uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 413 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 577-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 192-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 413 obunachiga ega bo‘ldi.

13 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 71 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.53% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.38% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 933 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 446 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 23 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 413
Obunachilar
-324 soatlar
+357 kunlar
+7130 kunlar
Postlar arxiv
#✤#በኣታ_ለማርያም፤ እመቤታችን አባትና እናቷ ኢያቄምና ሐና በስዕለት(ለቤተ መቅደስ ሊሰጡ ብፅዓት ገብተው) ያገኟት ናት፡፡ በአባት በእናቷ ቤትም ፫ ዓመት ተቀመጠች፤ ከእንግዲህ ወዲያማ ስእለት መብለት ይሆንብን የለምን ወስደን እንስጥ ብለው ይዘዋት ወደ ቤተ መቅደስ ሲሄዱ ዘካርያስም ሕዝቡን ሰብስቦ ጉባኤ አድርጎ ቆያቸው። **ከዚያውም ደርሰው እነሆ ተቀበሉን አሏቸው እነርሱም እንቀበላለን ብለው ቢያዩዋት ከፀሐይ ፯ እጅ አብርታ፥ ከመብረቅ ፯ እጅ አስፈርታ፥ ዕንቈ ባሕርይ መስላ ታየቻቸው፤ እነርሱም እኛ ይህችን የመሰለች ፍጡር ምን እናደርጋታለን? ምን እናበላታለን? ምን እንጋርድላታለን? ብለው ሲጨነቁ በዚህም መካከል እመቤታችንን እግዝእትነ ማርያም መንፈሳዊ ረኀብ ተነስቶባት ምርር ብላ አለቀሰች። ያን ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል በመሶበ ወርቅ ኅብስት ሰማያዊ፤ በብርሃን ጽዋዕ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው፡፡ ሕዝቡም ዘካርያስን አባታችን ይህ የወረደው ክብር ላንተ ነው የሚኾነውና ተነስተህ ታጥቀህ እጅ ነስተህ ሰግደህ ተቀበል አሉት፤ ዘካርያስም እሽ ብሎ እጅ ነስቶ ሰግዶ እቀበላለሁ ብሎ ሲጠጋ ወደ ሰማይ ራቀው፥ መጠቀው፡፡ ከሕዝቡም እያንዳንዱ እየተነሱ እንቀበላለን ብለው ቢያዩ ወደ ሰማይ ራቃቸው፥ መጠቃቸው፡፡ **ከዚህም በኋላ ዘካርያስ ሐናን ጠርቶ ለናንተ ለእንግዶች የወረደ ክብር እንደሆነ ሕፃኒቱን ይዘሽ ወደዚያ ፈቅ ብለሽ ተቀመጪ አላት፡፡ እርሷም ሕፃኒቱን ይዛ ወደዚያ ፈቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ መልአኩም ከራሳቸው ላይ ረቦ አልወርድም አለ፡፡ ***ሁለተኛም ዘካርያስ ሐናን ጠርቶ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ነገር የሚያውቅ የለም፤ ሕፃኒቱን ከዚያው ትተሽ አንቺ ወዲህ ነዪ አላት፤ እሽ ብላ ሕፃኒቱን እዚያው ትታ ወደነሱ ሄደች፡፡ ያን ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል ወርዶ ፩ ክንፉን ጋርዶ ፩ ክንፉን አጎናፅፎ ኅብስቱን አብልቷት፥ ወይኑን አጠጥቷት፤ እመቤቴ ሆይ መንገድ ባስመታሁሽ ማሪኝ ብሎ የብርሃን መሶብ፥ የብርሃን ጽዋ ይዞ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ **ሕዝቡም የምግቧማ ነገር ከተያዘ ከሰው ጋራ ምን ያጋፋታል፤ ቦታዋ ከቤተ መቅደስ ይሁን እንጂ ብለው ዙፋኑን ዘርግተው፥ ምንጣፏን አንጥፈው፥ መጋረጃውን ግራና ቀኝ ጋርደው ከቤተ መቅደስ አኖሯት፡፡ ***ይኸውም የተደረገው ታኅሣሥ ፫ ዕለት ነው፤ በአታ የሚለው ስያሜም የተሰጠው በዚሁ ነው፡፡ ‹‹አመ ፫ ለታኅሣሥ በኣታ›› እንዳለ መቅድመ ተአምር፡፡ በዚህም፤ ✤#መቅደሲቱ_ወደ መቅደስ ገባች፤ #ቅድስቲቱ_ወደ ቅድስት ገባች፤ #ክብርቲቱ_ወደ ክብርት ቤቷ ገባች፤ #ልዩ_የሆነችው_ወደ ልዩ ሥፍራ ገባች፤ #ቅድስተ_ቅዱሳኗ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ገባች፤ #ንጽሕተ_ንጹሐኗ ወደ ንጽሕ አዳራሽ ገባች፤ #ቤተ_መቅደሷ ወደ ቤተ መቅደስ ገባች፡፡ ሊቃውንትም ‹‹መቅደስ ዘኢትትነሠት /የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ››/ እያሉ አመሠገኗት፡፡ **እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ኅብስት ሰማያዊ እየተመገበች፤ ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከመላእክት ጋራ እየተጫወተች 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች፡፡ ‹‹ከመዝ ነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ፤ ወመላእክት ያመጽኡ ወትረ ሲሳየኪ ከመዝ ነበርኪ ፲ተ ወ፪ተ ዓመተ እንዘ ትትናዘዚ እምኀበ መላእክት ወስቴኪኒ ስቴ ሕይወት ውእቱ። ወመብልዕኪኒ ኅብስት ሰማያዊ››። እንዳለ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ***ምግቧ ከየት የተገኘ ነው ቢሉ በገበሬ እጅ ያልተዘራ በቤተ ሰብእ እጅ ያልተሠራ በእግዚአብሔር እጅ የተፈጠረ ያማረ የተመረጠ ነው እንጂ ፡፡ ‹‹ኦ ድንግል አኮ ኅብስተ ምድራዌ ዘተሴሰይኪ፤ አላ ኅብስተ ሰማያዌ እም ሰማየ ሰማያት ዘበሰለ፡፡ ኦ ድንግል አኮ ስቴ ምድራዌ ዘሰተይኪ አላ ስቴ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘተቀድ›› (ድንንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለሽም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን እንጂ፡፡ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለሽም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጥን ነው እንጂ፡፡) /እንዳለ ሊቁ አባ ሕርያቆስ/። ***ስታድግም በንጽሕናና በቅድስና ነው፡፡ ‹‹ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና ኖርሽ እንጂ።›› /እንዳለ ሊቁ አባ ሕርያቆስ/ ***እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሳለች አይሁድ ብዙ የክፋት ምክር ይመክሩ ነበር። ከዚህም ውስጥ አንዱ መጥቁል ወደሚባል ጠንቋይ ሄደው ‹‹ፍታሕ ማዕከሌነ ኢያቄም ወሐና›› ብለው እመቤታችንን እንዲያጠፋ እጅ መንሻን ሰጡት፤ መጥቁልም በመካከል አይሁድ በኋላ ሁነው ነጋሪት እየጎሰሙ፥ እምቢልታ እየነፉ እመቤታችንን እግዝእትነ ማርያምን ለመግደል ለቤተ መቅደስ ፪ ምንዳፈ ሐፅ ሲቀራቸው፤ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ እዚያ ድረስ ያልተደረገና ያልተነገረ መብረቅ ነጎድጓድ ወርዶ አጋንንትንም፥ መጥቁልንም፥ አይሁድንም ቀጥቅጦ አጠፋቸው። እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም በማግሥቱ ወጥታ አይታ መጥቁል ሆይ እኔን አጠፋ ብለህ መጥተህ አንተ እንዲህ ሆንህ ካንተ መከራ መዓት ያወጣኝ አምላክ ይክበር ይመስገን ብላ ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ ከዚህ በኋላ በድኑ ለዝክረ ነገር የ፫ ቀን መንገድ እየሄደ ይሸት ጀመር። እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ‹‹ዮሰሜር፣ አድሜሽ፣ ድቸር፣ አዶናዊሮስ፣ ሰራሰቅሰሬል›› ብላ የአምላክ ኅቡዕ ስምን ብትደግም መሬት ተከፍቶ ዋጣቸው ከነሥጋቸውም ሲኦል ወረዱ፡፡ ከዚህ በኋላ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እጅግ ታፈረች የሚናገራት ጠፋ ‹‹ኦ ግርምት ድንግል›› /እንዳለ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም/። ✤#በዓለ_ሢመቱ_ለቅዱስ_ፋኑኤል_ሊቀ_መላእክት፤ #ሰዳዴ አጋንንት ነው፤ /ሄኖክ 10፥8፣ ድርሳን ዘፋኑኤል/ #መጋቤ ድንግል ነው፡፡/ተአምረ ማርያም/ #ማኅሌታዊ ነው፤ #በመንበረ መንግሥቱ ዙሪያ ከሚቆሙት ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው፡፡ /ሄኖክ 20፥39/ #በአራቱ የዓለም ማዕዘናት ሹም አንዱ ነው፡፡ #ለመልካም ነገሮች ከሚራዱ መላእክት አንዱ ነው /መዝ. 33፥7/ #ካህነ ንስሐ ነው /ሄኖክ 10፥5/ #ዐቃቤ ጻድቃን ነው፡፡ /2ኛ ነገ. 6፥14/ #ምስለ_አብያጺሁ_ከመ_አብ_እንዘ_ይሴስየኪ_መና፤ #ፋኑኤል_ጽጌ_ነድ_ዘይከይድ_ደመና፡፡ ✤#ኢትዮጵያዊው_አቡነ_ዜና_ማርቆስ_በዓለ_ዕረፍታቸው ነው፡፡ እኒህ ታላቅ አባት በምድረ ጉራጌ በሚገኘው በምሁር ኢየሱስ ገዳም 40 ዓመታትን ሱባኤ የገቡ፤ ምድረ ጉራጌን (ሙሉ ሸዋን ጨምሮ እስከ ደቡብ) እንዲሁም በሌሎችም የሃገራችን ክፍሎች ያስተማሩ፤ በርካታ ሊቃውንትን /አባ ጽጌ ድንልንና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታን ጨምሮ ሌሎችን ሊቃውንትም/ ያፈሩ ፈርጥ ሲኾኑ፤ በስተመጨረሻ በተአምራት የተሞላውን ታላቁን ገዳም ደብረ ብሥራትን (ጅሩ) መሥረተው በክብር አርፈዋል፡፡ #ከዋይዜማው_ጀምሮ_የሚቆመውን_የበኣታ_ለማርያም_ሥርዐተ_ማኅሌትንም_አቅርበንላችኋል_ላልደረሰው_አዳርሱ፡፡

✤#የበኣታ_ማርያም_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ደብረ ኤረር በዓታ ወልደታ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብራሃ ወአጽብሃ የተመሠረተ፡፡ #ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ ዑርኤል ወበኣታ፤ ጎንደር ከተማ፤ ከ300ዓመታት በፊት በጎንደር ዘመነ መንግሥት የተሠረተችና የታች ቤት አቋቋም ዋና ምስክር ጕባኤ ቤት፡፡ #ታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም ወስዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት፤ /አ.አ. መካነ አጽሙ ወተዝካረ ስሙ ለዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ፤ 1910ዓ.ም. በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለአባታቸው ምኒልክ መታሰቢያ የተሠራ/ #መቀሌ በኣታ ለማርያም #ባሕር ዳር በኣታ ለማርያም፤ #ጮቢ በኣታ ለማርያም ገዳም፤ ሸዋ #ሆሳዕና በኣታ ለማርያም፤ /በዛፍ ላይ ድንቅ ተአምር የሚታይበት/ #ጂንካ በኣታ ለማርያም፤ #ደብረ በአታ ለማርያም /ሂውስተን አሜሪካ/ ✤#የቅዱስ_ፋኑኤል_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ጋዥ ሜዳ ድሬ አክርሚት ፋኑኤል፤ /ሰሜን ሸዋ፥ ሃገረ ማርያም/ #አዲስ አበባ ካራ ቆሬ ቅዱስ ፋኑኤል ቤ.ክ. #አዲስ አበባ አያት ቅዱስ ፋኑኤል ✤#የአቡነ_ዜና_ማርቆስ_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ምሁር ኢየሱስ ገዳም /ጉራጌ ሃገር/ #ደብረ ብሥራት /ሰሜን ሸዋ፥ እነዋሪ፥ ጅሩ/ …………. ሌሎችን በየአጥቢያችሁ ያሉትንና የምታውቋቸውን አብያተ ክርስቲያናት እናንተ ጨምሩበት

ዋርያ ነግሮናል ያዕ 5፡17-20፡፡ ከኤልያስ ብዙ ነገር ወይም ተግባር ስለሚማሩ ከቅዱስ መጽሐፍ ከ 1ኛ ነገሥ 17፡1 ጀምረው እስከ 2ኛ ነገሥ 2፡11 ረጋ ብለው ይመርምሩ ክርስትናዎትንም ይፈትሹ፡፡ #ታኅሣሥ_1 #ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው፤ *በጥንታዊው ደብረ ኃይል እንጦጦ ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ፤ *በደብረ ኤልያስ ጎጃም፤ *በገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት አለ) *በብሥራተ ገብርኤል ቅዱስ ኤልያስ (ኋላ ብሥራተ ገብርኤል በመባል በሚጠራው) *በሻሸመኔ ልደታና በሌሎችም የቅዱስ ኤልያስ አድባራትና ገዳማት ይከበራል፡፡ ሥርዐተ ማኅሌቱን በዜማ መጻሕፍት ያልተጻፈ በመኾኑ ላልደረሰው በ Facebook, Email, Viber, Xender, Bluetooth በማድረስ ይተባበሩ፡፡ #በጸሎታችሁ_ሰ/ት/ቤታችንን#አትርሱን፨ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/joinchat/AAAAAE2hgYCjGkwz9N1jIw /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#ኤልያስ የሚመስጠውንና ብዙ ቁም ነገር የሚሸመትበትን የነቢዩ አልያስ ታሪክ እነሆ፤ #ደመና ደመና ….. በሠረገላ፤ ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤… ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤ ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤ በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤ አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡ እንኳን ለቅዱስ ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል (የልደት ቀን) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ ይባላል፡፡ በነቢይነትም ሆነ በብቃት ኤልያስን የሚያክል፤ በሥራው የሚወክል ከእሱ በፊትም ኾነ በኋላ በተአምራት የተሞላ እሳት ለበስ ነቢይ እሱ ከመረጠው ከደቀ መዝሙሩ ከኤልሳዕ በቀር አልተነሳም፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ከኢዮርብዓም እስከ እርሱ ድረስ ለአያሌ ዓመታት በሰይጣን ግፊት በሰው ሠራሽ ጣዖት የተመረዘ በኃጢአትም ረዘረዘ፣ የግፈኛው አክአብና የዘማዊቷ ኤልዛቤልን መንግሥት በሦስት ዓመት ከመንፈቅ በከባድ ድርቅ በመናጥ፣ እንዲሁም አፈር እንደበላው ብረት የዛገ አስተሳሰባቸውን በሰው ደምና በቅሚያ ገንዘብ የተሞላ ሰውነታቸውን በማን አለብኝነት ያበጠ ልባቸውን እንደሰም በማቅለጥ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ያሳጣ በፈጣሪው ለዚህ ሥራ የተመረጠ ሰመ ጥር ነቢይ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ነውና፡፡ ኤልያስ የከተማ ነቢይ ብቻ አይደለም ባሕታውያን ተብለው ከሚጠሩት ነቢያተ ጽድቅም አንዱ እንደነበር ሕልውናው ምስክር ነው፡፡ (( ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን እንዳታጸድቅ የዘሩባትን እንዳታበቅል ለባለንብረቱ አመለከተ ይህም ጥያቄው ከእግዚአብሔር መልስ አግኝቷል፡፡ ነገሥ 17፥1-2፡፡ ከዚህ ላይ የሊቀ ነቢያት ሙሴንና የኢሳይያስን ቃል ያስጠቅሳል ዘዳ 32፥1-4፣ ኢሳ 1፥2-5፡፡ በእነዚህ እስከፊ ዓመታት ውስጥ በመሪዎች አመፅ በኤልያስ ተግሣጽ የሚመለከተውም የማይመለከተውም የሚልሰውና ሚቀምሰው አጥቶ በዋለበት እንደ ቅጠል ረገፈ እንደሻሸተ ነጠፈ፡፡ የኀጥአን ፍዳ ጻድቅ ይደፋ ይሏል ይህ ነው፡፡ ዛሬም በአምስቱ ክፍለ ዓለም የብዙኃኑ እልቂት ሲፈጸም የሚታየው በጥቂት እግዚአብሔር የለሽ ሰይጣን ጁንታዎች ሽፍቶች መሆኑን ከአክአብና ኤልዛቤል ይማሯል፡፡ ይህን የኤልያስን ጠበቅ ያለ እገዳ ከስምንት መቶ አምሳው ነቢያተ ሐሰት ካህናተ ጣዖት አንዱም ወደ ሚመለከተው በጸሎቱም ሆነ በመሥዋዕቱ አመልክቶ ሊያስነሳ ወይም ለማስነሳት የቻለ የለም፡ ጠንቋዮችና አታላዮች በብሉይ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከቤተ መንግሥት ተለይተው አይርቁም፡፡ 1ኛ ነገሥ 18፥22፣ዳን 2፥1-14፡፡ ✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18፥41-46፣ ያዕ 5 17-18 እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የገባውን ቃል ኪዳን አያጥፍም አቁም ሲሉት ያቆማል ስጥ ሲሉት ይሰጣል እንጂ ምን አገባቸው ብሎ እንደፈለገው አያደርግም፡፡ የእግዚአብሔር ሐዋርያ ስለ ኤልያስ ማንነት ሲያደንቅ ኤልያስ እንደኛ ሰው ነበር ዝናም እንዳይዘንም ከለከለ እንደገናም እንዲዘንም አደረገ በማለት በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖች ከቀና ክርስትናቸው ምን እንደሚጠበቅባቸው ከእምነታቸው ምን ማግኘት እንዳለባቸው ይጠይቃል ያዕ.5፥13-20፡፡ ዛሬስ ምን ይመስሎታል፡፡ ኤልያስ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ነገር ግን በረዶ ያዘነመላቸው አንደኛ ሙሴ ዘፀ 9፥13-21 ሁለተኛ ኢያሱ 10፥9-12 ሦስተኛም ሳሙኤል 1ኛ ሳሙ 12፥1-19 ይመለከታል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች ከየት እንደሚያመጡት የማይታወቅ እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማራል፡፡ ✤ 4.ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፡፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት ሴት ልጇ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ይህች ሴት በእምነቷ አርአያነት ያላት ደገኛ ሴት ናት፡፡ ኤልያስን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ፣ ኀጢአቴንስ ታስብ ዘንድ ልጄንስ ትገድል ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን ብላዋለች፡፡ ኤልያስም በእግዚአብሔር ኀይል ማንኛውንም ችግር ለመፍታት ሙሉ መብት ነበረውና ወዲያውኑ የሞተውን ብላቴና ጠጋ ብሎ ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት አስነስቶ የብላቴናውን እናት አስደስቷል 1ኛ ነገሥ 17 17-24 ሐዋርያ እምነት ጀግኖችን በመዘገበበት አንቀጽ ይችን ሴት ልብ ይሏል፤ ዕብ 11፥35፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ያሉ እናቶች ያስፈልቷል፡፡ ይህችን ሴት የሚመስሉ እናቶች 2ኛ ነገሥ. 4፥18-38 ፣ሉቃ 7፥11-17 ተመዝግበዋል፡፡ በሐዋርያት ሥራም ያሉት እናቶች ከእነዚህ ጋር ያነጻጽሯል የሐዋሥ 9 36-43፡፡ ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ 1ኛ ነገሥ 18 20 -29፡፡ ሰይጣን በሰማርያ በምድር እንደዚያ ቀን ሰው መዘባበቻ በመሆን የውርደት ቀን ገጥሞት አያውቅም፡፡ በገዛ አገሩና መንደሩ፡፡ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት 1ኛ ነገሥ 18 30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብ መጠጥ ተጉዟል 1ኛ ነገሥ 19፥5-7 ✤ 9. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት ምሉአነ ኀጢአት የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሸግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11 ✤ 11. ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራው ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አርጓል 2ኛ ነገሥ. 2 6-9 ✤ 12. እንደ እያስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17 ፥3 ፡፡ ከዚህ ዓለም ከተሰናበቱ በኋላ ወደዚህ ዓለም መጥተው የፈጣሪጣቸውን ሰው መሆን ያዩ ከነቢያተ ጽድቅ ሙሴና ኤልያስ ብቸኞች ናቸው ብፁዓን ከተባሉት ሐዋርያትም ተቆጥረዋል፤ በዚህም ቅዱሳን ከሞት በኋላ እንደሚያማልዱም መስክሯል፡፡ ማቴ 13፥16-17፡፡ ኤልያስ ሰው መባል ወይም ተብሎ በመጠራት እንደማንኛውም ሰው መሆኑ መልአክ አለመሆኑን ሐ

#ቅዱስ_ፊልሞና_ሐዋርያ_(_ጥዑመ_ቃል) ✤ከ72ቱ አርድእት አንዱ የኾነና 'ጥዑመ ቃል (አንደበቱ የሚጣፍጥ) በመባል የሚታወቅ ሲኾን፤ በዘመነ ሐዋርያት በጣም ልጅ በመሆኑ እየተሯሯጠ ለአበው ይታዘዝ ነበር፡፡ ከቅዱስ እንድርያስ ጋር ለስብከት ወጥቷል፤ ሃገረ ስብከቱም ልዳ ነበረች፤ እርሱ ሲያስተምርና ሲያነብብ ሰው ሁሉ በተመስጦ ይሰማው ነበር፤ አንዳንድ ቀን ደግሞ ወፎችና ርግቦች ያደምጡት ያዋሩትም ነበር፡፡ ሊገድሉት የመጡ ወታደሮች እንኳን በተደሞ መግደላቸውን ይረሱት ነበር፡፡ ይህ ታላቅ አርድእትና ሐዋርያ በዛሬው ዕለት ነው ያረፈው፡፡

#ያዕቆብ_ዘግሙድ_፤_የፋርሱ_ኰከብ፤ 42 አካላቱ ተቆራጠው ሰማዕት የኾነ፡፡ *ከክርስቲያን ቤተሰብ የተወለደው ቅዱስ፤ ሚስት አግብቶ በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ሠክራድ ጋር በጣም ይዋደዱና አማካሪውም ነበርና በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ሹም አድርጐ አስቀመጠው፤ በሒደትም ንጉሡ የሚለውን ሁሉ የሚፈጽም ሰው ሆነ፤ ንጉሡም "ለእሳትና ለፀሐይ ስገድ፤ እነሱንም አምልካቸው" ሲል ጠየቀው:: ያዕቆብም ገና በእምነት ያልጠነረ በመኾኑና ከንጉሡ ጋር ወዳጅ ስለነበረ ንጉሡን ለማስደሰት ብሎ የክርስትና እምነት የማይፈቀድወን ለሌሎች አማልክት (ለፀሐይ ሰገደ፤ እርሷንም አመለከ)፤ ክርስቲያኖቹ ይህንን ሲሰሙ እጅግ አዘኑ ይልቁኑ ደግሞ የቅርብ ወዳጆቹ የሆኑት እናቱ፥ እኅቱና ሚስቱ ይህንን ሲሰሙ እጅግ በማዘናቸው ደብዳቤ ጽፈው ተፈራርመው ላኩለት፤ የደብዳቤው ይዘት እንዲህ ይላል፤ "አንተ ክርስትናህን መካድህን ሰምተን አዘንን፤ በዚህም ምክንያት ከዚህ በኋላ በአካባቢህ መኖርን አንፈልግም፤ ከቅዱሳት መጻሕፍትም እየጠቀሱ፤ ለሞተልህ ለክርስቶስ ካልታመንሀ እኛ አንተን እንደ ልጅ፣ እንደ ወንድምና እንደ ባል ልናምንህ ይከብደናል፡፡››፤ ይህንን ደብዳቤ ልከውለት እነርሱ አካባቢውን ለቀቁ፤ ቅዱስ ያዕቆብ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደ ቤቱ ገብቶ ሲያነበው ደነገጠ፤ በዚህ ምድር ያሉት ዘመዶቹ ሚስቱ፣ እናቱና አንዲት እኅቱ ብቻ ናቸውና ውስጡ ተሸበረ፤ ተደፍቶም ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ *በመሸም ጊዜ ጸሎት ሲያደርግ ከንጉሡ ጋራ ያደረገውን ያልተገባ ቅርርብና ስህትት እግዚአብሔር ግልጽ ብሎ እንዲታየው አደረገ፤ እርሱም ‹‹ጌታ ሆይ፤ በምድር ካሉ የሥጋ ዘመዶቼ መለየት እንዲህ ካሸበረኝ፤ ካንተ ፍቅር መለየትማ እንደ ምን ይጨንቅ ይሆን፡፡ በሰማያዊ ዙፋንህ ፊትስ እንዴት ብዬ እቆማለሁ፡፡›› እያለ ሌሊቱን ሙሉ በእንባና በጸሎት አድሮ በጠዋት ንስሐ ገባ፡፡ ከዚህች እለት ጀምሮም ፍፁም በክርስቶስ ፍቅር ተጠመደ፤ ጾምና ጸሎትንም ወዳጆቹ አድርጐ ከንጉሡ እልፍኝና አደባባይ ቀረ፡፡ *ንጉሡም ይህንን በሰማ ጊዜ ጠርቶ ለምን እንዲህ አደረግክ ሲለው፤ ‹‹የፈጠረኝን ክርስቶስን ትቼ አንተን በባዕድ አምልኮ አስደስትህ ዘንድ የሚገባ አይደለም›› ሲል ተናገረው፤ ንጉሡም በብዙ ሽንገላ ሊያታልለው ቢሞክር እምቢ ስላለው ብዙ መከራን አደረሰበት ደሙ በመሬት ላይ እስኪንፈስ ድረስም አስገረፈው፣ አስደበደበው:፤ ጭንቅ መከራዎችንም አደረሰበት፡፡ **ቅዱሱ ግን በፍቅረ ክርስቶስ ጸና፤ በዚህ የተበሳጨው ንጉሡ በየቀኑ አካሉን እንዲቆራርጡት ግን ቶሎ እንዳይገሉት አዘዘ፡፡ ቀን በቀን እየገቡ ከአካሉ ይቆርጡ ጀመር፡፡ መሐል አካሉ (ወገቡና ራሱ) ብቻ እስኪቀሩ ድረስም ከጣቶቹ ተነስተው እጆቹን እስከ ክንዱ፤ እግሮቹን እስከ ታፋው ድረስ፤ ደረቱና አካሉ ግንድ እስኪመስል ድረስ ቆረጡ፤ ቅዱሱም እንዲህ እያለ በትጋት ይጸልይ ነበረ ‹‹የወይን ግንድ ሆይ፤ እኔን ቅርንጫፍህ አድርገኝ›› /ዮሐ. 15፥:5/ ይለው ነበር፤ ከአካሉ እየቆረጡ የጣሉትም ሲቆጠር 42 ሆነ:: 43ኛ ደግሞ የተረፈ ደረቱና አካሉ ነበርና፤ ተቆንጽሎ በቀረው ግማሽ አካሉ ‹‹አቤቱ ወደ አንተ የማነሳው አካል የልቀረልኝምና ነፍሴን ተቀበል›› እያለ ይጸልይ ነበር፤ ጌታችንም ተገልጾ ካረጋገው፣ ካጽናናውና ብዙ ቃልኪዳንን ከሰጠው በኋላ ከንጉሡ ጭፍሮች መካከል አንዱ መጥቶ አንገቱን በሰይፍ ቅረጠውና የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ኾነ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ታቅፎ ወደ ሰማይ አሳረገው፡፡ እናቱ፣ እኅቱና ሚስቱ ይህንን ሲሰሙ እያለቀሱና እየዘመሩ አካሉን ሰብስበው በክብር ቀበሩት፤ በደጋጎቹ ክርስቲያኖች በአኖሬዎስና በአርቃዴዎስ ዘመን ምዕመናን ውብ ቤተ ክርስቲያን ሰርተው በዚያ ሥጋውን በክብር አኖሩ፡፡ ✤#_አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት_ዘደብረ_ጽሙና_(_ዘገበርማ) **በምድረ አፋር(ለ14ዓመታት)፣ እንዲሁም በምድረ ሸዋና ጐጃም የሰበኩና ያስተማሩ አባት ናቸው፡፡ ከአባታቸው እንድርያስ (የአናዕርት ሃገረ ገዥ)ና ከእናታቸው እሌኒ፤ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወለዱና በዘመኑ ካሉ ዐበይት ጻድቃን አንዱ ናቸው፡፡ ገና በእናታቸው ማኅጸን ሳሉ አጋንንትን ያቃጥሉና ያጠፉም ነበር፡፡ *በዲቁናም ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመግባት እስከ ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ ደርሰዋል፤ ሥውራን የኾኑ ቅዱሳንም እየተገለጡ ምሥጢራትን ይነግሯቸው ነበር፡፡ ከስግደታቸው ብዛት የተነሣ የእጆቻቸው አጥንቶች እስከ መሠበር፥ ከቁመታቸውም ብዛት የተነሣ እግሮቻቸው እስከማበጥ ደርሰዋል፡፡ *ሲቀመጡና ሲሰግዱ የጌታችንን መከራ እንዲያስቡ፤ 8 ጦሮች ያሉበትን ሰንሰለት በአራቱ አቅጣጫ በወገባቸው ታጠቁ፡፡ ከልደት፣ ከጥምቀትና ከትንሣኤ በቀርም ከወገባቸው አይፈቱም ነበር፡፡ *ቅዱስ ሚካኤልም ዕፀ ገነት አምጥቶ ካሸተታቸው በኋላ ምድራዊን ነገር ለመቅመስ የሚጸየፉ ኾኑ፡፡ *ቅስናን እንዲሾሙ አበምኔቱ ሲጠይቃቸው እምቢ በማለታቸው ወደ ሊቀ ጳጳሱ መልእክት አድርሱልኝ ብለው በላኳቸው ጊዜ ጳጳሱ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ቅስናን ሹሟቸዋል፡፡ *ወደ ደብረ ጽሙና ጻድቁ አቡነ አትናቴዎስ መቃብር ሂደው በሚጸልዩበት ጊዜም ብርሃን ይወርድላቸው ነበር፤ እግራቸው በረገጠበት ቦታም ጸበል ፈልቆላቸው ቦታውን ላሳየቻቸው እግዚእ ክብራ ለተባለች ጻድቅት በጽዋ ሞልተው ሰጧት እርሷም መካን ለነበረችው አገልጋይ ብትሰጣት ልጅ ወለደች፤ ይህ ጠበላቸው እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ገቢረ ተዓምራትን እየሠራ በገዳማቸው ገኛል፡፡ መልአኩም ወደ በረሃ እንዲወርዱ በነገራቸው መሠረት ወደ ምድረ ሐጋይ በመሄድ ለ41ዓመታት በጽኑ ተጋድሎ ቆይተዋል፡፡ **ወደተለያዩ ገዳማት በመሄድም 40 ቀን (ከሰንበት ውጪ ሳምንቱን ሙሉ እያከፈሉ) ይጾሙና ይጸልዩ ነበር፡፡ ወደ ታላቁ ገዳም ወደ ዋልድባ ገብተው ሲወጡም ወደ ድባብ ገዳም ገዳም ሄደው 40ቀን ሲጾሙ ጌታችን ወዳልተጠመቁ ሄደው እንዲያስተምሩ አዝዟቸው አስተምረዋል፡፡ * ጻድቁ 3ት ነገሮችን እፈልጋለሁ፤ እነርሱም፤ ከሐሜት መራቅን፤ ክፉ ነገርን ከማየት መራቅን፤ ከንቱ ነገርን ከመስማት መራቅን፤ እያሉ ይናገሩ ነበር፡፡ *ሰማዕት እንዲኾኑም ይለምኑ ነበረ፤ እመቤታችንም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በመምጣት ‹‹የጳውሎስ አበባ፥ የጴጥሮስ ፍሬ፥ የልጄ ተክል›› የለመንከውን ታገኛለህና በርታ አለቻቸው፤ አርሳቸውም በነገረ ሠሪ ከንጉሡ ጋራ እንዲጣሉ አደረጓቸው፤ በንጉሡ ዘርዐያዕቆብና በሠራዊቶቻቸው ብዙ መከራን ተቀብለው በ71 ዓማታቸው በሰማዕትነት አረፉ፤ ከ14 ዓመት በኋላም በንጉሡ ዘርዐያዕቆብ ወንበር ልጁ በዕደ ማርያም በነገሠ ጊዜ ሥጋቸውን አፍልሶ በደብረ ጽሙና በክብር አሳረፈው፡፡ ጻድቁ በታላቁ ገዳማቸው በደብረ ጽሞናና በደብረ ሊባኖስ አጠገብ በሚገኘው በአጋት መድኀኔ ዓለም ክብረ በዓላቸው ይከበራል፡፡ ***ጻድቁ በተባሕትዎም ኾነ በትሩፋት እጅግ የተደነቁ አባት ነበሩ፡፡ ለአብነትም ያህል፤ * በትራቸው እንደ ሙሴ በትር ተዓምራትን ታደርግ ነበር፡፡ በብርሃን ሠረገላም ይጓጓዙ ነበር፡፡ * ክርስቶስን በመከራው ይመስሉት ዘንድ ዘወትር ይተጉ ነበር፤ *ሥጋ ወደሙ የተቀበለ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲያስመልሰው ተመልከተው ሁሉ ተጸይፎ ሲሸሽ እሳቸው ግን የፈጣሪን ሥጋና ደም በመመልከት ደስ እያላቸው እንደ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ተመግበውታል፤ በዚህ ጊዜም ጌታ ከሰማይ ወርዶ በግንባራቸው ላይ ፀሐይን ስሎባቸዋል፤ በዚህ ምክንያትም ፊታቸው ያበራ ነበር፡፡ *በገዳማቸው አንድ ዶሮ ለእንግዳ ሊያርዱት ሲሉ አፍ አውጥቶ ‹‹በአባ ተክለ ሐዋርያት ተማጽኛቹሃለሁ›› በማለቱ ትተውታል፡፡

#✤#መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ✤ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበትን መራራ ሐሞትን ስለኔ ሕይወት የጠጣህ የአቀረብኳትን አነስተኛ የምስጋና መባዕ በቸርነትህ ተቀበል፡፡ ***በፎቶ የምታይዋቸው አብያተ ክርስቲያናት #✤#ደብረ_ቀራንዮ_መድኀኔ_ዓለም፤ #በ1826_ዓ.ም. #በንጉሥ_ሣህለ_ሥላሴ የተመሠረተ፤ ጠፍነት ሳያጋጥመው በመቆየት በአ.አ የመጀመሪያው ቤተ ክርስቲያን (በአ.አ. ላይ ከቀራንዮ የሚቀድሙ ጠፍነት ያጋጠማቸውና ኋላ መልሰው የተሠሩ ግን በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መኖራቸውን ልብ ይሏል፡፡) #✤#ቀጨኔ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔዓለም፤ #በ1903ዓ.ም. #በአቤቶ_(#ልጅ_ኢያሱ_የተመሠረተ፤ በአዲስ አበባ በመድኀኔዓለም ስም ከተመሠረቱት አብያተ ክርስቲያናት 2ኛው፡፡

#_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተማርያም፡፡ በሽዋ (የራውዕይ) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክ ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መናኝ ነበረች፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል፤ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ መንነዋል፤ ከታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በኋላም ብዙ ትርፋትንና ተጋድሎን ሠሩ፡፡ ለአብነትም፤ *ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ *በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ *በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ *ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው *በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ *ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ፤ ክቡር ደሙን ይጠጣሉ *በልባቸው ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አላሳደሩም፡፡ *"ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔዱ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው:: +"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" +"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት:: ✤ ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፤ 1. #_መብረቅ፣ 2. #_ቸነፈር፣ 3. #_ረሃብ፣ 4.#_ወረርሽኝ፣ 5.#_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በዛሬው ዕለት በኅዳር 26 ባረፈ ጊዜ፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማህሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) #_በዛሬዋ ዕለት #በናግራን ያሉ ክርስቲያኖች በ6ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት የኾኑበት ዕለትም ነው፡፡

#አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ፤ #_የወርቃማ_ዘመን_መሥራች፤ በሐይቅ የኖረ፥ እንደ እስጢፋኖስ ጸጋን ጽድቅንና ሞገስን የተመላ፥ በሥራው ፍጹም የኾነ፥ #_ወላዴ_አእላፍ_ቅዱሳን_የኾነ አባት *በበጌምድር ዳኅና(አሁን ስማዳ) ገብርኤል በተባለ ቦታ ከአባታቸው ዘክርስቶስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ነሐሴ 26 ሰኞ ተጸንሰው፤ ግንቦት 26/1205 ዓ.ም. ረቡዕ በቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ተወለዱ፡፡ ወንድሞቻቸው ገብረ ጽዮንና ስቡሕ አምላክ ይባላሉ፡፡ *እስከ 30 ዓመታቸው ድረስ በእናት አባታቸው ቤት እያገለገሉና ትምህርት እየቀሰሙ ቆዩ፤ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾላቸው ወደ 5ኛው የደብረ ዳሞ አበምኔት ዳግማዊ አቡነ ዮሐኒ ዘንድ እንዲሄዱ በራዕይ ነገራቸው፤ በመንገድም ሲሄዱም የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አግኝተው ይምጻአ ምሕረት የሚባል ዲያቆንን አስከትለው ወደ ደብረ ዳሞ እንዲሄዱ መልአኩ ባዘዛቸው መሠረት ወደ ገዳሙ አቀኑ፡፡ *በደብረ ዳሞ ቆይታቸውም እህልን በመፍጨትና ለገዳሙ ንግድን (ሩቅ መንገድንና አስጨናቂ ኹኔታዎችን በማለፍ ) ይነግዱ ነበር፡፡ እንዲሁም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመጻፍ (በመገልበጥም) ትጉህ ጸሓፊ ናቸው፤ ይህ ይታወቅ ዘንድ በቅርብ የደብረ ዳሞ ዕቃ ቤት እስከተቃጠለበት ድረስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእጃቸው የጻፉት ወንጌል ይገኝ ነበር፡፡ *37ዓመት ሲኾናቸው ከአባ ዮሐኒ ሥርዐተ አስኬማ ዘመላእክትን ከተቀበሉ በኋላ መልአኩ ወደ ሐይቅ እንዲሄዱ በገለጻላቸው መሠረት በ1237ዓ.ም. ወደ ሐይቅ በመምጣት በሐይቁ ዳር በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ.ክ. ለ6ወራት አገለገሉ፤ በዚሁ ደብር የሚገኘው ‹‹ሔር አምላክ›› የተባለ ካህንም የጻድቁን ታሪካቸውን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ወደ ደሴቱ አስገባቸው፤ የአካባቢው ሕዝብም አገልግሎታቸውንና መንፈሳዊ ተጋድሏቸውን አይተው ንጉሡ ይትባረክ ዘንድ በመሄድ የገዳሙ አበምኔት እንዲያደርገው ጠየቁት እርሱም ሾመው፡፡ ጻድቁም ይህን ገዳም በዮዲት ጉዲት ከጠፋ ከ300 ዓመታት በኋላ ዳግም አቅንቶታል፡፡ *እርሳቸውም ደሴቲቷም ስለወደዷት ከገዳሟ ላለመውጣት፤ የባሕሩን ወደብም ላለመርገጥ ብፅዓት ገብተው 20 ዓመታት ያህል እንደኖሩ፤ አፄ ይኵኖ አምላክ እንደነገሠ ጻድቁ ወደ ንጉሡ እንዲመጡ ላከበቸው፤ እርሳቸው ግን ከሐየቅቁ እንደማየወጡ ብፅዓት እንዳለባቸው ንጉሥ ወደእርሳቸው እንዲመጣ ላኩበት፤ ንጉሡም በበቅሎ እስከ ጉልበቱ ድረስ ወደ ባሕሩ ገብቶ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ኂሩተ አምላክና ኀረየነ ክርስቶስ ከሚባሉ ደቀመዛሙርቶቹ ጋር በታንኳ (በጀልባ) መጥተው ተጨዋወቱ፤ ንጉሡም ምን ላደርግልህ ትወዳለህ ሲላቸው፤ * ገዳሟ የወንዶች ገዳም እንድትኾን ነው አሉት፤ ንጉሡም በቦታው ያሉትን ሴቶች ይህ ቦታ የወንዶች ገዳም ብቻ እንዲኾን ስለወሰንኩ የፈቀዳችሁ ከእኔ ጋር በከተማዬ መኖር አሊያ በፈቀዳችሁትና በመረጣችሁት ቦታ መኖር ትችላላችሁ የምትፈልጉትንም ኹሉ እሰጣችኋለሁ በማለት ሥርዐት አበጁለት፡፡ ደሴቲቱን ለቀው እየሄዱ ካሉት ሴቶች መካከልም አንዲቷ ምጧ ደርሶ ነበረና በደሴቱ ጫፍ ወለደች ቦታውም ‹‹ምጥ ገበታ›› ተባለ፡፡ ዛሬ ክብረ በዓል የሚከበረው በዚሁ ምጥ ገበታ በተባለው ቦታ ነው፡፡ (ከምጥ ገበታ በስተምዕራብ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ፤ በስተሰሜን ምዕራብ መካነ አእምሮ (University)፤ በስተሰሜን የሴቶች ገዳም ይገኛል) * በንግግራቸው ሳሉም እባብና አለቅት በንጉሡን በቅሎ እግር ላይ ተጠመጠሙ፤ ጻድቁም መርዛማነት ያላቸውን እንስሳት በዚህ ገዳም ሰውን እንዳይጎዱ አወገዟቸው፤ የደወልም ድምፅ ተሰማ ንጉሡም አሁን ስንት ሰዐት ነው የደወል ድምፁስ ምንድን ነው ብሎ ጻድቁን ጠየቀ፤ ጻድቁም ፱ኝ ሰዐት በመኾኑ ደወሉ ከገዳሙ የተደወለ መኾኑን ነገሩት ንጉሡም ለጻድቁ የዐቃቤ ሰዐት ማዕርግን ሰጣቸው፡፡ (ምንም እንኳን እርሳቸው በሹመቱ ለመጠቀም ባይፈልጉም)፤ ከተከታያቸው ከአባ ዘኢየሱስ አንስቶ እስከ 16ኛው መጀመሪያ አጋማሽ ድረስ በሐይቅ መምህራን እጅ ቆይቷል፤ ኋላ የንጉሦች መናገሻ ከሸዋ ወደ ጎንደር ሲዛወር በቦታ ርቀት ምክንያት ይህ ሹመት በገጽ የሚሰጥ ሹመት ሁኗል፡፡) ✤ንጉሡ ይኵኖ አምላክ ለገዳሟ የሚከተለውን ሥርዐት ሠርተው መደ መናገሻቸው፤ ጻድቁም ወደ ደሴታቸው ተመለሱ፤ **መኳንንት፣ መሳፍንትና ነገሥታት የሰጡትን ገዳሙን ርስት ጉልት ማንም እንዳይነካ፤ **ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይገቡ (የአባቶች መነኰሳትና የባሕታውያን ብቻ መኖሪያ እንዲኾንና እኅቶች እንዳይቀላቀሉ በማሰብ) **መነኰስ ያልኾነ ማንም በሐይቅ ገዳም ቤትን እንዳይሠራ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በሃገራችን አንጋፋና ቀደምት በኾነው ደብረ ዳሞ መካነ አእምሮ (University) የተማሩ እንደመኾናቸው፤ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሲመለሱም በሃገራችን በትምህርት መካነ አእምሮነቱ ዋናና ግንባር ቀደምቱን፤ በርካታ ሊቃውንትን ቅዱሳንን ያፈለቀውን የሐይቅ እስጢፋኖስ መካነ አእምሮ መሠረቱ፤ በዚህም የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን መሥራች ነው፤ ልጆቻቸውም ይህን ወርቃማ ዘመን አስቀጥለውታል፡፡ በቆብ የወለዷቸው ቅዱሳን ሊቃውንት ብዙ ቢኾኑም ለአብነት ያህል ዐበይቶቹ፤ ✤ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል (ምድረ ዐማራን፣ ሸዋንና ደቡብን፤ ምድረ ትግራይን ያስተማሩ፤ የአቡነ ተክለሃይማኖት የመጀመሪያ መምህር የኾኑ) ✤ አቡነ ተክለሃይማኖት (ሐዲስ ሐዋርያ ተብሎ የተሰየመ፤ ከመመነኰሳቸው በፊት 7 ዓመታት፣ ከመነኰሱ በኋላ 3 ዓመታት ተቀምጠዋል) ✤ አባ ሕዝቅያስ (ከምድረ ወግዳ ይዞ እስከ ጎጃም ያስተማሩ) ✤ አባ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት (በጸበላቸው የእንጨት ቅርፊትን እንደ ደንጊያ መቁጠሪያ የሚያደርጉ፣ በድንጋይ ሠረገላ የሚጓጓዙ) ✤ እጭጌ አባ አሮን ዘደብረ ዳሪት (ከምድረ ዋድላ አንስቶ እስከ ዳውንት፤ ከበጌምድር እስከ ደምቢያ የሰበከ) ✤ አባ ገብረ ናዝራዊ ዘበለሳ (ምድረ ትግሬን ያስተማረ) ✤ አባ ኂሩተ አምላክ ዘዳጋ (እንደ መምህሩ በእስጢፋኖስ ስም በጣና ላይ የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳምን የመሠረተ፤ ምድረ ሳርክን ይዞ እስከ ጋዝጌ፤ መላዋን የአላፋና ጣቁሳ እና የአገው ምድርን ያስተማረ) ✤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ዘደብረ ባሕርይ) (የኢትዮጵያ መብራት)፤ አብዛኛዋን የኢትዮጵያ ምድር ያስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ከ40 በላይ በሚደርሱ ድርሳናቱ ያስጌጣት፡፡ ✤ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፡፡ ✤✤ እንዲሁም ንጉሡን ይኵኖ አምላክ (ከንግሥናው በፊት በልጅነቱ ያደገውና የተማረው ከጻድቁ ዘንድ ነው፡፡) በአጠቃላይ 44 ዓመታትን ማለትም፤ *20 ዓመት በይትባረክ ዘመነ መንግሥት *15 ዓመት በይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት *9 ዓመት በአግብዓ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የኖሩ ሲኾን፤ ለ44 ዓመታት በገዳሙ ቆይታቸው ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም፤ ለሰውነታቸውም(ለጎናቸውም) ምኝታን አላስለመዱትም፡፡ ‹‹እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ፤ መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ፡፡›› እንዲል፡፡ ጻድቁ በሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩም የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር፡፡ የማረፊያው እለት በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱና ሰዎች ተሰባሰቡ፤ በደብረ ነጐድጓድ ያደገውን ተክለ ኢየሱስን መምህር አድርጎ ሾመላቸው እነርሱንም ባርኳቸው፤ ኅዳር 26 በ1286ዓ.ም. በእለተ እሑድ ጧት ፀሐይ ስትወጣ ዐረፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም እንደሚገባ አድርገው በፍየል ሌጦ አድርገው ገንዘው በክብር ቀበሩት፡፡