HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 278
Obunachilar
+324 soatlar
+137 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
ተጠንቀቁ!! በጸጉር ቀለም የገባ የመተት መንፈስ!! አብዛኛው ጋብቻ እየፈረሰ ያለው ለዚህ ነው!! አትናገር የተባለው የምስጢር መተት!! #ethiopia 😱😭💥😭 https://youtu.be/KiXoHUXHOic
አገልጋዮችን "የውጭ አልጋ፥ የቤት ቀጋ" እያደረገ ያለው የEcumenism ምች!!! ገድላትና ድርሳናት ተአማኒነት የላቸውም የምሉ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች!! https://youtu.be/uProshWvBW4
አብዛኛዎቻችን እኮ እንዲህ ነን!! በመተት የመጣ ዓይነጥላና ሴራው! አባ ገብረኪዳን ደብተራዎችን አስጠነቀቁ! ጽድቁንና መንግሥቱን መሻት ለምን አቃተን?? 😱😭😱 https://youtu.be/R9syNcxTZ5g
የባርቶስ ጸሎትን ትክክለኛነት ለተጠራጠራችሁ ድንቅ ምስክርነት!! ደቂቀ እስጢፋ ይጠሉት የነበረው ጸሎተ ባርቶስ!! የባርቶስ ጸሎትን ሰዎች ለምን ይጠሉታል! 😭💥
https://youtu.be/yviWkHwyjec
ለሰይጣን አስተማሪ የሆኑ ክፉ ሰዎች!! ለእንጀራ ብቻ መኖርን ምርጫ አደረግነው!! ዲያብሎስ ሁለም አለኝ የምትለውን ሁሉ ይወስዳል!! የሰይጣን ትልቁ ጥበብ!! https://youtu.be/Ie81xF_TJB8
Repost from የጥያቄዎቻችሁ መልስ
አንዲት እናት በቲክቶክ ያስቀመጠችልኝን መልእክት ላካፍላችሁ
"የልጅ እናት ነኝ ከህጻን ልጄ ጋር ነው የምኖረው አሞኝ ቤት ተኝቼ በመድኃኒት ያለኝን ብር ጨርሻለሁ አሁን የቤት ኪራይ እንኳን መክፈል አልቻልኩም የቤት ኪራይ 4500 ብር ነው። እጄ ላይ ምንም ብር የለኝም አግዙኝ ትንሽ እንኳን እጄ ላይ ዛሬን የማልፍበት ካገኘሁ ስራ እየፈለግኩኝ ነው ስራ እጀምራለሁ። ብቻዬን ብሆን ለመጠየቅ አልደፍርም ነበር ልጄን ምን ላድርግ? በቅዱስ ሚካኤል አግዙኝ"
ለእናታችን "አይዞሽ እኔን የሚያውቁኝ እንዲያግዙሽ አሳውቅልሻለሁ" ብያታለሁ እስኪ እባካችሁ ትንሽ እንኳን ብርታት እንሁናት ይኸው የላከችልኝ የባንክ አካውንት
077 86312 31701 ምዕራፍ ይድነቃቸው / ወጋገን ባንክ (የራሷ)
1000207149447 ትርንጎ አበዩ / ንግድ ባንክ (የጉረቤቷ)
እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ!!
=> ቅድስት ኢየሉጣ በሮም ግዛት በሚገኝ አንጌቤን በሚባል አገር በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በክርስትና ሃይማኖት እና በበጎ ምግባር ጸንታ ትኖር የነበረች ደግ ሴት ነበርች፡፡ በሥርዓት ያሳደገችው ቂርቆስ የሚባል ሕፃን ልጅም ነበራት፡፡ ይህቺ ቅድስት የዘመኑን አረማዊ መኰንን እለእስክንድሮስን በመፍራቷ ከልጇ ጋር ከሮም ወደ ጠርሴስ በተሰደደች ጊዜ መኰንኑ እነርሱ ከሚገኙበት አገር ገብቶ ክርስቲያኖችን እያሳደደ መግደል ጀመረ፡፡ የንጉሡ ወታደሮችም እግዚአብሔርን እንዲክዱ፣ ለጣዖት እንዲሰግዱ ቅድስት ኢየሉጣንና ቅዱስ ቂርቆስን አስፈራሯቸው፡፡ ቅዱሳኑ ግን ሃይማኖታቸውን ለመለወጥ ፈቃደኛ አልሆኑም ነበር፡፡ በዚህም መኰንኑ ተቈጥቶ በዓይንና በአፍንጫቸው ውስጥ ጨውና ሰናፍጭ በመጨመር፤ በጋሉ የብረት ችንካሮች በመቸንከርና መላ ሰውነታቸውን በመብሳት በብዙ ዓይነት መሣሪያ አሠቃያቸው፡፡ እግዚአብሔርም የጋሉ ብረቶችን እንደ ውኀ ያቀዘቅዝላቸው፤ ሥቃያቸውንም ያቀልላቸው ነበር፡፡
=> በሌላ ጊዜም በገመድ አሳሥሮ ንጉሡ ሲያስጨንቃቸው ከቆየ በኋላ ራሳቸውን ከቆዳቸው ጋር አስላጭቶ እሳት አነደደባቸው፡፡ ዳግመኛም ከትከሻቸው እስከ እግራቸው ድረስ በሚደርሱ ችንካሮች ቸነከራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ከሥቃያቸው አድኗቸዋል፡፡ አሁንም ቀኑን ሙሉ በልዩ ልዩ የሥቃይ መሣሪያዎች ቢያስጨንቃቸውም የእግዚአብሔር ኃይልና የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት አልተለያቸውም ነበርና ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም፡፡ እንደ ገናም በመጋዝ ሰንጥቀው በብረት ምጣድ በቆሏቸው ጊዜ ጌታችን ከሞት አነሣቸውና በመኰንኑ ፊት ድንቅ ተአምራትን አደረጉ፡፡ ከተአምራቱ መካከልም ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ የመኰንኑን ጫማ በጸሎት ወደ በሬነት እንዲቀየር ማድረጉ ተጠቃሽ ሲሆን፣ መኰንኑ በተአምራቱ ተቈጥቶ የቅዱስ ቂርቆስን ምላስ አስቈርጦታል፤ ጌታችንም ምላሱን አድኖለታል፡፡
=> ዳግመኛም በፈላ የጋን ውኀ ውስጥ ቅዱሳን ቂርቆስና ኢየሉጣን ሊጨምሯቸው ሲሉ ቅድስት ኢየሉጣ በፈራች ጊዜ ቅዱስ ቂርቆስ ‹‹እናቴ ሆይ አትፍሪ›› እያለ ያረጋጋትና በተጋድሎዋ እንድትጸና ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ተያይዘው ወደ ጋኑ ውስጥ ገቡ፡፡ ውኀውም እንደ ውርጭ ቀዘቀዘ፡፡ ደግሞም ወታደሮቹ መንኰራኵር ባለበት የብረት ምጣድ ውስጥ አስገብተው ሥጋቸው እስኪቈራረጥ ድረስ በጎተቷቸው ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል አድኗቸዋል፡፡ በመጨረሻም ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ተቀብለው በመንፈቀ ሌሊት አንገታቸውን ተቈርጠው በሰማዕትነት ጥር ፲፭ ቀን ዐርፈዋል፡፡ እስከ ሞት ድረስ በታመኑበት ተጋድሏቸውም ከእግዚአብሔር ዘንድ የሕይወትን አክሊል ተቀብለዋል፡፡
=> ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣ የዚህን ዓለም ጣዕም በመናቅ ‹‹ሞት ቢሆን÷ ሕይወትም ቢሆን÷ መላእክትም ቢሆኑ÷ ግዛትም ቢሆን÷ ያለውም ቢሆን÷ የሚመጣውም ቢሆን÷ ኃይላትም ቢሆኑ÷ ከፍታም ቢሆን÷ ዝቅታም ቢሆን÷ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ እግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ›› (ሮሜ. ፰፥፴፰) በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረውን ቃል በተግባር በማሳየት ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ ራሳቸውን ለመከራና ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ቅዱሳኑ ተጋድሏቸውን እስኪፈጽሙ ድረስም ቅዱስ ገብርኤል አልተለያቸውም፡፡ በቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ቅድስት ኢየሉጣና ቅዱስ ቂርቆስ ብቻ ሳይሆኑ ዐስራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች ሰማዕታት ሆነዋል፡፡
=> እኛም በሃይማኖታችን ምክንያት መከራ ባጋጠመን ጊዜ ቈራጥ ልብ ያለው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ‹‹እናቴ ሆይ አትፍሪ›› እያለ እናቱን በመከራ እንድትጸና እንዳረጋጋትና ለሰማዕትነት እንድትበቃ እንዳደረጋት ሁሉ፣ ዘለዓለማዊውን የእግዚአብሔርን መንግሥት በአንድነት ለመውረስ እንድንችል ‹‹አይዞህ! አይዞሽ! አትፍራ! አትፍሪ›› በመባባል በዚህ ዓለም የሚገጥመንን መከራ ታግሠን፣ እስከ ሞት ድረስ በሃይማኖታችን ጸንተን መኖር ይገባናል፡፡ ክርስትና ለብቻ የሚጸደቅበት መንገድ ሳይሆን በጋራ ዋጋ የሚያገኙበት የድኅነት በር ነውና፡፡ ከዚሁ ሁሉ ጋርም ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን የተራዳው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በአማላጅነቱ እንዲጠብቀን ‹‹በተአምኖ ንሴፎ ትንባሌ ዚአከ መዓልተ ወልሊተ፤ በእግዚአብሔር ታምነን በቀንም በሌሊትም የአንተን ልመና ተስፋ እናደርጋለን›› እያልን ዘወትር ልንማጸነው ያስፈልጋል፡፡ እርሱ ከፈጣሪው ከእግዚአብሔር በተሰጠው ቃል ኪዳን መሠረት ከሚደርስብን ልዩ ልዩ መከራና ሥቃይ ያድነናልና፡፡ ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል፤ ያድናቸውማል›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (መዝ. ፴፬፥፯)፡፡ ይህን እንድናደርግም የቅዱሳን ተራዳኢነት አይለየን፡፡ የቅዱስ ገብርኤል፣ ቅድስት ኢየሉጣ እና ቅዱስ ቂርቆስ ጸሎታቸው፣ ምልጃቸው ይጠብቀን፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የእናት አባቶቼን ከራማ እንዴት ሰይጣን ትላለህ!! የመንፈስ አንድነት በሕይወታችን ለምን አጣን?? የእናቶቻችን አስተሳሰብ ስለ አጋንንት!! #ethiopia 😭😱 https://youtu.be/hpIm0wRTrDc
በጥምቀቱ የታዩ አሳዛኝ ክስተቶች!!! በእንቁላል ተደግሞ የገባ የምስጥር መተት!! እምነትና ባህልን አትደበላልቁ!! ሰንበት ተማሪዎቹ ለምን እንዲህ ያደርጋሉ??
https://youtu.be/87cDmAiaHYQ
በጥምቀቱ የታዩ አሳዛኝ ክስተቶች!!! በእንቁላል ተደግሞ የገባ የምስጥር መተት!! እምነትና ባህልን አትደበላልቁ!! ሰንበት ተማሪዎቹ ለምን እንዲህ ያደርጋሉ??
https://youtu.be/87cDmAiaHYQ
በጥምቀቱ የታዩ አሳዛኝ ክስተቶች!!! በእንቁላል ተደግሞ የገባ የምስጥር መተት!! እምነትና ባህልን አትደበላልቁ!! ሰንበት ተማሪዎቹ ለምን እንዲህ ያደርጋሉ??
https://youtu.be/87cDmAiaHYQ
+1
«እንኳን ለቅዱስ ሩፋኤል፣ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ዘርዓ ብሩክ እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን በዛሬው ቀን ስለሚታሰቡት አባቶቻችን እናቶችቻችን ወርሃዊና አመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። በረከታቸው ረድኤታቸው ይደርብን! ምልጃ ቃልኪዳናቸው አይለየን። መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን። እንበርታ እንጠንክር።» ሸር እናድርግ ቤተሰቦቼ!!
ሽቶና ጌጣጌጦች የሚወዱ የዛር አጋንንቶች!! የዶክተሩና የመምህር ግርማ ገጠመኝ!! ትውልዱን ረስተን ዲያብሎስ ይጫወተናል!! ከመከራ ከፈተና ማምለጫው መንገድ!! https://youtu.be/5kOmWF9f0Ks
"ወይን እኮ የላቸውም"
=> የቃና ዘገሊላ ታሪክ ውስጥ አስደናቂ ከኾኑ ክስተቶች ውስጥ አንዱ የወይን ማለቅ ጉዳይ ነው። በእርግጥ ቃና ዘገሊላ ውስጥ የተፈጸመው የሰርግ ጉዳይ ጥልቅ መልእክቶችን የተሸከመ መኾኑ በብዙ የሚብራራ ነው። ታሪኩን በጥልቀት ለመረዳት ግን ወደ ታሪኩ ጥልቀት ውስጥ የምንገባበትን በር ማግኘት አለብን። የዮሐንስን ወንጌል ምሥጢራዊነት ወደ መረዳት ከፍታ እስካልወጣን ድረስ በወንጌሉ ውስጥ የተፈጸሙትን አስደናቂ ክስተቶች በአግባቡ መረዳት አንችልም። ማክሲመስ ተናዛዚው መጽሐፍ ቅዱስን በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያን ይመስልና የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለችውን ቅድስተ ቅዱሳን ትመስላለች ይላል። ይህ የሚያመለክተው ወንጌሉ የተሸከመውን ጥልቅ ምሥጢር ነው። እንዲያውም ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ ሦስቱን ወንጌላት በሥጋ የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በመንፈስ ይመስላል። የሌሎቹ ወንጌላት እስትንፋሳቸው የዮሐንስ ወንጌል ነውና!!
=> ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ የዮሐንስን ወንጌል ለመረዳት ሊቁ ኦሪገን እንዳለው ወደ ጌታ ደረት ጋር ጠጋ ብሎ እንደ ዮሐንስ ከጌታ እመቤታችንን መቀበልን ይጠይቃል። ይህ ኹሉ የሚያመለክተው በወንጌሉ ላይ የተጻፉ ክስተቶችን በችኩልነትና በለብ ለብ ስሜት አልፈን እንዳንሄድና በጥልቀት እንድንመረምር ነው። ሰርግ የተፈጸመባት የገሊላዋ ቃና ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን በመያዟ ከሚመጣባት ጉድለት ስትድን እንመለከታለን። ከክርስቶስ ጋር ለምናደርገው ግንኙነት የእመቤታችን ልመና እጅግ አስፈላጊ ነው። እርሷ ቀድማን ጉድለታችንን ባታሰማልን ኖሮ መሽራው ክርስቶስ እንዴት ይቀበለን ነበር!!
=> እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤተ አይሁድ ወገን ስለ ኾነች የአይሁድን ጉድለት በእጅጉ ታውቀዋለች፤ ስለዚህ የሚጠቅማቸውን ወይን ይሰጣቸው ዘንድ ትለምናለች። በመጽሐፍ እንዲህ ተብሏል “እናንተ ሰካራሞች ንቁ ለመስከርም ወይን የምትጠጡ እናንተ ሁላችሁ! ተድላና ደስታ ከአፋችሁ ጠፍተዋልና አልቅሱ፤ እዘኑም።" ኢዩ 1፥5። በመኾኑም አይሁድ የድኅነትን ደስታ በማጣት በኀዘን ውስጥ ናቸው፤ ይህ ነውና የወይን ማጣት!! ወይን እኮ የላቸውም የድኅነት ደስታ ከደጃቸው ጠፍታለችና ስጣቸው ማለቷ ነበር። በተራው ምድራዊ ወይን ሰክረው የድኅነትን ወይን በማጣት ጨለማ ውስጥ ገብተው ነበርና ጉድለታቸውን የምታውቅ ፈጣኗ እናት ለመነችላቸው።
=> ወይን እኮ የላቸውም ርቱዕ እምነት የላቸውም። አኹንም በኦሪታቸው ውስጥ የምትታየውን አንተን ወደ ማወቅ አልመጡምና አይኖቻቸውን ከፍተህ ብርሃነ ወንጌልህን ግለጥላቸው። በጨለማ ውስጥ ያለን ነገር ለማየት የግድ ብርሃን እንዲያስፈልግ በእምነት ጨለማ ውስጥ ያሉትን ወይን ርቱዕ እምነትን ሰጥተህ አድናቸው ማለቷ ነው። ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው በሐዲስ ኪዳኗ ትክክለኛዋ እምነት በኩል ከእግዚአብሔር ጋር እስካልተገናኘን ድረስ በእርግጥም ወይን እኮ የለንም!!
=> እመቤታችን ወይን እኮ የላቸውም ማለቷ ሰዎች ከፈሪሓ እግዚአብሔር በመራቃቸው ምክንያት የደረሱበትን መልከ ጥፉነት ለማመልከትና ከዚያ እንድንፈወስ ለማስደረግ ነው። መዝ 127 “ብፁዐን ኩሎሙ እለ ይፈርሕዎ ለእግዚአብሔር ወለ እለ የሐውሩ በፍናዊሁ። ፍሬ ጻማከ ተሴሰይ፣ ብፁዕ አንተ ወሠናይ ለከ፤ ብእሲትከ ከመ ወይን ሥሙር ውስተ ጽርዓ ቤትከ - እግዚአብሔርን የሚፈሩ ኹሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ የድካምህን ዋጋ ትበላለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይኾንልሀል፤ ምስትህም በቤትህ ውስጥ እንደ ወይን የተወደደች ናት።" በማለት በብዙ አንቀጽ ጀምሮ በአንድ አንቀጽ ወደ ማውራት ይመጣል። ይህ የሚያመለክተው የክርስቶስንና የእርሱ የኾነችውን ቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ነው። በቤትህ እንደ ወይን የተወደደች ናት በማለት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ውበት ያነሣል። ስለዚህ በፈሪሓ እግዚአብሔር ውስጥ የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያን አካሎች የምግባር ውበታቸውን ሳያጡት እንደሚኖሩ፤ ወይን እኮ የላቸውም የተባሉት በዚህ ዓለም ፍልስፍናና ፍቅር የነጎዱትን ነው። የጠፉትን ወደ በረቱ ለመሰብሰብ የተደረገ የፍቅር ጥሪ ነው!!
=> ወይን እኮ የላቸውም። ፍቅረ ቢጽ ወፍቅረ እግዚአብሔር የላቸውም። የራሳቸውን ስሜት በመውደድ የሠለጠኑ ናቸውና ወይን ፍቅር የላቸውም!! ወይን ጣዕሟ እንደሚያረካ ነፍሳቸው የምትረካባቸው ቃለ እግዚአብሔር የላቸውም!! ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው ተብሏል እነርሱ ግን ይህ በአንተ ቃል የመመራት ሐሳብ የላቸውምና በቃልህ የመመራት ኃይልን ሙላባቸው!! እንግዳ ክፉ ፈቃድ ተነሥቶባቸዋልና ይህን ድል የሚያደርጉበትን ወይን ትዕግሥትን ስጣቸው። መናፍቃን ለሚያቀርቡባቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው ሰውነታቸውን በእውነት መሠረት ላይ ይገነቡት ዘንድ ወይን ማስተዋል የላቸውምና ማስተዋሉን አድላቸው!
=> ወይን ሕገ ወንጌል ናት። በሕገ ወንጌል ወይን ውስጥ ገብተው ይኖሩ ዘንድ ወይን የወንጌል ምሥጢራትን የሚረዱበት ሀብተ ትርጓሜ የላቸውም። በወንጌል ውስጥ የተዘገበው ሰላም ቀድሞ ባለበሳቸው ጥላቻ ምክንያት አልተገኘላቸውምና “ወይን እኮ የላቸውም" ። የሕይወት ወይን አንተን ራስህን በማጣት ሕማም ውስጥ ገብተው ቆስለዋልና አምላክነትህን ገልጠህ አሳያቸው። በሕይወት ውጣ ወረድ ውስጥ የሚገጥማቸውን መከራ በጽናት ይቀበሉ ዘንድ ወይን እኮ የላቸውም። በእርግጥ የእመቤታችን ድምጿ በልጇ ዘንድ ይሰማል። የእኛ ጉድለትም ስለ እርሷ ሲባል ይሟላል። ብቻ እናታችን ቅድስት ኾይ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ደስ የሚያሰኘንን እኛን ወይን እኮ የላቸውም በይልን!! ጌታ ሆይ ወይን ደምህን ጠጥተን ምሬተ ኃጢአታችንን ታስወግድ ዘንድ ስለ እናትህ ብለህ ወይንህን ስጠን! አሜን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
አፋትቼ ማጋባት እችላለሁ!! ከጥምቀቱ በኋላ የእኛስ መገኛ የት ይሆን?? ከሀገር ወጥቶ እንዲንከራተት አደረግነው!! የወጣቶች የዩኒቨርስቲ አጋንንታዊ ፈተናዎች!
https://youtu.be/3gcin8XjlMg?si=ZVdSU4LdaLCdIJIH
ዘወትር በጸሎታችን ልኖሩ የሚገቡ ነገሮች!! መናፍስትን ዘወትር ለምን እናስራለን?? ጸሎታችን ለምን ፈተና በዛበት? መሠረታዊ የጸሎትና የስግደት አካኼዶች! 💥😱
https://youtu.be/cewOqXm_5DI
#ካህናቱ የወንዙን ዳርቻ በረገጡት ጊዜ ውኃው ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ወደ ላይ ቆሟል
እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ ባርነት ወጥተው ለአርባ ዘመን ከተጓዙ በኋላ ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመግባት የዮርዳኖስን ወንዝ ሲሻገሩ፡- ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳኑን ታቦት በድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ በዙሪያው፣ ካህናቱ ደግሞ በውስጥ ኾነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አድረው በማለዳ መሻገራቸው በኢያሱ 3÷8-9 ተጽፎ ይገኛል፡፡ ካህናቱ የቃል ኪዳኑን ታቦት አክብረው የወንዙን ዳርቻ በረገጡት ጊዜ በኃይል ይወርድ የነበረው ውኃ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቀጥ ብሎ ቆሟል፡፡ ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ታቦተ ጽዮንን ያከበሩት ካህናት ከወንዙ መሀል ይቆሙ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ‹‹ወተጠምቃ እገሪሆሙ ለካህናት›› ይህም ‹‹የካህናት እግሮቻቸው የዮርዳኖስን ውኃ በመርገጣቸው እንደ ጥምቀት ሆናቸው›› በሐዲስ ኪዳነ ጌታችን ለመሠረተው ሥርዐተ ጥምቀት ምሳሌ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን የጥምቀትን ዋዜማ ከተራ ብላ የጠራችው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 113÷3-6 “ባህር አየች ሸሸችም፣ ዮርዳኖስም ወደ ኋላም ተመለሰ፣ ተራሮች እንደ ኮርማዎች ኮረብቶችም እንደ ጠቦቶች ዘለሉ፡፡” በማለት እንደተናገረው ጌታችን በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ የዮርዳኖስ ወንዝ የላይኛው ሸሽቶ ወደ ላይ ተመልሶ ሽቅብ ፈሷል፡፡ የታቹም ወደ ታች ሸሽቷል፡፡ የላይኛው ፈሳሽ ተቋርጦ እንደ ክምር ተቆልሎ ቀርቷል። ይህም ምሳሌነቱ ከአዳም ጀምሮ ክርስቶስ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ቤዛነት መቋረጡ፤ የታቹም ፈጽሞ መድረቁ ኃጢአተ አዳም የመጥፋቱ ምሳሌ ነው፡፡ እስራኤል ፈለገ ዮርዳኖስን ተሻግረው ወደ ኢያሪኮ መሔዳቸው ምእመናን በጥምቀት ከኃጢአት ቍራኝነት ተላቀው እግራቸውን ወደ ልምላሜ ገነት ወደ ዕረፍት መንግሥተ ሰማያት ለመሔዳቸው ምሳሌ ነው፡፡ እስራኤልን ይመራ የነበረው ኢያሱ የጌታ፣ ህዝበ እስራኤል የምእመናን፣ ዮርዳኖስ የጥምቀት፣ ምድረ ርስት የገነት መንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው፡፡
የከተራ በዓል በተለይ ከዋና ከተሞች ውጪ በሆኑ አካባቢዎች ወራጅ ወንዞች ተከትረው የሚከበረው ይህን የሰው ልጅ ፍዳ መርገም መቅረት ለማሰብ ሲሆን አሁን ባለው ስርዓት እንዲከበር ታላላቆቹ ነገስታት አጼ ገብረ መስቀል፣ ቅዱስ ላሊበላ፣ አጼ ይኩኖ አምላክ በታላቁ ኢትዮጵያዊ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አሳሳቢነት፣ እንዲሁም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በየጊዜው ያሳለፏቸው ሃይማኖታዊ መሠረት ያላቸው ውሳኔዎች ናቸው፡፡ በታላቁ ቅዱስ ንጉስ ላሊበላ ዘመነ መንግስት በሀገራችን የነበሩት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ ምንፈስ ቅዱስ በአክሱም በዓሉ በሚከበርበት የንግስተ ሳባ መዋኛ “ማይሹም”፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱንና የተከተረውን ውሃ ይባርኩ እደነበር የቤተክርስቲያናችን መጻሕፍት ያሳያሉ፡፡ ሰላም ማጣታችን እዲከተር፣ የኃጢአት ስራችን እንዲገታ በዚህ ታላቅ በዓል ገዳማትን እንርዳ፣ መነኮሳቱንም እንደግፍ፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
