uz
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Kanalga Telegram’da o‘tish

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Ko'proq ko'rsatish
2 269
Obunachilar
+224 soatlar
+177 kunlar
+2930 kunlar
Postlar arxiv
🍂✨ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥነህ ነው እኮን። #ጊዮርጊስ ሆይ የዘውትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅ
🍂✨ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥነህ ነው እኮን። #ጊዮርጊስ ሆይ የዘውትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደኔ ቅረብ። /መልክአ ጊዮርጊስ/ የታላቁ ሰማእት የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከቱ ጥበቃው አማላጅነቱ ከሀገራችን ከ #ኢትዮጵያ ከእኛም ጋር ጸንቶ ይኑር!!

በአረብ ሀገራት በስደት ሆናችሁ ይኼንን ያህል መትጋትና መበርታት ምንኛ መታደል ነው!! ሰባት እናቶች በአንድ ጊዜ ጬሌና አቴቴ እንዴት መጣል ቻሉ? https://youtu.be/Hh4LYKQY8Cs?si=eFXO7dHax1fUkzOL

+ እግዚአብሔር ይመስገን! የተወገዘ የምግብ አብሳይ የዘረኞች ቡድን የማያስቆመዉን መንፈሳዊ አገልግሎት እሑድ መሰከረም 25 እና ሰኞ መሰከረም 26, 2018 ዓ.ም Sunday - October 5 To
+ እግዚአብሔር ይመስገን! የተወገዘ የምግብ አብሳይ የዘረኞች ቡድን የማያስቆመዉን መንፈሳዊ አገልግሎት እሑድ መሰከረም 25 እና ሰኞ መሰከረም 26, 2018 ዓ.ም Sunday - October 5 To Monday October 6, 2025 G.C ለመስጠት  በሰላም አሜሪካን ገብተናል! + ህዝበ ክርስቲያን የሚድነዉ በሰላጣ አሰራር፣ በጥሬ ስጋ አቆራረጥ ሳይሆን ለቅዱስ እግዚአብሔር ዝቅ ብሎ በመንበርከክ ስጋን በማድከም ነፍስን በበረከት በማጎልበት እንደሆነ ህዝበ ክርቲያኑ ከሚባለዉ እና ከሚነገረዉ በላይ ተረድቶ በኑሮዉም ላይ ለዉጥ አይቶበታል። ታድያ ይሄን ጠንካራ መንፈሳዊ ምዕመን ለማሰናከል መሞከር የሆነ ሚድያ ላይ ቢላዋና መክተፊያ ይዞ ስለ ምግብ ቅቀላ እንደማዉራት ቀላል አይደለም። + አገልጋይ የሚመራ ነው፡፡ ከፊት ይቀድማል፡፡ አገልጋይ የሚከተል ነው፡፡ ለእውነት ዘብ ይቆማል፡፡ አገልጋይ የሚመክር ነው፡፡ በአንደበቱ ብቻ አይደለም ሕይወቱም ይመሰክራል፡፡ አገልጋይ የሚገስጽ ነው፡፡ ትውልዱ ግራ ዘመም በሆነ ጊዜ ቀኙን ያሳያል፡፡ አገልጋይ የሚያጽናና ነው፡፡ ግራ ግብት በሚለን ጊዜ ምርኩዝ ይሆናል፡፡ አገልጋይ ከምንም ከሁሉ አስቀድሞ ከወደቁት ጎን የሚሰለፍ ነው፡፡ ታች ያሉትን የሚያይ፡፡ ዘመን፣ ሰይጣንና ሰው የጣላቸውን ሰዎች ማየት የሚችል፡፡ ችግራቸውን የሚካፈል። ስቃያቸውን የሚጋራ፡፡ ማንም ያላያቸውን የሚያይ ነዉ፡፡ እውነተኛ አገልጋይ የሚዋጋው ከፊት ያለውን ስለሚጠላ ሳይሆን ከኋላ ያሉትን ስለሚወድ ነው! + የመንፈሳዊ ዝምድና ሞትን ተሻግሮ የሚሄድ ለዛ ነው ወዳጄ ዝምታው አቅቶን አይደለም ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው። ለዛ ነው ዝምታው አቅም አንሶን ጉልበት አጥተን አይደለም። "ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም" (የዮሐንስ ወንጌል 3፥20)

አጋንንትና ሰይጣን ካንተ እንዲርቅ ከፈለክ አሁኑኑ ገንዘባቸውን መልስላቸው!! በቤተመቅደሱ እየኖርን መፈወስ መዳን መቀየር ለምን አልቻልንም? አባ ዮሐንስ ተስፋማሪያም ጸበል አያጠምቁም!! https://youtu.be/H2nTX8J5vKs?si=Fveh4e8P-ZhS0f1y

በይሉኝታ ምክንያት ኃጢአትን የምትፈጽሙ ይኼንን ልታዳምጡ ይገባል!! ይኼ ትውልድ ጸሎትንና ምስጋናን ንቆ እንዲህ ሆነ!! #ኃጢአት #መናፍስት https://youtu.be/gV2PV4VMWUM

«ትሕቷን ቅድስት ድንግል ማርያምን በትሕትና እናክብራት!» "ትሑት ነፍስ ምስጉን ናት። ጌታ ይወዳታልና። እመ አምላክ ከኹሉም የምትበልጥ ትሕት ናት፤ ስለዚህም በምድር ላይ የሰው ልጆች በሙሉ ያመሰግኗ
«ትሕቷን ቅድስት ድንግል ማርያምን በትሕትና እናክብራት!» "ትሑት ነፍስ ምስጉን ናት። ጌታ ይወዳታልና። እመ አምላክ ከኹሉም የምትበልጥ ትሕት ናት፤ ስለዚህም በምድር ላይ የሰው ልጆች በሙሉ ያመሰግኗታል፥ ሰማያውያን ኃይላትም ያገለግሏታል። ጌታ የተመሰገነች እናቱን ለእኛ ጠባቂና ረዳት አድርጎ ሰጠን።" (St. Silouan the Athonite, Writings III.14) በእርግጥ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የትሕትና ትምህርት ቤት ናት። ለእርሷ ያለን ፍቅር የሚገለጠውም እርሷ የምትወደውን ትሕትና ገንዘብ ስናደርገው ነው። ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ በየዕለቱ እስካልተጋን ድረስ ደርሶ የሚገኝ ጸጋ አይደለም። በእመቤታችን ዕለት ከእርሷ ጋር መኾናችን አንዱ የሚረጋገጠው ትሕትና ያለን እንደ ኾነ ነው። በትዕቢት እየተቃጠልን ሺህ ጊዜ ለእመቤታችን ፍቅር አለን፤ ማርያም ማርያም ብንል ምን ጥቅም አለው? ዋናው ጉዳይ ለራሳችን በፈቃዳችን ጥመት ያለበስነውን ትዕቢት ክፉ መኾኑን አምነን በማውገዝ ወደ ትሕትና ለመድረስ እንትጋ እንጂ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.youtube.com/@estifo2239

✨🌹   #ብዙኃን_ማርያም   🌹 መስከረም  21 ✨በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡     በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ ✨ #የመጀመሪያው በቤተክርስቲያን ታሪክ በ፫፻፳፭ ዓ/ም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት  ከሩቅም ከቅርብም በኒቂያ የተሰባበሰቡት ቀን፤ ✨ #ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል / ግማደ መስቀሉ / በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ✨ +   +   +    #ጉባዔ_ኒቅያ    +   +   + ✨ 🍂  በ፫፻፳፭ ዓ.ም አርዮስ የሚባል መናፍቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ 🍂  ጊዜው ታላቁ ንጉሥ #ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአርዮስ ክህደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡ 🍂 በዚህም መሠረት ከሚያዝያ ፳፩ ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም ፳፩ ቀን ድረስ ፳፫፻፵፰ /  #ሁለት_ሺሕ_ሦስት_መቶ_ዐርባ_ስምንት / ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ 🍂 ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በ #እለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን “ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ” ባላቸው ጊዜም ከ፳፫፻፵፰ቱ (2348) መካከል ፫፻፲፰ (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው “ #ዘዕሩይ_ምስለ_አብ_በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው” ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ 🍂  ንጉሡም “ #ሃይማኖት እንደ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት ይኹን” ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት ፫፻፲፰ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው /ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት ✨ “ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን” የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት #መስከረም_፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት “#ብዙኃን_ማርያም” እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡ ✨ +    +   +    #ዕፀ_መስቀል    +   +  + ✨ 🍂 በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ 🍂   +     +     +   🍂   የእመቤታችን  ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት 🙏🏽 የቅዱስ መስቀሉ ረድኤት ጥበቃ አይለየን 🙏🏽 በዓሉም የሰላም የበረከት የረድኤት በዓል ይሁንልን🙏🏽      ✨✨✨✨✨✨✨

ይኼንን ጉድ ሰምታችሁ እራሳችሁ ፍረዱ ጸበልን አጥፍቶ ሆስፒታል መገንባት ለምን? እንዳንለወጥና እንዳንቀየር ዲያብሎስ የሚያቀርባቸው ማሳሳቻዎች! https://youtu.be/UOTiHsPn_PE

በመምህር ግርማ ቪዲዮ ከጠንቋይነትና ከፈራጅነት ተላቅቄ ንስሐ ገብቼ ቆረብኩ!! በምግብ የገባን የመተት መንፈስ ለመላቀቅ ይኼንን አድርጉ!! መስቀልና የመናፍስት መታደ ነገር በሀገራችን!! https://youtu.be/HUQtnKjC1KQ?si=b42ji9Edi6LOnm3k

ለመቁረብ ለምትጓጓ ነፍስ የተሰጠ ኦርቶዶክሳዊ ምላሽና ምክር ለመቁረብ የንስሐ አባት ፈቃድ ያስፈልጋል? ቅዱስ ቁርባን እና ያልተለመዱ መስፈርቶች #ንቁ https://youtu.be/tAeab1IK-jM

የሃይማኖት ጦርነት ለማስነሳት የምትጣደፉ አርፋችሁ ተቀመጡ!! የአቡነ አብርሃም ጥብቅ መልዕክት!! የመስቀል ክብረ በዓልን ለምን እናከብራለን?? #መስቀል #ንቁ https://youtu.be/GHbN2wvv_AA

በመምህር ተስፋዬና በወንድማችን መዝሙር ያሬድ መካከል የተፈጠረው ምንድነው?? መምህራን የመናፍስትን ሴራ ማስተማር ለምን ይፈራሉ? https://youtu.be/LA4gdH08J9Y?si=Ph6dKhO2XnpD6MaC

«ሁሉን ነገር በቁጥጥሬ ስር ለማድረግ ስታገል፣ እጆቼ በሀሳብ፣ በጭንቀትና በምኞት ተሞልተው ነበር። አንተ ልትሰጠኝ የዘረጋኸውን የሰላም ስጦታ ለመቀበል እጆቼ ባዶ አልነበሩም። ሁሉንም ነገር ለቅቄ፣
«ሁሉን ነገር በቁጥጥሬ ስር ለማድረግ ስታገል፣ እጆቼ በሀሳብ፣ በጭንቀትና በምኞት ተሞልተው ነበር። አንተ ልትሰጠኝ የዘረጋኸውን የሰላም ስጦታ ለመቀበል እጆቼ ባዶ አልነበሩም። ሁሉንም ነገር ለቅቄ፣ እጄን ወደ አንተ ባዶ አድርጌ ስዘረጋ ግን፣ ከምሸከመው ሸክም ሁሉ የከበደውን ፀጋህን ተቀበልኩ። ለካስ መቀበል ማለት መተው ኖሯል።»

«ጥላውን የወደድኩት ብርሃኑን ስለምፈራ ነበር። በራሴ ጉድለትና ድክመት ጨለማ ውስጥ ተደበቅኩ። ብርሃንህ ሲበራ ስህተቴንና ባዶነቴን ያጋልጥብኛል ብዬ ሰጋሁ። ነገር ግን ስትቀርበኝ፣ ብርሃንህ የሚያጋል
«ጥላውን የወደድኩት ብርሃኑን ስለምፈራ ነበር። በራሴ ጉድለትና ድክመት ጨለማ ውስጥ ተደበቅኩ። ብርሃንህ ሲበራ ስህተቴንና ባዶነቴን ያጋልጥብኛል ብዬ ሰጋሁ። ነገር ግን ስትቀርበኝ፣ ብርሃንህ የሚያጋልጥ ሳይሆን የሚያነፃ፣ የሚያዋርድ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ተረዳሁ። ጨለማዬን የወደድኩት፣ የብርሃንህን ታላቅ ፍቅር ገና ስላላወቅኩት ነበር።»

ጸልያችሁ ስግዳችሁ መናፍስት አልጋለጥ አልያዝ ካሉ ይኼንን አድርጉ!! ከጭንቀት ለመገላገል አሁኑኑ ይኼንን ማድረጋችሁን እንዳትረሱ!! #አጋንንት #ጭንቀት #ንቁ https://youtu.be/MSXp9ZeMtzo

"...ከአንተ ስርቅ ነፃ የወጣሁ መስሎኝ ነበር። የራሴን መንገድ መረጥኩ ያልኩት፣ እንደጠፋ በግ በጨለማ ጫካ ውስጥ መባዘኔን ዘነጋሁት። መንገዶቼ ሁሉ ወደ ተስፋ መቁረጥ፣ ነፃነቴ ሁሉ ወደ ባዶነት እ
"...ከአንተ ስርቅ ነፃ የወጣሁ መስሎኝ ነበር። የራሴን መንገድ መረጥኩ ያልኩት፣ እንደጠፋ በግ በጨለማ ጫካ ውስጥ መባዘኔን ዘነጋሁት። መንገዶቼ ሁሉ ወደ ተስፋ መቁረጥ፣ ነፃነቴ ሁሉ ወደ ባዶነት እስር ቤት መራኝ። በመጨረሻ ስደክም ስትጠራኝ ሰማሁህ። ያኔ ገባኝ፤ እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን መንገድ መከተል ሳይሆን፣ በእውነተኛው እረኛ መመራት መሆኑን።" #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.youtube.com/@estifo2239

".. የአለም ጩኸት ጆሮቼን ሲደፍነው፣ ያንተን ለስላሳ ሹክሹክታ መስማት ተሳነኝ። በሰዎች አስተያየት ማዕበል ስወሰድ፣ በራሴ ምኞት ጫጫታ ስዋጥ፣ የነፍሴን ፀጥታ አጣሁ። አሁን ግን ዙሪያዬ ካለው ግር
".. የአለም ጩኸት ጆሮቼን ሲደፍነው፣ ያንተን ለስላሳ ሹክሹክታ መስማት ተሳነኝ። በሰዎች አስተያየት ማዕበል ስወሰድ፣ በራሴ ምኞት ጫጫታ ስዋጥ፣ የነፍሴን ፀጥታ አጣሁ። አሁን ግን ዙሪያዬ ካለው ግርግር ራሴን ሳገልል፣ በውስጤ ፀጥታ ውስጥ አስተጋብቶ የሚሰማው ያንተ ድምፅ ብቻ ሆነ። ለካስ ላንተ ለመቅረብ፣ ከአለም መራቅ ሳይሆን ከራሴ ጫጫታ መውጣት ነበረብኝ።" #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.youtube.com/@estifo2239

በመርዙ እንደሚጎዳ ሁሉ ዲያብሎስም በክፋቱ ሰውን ይጎዳል። የናስ እባብ የጌታ ምሳሌ ነው። ናስ መርዝ እንደሌለው ሁሉ ክርስቶስም ንጹሐ ባሕርይ ለመሆኑ ምሳሌ። በእባብ የተነደፉት የናሱን እባብ እያዩ እንደተፈወሱ ሁሉ በኃጢአት የተያዙ ምእመናንም በመስቀል የተሰቀለውን ጌታ እያዩ ንሥሓ ገብተው ሥጋውን ደሙን ተቀብለው ፈውሰ ሥጋን ፈውሰ ነፍስን የማግኘታቸው ምሳሌ ነው። = "ገብረ ሰላመ ማዕከሌነ በመስቀሉ" ቅዱስ ኤፍሬም (ውዳሴ ማርያም ዘዓርብ)። በእኛ እና በእርሱ መካከል የነበረውን የጥል ግድግዳ አፍርሶ ሰላምን የሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሁል ጊዜም ጌታ በዕለተ ዓርብ ያደረገልንን የማዳን ሥራ ማሰብ መዘከር ይገባናል። በነገራችን ላይ ከሐሳቦች ሁሉ የሚበልጥ ሐሳብ ይህ ነው። እግዚአብሔርን ማሰብ። በረከተ መስቀሉ ይደርብን መልካም ዘመን ያድርግልን ፈጣሪ ምሕረቱን ይላክልን ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን። #መስቀል #በቅዱስ #ያሬድ #ድጓ = መስቀል ረድኤት ወሕይወት፡፡ በመስቀሉ ገብረ መድኃኒተ ወሕይወተ፡፡ ዮም መስቀል ተሰብሐ ለአኃው አብርሀ፡፡ መስቀል ብርሃን ለኩሉ ዓለም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን፡፡ መስቀል ቤዛነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ አይሁድ ክሕዱ ወንሕነሰ አመነ፡፡ እለ አመነ በመስቀሉ ድኅነ፡፡ በኃይለ መስቀሉ ይዕቀበነ ወይክስት አዕይንተ አልባቢነ፡፡ መስቀል ዕፀ ሕይወት ዕፀ መድኃኒት፡፡ መስቀል መድኃኒቶሙ ለነገሥት፡፡ መስቀል ብርሃን ለኩሉ ዓለም፡፡ መስቀልከ እግዚኦ መንሥኤ ሙታን፡፡ መስቀል ረድኤት ጽንዕ ለትኩዛን አአትብ ገጽየ በትእምርተ መስቀል፡፡ ዮም ተረክበ ዕፀ መስቀል ሠናይ ዘአርኀወ ገነተ ለፈያታይ፡፡ በመስቀሉ አርኀወ ገነተ፡፡ መስቀልከ መርሐ ይኩነነ፡፡ በባሕረ ኤርትራ አማዕተበ ሙሴ፡፡ መስቀል ያድኅነነ እምእደ ጸርነ፡፡ ትምክህትነ ወሕይወትነ መስቀል ኮነ ለነ፡፡ ሀለዉ እለ ይቤሉ ለዕፅኑ ታመልኩ ወለዕፅኑ በዓለ ትገብሩ፡፡ ኢቀደሶኑ ደሙ ክቡር ለዕፀ መስቀሉ ወበእንተዝ ንሕነ ናመልኮ፡፡ መስቀል ለነገሥት ዕበይ ወስን፡፡ እግዚአ ሕያዋን ወሙታን ገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር በኢየሩሳሌም ሀገር፡፡ ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ ይቤ ዳዊት በመንፈሰ ትንቢት በእንተ ዝንቱ ዕፀ መስቀል፡፡ ወካዕበ ይቤ ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ፡፡ መስቀል ፍጽምነ ወከዋላነ ምጽንዐተ ቅጽርነ፡፡ ጸለየ ኪራኮስ ምእመን፡፡ ዕሌኒ ንግሥት ነገደት ጎልጎታ ኀበ ተኀሥሥ ዕፀ መስቀሉ ለክርስቶስ፡፡ ዘዕጣን አንጸረ ሰገደ ጢስ፡፡ በቅንዓቶሙ አይሁድ መስቀሎ ደፈኑ፡፡ ትቤሎ ዕሌኒ ለኪራኮስ ንግረኒ አፍጥን ኀበ ሀሎ መስቀሎ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ የበበት ዕሌኒ በአፉሃ ወአጽሐሰት በእገሪሃ ወጠፍሐት በእደዊሃ ሶበ ትሬኢ ቅንዋተ መስቀል፡፡ = ዕንባቆም ነቢይ ዘአንከረ ግብሮ ዕሌኒ ንግሥት ኀሠሠት መስቀሎ፡፡ ህየ ንሰግድ ኩልነ ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ። መስቀልየ በዲበ መስቀል አንብር፡፡ ፍጽምነ ንዕተብ በዕፀ መስቀሉ ነግሀ ነቂሀነ እምንዋም፡፡ መስቀል ረድኤት ወልታ መድኃኒት፡፡ መስቀል መርሕ ለፍኖት፡፡ በመስቀሉ ለክርስቶስ እሞት ድኅነ፡፡ በመስቀልከ ክርስቶስ መራሕኮ ለአዳም ውስተ ገነት፡፡ ወነገረ መስቀሉሰ ዕፁብ ለተናግሮ። መስቀል ዕፅ ዘኢይነቅዝ፡፡ ዕፅ ዘሰጸረ አብርሃም ለምሥዋዕ፡፡ መስቀል መልእልተ ኩሉ ነገር፡፡ ሰቀልዎ ለዘሰቀሎ ለሰማይ ከመ ቀመር፡፡ አቡነ አብርሃም ወሰዶ ለይስሐቅ ወልዱ ከመ ይሡዖ አውረደ ሎቱ ቤዛሁ በግዐ እኁዝ አቅርንቲሁ በዕፀ ሳቤቅ፡፡ ዕፀ ሳቤቅ ብሂል ዕፀ ሥርየት መስቀል፡፡ መላእክት ደንገጹ ወፈርሁ ርእዮሙ እግዚኦሙ ስቁለ ዲበ ዕፀ መስቀል፡፡ መስቀል አምዳ ወድዳ ለቤተክርስቲያን፡፡ ዝንቱ መስቀል ለአይሁድ ስደት ለመሐይምናን ሰላም፡፡ ሞገሦሙ ለጻድቃን፡፡ መስቀል መድኃኔ ዓለም፡፡ መስቀልከ እግዚኦ ሐጹር ወጥቅም፡፡ መስቀል ጸገየ ዘጋዲ፡፡ © ምንጭ:- የአጫብር ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን አደረሳችሁ