HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 280
Obunachilar
-124 soatlar
+107 kunlar
+3530 kunlar
Postlar arxiv
«ልብስህን ማን ወሰደው»
◈ በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ በሄደ ጊዜ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፤ ለራሱም "ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ 'ታርዤ አልብሳችሁኛልና' ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ እየተሰቃየ እንዴት አልፌው እሄዳለኹ?" ብሎ ፈጥኖ ልብሱን በማውለቅ ይለብሰው ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡
◈ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደ ያዘ እርቃኑን በጎዳናው ዳር ተቀመጠ፤ እርሱን የሚያውቀው አንድ የከተማው ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፤ ቅዱሱም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፤ ያም ባለጠጋ አዲስ ልብስ ገዝቶ አለበሰው።
◈ ከዚህም በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ሲሄድ ዕዳውን መክፈል ባለመቻሉ እያንገላቱ ወደ ወኅኒ ቤት የሚወስዱትን አንድ ምስኪን ሰው ተመለከተ፤ እርሱም የያዘውን መጽሐፍ ቅዱስ ፈጥኖ በመሸጥ የዚያን ሰው ዕዳ ከፍሎ ነጻ አደረገው፤ ይህንንም አድርጎ ጉዞውን ሲጀምር እንደ ገና ሌላ የታረዘ ነዳይ ሲለምን ተመለከተ።
◈ አባ ሰራብዮንም እንደ ቀድሞው የለበሰውን ልብስ አውልቆ ለነዳዩ በመስጠት እርሱ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፤ ደቀ መዛሙርቱም መምህራቸውን እርቃኑን ባዩት ጊዜ ደንግጠው ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፤ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡
◈ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የምታጽናናበት መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን?› ሲሉ ደግመው ጠየቁት፤ አባ ሰራብዮንም ‹በእጄ የነበረው መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ ያለኝ እርሱ ነበር እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡
◈ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው "ምጽዋት የፊት መብራት ናት፤ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፤ ጾም፣ ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፤ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፤ የምጽዋትን ታላቅነት ልንረዳ ይገባል፤ ዓለም ሁሉ ከወደቀበት የሕግ እርግማን የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና።"
ለሌሎች ሼር በማድረግ እንድታደርሱ በፍቅር እጠይቃለሁ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
አልወጣም፣ አለቅም የምሉ ክፉ መንፈሶች ከንስሐ በኋላ ዳግም ጸጸት የብዙዎች ፈተና የምንጠፋው በእሳት ነው || በቆረብን ቀን በዝንየት መመታት 💥😱🙏🚩
https://youtu.be/jeSPYysWavg?si=2AZgsti7-km_qHFJ
«ንጹሕ ሆነን የረከሰ ምራቅን አለመጠየፍ እንዴት ይቻለናል? ያለ በደል የሚደረግ ውንጀላ እና ግፍንስ "በቃ" አለማለት እንዴት ይሆናልናል? ያለ ጥፋት የሚመጣብንን ምን ያህል ጥፊዎች እንታገሳለን? ስንት ጅራፎችንስ እንቀበላለን? ስንት ውርደቶችንስ እንሸከማለን? መድኃኔዓለም ይህን ሁሉ ነገር የተቀበለው ስለ እኛ መዳን ነው። እኔ ግን ስለ ራሴ መዳን በጀርባህ ላይ ካረፉት ጅራፎች የአንዲቱን ሰንበር ያህል እንኳን መከራ ለመቀበል ትዕግስቱ የለኝም።»
"ተሰሃለኒ እግዚኦ በከመ ዕበየ ሳህልከ" - "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ" መዝ 50፥1
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"...ለመሰንበት ስንል መመገባችን ያለመሰልቸትና ድካም እንደሆነ ሁሉ ጽሎታችን፤ ምስጋናችን፤ ክርስትናችንም እንዲሁ ወቅታዊ ብቻ ያልሆነ በማጣትም በማግኘትም ወቅት ጸሎታችን አይቋረጥ ምስጋችንም ይቀጥል ለመደሰት ምክንያት የሚፈልጉ ከሆነ ክብር ይግባውና የድንግል ልጅ አለልዎ። በቁስና ምድራዊ ምኞት የደስታ ሀገሩ ሩቅ፤ የማይደረስበት ሲቀርቡት የሚርቅ ነው! ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን።"
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
እባካችሁ አጋንንት የምስቡ ልብሶችን አቁሙ! || ከአባት ወደ ልጅ የሚዋረሱ መንፈሶች || የልብ ደስታ አላችሁን? || ጸሎት ስንጀምር ፈተና ይበዛል #ንቁ 😱💥 https://youtu.be/OPULo1rYQEw
"መንፈሳዊ ጸሎት ለማድረግ ራሳችንን ማስገደድ አለብን። ለእግዚአብሔር ፍቅር የማይከፈት ልብ ቢኖረን እንኳን ለጸሎት የምናደርገውን ጥረት ተመልክቶ እውነተኛውን የመንፈስ ጸሎት ይሰጠናል።" (አባ መቃርዮስ)
"ያለፈውን አሳፋሪ ተግባሬን እና የነፍሴን ሥጋዊ ርኩሰት ማስታወስ እፈልጋለሁ አቤቱ ፈጣሪዬ ትዝታው ስለሚናፍቀኝ አይደለም፤ አንተን ማፍቀር እችል ዘንድ ነው።" (ቅዱስ አውግስጢኖስ)
"በጠላቶችህ እጅ እንዳትወድቅ ወደ አቆምካቸው ኃጢአቶችም እንዳትመለስ በሌሎች ላይ አትፍረድ። ምንም እንኳን ምክንያት ቢኖርህም ማንንም አትንቀፍ፤ ህጉን ለመፈጸም አቅቶት ወንድምህን ብታየው እንኳን አትማው ስሙንም አታጥፋ።" (ቅዱስ እንጦንስ)
"እነዚህን ሁለት አሳቦች እወቁና ፍሯቸው። አንዱ አንተ #ቅዱስ ነህ የሚል ሲሆን ሌላኛው ደግሞ #አትድንም የሚል ነው። እነዚህ ሁለቱም አሳቦች የጠላት ናቸው። በውስጣቸውም እውነት የለም። ነገር ግን እንዲህ ብላችሁ አስቡ እኔ ታላቅ #ኃጢአተኛ ነኝ ጌታ ግን መሐሪ ነው፤ እርሱ ሰዎችን በጣም ይወዳል፤ እናም ኃጢአቶቼን ይቅር ይላል።" (ቅዱስ ሲሎአን)
"እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ኤልሳቤጥን ልትጎበኛት በሄደች ጊዜ ክርስቶስን በማህጸኗ ተሸክማ ነበር የሄደችው። እኛም በተለያዬ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ወዳጆቻችንን ለመጎብኘት ስንሄድ ቂምን፣ ቅናትን፣ ሀሜትን ተሸክመን ሳይሆን ክርስቶስን ተሸክመን ልንሄድ ያስፈልጋል።"
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
Repost from HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
✨ ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ✨
✨ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ✨
#ሰኔ_12
✨ የከበረች አፎምያ ያረፈችበት ዕለት ነው፤ እግዚአብሔርን የሚፈራ የአንድ ሰው ሚስት ነበረች። ባሏ ብዙ ምጽዋትን ያደርግ ነበር በየወሩም ሦሶቱን በዓላት ያደርግ ነበር፤ እነዚህም፦
* በ29 /የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት መታሰቢያ/
* በ21 /የቅድስት ድንግ ማርያምን/
* በ12 /የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤልን/
✨ የሚሞትበት ቀን በደረሰም ጊዜ እርሱ ያደርገው የነበረውን ምጽዋት እንዳታስታጉል እነዚህንም 3 በዓላት እንድታከብር አዘዛት። ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አስሎ ይሰጣት ዘንድ ባሏን ለመነችው። እርሱም አደረገላት እርሱም ካረፈ በኋላ ያደርገው የነበረውን እያደረገች በቅድስና ሕይወት ጸንታ ትኖር ጀመር። ጸላዔ ሠናይ የሆነ ሰይጣን ስለቀናባት ይፈትናት ዘንድ መነኩሲት ተመስሎ፤ ባልሽ በስጋ ተለይቶሻል ከእንግዲህ ምጽዋትን አታድርጊ፣ ሌላ ባል አግብተሽ በደስታ ኑሪ እያለ ክፉ ምክርን ይመክራት ጀመር።
✨ እርሷም ሌላ ላላገባ ለእግወዚአብሔር ምያለው፤ ርግቦችም እንኳን ከአንድ በቀር ሌላ አያውቁም፤ አለችው ምክሩንም እነዳልተቀላት ባወቀ ጊዜ መልኩን ለውጦ ጮኸባት በሌላም ቀን እመጣለው ብሏት ጥሏት ሄደ። በሰኔ 12 ቀንም የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ስታከበር ሰይጣን አንደለመደው ይፈትናት ዘንድ መልአክ ተመስሎ ወደርሷ መጣ። የቀደመ ክፉ ምክሩን ከመጻህፍት እየጠቀሰ ያስታት ዘንድ ይነግራት ጀመር። የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክስ የያዝከው በትረ መስቀልህ ወዴት አለችው።
✨ ሥዕለ ቅዱስ ሚካኤልን አምጥታ ብታሳየው፤ ወደ ከበረ ሚካኤል ብትለምን ፈጥኖ ደርሶ አዳናት። ዲያብሎስንም ከእርሷ አሳደደው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ቅድስት አፎምያን አንቺ በዚህች ቀን ከዚህ ዓለም ወደማያልፈው ዓለም በምት ትለያለሽና ሄደሽ ስራሽን አከናውኚ። እነሆ እግዚአብሔር ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን አዘጋጅቶልሻልና አላት ሰላምታም ሰጥቷት ወደ ሰማይ ዓረገ።
✨ የበዓሉንም ሥርዓት በሚገባ ፈጸመች። ኤጲስ ቆጶሱን ካህናቱን ወደ ጠራች እነርሱም መጡ። ገንዘቧን ሁሉ ለዳያን መጸወተች ከዚህም በኋላ ቆማ ጸለየች፤ የከበረ መልአክ የሚካኤልን ሥዕል ከፊቷ አደረገች በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ በሰኔ 12 ቀንም አረፈች።
አፎምያን ከመከራ ከመከራ ነፍስ የታደጋት፤ የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አይለየን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"መታሰርን አልፈራም፤ ግን በአባቶች በጣም አዝኛለሁ" || ከኃጢአት ለመራቅ ይሄንን አድርጉ || በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ #ethiopia #ንቁ 🔥💥😱😭 https://youtu.be/RqI0gx8ZoyI
"ከጸሎት በፍት መንፈሳዊ መጻህፍትን ማንበብ በጣም ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም ነፍስ ስለምትሞቅና አእምሮም ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስለሚሸጋገር ነው።" (ቅዱስ ፓይሲዮስ)
"የዓለምን ደስታ መውደድ ስሜታዊ ወደ መሆን ይወስዳል፤ ይህም የኃጢአት ሁሉ መራቢያ ነው። ስሜታዊ የሆነ ሰው በአሳቡ የመጣለትን ኃጢአት የመፈጸም እድሉ ከፍተኛ ነው።" (ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ)
"ፈተናዎች በደረሱብን ጊዜ እግዚአብሔር እኛን ለመተው እና ለመናቁ እንደ ምልክት አድርገን አናስበው። ነገር ግን ይህ እግዚአብሔር ለእኛ እንደሚያስብ ምልክት ይሁነን፤ ምክንያቱም ፈተናዎች ወደ እኛ እንዲመጡ በመፍቀድ ከኃጢአታችን ያነጻናልና።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
"በሙሉ ሰዓታችሁ ለማምለክ ያልፈለጋችሁትን እግዚአብሔር እንዴት በሙሉ ሰዓታችሁ እንዲከተላችሁ ትፈልጋላችሁ።" (ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ)
"እመኑኝ እንደ እግዚአብሔር ትእዛዛት የሚኖር በችግር ወይም በህመም ጊዜ እንኳን ደስ ይለዋል። ሁልጊዜም እግዚአብሔር እንደሚረዳው እና እንደማይተወው ይሰማዋል።" (እናት ሄራኒ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«የአባቶቻችን ድንቅ ንግግሮች!»
"ክርስትና ሰዎችን በተወሰኑ ሀሳቦች ማሳመን አይደለም። ይልቁንም ከክርስቶስ ፍቅርና ታላቅነት ይካፈሉ ዘንድ መጋበዝ ነው። ሰዎችን በጥዑም ንግግር ለመማረክ ብላችሁ ወጥመድ ውስጥ እንዳትወድቁ ጸልዩ። በትህትናም መናገርን ልመዱ ሰዎችንም በራሱ በክርስቶስ መማረክ ይገባችኋል።" (ቅዱስ አግናጥዮስ ዘ አንጺኪያ)
"እያንዳንዱ ሰው ስለ ሕይወቱ እንደገና እንዲያስብና ስህተቱንም እንዲያርም ጊዜ አለው። ይህንንም ማድረግ ይገባዋል።" (አባ አርሴኒ)
"ቁጣ አዋቂን ባሪያ ያደርጋል፡ ወንድምህንም በክፉ መንፈስ እንድታየው ያደርግሃል፤ ከተሸነፍክለት ልቦናን በማይ'ገሩ የሥጋዊ ፍላጎቶች ሰንሰለት አስሮ ለክፉ መንፈስ ይዳርግሃል።" (ቅዱስ ማርቆስ ዘ አስቄጥስ)
"የማይጠፋው ከክርስቶስ ጋር ያለህ ጊዜ ብቻ ነው። ሌላ ምንም ነገር ብታደርግ እዚህ ይቀራል፤ ከመቃብር በለይ የሚቆም አንዳችም ነገር የለም።" (አባ ዲሜጥሮስ ፓናጎፓሎስ)
"ከኢየሱስ ክርስቶስ እርዳታ ትጠይቃላችሁ? ወይስ ለብቻችሁ እየታገላችሁ ነው? ለክርስቶስ ድክመታችሁን ንገሩ ራሳችሁን ዝቅ አድርጉና እርሱን ጠይቁ። በጥረቴ ውስጥ ችግሮች አሉብኝና እርዳኝ በሉት አንድ ሰው ትሑት ሆኖ ከክርስቶስ እርዳታ ሲጠይቅ እርሱ ይረዳዋል።" (አባ ፓሲዮስ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
✨ ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ✨
✨ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ✨
#ሰኔ_12
✨ የከበረች አፎምያ ያረፈችበት ዕለት ነው፤ እግዚአብሔርን የሚፈራ የአንድ ሰው ሚስት ነበረች። ባሏ ብዙ ምጽዋትን ያደርግ ነበር በየወሩም ሦሶቱን በዓላት ያደርግ ነበር፤ እነዚህም፦
* በ29 /የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት መታሰቢያ/
* በ21 /የቅድስት ድንግ ማርያምን/
* በ12 /የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤልን/
✨ የሚሞትበት ቀን በደረሰም ጊዜ እርሱ ያደርገው የነበረውን ምጽዋት እንዳታስታጉል እነዚህንም 3 በዓላት እንድታከብር አዘዛት። ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አስሎ ይሰጣት ዘንድ ባሏን ለመነችው። እርሱም አደረገላት እርሱም ካረፈ በኋላ ያደርገው የነበረውን እያደረገች በቅድስና ሕይወት ጸንታ ትኖር ጀመር። ጸላዔ ሠናይ የሆነ ሰይጣን ስለቀናባት ይፈትናት ዘንድ መነኩሲት ተመስሎ፤ ባልሽ በስጋ ተለይቶሻል ከእንግዲህ ምጽዋትን አታድርጊ፣ ሌላ ባል አግብተሽ በደስታ ኑሪ እያለ ክፉ ምክርን ይመክራት ጀመር።
✨ እርሷም ሌላ ላላገባ ለእግወዚአብሔር ምያለው፤ ርግቦችም እንኳን ከአንድ በቀር ሌላ አያውቁም፤ አለችው ምክሩንም እነዳልተቀላት ባወቀ ጊዜ መልኩን ለውጦ ጮኸባት በሌላም ቀን እመጣለው ብሏት ጥሏት ሄደ። በሰኔ 12 ቀንም የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ስታከበር ሰይጣን አንደለመደው ይፈትናት ዘንድ መልአክ ተመስሎ ወደርሷ መጣ። የቀደመ ክፉ ምክሩን ከመጻህፍት እየጠቀሰ ያስታት ዘንድ ይነግራት ጀመር። የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክስ የያዝከው በትረ መስቀልህ ወዴት አለችው።
✨ ሥዕለ ቅዱስ ሚካኤልን አምጥታ ብታሳየው፤ ወደ ከበረ ሚካኤል ብትለምን ፈጥኖ ደርሶ አዳናት። ዲያብሎስንም ከእርሷ አሳደደው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ቅድስት አፎምያን አንቺ በዚህች ቀን ከዚህ ዓለም ወደማያልፈው ዓለም በምት ትለያለሽና ሄደሽ ስራሽን አከናውኚ። እነሆ እግዚአብሔር ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን አዘጋጅቶልሻልና አላት ሰላምታም ሰጥቷት ወደ ሰማይ ዓረገ።
✨ የበዓሉንም ሥርዓት በሚገባ ፈጸመች። ኤጲስ ቆጶሱን ካህናቱን ወደ ጠራች እነርሱም መጡ። ገንዘቧን ሁሉ ለዳያን መጸወተች ከዚህም በኋላ ቆማ ጸለየች፤ የከበረ መልአክ የሚካኤልን ሥዕል ከፊቷ አደረገች በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ በሰኔ 12 ቀንም አረፈች።
አፎምያን ከመከራ ከመከራ ነፍስ የታደጋት፤ የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አይለየን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
◈ ባልታጠቡ ጋኖች ላይ ወይኑ አይሞላም፡፡ ከክፋት ባልጸዳ ልብ ላይ ሰማያዊ ጥበብ አይኖርም፡፡ ከምቀኝት ባልወጣ አስተሳሰብ ላይ ብልጽግና አይመጣም፡፡ ከተንኮል ባልተለየ እቅድ ላይ ስኬት አይኖርም፡፡ ንስሐ ባልገባ ክርስትና ላይ የአምላክ ንጹሕ ሥራዎች አይጸኑም፥ ኃጢአት እያጎመዘዘ ያናውጣቸዋልና፡፡
◈ የአዲሱ አቁማዳ ባሕሪይ አዲሱን የወይን ጠጅ ይቀበላል፡፡ አዲሱም የወይን ጠጅ አዲሱ አቁማዳ ይስማማዋል፡፡ ሁለቱ እርስ በእርስ ይጠባበቃሉ፡፡ ንስሐ የገባ ሕይወትና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ በእርግጥም እርስ በእርሳቸው ይጠባበቃሉ፡፡ ሕግ በሰው ትከበራለች፥ ሰውየውም በሕጊቱ ይከብራል፡፡ ወንጌል በምዕመን ትገለጻለች፥ ምዕመንም በወንጌል ይገለጻል፡፡
◈ ስለዚህ ጠላት ልክ ነዋ! ለምን ታሰቃየኛለህ ትለው ዘንድ አትችልም፡፡ ፈቃዱን፣ ስሜቱን፣ ጠባዩንና ሥርዓቱን እስከጠበክለት ድረስ፤ እርሱ ደግሞ አንተን በክፋት ይጠብቅብህ ዘንድ መብት አለው፡፡ በጎነትን ሳታስቀድም፣ ርኅራኄን ሳትወደው፣ ምቀኝነትን ሳትተወው፣ ጉቦን ሳትጠየፈው .. በጠቅላላው ኃጢአትን ሳትናዘዘው፤ "ከክፉ ሁሉ አድነኝ" እንጂ ብለህ መጸለይ መንፈሳዊ ስላቅ ይሆንብሃል፡፡ ከተኩላው በረት ሰተት ብለህ ገብተህ ከተኩላ አስጥለኝ እንደምን ትላለህ?
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ታላቁ ሰማዕት ማር #ገላውዴዎስ
(ሰኔ 11 የዕረፍት በዓል)
🙏 #ቅዱስ ገላውዴዎስ የተወለደው
በ3ኛው መቶ ክ/ዘ በድሮው የሮም ግዛት በአንጾኪያ (አሁን ሶርያ ውስጥ) ነው:: አባቱ አብጥልዎስ የሮም ቄሣር የኑማርያኖስ ወንድም ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ያደገው በቤተ መንግሥት ውስጥ ነው::
🙏 ወቅቱ መልካምም ክፉም ነገሮች ነበሩት:: መልካሙ ነገር በቤተ መንግሥት አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ልዑላኑ አብዛኞቹ በፍቅረ ክርስቶስ የታሠሩ ነበሩ::
🙏 ከእነዚህ መካካከል “#ቅዱስ ፋሲለደስ #ቅዱሳኑ ፊቅጦር #ቅዱስ ቴዎድሮስ #ቅዱስ አባዲር #ቅዱስ አውሳብዮስ #ቅዱስ ዮስጦስ #ቅዱስ አቦሊ #ቅዱስ እስጢፋኖስ . . .” ነበሩ ::
🙏 ቅዱሳቱ “ቅድስት ማርታ ቅድስት ታውክልያ፤ ቅድስት ኢራኢ፤ ቅድስት ሶፍያ. . .” ነበሩ::
🙏 አስቸጋሪው ነገር ደግሞ ነጋ መሸ ኑሯቸው ጦርነት ነበር:: የዘመኑ የፋርስና የቁዝ መሪዎች ጦረኞች ነበሩና ዕለት ዕለት ፍልሚያ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ገላውዴዎስ የተመሠከረለት አርበኛና የተባረከ ንጹሕ ክርስቲያን ሆኖ አድጓል:: ከልጅነቱ ጀምሮ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማጥናቱ ሕይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት ታሽቷል:: እርሱ የነገሥታቱ ቤተሰብ ነው:: ማዕዱ በየዓይነቱ ሞልቶ ካልመሸ እህል አይቀምስም:: ጸሎቱ ስሙር: ስግደቱ ከምድር: አኗኗሩ በፍቅር ሆነ:: በዚያውም ላይ በድንግልናው የጸና ኃያል ነበር::
🙏 በጊዜው የቅዱስ ገላውዴዎስን ያህል መልኩ ያማረ (ደመ ግቡ) በአካባቢው አልነበረም:: ይህ ግን ሊያታልለው አልቻለም:: ሁሉ በእጁ ቢሆንም ለእርሱ ግን ብቸኛ ምርጫው ሃይማኖተ ክርስቶስ ነበር::
✨ #ቅዱስ ገላውዴዎስ ለጦርነት ወጥቶ ሲመለስ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ሃይማኖቱን ክዶ ሕዝቡን ለጣዖት ሲያሰግድ ክርስቲያኖችን ሲገድል ደረሰ::
✨ #ቅዱሱ ኃያል የጦር ሰው ነውና ንጉሡን መግደል ሲችል ተወው:: በዚያ ሰሞንም ለገላውዴዎስ ሁለት ምርጫዎች ቀረቡለት:-
1. ክርስቶስን ክዶ የንጉሡ ተከታይ መሆን።
2. በክርስትናው ደሙን ማፍሰስ::
🙏 የቅዱሳኑ ምርጫቸው የታወቀ ነውና ታስሮ ወደ ግብጽ ተጋዘ:: በዚያ ከመኮንኑ ጋር ስለ ሃይማኖት ተከራክረው መኮንኑ ስለተበሳጨ ቅዱሱን በረዥም ጦር ጐኑን ወጋው:: ዘለፍ ብሎ ነፍሱን ሰጠ:: ሕዝበ ክርስቲያኑ በድብቅ መጥተው የቅዱሱን ሥጋ ሽቱ ቀብተው ከዝማሬ ጋር ገነዙት:: የጓደኛው እናት ቅድስት ሶፍያ መጥታ ወደ ሶርያ ወስዳዋለች:: ተወዳጅ ኃያል ቡሩክና መልካም ሰው ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት በሆነባት በዚሕች ዕለት በመላው ኦርቶዶክሳውያን ይከበራል::
የታላቁ ሰማእት የቅዱስ ማር ገላውዴዎስ ረድኤት በረከት ይደርብን 🙏🏽 ✨ 🙏🏽
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
አጋንንት ዝም ብሎ መውጣት አለበት ለምሉ! || ስንቶቻችን በትዳር ይሄ ገጥሞናል || የመምህር ምህረተአብ መልዕክት || መምህር ተስፋዬ አበራ #eotc 😱💥🚩🔥 https://youtu.be/Eq7JBKP4MVI
አጋንንት በጭራሽ አላማውን አይረሳም! በአላማ መስገድና መጸለይ በውርስ የሚያጣሉና የሚያገዳድሉ ክፉ መንፈሶች || ስማሩና ስናገሩ በአጋንንት! 💥🚩🔥😱
https://youtu.be/MfT4DdBgL9M?si=NwO3ivkV8xJ932mX
በቡዳ የተበሉ ሕጻናትን መርፌ ማስወጋት ጉዳቱ መንፈሳዊ ሰው እንዴት እንሁን? በቤት ውስጥ ሆነው የጠፉ ማዕተብ የሚያስበጥሱ #ethiopia #ንቁ 🚩💥
https://youtu.be/QNK25Vl9D4g
ለሴቶች እህቶቼ ይድረስ || በትዳር ውስጥ የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት || ክታብ አጋንንታዊ ነው || ሽንጥና ዳለ አመስጋኞች || ቅመኛ እና ውሸታም አትሁኑ 🚩💥😭 https://youtu.be/qNOrGmJXrmM
