uz
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Kanalga Telegram’da o‘tish

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Ko'proq ko'rsatish
2 280
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+77 kunlar
+3930 kunlar
Postlar arxiv
በሕክምና ዲዳና ኦቲስትክ የተባለው ሕጻን ፡ ከ5 ዓመታት በኋላ አንደበቱ ተፈታ ደስታችንን በዲያብሎስ ተነጥቀናል የልጆቻችን የመናፍስቱ ፈተና 💥😭🚩😱🔥 https://youtu.be/z91kc9h7Ikg?si=iFo2OmM_rQhi4i4G

በሞት ዙሪያ የሚታዩ ሕልሞችና ትርጉማቸው || መፍትሔዎቹስ ምንድናቸው? || ሰው እንዴት ሕልም ያያል? | እውነተኛ ሕልም ለማየት #ethiopia #ebs 🚩💥😱 https://youtu.be/NT8OA8Oth0A

«መንፈሳዊው ገበሬ» ◈ “አንድ ገበሬ ዘር መዝራት ስላለበት ብቻ እንዲሁ አይዘራም፤ አስቀድሞ መሬቱን ማረስ፣ ማለስለስ አለበት፤ ካረሰ ካለሰለሰ በኋላ ዘሩን ይዘራዋል አሁንም ግን መዝራቱ ብቻ በቂ አይደለም፤ የዘራውን ዘር አፈር ሊያለብሰው ይገባዋል፤ እንዲያ ካላደረገ ወፎች መጥተው ይለቅሙታልና፡፡ እንደዚሁ እኛ ክርስቲያኖችም በእኛ ላይ የተዘራውን ዘር (ቃለ እግዚአብሔር) በየጊዜው እንደ ገበሬው የማንከታተለው ከሆነ በአየር ላይ እንደተዘራ ዘር ይሆንብናል፤ ሰይጣን ይለቅምብናል፤ የራሳችን ስንፍና እንዲጠወልግ ያደርጓል፤ ፀሐይ ያደርቋል፤ ጐርፍ ይወስዷል፤ እሾክ አንቆ ይይዟል፡፡ ◈ ዘር ዘርቶ ዞር ማለትን አያስፈልግም ማለት ነው፤ በየጊዜው መኮትኮት፣ ወፎችን ማባረር፣ የበቀለ አረም ካለ ማረም፣ ጭንጫ የበዛበት አከባቢ ካለ የለሰለሰ አፈር መጨመር፣ በየጊዜው መከታተል፣ አጥር ማጠር፣ እንዲሁም ማንኛውም የተዘራውን እህል ሊያበላሹ የሚችሉ ነገሮችን ማስወገድ ያስፈልጋል፤ ምናልባት በሰብሉ እርሻ የገበሬው ትጋት ብቻ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፤ ምክንያቱም መሬቱ ግዑዝ ነገር ስለሆነ፡፡ በመንፈሳዊው እርሻ ግን እንዲህ አይደለም፤ ኃላፊነቱ የገበሬው ማለትም የመምህሩ ብቻ አይደለም፤ ከግማሽ ወይም ከዚያ በላይ የደቀመዝሙሩ (የምእመኑ) ኃላፊነት ነው፤ በርግጥ መምህሩ ዘሩን መዝራት አለበት ነገር ግን ደቀ መዝሙሩ የተነገረውን ቃል ሁል ጊዜ መስማት ብቻ ሳይሆን ማድረግም አለበት፤ በግብር ፍሬ ማፍራት አለበት፤ የበቀሉ አረሞች ካሉ በየጊዜው መንቀል አለበት፡፡ ◈ የገበሬ ልጆች በሰብሉ መካከል የበቀለ አረም ካለ እንዲሁ ጫፍ ጫፉን ብቻ አይቆርጡትም፤ ከሥር ይነቅሉትና በመጨረሻም በእሳት ያቃጥሉታል እንጂ በእኛ ላይ የበቀሉ አረሞችም (ጥርጥሮች፣ ክሕደቶች፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ማነቆ የሆኑብንን ነገሮች…) ከሥራቸው ነቅለን ልናቃጥላቸው ይገባናል።” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ያሳዝናል! ተጋብተው በአንድ አልጋ ተኝተው ፡ ለአራት ዓመታት ግንኙነት የማያደርጉት ባለትዳሮች | በመጠመቅ ብቻ አጋንንት አይለቅም! የሰይጣን ማምለኪያ 😱🚩💥😭 https://youtu.be/f03Z-tFEFRs?si=wG6fGxR_FQwrExqN

3ቱ ወሳኝ የጸሎት አይነቶች እጅ በማስጫን የሚገቡ አጋንንቶች የፓስተሮች ልሳንና መልክአ ሳጥናኤል || ሰባቱ የጸሎት ሰዓታት #ebs #ጸሎት 💥🚩🔥😱 https://youtu.be/E3mdfx31K3w

"በውድቀታችን ተስፋ ባለመቁረጥ ራሳችንን እናንሳ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው ኃጢአተኞችን ለማዳን ነው። ስለሆነም ልንከተለው ፈቃደኛ ከሆንን ለመዳን መንገድ አለን።" (ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ) "ፍርድ ከሌለ እግዚአብሔር ፋታሔ አይደለም። ፈታሔ ካልሆነም በጥቅሉ እግዚአብሔር የለም። እግዚአብሔርም ከሌለ ሁሉ ነገር ውጥንቅጥ ይሆናል። ምግባርም ምንምና ምንም ይሆናል።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) "ክርስቶስ እንድንዋደድ ሲያዘን ይህን የምናደርግበትንም አቅም ሰጥቶን ነው። እኛ ፍቃደኞች ከሆንን ትዕዛዙን መፈጸም ይቻለናል።" (አባ አርሳኒ) "ክርስቲያን ክርስቶስ የሚያስብበት አእምሮ ነው፤ ክርስቶስ የሚያፈቅርበት ልብ ነው፤ ክርስቶስ የሚናገርበት ድምጽ ነው፤ እንዲሁም ክርስቶስ የሚረዳበት እጅ ነው።" (ቅዱስ አውግስጢኖስ) "ሕይወታችን ሆነ ሞታችን ከወንድማችን ጋር ነው። ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን አግኝተነዋል። ወንድማችንን ከነቀፍነውና ካሳዘነው ግን ክርስቶስን በድለናል። ለአንተ ጠቃሚ የሆነ ወንድምህን ሊጎዳ የሚችል ምንም ነገር አታድርግ።" (ቅዱስ እንጦንስ) "አምላኬ ሆይ ልቤ እንደ ጠባብ ቤት አንተን ለማስገባት የማይችል በጣም ትንሽ ነው አንተ ሰፊ እንድታደርገው እለምንሃለሁ። በልቤ ቤት ውስጥ ስታያቸው ደስ የሚያሰኙህ ነገሮች እንዳሉ አውቃለሁና አልደብቃቸውም። ከአንተ በቀር የውስጤን ቆሻሻ ሊያስወግድ የሚችል ምንም እንደ ሌለ አውቃለሁና።" (ቅዱስ አውግስጢኖስ) "በፍቅር የሚኖር ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ የሕይወትን ፍሬ ያፈራል። በዚህ ዓለም ሲኖር ደግሞ የትንሳኤውን አየር ይተነፍሳል።" (ማር ይስሐቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በእውነት በጣም ያሳዝናል!! ውርጃ መፈጸም ይፈቀድልን!! መምህር ግርማ ጠንቋይ አይደሉም! የሴቶችጥፍርና አጋንንታዊ ሴራው | መምህር ግርማ ተስፋዬ አበራ 💥🚩 https://youtu.be/s1NKGjE-Gx0

“የትዕቢት መጀመሪያ ሰውን ከእግዚአብሔር ትለየዋለች” (ሲራክ 10፥2) ◈ ሳጥናኤል ከቀደመ ክብሩ ተዋርዶ ዲያብሎስ የኾነው “ይኽ ሕዝብ ፈጣሪውን አጥቶ ተጨንቋል፤ እኔ ፈጠርኳችሁ በማለትም ፈጣሪነትን በእጄ ልያዝ” ብሎ በታበየ ጊዜ ነው፤ ዲያብሎስ ዲያብሎስ የኾነ አስቀድሞ ዲያብሎስ ኾኖ ስለተፈጠረ አይደለም፡፡ በትዕቢት ከመውደቁ በፊት የዐሥሩ ነገደ መላዕክት የአጋዕዝት አለቃ ንዑድ ክቡር መልዐክ ነበርና፤ ከዚኽ ክብሩና ሹመቱ ያዋረደው ትዕቢቱ ነው፤ እሳቱ ወደማይጠፋ ትሉ ወደማያንቀላፋ እሳት የጣለው ትዕቢቱ ነው፤ ወደ ዘለዓለማዊ ሐሳር የጣለው ትዕቢቱ ነው፡፡ ◈ ተወዳጆች ሆይ! ትዕቢት የነበረንን መልካም ምግባር ሁሉ የሚየሳምም ደግሞም የሚገድል ክፉ ደዌ ነው፤ ወንጌላዊው “በሰው ዘንድ የከበረው በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የተዋረደ ነው” እንዲል ውስጣችን በትዕቢት የተሞላ ከኾነ በአፍአ ብንመጸውትም፣ ብንጸልይም ምጽዋታችን ወይም ጸሎታችን በእግዚአብሔር ዘንድ ርኵስ መሥዋዕት ነው፡፡ (ሉቃ 16፥15) ◈ ትዕቢት ካለብን ውስጣችን ንጽሕና የለውም፤ ስለዚኽ ሰው ንጽሕናውን እንዲያጣ የሚያደርገው ዝሙት ወይም ማመንዘር ብቻ አይደለም ማለት ነው፤ ትዕቢት ጭምር እንጂ፤ እንደውም ትዕቢት ከዝሙት ወይም ከማመንዘር በላይ እኛን ያቆሽሻል፤ ለምን? ምንም እንኳን ዝሙት ንስሐ ካልገቡበት ሥርየተ ኀጢአት የሌለው በደል ቢኾንም በዝሙት የቆሸሸ ሰው ንስሐ ለመግባት ቅርብ ነው፤ በትዕቢት የታመመ ሰው ግን እንዲኽ እንደ ዘማዊው ያለ ዓቅምን አያገኝም፤ ስለዚኽ ትዕቢት እጅግ አደገኛ ደዌ ዘነፍስ ነው ማለት ነው፡፡ ◈ ከትዕቢተኛ ሰው በላይ ጐስቋላ ሰው የለም፤ የፈለገ ያኽም ብዕል (ሃብት)፣ የዚህን ዓለም ዕውቀት ቢኖረውም ከትዕቢተኛ ሰው የባሰ ጐስቋላ ሰው የለም፤ በንግሥና ወንበር ቢቀመጥ፣ በሰዎች ዘንድ እጅግ “የተከበረ” ቢኾንም ከዚኽ ሰው በላይ ጐስቋላ ሰው የለም ብዬ በእውነት እነግራችኋለኁ፤ እስኪ ንገሩኝ! የዚኽን ከንቱ ደግሞም ኀላፊና ጠፊ ዓለምን ነገር ይዞ ከመታበይ በላይ ምን አላዋቂነት አለ? ◈ ነገ የሚጠወልገውን የመስከረም አደይ አበባን (የዚኽን ዓለም ክብር) ይዞ ከሚታበይ ሰው በላይ ማን ነው ጐስቋላ? ሕልምን ይዞ እውኑን ዓለም ከሚያጣ ከዚኽ ትዕቢተኛ ሰው በላይ ማን ጐስቋላ ሰው አለ ልትሉኝ ትችላላችሁ ? አኹን በወርቅ አልጋ ላይ ስለተኛ ከሚታበይ ሰው በላይ ማን ድኻ አለ ልትሉኝ ትችላላችኁ? (ከቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ስንት ይሁዳ እያለላችሁ እኔን ለምን በየዓመቱ ትወግራላችሁ? በምናብ የሳልኩት የይሁዳ የሲኦል ብሶት ይሁዳ ለምን ክርስቶስን ሸጠ? #ebs #ንቁ 🚩😱💥 https://youtu.be/Sn99kjg4qMM?si=FsjK634TOE-zYkay

በመምህር ተስፋዬ ቪዲዮ በኮሜንቶች እንማማር ክፍል 1 (ፈተና ገጠመኝ 235ኛ) | የደንቃራ መተትና ፈተናዎቹ | የደንቃራ መተት ምንድነው? #ebs ገጠመኝ 😱🚩 https://youtu.be/o1NnYAejfFo

ፀጉር የሚነቃቅለው እና ፊት የሚያበላሸው የቡዳ መንፈስ? https://youtu.be/ImN4gCV6vu4

የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ይገርማል በእውነች! አባታችን እግዚአብሔር ረጅም እድሜን ያድልልን በእውነት! https://youtu.be/QDCkcWcY5sA?si=NwoiOixbjIWI7xJw

4ቱ የርኩሳን መናፍስት አያያዝ መንገዶች ጤናን የማይነኩ አጋንንቶች እሳት የጨበጡ እጆች || ዳንሰኛውን አጫሹን ማን ይመልሰው? #ebs #live 💥🔥 https://youtu.be/K5uZI-o7sw8

"እግዚአብሔር ሆይ አትተወኝ! ከፊትህ መልካም የሆነ ምንም ምግባር የለኝም፤ ነገር ግን ስለቸርነትህ ስትል መልካሙን ነገር እንዴት እንደምጀምር ግለጥልኝ።" (አባ አርሳንዮስ) "እመቤቴ ድንግል ማሪያምን "እንደ እኔ ሰው እኮ ናት" ብለኽ ክብሯን ለማሳነስ ትሞክራለህ? ወዳጄ እውነት አንተ እንደ እርስዋ ነህ? ብርሃናዊ መልአክ ከፍትህ ቆሞ አመስግኖህ ያውቃል? እንኳንስ ከሰማይ የተላከ እንግዳ መልአክን ቀርቶ አብሮህ ያለውን መልአክህንስ አይተኸው ታውቃለህ? እንደ ድንግልቱ የመላእክትን ዝማሬ ከሆድህ ሰምተሃል? እግዚአብሔር እንኳንስ በአንተ ሊያድር በሕልም እንኳን አነጋግሮህ ያውቃል? እውነቱን ንገረኝ ካልከኝ እንኳን ሊወለድብህ በቃል ሊያነጋግርህም አልመረጠህም።" (ከብርሃን እናት መጽሐፍ) "የተወደድክ ወንድሜ ሆይ! በጣም አዝንልሃለው ምክንያቱም የተወሰነ የጽድቅ ሥራ ከሠራህ በኋላ አንተው ራስህ ትገልጠዋለህ። ሰይጣንም የሰራኸውን ትንሽ ጽድቅ ወዲያውኑ ይወስድብሃል። እነሆ ልፋትህ ሁሉ በከንቱ ውዳሴ ፍለጋ ምክንያት ባከነ፤ ከአንተም ራቀ።" (ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ለአጋንንት ግብር ውርጃ የሚፈጽሙ ዶክተሮች | ከመምህር ተስፋዬ Live የተወሰደ አስተማሪ ቪዲዮ | የአዳልሞቴና የደም ግብር የለመዱ መናፍስቶች https://youtu.be/y6Qayz2ZWjs

#በሳልትበርን_ከተማ_ቅዳሜ_እና_እሑድ_አገልግሎት_አለን! በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም #Share ይደረግ! ተወዳጆች ሆይ በእንግሊዝ ለአንድ ወር ከሃያ ሦስት ቀን አገልግሎት ስሰጥ ቆይቼ በመሃል የምወ
+1
#በሳልትበርን_ከተማ_ቅዳሜ_እና_እሑድ_አገልግሎት_አለን! በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም #Share ይደረግ! ተወዳጆች ሆይ በእንግሊዝ ለአንድ ወር ከሃያ ሦስት ቀን አገልግሎት ስሰጥ ቆይቼ በመሃል የምወዳቸው የፈጠሩኝን የአብርሃሙን ቅድስት ሥላሴን ሐምሌ 7 ለመዘከር ወደ ሀገሬ ኢትዮጲያ ሄጄ በሜቄዶንያ አረጋውያንን እና የአእምሮ ሕሙማን ከወዳጆቼ ጋር ዘክረን በድጋሚ ወደ እንግሊዝ ተመልሻለሁ። አንዳንድ የአገልግሎቱ ተቃዋሚዎች ወደ ኢትዮጲያ ስሄድ ዳግም ወደ እንግሊዝ ለአገልግሎት መመለስ እንደማልችል አድርገው ሲያስቡ ነበር። ደግነቱ ሀገሩ፣ የሀገሩ ሕግ ለእኔም ለእነሱም አንድ ነው። ስለዚህ የፊታችን ቅዳሜና እሑድ July 20 እና July 21 በሳልትበርን ከተማ ሰፊ አገልግሎት ይኖረናል። ስለ አገልግሎቱ ሰፊ መረጃ ለማግኘት በዚህ ሊንክ ዩትዩብ ላይ ገብታችሁ ማየት እና ማግኘት ትችላላችሁ። በእንግሊዝ አገልግሎቱ ይቀጥላል። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ከሰው ጋራ እንዴት እንኑር» ◈ ይህ ዓለም የፈረስ የበሰበሰ የከፋ የከረፋ በድን ነው፤ ይህን ዓለም የሚፈልገውም ውሻ ነው፤ ክፉ ዘመን በመጣብህ ጊዜ  ከሰው ተልይተህ ራቅ የበቃ መነኩሴ ነው እንዳይሉህ እገሌ ጻቅድ ነው እገሌ ባልንጀራዬ ነው እገሌ ክፉ ነው አትበል ለሰው መልካምነት  የለውምና። የሰውንም ልቡን የሚያውቅ የለምና ሰው ከሚቀርብህ ጊንጦች ቢቀርቡህ ይሻልሃል፤ የፈራ ድኗል የታበየ አዝኗል የተራራ ፈሳሾች በምንጭ ያልቃሉ የሰው ሕይወቱም በዕለታት ያልቃል ትድን ዘንድ እውነትን ተናገር ክፉ እንያዳያገኝህ ሐሰትን አትናገር ዳግመኛም እንዲህ ተብሎ ተነግሯል እንደ ከርቤ እስክትመርር ድረስ እውነትን ተናገር የፈጣሪህን እንጂ የሰው ፊት አትመልከት። ◈ ሰው ሆይ ትግስትን አዘውትረህ ታገስ ትግስት አስቀድሞ ይመረሃል ፍጻሜው ግን ከማር ይልቅ ይጣፍጥሃልና፤ ጠቢብ እንዲህ አለ ልጄ ሆይ  ትምህርቴን ስማ ምክሬን ያዝ ሁል ጊዜ ንጹሕ ቅዱስ የሚሆን የፈጣሪህን ፊት ፈልግ። ትምህርቴ ፍሬን የተሞላ ነውና ከእርሱ መልካም ፍሬን ልቀም ጉንዱንም ከነቅርጫፎቹ ቁርጥ በእሳትም አቃጥለው ተብሎ እንደተነገረ፤ ጠቢብ እንዲህ አለ ብዙ ምግባራትን ታገኝ ዘንድ ትምህርትን ሁሉ ጠብቅ በአንድ ትምህርት ብቻ አትኑር፤ በአንድ ትምህርት ብቻ የሚኖር እርሱ ሰነፍ ነውና። ◈ እስኪ ወደ ንብ ተመልከት እንዴት በየዕፅዋቱ አበባ እንደሚቀስም እንዴት መዓዛዎቹን  እንዲሚሰበስብ አስተውል  እነዚህን ስብስቦ ነገሮችን አዘጋጀ እነዚህም ማርና ሰም ናቸው፤ ሰሙ የሚያበራ መብራት ሆነ ወልላውም ለሰው ደስታ ሆነ ጠቢብ እንዲህ አለ ለወፍ ጸጉሩ  ለሰይፍ ሰገባው ለንጉስ ሠራሚቱ ጌጡ ክብሩ እንደሆነ ለሰው ጌጡና ሽልማቱ ሰው ነው። ከጠላትህ አንድ ጊዜ ከወዳጅህ መቶ ጊዜ ተጠብቅ፤ ወዳጅህ ምሥጢርህን ያውጣል ጠላትህ ግን ምሥጢርህን አያውቅምንና። ለአባታችን ለአባ ገብረ ኪዳን ቃለ ህይውት ያሰማልን ጸጋውን በረከቱን ያድልልን በእድሜ በጤና ያቆይልን። "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" ምሳ 1፥33 መጋቢ ብሉይ ወሐዲስ መምህር አባ ገብረ ኪዳን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239