገለጥ | የአብሾና አፍልሆ መንፈስ | መምህር ግርማ | ተስፋዬ አበራ 😱💥🚩🔥 https://youtu.be/5DO3YU4fA3A

"ራስን ማየት => አንድ ወቅት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ አንድ በእድሜ ጠና ያሉ በመልካም ትዳር ያለፉ አንድ አዛውንት ነበሩ፤ እርሳቸውም ሆነ ባለቤታቸው ያላቸው መንፈሳዊ እውቀት የተራራቀ አልነበረም፤ አንድ ነው ቢባል ይቀላል። => ከእለታት በአንድ ቀን አዛውንቱ ጠዋት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገስግሰው ኪዳኑን አድርሰው እንደጨረሱ ዕለቱ ረቡዕ ነበረና፤ የግል ጸሎታቸውን ለማድረግ ወደ መጠለያ ገቡ፤ በዚያው መጠለያ ሌሎች የግል ጸሎታቸውን የሚያደርሱ በእጅ የሚቆጠሩ ሰዎች ነበሩ። => እርሳቸውም "በስመ አብ . . ." ብለው ጸሎታቸውን ጀመሩ፤ በጸሎታቸው መካከል ሁለት ከባድ ገጠመኝ ገጥሟቸው ኖሮ፤ እየተበሰጫጩ ወደ ቤታቸው አቀኑ። => ከቤታቸውም ደርሰው ምርር ብለው ለባለቤታቸው እንዲህ ሲሉ ገጠመኛቸውን መንገር ጀመሩ "ይገርምሻል! እኔ ምን አይነት ዘመን እንደመጣብን አላውቅም?"፤ ባለቤትም መልሰው "ምን ሆነህ ነው?" ብለው ጠየቁ፤ እርሳቸውም መልሰው "ቤተ ክርስቲያን ከመጠለያው ተገኝቼ 'በስመ አብ. . .'ብዬ ጸሎቴን ከመጀመሬ፤ በስተ ቀኜ ቆሞ የጸሎት መጽሐፉን ይዞ የሚጸልይ አንድ ጎልማሳ፤ ጸሎቱን አቋርጦ ድምጽ አሰምቶ ወደ መቅደስ እያዘገመ የነበረ ባልንጀራውን ጠርቶ፤ ስለ ዕቁብ ጉዳይ አንስቶ የባጡን የቆጡን ሲነጋገሩ፤ ቀና ብዬ እያየኋቸው 'እኔ እንዲህ ያዘንኩኝ ፈጣሪ ምን ያህል ያዝን ይሆን?' በማለት ከልቤ እያዘንኹኝ ሳለ፤ ይህ አላንስ ብሎኝ ፊት ለፊቴ የነበሩ እንደ አንቺ ዕድሜ የጠገቡ ሁለት እናቶች፤ የቤታቸውን ጉዳይ አንድም ሳያስቀሩ ያወጋሉ፤ ሰሞኑን ውኃ እንደሚጠፋ ጭምር ሲነጋገሩ ሰምቻለሁ፤ እኔም ነገራቸው አስገርሞኝ፤ ምን አለ ከሚያወሩ ጥቂት ቢጸልዩ እያልኩኝ ጨጓራዬን ስልጥ ቆይቼ 'ይህን ያሳየኽኝ አደራህን ሰላም አውለኝ' ብዬ ወደ ቤቴ መጣሁ እልሻለሁ፤ እንደው አይገርምሽም ጉድ እኮ ነው?" ብለው ንግግራቸውን በመጠይቅ አሳረፉ። => ሚስትየውም በአግራሞት ቀጠል አድርገው "እውነት ነው ይገርማል! እኔ ግን የገረመኝ ይህን ሁሉ ጉድ በዐይንዎ አይተው በጆሮዎስ ሰምተው ነው?" በማለት ይጠይቃሉ፤ ከንዴት በረድ ያሉት አባወራ ቀጠል አድርገው "በዐይኔ ሳላይ በጆሮዬ ሳልሰማ ከየት አምጥቼ አወራለሁ?"፤ ሚስትየውም መልሰው "ታዲያ እርስዎስ ከሰዎቹ በምን ተሻሉ፤ ይህን ሁሉ የሰው ጉድ ሲመለከቱ እርስዎስ ምኑን ጸሎት አደረጉት፤ በሰው ከሚናደዱ በራስዎ ነው ሊናደዱ የሚገባው፤ ሌላው ሲሠራ መጥፎ የተባለ ለእርስዎ ጥሩ ሊሆን፤ ለሌላው ሬት የሆነ ለእርስዎ ማር ሊሆን አይችልም" ብለው ገሰጿቸው። "ጭብጥ => ለሌሎች ስናስተምር ራሳችንን እንዳንጥል፤ በነቀፌታ ውስጥ እንዳንገኝ ልንጠነቀቅ ይገባል፤ የጨው ዕቃ ሌላውን ሲያጣፍጥ ለራሱ መጣፈጥ የለውም፤ እንደዚያ እንዳንሆን ራሳችንን ቆም ብለን ማየት ይገባናል። => "ነገር ግን ሌሎች ከሰበክኹ በኋላ ለራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛለሁ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ። (1ኛ ቆሮ 9፥27) አባ ጴሜንም ሌሎችን እያስተማረ እርሱ የማይኖርበትን ሰው እንዲህ በማለት ይገልጸዋል => "የሚያስተምር ነገር ግን የሚያስተምረውን የማይፈጽም ሰው ማለት ለብዙዎች ለጥማቸው ማርኪያ፤ ለንጽሕናቸውም ምንጭ እንደሚሆን ነገር ግን ራሱን እንደማያጠራ ምንጭ ማለት ነው።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የዝሙት ቪዲዮ የሚመለከቱ አገልጋዮች! | ሰው ለምን ተፈወሰ ብለው ለሚናደዱ | ኃጢአትን Normal የማድረግ በሽታ | የጋብቻ ሥርዓታችን ወዴት እየሄደ ነው?? https://youtu.be/VflPf-W7z18

=> ብሥራተ ገብርኤል እንኳን ለወርሃዊው የብሥራተ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን! => "መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ
=> ብሥራተ ገብርኤል እንኳን ለወርሃዊው የብሥራተ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን! => "መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።" (ሉቃ. ፩፥፳፰ /1፥28/) ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሐርና ወርቅ አስማምታ ትፈትል ነበር => ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በቤተ መቅደስ ተገልጦ "ከእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና እነሆ ትፀንሺያለሽ፤ ትወልጂማለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ" ብሎ አበሰራት። ይህ ቀን በሰው ልጆች ከሞት መዳን፤ ልጅነትን የማግኘት የመጀመሪያው መነሻ ነጥብ ተደርጎ በክርስቲያኖች ዘንድ ይከበራል። ሊቁ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ላይ ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብሥራትና ስለ አምላክ ሰው መሆን ሲመሰክር። => "እርሱ እግዚአብሔር አብ ንጽሕናሽን ባየ ጊዜ ስሙ ቅዱስ ገብርኤል የሚባል መልአክ ወደ አንቺ ላከ፤ መንፈስ ቅዱስ በላይሽ ያድራል፤ የልዑል ሀይልም ይጋርድሻል አለሽ" እያለ ይተነትናል። => ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ድኅነት የማግኛችን የመጀመሪያው ነጥብ የተጀመረው በዚህ ዕለት ስለሆነ በዓሉን በድምቀት እናከብረዋለን የእመቤታችን አማላጅነት፣ የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት አይለየን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ብዙዎች የማይናገሩት እውነት ተገለጠ! || ከአጋንንት ለመላቀቅ ወሳኙ ነገር || ብልጥነት በክርስቶስ አይፈለግም || መምህር ግርማ ወን | ተስፋዬ አበራ 💥🔥😱 https://youtu.be/hM9SiXjffwU

"ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ።" (ኤር. ፴፫፥፫ /33፥3/) => ጸሎት በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ ነው፤ ማዕበል ለሚያንገላታቸው መልህቅ ነው፤ የድሀው ሀብት፣ የባለፀጋው ደህንነት፤ የታማሚው መዳኛ፣ ጤና ማግኛ ነው። ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል። => ዘወትር ስንጸልይ ከክፉ እንርቃለን ከአምላካችን ጋር ይበልጥ እንቀራረባለን። ዘወትር እንጸልይ። በበረከቱም ይጎብኘን። አሜን። እንበርታ 🙏🙏🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ይድረስ ለመምህር ተስፋዬ አበራ ዕድላችን ሲያዝብን ምን እናድርግ? ወሳኝ የቅዱስ ቁርባን ጥቅሞች || ሰይጣን ነው የሚያጠምቃቹ ተጠንቀቁ! #ebs 🚩😱 https://youtu.be/LvPG5BUzZns?si=xZlLpyWRT4MLaW1T

=> ድንግል ሆይ፣ ቅድስት ሆይ፣ ንጽሕት ሆይ፣ የተመሰገንሽ ቡርክት ሆይ የድግልናሽ ምስጋና በኹሉ መላ። ውዳሴሽም በዓለም ዙሪያ ሰፈፈ => የውቅያኖስ ባሕር በምልአቱ ውሱን ነው የሐኖስም ባሕር በመጠ
=> ድንግል ሆይ፣ ቅድስት ሆይ፣ ንጽሕት ሆይ፣ የተመሰገንሽ ቡርክት ሆይ የድግልናሽ ምስጋና በኹሉ መላ። ውዳሴሽም በዓለም ዙሪያ ሰፈፈ => የውቅያኖስ ባሕር በምልአቱ ውሱን ነው የሐኖስም ባሕር በመጠኑ ልክ አለው፤ => ለአንቺ ምስጋና ግን ልክና መጠን ወሰንና መስፈርት፣ ማለቂያም የለውም አእምሮም አይወስነውም አንደበትም ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም። => ኦ ድንግል፣ ኦ ቅድስት፣ ኦ ንጽሕት፣ ኦ ቡሩክት፣ ኦ ኅሪት፣ ስብሐተ ድንግልናኪ መልአ በኵለሄ ወውዳሴ ዚአኪ ሰፈፈ ውስተ ኵሉ አጽናፈ ዓለም፤ ባሕረ ውቅያኖስ ውሱን በድንጋጊሁ ወባሕረ ሐኖስኒ ዐቅም ቦ በአምጣኒሁ ወለስብሐተ ዘኣኪሰ አልቦቱ ማኅለቅት ወኅሊናኒ ኢይክል አግምሮቶ ወልሳንኒ ኢይክል ፈጽሞቶ" (አርጋኖን ዘሰኑይ ፰ ÷ ፲ - ፳፰) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

እኛን የሚያስተካክሉ ድንቅ ትምህርቶች በንስሐ አባት ሽፋን መተት የሚመትቱ አጋንንት ከሚስቡ የንስሐ አባቶች ተጠበቁ | ቀሲስ ሄኖክ | መምህር ተስፋዬ https://youtu.be/QQKN6Me2eGM

=> በቀን መጨረሻ ዝና፣ ውበት፣ ሥልጣን፣ ሐብት ትርጉም የላቸውም፡፡ የኑሮአችን የመገባደጃ ትውስታ ፍቅር ናት፡፡ በልጽገን ለብቻችን ከበላነው ቡፌ ይልቅ በድህነት በአንድ ሳህን የቆረጠምናት ቆሎ ሆድ ትወጥራለች፡፡ ግዴለም ሰውን እናፍቅር! ሁሉ ሰውን እናፍቅርና ሙሉ ሰውን እንሁን፡፡ መጽሐፉም እንዳለ፦ የጐመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል።" (ምሳ. 15፡17) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በፍጹም ክፉ መንፈስ ነው ብለን ሳይሆን ‹‹ሰው ነው፣ እከሌ ነው እንዲህ ያደረገኝ፣ ያበላሸብን›› ብለን ስለምናስብ በውጭ ሆነው የሚፈትኑን ክፉ መናፍስትን ሴራቸውን፣ በእኛ ላይ ያለቸውን ውጫዊ ጠላትነታቸውን በቀላሉ አንረዳም፡፡ የውስጣዊ ጠላት የሆኑት ክፉ መናፍስት ውስጣችን ስላሉ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ ጸበል በመጠመቅ፣ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል ድል ልንነሳቸው እና ከሕይወታችን ልናርቃቸው እንችላለን፡፡ የውጫዊ ጠላቶቻችን ግን በሰው ላይ እያደሩ፣ ከፊት እየቀደሙ ስለሚፈትኑን በቀላሉ በመንሳዊ የጦር ዕቃዎች ተዋግተን ልናርቃቸው አንችልም፡፡ ካወቅንባቸው ፈጣሪ ከእኛ እንዲያርቃቸው መጸለይ ነው፡፡ ምክንያቱም የሚዋጉን በውስጥ እና ፊት ለፊት ሳይሆን የእነሱ ተወካይ በሆነው በሰው ላይ አድረው ስለሆነ ነው፡፡ ውጊያቸው የትንቅንቅ ሳይሆን የሽምቅ ነው፡፡ በሰው ላይ አድረው ብቅ ብለው የሚሠሩትን ሠርተው፣ ሰውዬውን እኛን ለመጉዳት እንደ መሣሪያ ተጠቅመው ሽል ይላሉ፡፡ አይዛዙም፣ አይታዩም፣ አይጨበጡም፡፡ ለምሳሌ ገርግር ዓይነ ጥላ የተባለውን ብንመለከት ይህ ክፉ መንፈስ በውስጣችን ሳይኖር ነገር ግን በሰው ላይ እያደረ ብዙ ነገራችንን ሊያበላሽ እና ሊዘጋብን ይችላል፡፡ በጥሩ ውጤት የተመረቃችሁበትን ዲግሪ/ ማስትሬት ዲግሪ/ እና ብቁ የሥራ ልምዳችሁን ይዛችሁ ተወዳድራችሁ ያለፋችሁትን ሥራ ግርግር ዓይነ ጥላ በሚፈትናችሁ ሰው ላይ አድሮ ሊጥላችሁ ይችላል፡፡ መንፈሱ ስለሚጠላችሁ የእውቀት ፈተናን አልፋችሁ የአንደበት ፈተና በሆነው ይጥላቹኃል፡፡ ፈተናችሁን እና ሁሉን ነገር በብቃት አልፋችሁ የቅጥር ውል ልትፈራረሙ ስትሉ ቀጣሪያችሁ ዓይነ ውኃቹን አይቶ አስጠልታችሁን ውሉን ሊተው ይችላል፡፡ ይህ እና ይህን የመሳሰሉት ዕድሎቻችን የሚበላሹት በውጭ ሆነው በሰው እያደሩ በሚፈትኑን ክፉ መናፍስት ነው፡፡ አንድ ነገር ጀምሮ በቀላሉ በሰው የሚበላሽበት ሰው የሚወቅሰው፣ አበላሸብን ብሎ የሚያስበው ሰውን እንጂ ውጫዊ ጠላቱን ክፉ መንፈስን አይደለም፡፡ በሰው የሚበላሹብን ነገሮች ውጫዊ ጠላቶቻችን የሆኑት ክፉ መናፍስት ናቸው ብለን በፍጹም አናስብን፡፡ ምክንያቱም የምንከሰው እና የምንወቅሰው በሥጋ ዓይናችን የምናየውን ሰውን እንጂ በዓይን የማናያቸውን ክፉ መናፍስትን ስላልሆ፡፡ የውጫዊ ጠላት ትልቁ ጉዳት፣ የእኛ ጠላት ብቻ ሳይሆን የሰውዬው ጠላትም ይጎዳናል ብዙ ነገር ያበላሽብናል፡፡ ለምሳሌ ሰውዬው ዛር ያለበት ከሆነ፤ እናንተ ደግሞ ጥሩ መንፈሳዊ እና የጸሎት ሰው ከሆናችሁ እናንተ ላይ ያለው ቅዱስ መንፈስ እና ሰውዬው ላይ ያለው ርኩስ መንፈስ ስለሚጋጭ ሰውዬው ያለምንም ምክንያት ሊጠላችሁ እና ጉዳያችሁን ሊፈጽምላችሁ ሊያስፈጽምላችሁ አይችልም፡፡ ሰውዬው ላይ ዓይነ ጥላ፣ ቡዳ እና የዛር ቡዳ ካለበት ገና ሲያያችሁ ታስጠሉታላችሁ፡፡ የእናንተን ጉዳይ ከሚፈጽም ሞት ይሻለዋል፡፡ ያመናጭቃችሃል፣ ያዋክባቹሃል፣ ያለ ምክንያት ምክንያት ፈልጎ ለሌላ ቀን ይቀጥራቹሃል አልያም አይፈጽምላቹም፡፡ አንዳንድ ሰው ጥሎበት በውስጡ ካሉት ውስጣዊ ጠላቶች ይልቅ የሰዎች ውጫዊ ጠላቶች እጅጉን ይፈትኗቸዋል ሕይወታቸውን ያከብዱባቸዋል፡፡ እነሱ ላይ ያለው ክፉ መንፈስ የእኛን ነገር በማነፍነፍ ለማበላሸት እና ለማጨናገፍ በብዙ ይጥራል፡፡ ብዙ ሰው ‹‹እከሌ ጎዳኝ፣ ይህን ነገሬን አበላሸብኝ›› ይላል፡፡ ነገር ግን በሰውዬው ላይ ያለው ወይም ያደረው የውጭ ጠላቱ ነገሮቹን እንዳበለሸና እንደጎዳው አይረዳም፡፡ ትዝ ካላችሁ የጌታችን ጠላት የሆነው ሰይጣን ጌታችንን ፊት ለፊት መዋጋት እና ማሳደድ ስላልቻ በሄሮድስ ላይ አድሮ ነው እስከሞት የፈለገው እና ያሳደደው፡፡ ሰይጣን ለጌታችን በሄሮድስ/በሰው ላይ ያደረ ውጫዊ ጠላት ነበር የሆነበት፡፡ እመቤታችን በስደቷ ወራት ሰይጣን ፊት ለፊት መዋጋት ስላልቻላት፣ በሰው ላይ እያደረ ውጫዊ ጠላት ሆኗት ሰዎች እንዳይራሩላት፣ ርቧት ምግብ እንዳይሰጧት፣ ውኃ ጠምቷት ውኃ እንዳይሰጧት ሲፈትናት ነበር፡፡ እኛንም ልክ እንደዚሁ ከሰዎች መልካም የሆኑ ነገሮች ወደ እኛ እንዳይመጡ፣ ሕይወታችንን እንዳይለውጡ በሰው እያደረ ያስቀራል ያበላሻል፡፡ ስለዚህ ‹‹እኔ ጠላት የለብኝም›› ብለን ከመዘናጋት ከውስጣዊ እና ከውጫዊ ጠላት ለመላቀቅ በአምልኮት ሕይወት መበረታት ይገባናል፡፡ ‹‹ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡፡ በምድሪቱ ዙሪያ ጠላት ይመጣል›› ት.አሞጽ 3÷11 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

"የተጎዳነው ጠላት የለብንም ብለን በማሰባችን ነው!" ተወዳጆች ሆይ እኛ ሰዎች በብዙ መልኩ የተለያዩ ጎዳቶችን በሕይወታችን እናስተናግዳለን፡፡ ነገር ግን በሕይወታችን እጅጉን የሚጎዳን አስተሳሰብ ‹‹እኔ ጠላት የለብኝም›› ብለን ማሰባችን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የጠላት የለብኝም አስተሳሰባችን በተግባር ተገልጦ ብዙ ነገራችንን አናውጦ እና በጥብጦ ይታያል፡፡ ለሰው ልጅ ዋነኛው ጠላቱ ጠላት የለብኝም ማለቱ ነው። እንኳን የሰው ልጅ እግዚአብሔር፣ ቅዱሳን መላእክት እና ቅዱሳን ጠላት አለባቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ ጠላት ሰይጣን ነው፡፡ መዝሙረኛው ዳዊት ‹‹ጠላት በቅዱሳንህ ላይ እንደ ከፋ መጠን›› ያለው ይህንን ነው፡፡ /መዝ 74÷3/ ዘርጋው ከፍተኛ የአማረኛ መዝገበ ቃላት ‹ጠላት› የሚለውን ‹‹ባላጋራ፣ ተፃራሪ፣ ወዳጅ ያልሆነ፣ ባላንጣ›› በማለት ይተረጉመዋል፡፡ ስለዚህ ሰይጣን ለእግዚአብሔር እና ለቅዱሳኑ በሙሉ ባላጋራ፣ ተፃራሪ፣ ወዳጅ ያልሆነ ነው፡፡ በሰው ልጅ ሕይወት ‹ጠላት› የለብኝም ብሎ እንደማሰብ ሞኝነት የለም፡፡ ሁላችንም ይብዛም ይነስም፣ በግልጽም ይሁን በስወር ጠላት አለብን፡፡ የቱንም ያህል ጻድቅ እና ለሰዎች እጅጉን መልካም ብንሆንም ጠላት አለብን፡፡ በዓለም ላይ ያለ ጠላት የሚኖር ሰው የለም፡፡ እኛ ለሰው ጠላት ላንሆን እንችላለን ነገር ግን እኛ ጠላት አናጣም፡፡ እስኪ አሁን ካለንበት ሕይወት ወደ ኃላ በሐሳባችን መለስ ብለን ብንቃኝ ዛሬ ላይ ያለውን የማንፈልገውን፣ መከራ፣ ፈተና የበዛበትን የስርጓሁጥ ሕይወት የመሩን ጠላቶቻችን ናቸው፡፡ ዛሬ ላይ ያለንበት ሕይወት ትላንት በጠላቶቻችን ተቀይሶ የምንኖረው የመከራ ሕይወት ነው፡፡ አንዳንዴ ‹‹እኔ ጠላት የለብኝም›› ማለት በራሱ ለጠላት ምቹ ስለሆነ ስውር እና ግልጽ ጠላት ያበዛብናል፡፡ እስኪ ጠላቶቻችንን በሦስት ዋናነት በአምስት ንዑስነት ከፋፍለን እንመልከት፡፡ ሦስት ዋና ዋና ጠላቶቻችን የምንላቸው አንደኛ ሰው ነው፡፡ ሁለተኛ ክፉ መናፍስት ናቸው፡፡ ሦስተኛ የለበስነው ሥጋ ነው፡፡ እነዚህን በንዑስ ስንመለከታቸው አንደኛ የውስጥ ጠላት፡፡ ሁለተኛ የውጭ ጠላት፡፡ ሦስተኛ የቤተሰብ ጠላት፡፡ አራተኛ የወዳጅ ጠላት፣ አምስተኛ የምቀኛ ጠላት ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የብዙዎቻችን ችግር ሰይጣንን እንደ ክፉ ጠላት አለማየት ነው። ወይም ለሰይጣን ያለን አናሳ ግምት ነው። አብዛኞቻችን "ሰይጣን" ስንል በአንድ ወቅት መልአክ እንደሆነ እንረሳለን። ከሰማይ መውደቁን፣ ሰማያዊ ክብሩን ማጣቱን እንጂ የወደቀ መልአክ፣ አጥፊ እና የሰው ሕይወት ገፊ መልአክ መሆኑን እንዘናጋለት። በዚህም ያለ ጸሎት፣ ያለ ስግደት፣ ያለ አምልኮት "ሰይጣን ምን ያመጣል፣ ምን አቅም አለው" እያልን ጥንተ ጠላታችን ፈታኛችን እንደሆነ ረስተናል። ጠላትን መርሳት እና መዘናጋት የሕይወት ዘመን ክፉ ዋጋ ያስከፍላል። በዓለም ላይ ከተደረጉት ጦርነቶች ውስጥ የማይሸነፉት ኃያላን የተሸነፋት ለጠላታቸው ዝቅ ያለ ግምት በመስጠት እና ጠላትን በመናቅ ነው። ጠላትን መናቅ በራሱ መሸነፍ ነው። ወዳጄ ለሰው ልጅ ጠላቱ ሰውም ነው፡፡ ሰው ለሰው መድኃኒቱም ገዳዩም ነው፡፡ የሰው ልጅ በክፉ ጠባዩ እና በጭካኔው አደገኛ ፍጡር ስለሆነ አንዳንዴ በሁለት እግር የሚሄድ አውሬ ይሆናል፡፡ ሰው ሰውን ሲገድል፣ ሲያጎሳቁል ስናይ የሰው ልጅ በሁለት እግሩ የሚሄድ አደገኛ አውሬ ይሆናል፡፡ ሌላው ለሰው ልጅ የለበሰው ሥጋ ካላወቀበት ከፍተኛ መረን የለቀቀ ክፉ የኃጢአት ፍላጎቱ ጠላት ይሆንበል፡፡ ስለዚህ በሕገ እግዚአብሔር ልጓምነት ያልታሠረ ሥጋ ለሰው ልጅ ጠላቱ ይሆንበታል፡፡ እስኪ ጠላቶቻችንን ዘርዝረን እንመልከት፡፡ ለሰው ልጅ አንደኛ ጠላቱ የውስጥ ጠላቱ ነው፡፡ ይህም በውስጣችን አብሮን የተለወደው፣ ያሸመቀው፣ ያደፈጠው፣ አብሮን ያደገው ነገር ግን በጭራሽ በውስጣችን እስከ መኖሩ የማናውቀው፣ የማንጠረጥረው ዓይነ ጥላ፤ በቤተሰቦቻችን በተለይም በእናት አባት እና በአያቶቻችን በኩል ዘራችንን ተከትሎ የሚመጣው፣ የሚዋረሰን፣ አብሮን የሚኖረው የቤተሰብ ዛር፤ በሕይወታችን፣ በኑሯችን፣ በስኬታችን፣ በትዳራችን፣ በሥራችን፣ በእውቀታችን፣ በተሰጦአችን በአጠቃላይ በመልካም ዕድላችን ሰዎች በመቅናት የሚልኩብን እና የሚያስልኩብን የዕድል መተት፤ በውበታችን፣ በደም ግባታችን፣ በተክለ ሰውነታችን /በዓይን፣ በጥርስ፣ በጸጉር፣ በቁመና ወዘተ/ ውበት የሚገቡት የቡዳ መንፈሶች፤ የወሲብ ቪዲዮ ስናይ ሳናውቅ ወደ ውስጣችን የምናስገባቸው የዝሙት አጋንንት እዚህ እና ሌሎችም ክፉ መናፍስት ውስጣዊ ጠላቶቻችን ይሆናሉ፡፡ እነዚህ ውስጣዊ ጠላቶች ክፉ መናፍስቶች ካላወቅን ካላስተዋልን፣ ስለ እነሱ ጎጂነት መረጃው ከሌለን በማናውቃቸው ነገር ግን በሚታወቁት ውስጣዊ ጠላቶቻችን ሕይወታችን ሊበላሽ፣ የውጭ ገጽታችን ሊሟሽሽ፣ የነገ ራዕያችን፣ ተስፋችን ሊደነብሽ ይችላል፡፡ ስለዚህ እነዚህ ውስጣዊ ጠላቶቻችን በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ እነዚህ የማናውቃቸው ግን የሚታወቁ ውስጣዊ ጠላቶቻችን የሚያበላሹት የሚታየውን ነገአችንን ብቻ ሳይሆን ለሰው የማይታየውን ሰላማችንን፣ ደስታችንን ጭምር ነው፡፡ የውስጣዊ ጣላቶታችን አንደኛው እና አደገኛው ነገር በውስጣችን ሆነው ውስጣችንን ይበሉታል፣ ይረብሹታል፣ ግራ ያጋቡናል፣ በሽታ/ደዌ ሆነው ሕይወታችንን ያከብዱታል፡፡ ለምሳሌ በውስጣችን ያደፈጠ ነገር ግን እራሱን በተንኮል የገለጠ ቡዳ ካለብን ዓይናችን ሕመምተኛ፣ ውስጣዊ ጤንነታችን በሽተኛ ይሆናል፡፡ የውስጥ ጠላት ባስ ሲል እራሱን በእንደዚህ ያለ የበሽታ ስቃይ ይገልጣል፡፡ ውስጣችን ያደፈጠ የቤተሰብ ዛር ካለ ውስጣችን፣ የሠራ አካላችን ሕመምተኛ ይሆናል፡፡ ክፉ መንፈሱ በውስጣችን ሆኖ በተለያዩ ለሐኪም ግራ በሚያጋቡና መፍትሔ በሌላቸው ሕመም እና በሽታ ያሰቃየናል፡፡ የወስጥ ጠላት ሆኖ የተቀመጠ፣ ያደፈጠ የቤተሰብ ዛር ሴራውንና ጥቃቱን ካላወቅንበት እስከ ሞት የሚያደርስ በሽታ ይሆናል፡፡ በውስጣችን ያለው ዛር ሥጋችን ላይ ሲቀመጥ ውጋት፣ ቁርጥማት ወዘተ ይሆናል፡፡ የውስጥ አካላችን ለምሳሌ ኩላሊታችን፣ ልባችን፣ ሳንባችን፣ ጉበታችን፣ ሴቶች ማሕጸናቸው ላይ ሲቀመጥ፤ ሳይንስ ያረጋገጠው እና ያወቀው የኩላሊት በሽታ፣ የልብ ሕመም/ የልብ ድካም ወዘተ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ደማችን ውስጥ ያለ ዛር ከሆነ የደም ካሰር፣ የደም መርጋት ወዘተ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ማህጸን ላይ ያለ ዛር ከሆነ የማህጸን ዕጢ/የማህጸን ካንሠር ወዘተ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ አጥንታችን ውስጥ ያለ ዛር ከሆነ የአጥንት ካንሠር እና ከአጥንት ጋር የተያያዘ በሽታ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ጭንቅላታችን/ሕሊናችን ውስጥ የተቀመጠ ዛር ከሆነ የጭንቅላት ዕጢ፣ የሚጥል በሽታ፣ የጭንቀት በሽታ፣ የኦቲዝም፣ የአልዛይመር፣ ንቃተ ሕሊና የማጣት ወዘተ በሽታ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ወዳጄ ውስጥ ያሸመቀ እና የተደበቀ ጠላት ካላወቅንበት እና ካልንነቃንበት፣ ጠባዩን እየቀያየረ፣ እኛንም እያስመረረ የዕድሜ ዘመን ችግር እና የዘመናት ስቃይ ይሆንብናል፡፡ ሁለተኛው ጠላቶቻችን ሁለት ናቸው፡፡ አንደኛው የምናየው ሰው ሲሆን ሁለተኛው ከውጭ ሆነው የሕይወት ጠላት የሚሆኑን ክፉ መናፍስት ናቸው፡፡ የሚታየውን ለሰው ውጫዊ ጠላት የሆነውን ሰውን ትተን ክፉ መናፍስትን ብንመከት፤ ለሰው ልጅ ውጫዊ ጠላቱ ክፉ መናፍስት ናቸው፡፡ በተለይ ከውስጥ ሳይሆን ከውጭ ሆኖ በሰው ላይ እያደረ በሥራችን፣ በዕድላችን ወዘተ የሚፈትነን ጠላት አደገኛ ነው፡፡ ምክንያቱም በሰው እያደረ ስለሚፈትነን፣ ዕድላችንን ስለሚዘጋ፣ ሕይወታችንን ስለሚያበላሽ