uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 323 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 647-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 194-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 323 obunachiga ega bo‘ldi.

17 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -87 ga, so‘nggi 24 soatda esa -13 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.14% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.89% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 240 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 515 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 23 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 18 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 323
Obunachilar
-1324 soatlar
-147 kunlar
-8730 kunlar
Postlar arxiv
/ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/fino
/ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

፨ መንፈሳዊ ጉዞ ፨ ወደ ደብረ ከርቤ ዳግማዊ ጎልጎታ ገዳም /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/Fi
፨ መንፈሳዊ ጉዞ ፨ ወደ ደብረ ከርቤ ዳግማዊ ጎልጎታ ገዳም /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

ምኵራብ፤ ሦስተኛ ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡ በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡ በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም  ያስተምሩ ነበር፡፡ በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡ በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡ በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ የኢሳይያስን መጽሐፍ ምዕራፍ ፷፩ን አንብቧል፡፡  በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡ ፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16 ፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52 ፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1 ፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ ጌታችን ቤተ መቅደሱን የንግድ ማዕከል ያደረጉትን ዓይቶና አዝኖ ነጋዴዎቹን ከነመንጋቸው በጅራፍ እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡   /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

* በሠርፀ ድንግል የተሠራው ቤ/ክ ራሳቸውን አንሳር(አሸናፊዎች) በሚሉና የሱፊ እስልምና ተከታይ በሆኑት የሱዳን መሐዲስት ደርቡሾች በተደጋጋሚ 3ት ጊዜ ጥፋትን አደረሱበት፤ እነዚሁም -ከ1659-1674ዓ.ም. የመጀመሪያው ጥፋት፤ -በዐፄ ቴዎድሮስና በዐፄ ዮሐንስና ዘመን /በጥር 27 1877ዓ.ም. የጎንደርና የደምቢያውን ዘገረ ገዢ ዳኅና ፈንታን ገደሉ ገዳሙን አቃጠሉ፥ መነኰሳቱን ፈጁ/ -በ1880ዓ.ም. ጎንደር አካባቢ ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት አቃጠሉ -ጥር 10 1880ዓ.ም. ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተዋጉ፤ ልጃቸው ምንትዋብ ተማረከች አልሰልምም ብላ በረሃብ ሞተች፤ ባለቤቷ ደጃች ጀምበሬ ሞቱ፡፡ -ነሐሴ 23 1880ዓ.ም. ጎንደር ገብተው ከ44ቱ ደብራት 40ውን አቃጠሉ፤ -መስከረም 25 1881ዓ.ም. ጎንደርን አቃጠሉ፤ ቀሪዎቹን 3ት ደብራት ሠለስቱ ምዕትን ግምጃ ቤት ማርያምን አቃጠሉ፤ የግምጃ ቤት 9ኝ የመጻሕፍት መምህራንን (ዛሬ የምንገለገልበትን አንድምታ ከመምህር ኤስድሮስ በኋላ ያቀኑትን እነ መምህር ወልደ ሚካኤልን) በቤተክርስቲያኑ መውጫ በርላይ ከነተማሪዎቻቸው ሰየፏቸው፡፡ ጩጊ ማርያምንም አቃጠሉ፡፡ ….. ዐፄ ዮሐንስ እየመጡ መኾኑን ሲሰሙ ወደ መተማ ሸሹ፡፡ **ዐፄ ዮሐንስም ወደ ማኅበረ ሥላሴ በመግባት ገዳማውያኑን በማጽናናት፤ የብራና ተዓምረ ማርያምና ሌላም መብዓ በመስጠት በየካቲት 27/1881ዓ.ም ወደ መተማ ወርደው ተዋጉ፤ በውጊያው ግን ንጉሣችን ተመትተው ቆሰሉ፤ ጦሩም ንጉሡን ይዞ ወደ ማጠቢያ (ጻድቁ ልብስ ያጠቡበት በመሆኑ ይህን ስም አግኝቷል) ሸሸ፤ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ በመጋቢት 3/1881ዓ.ም. ደርሶ ንጉሣችንን ገደለ፤ ንጉሣችንን አናስነካም ያሉ በርካታ ካህናትና ምዕመናንም በሰማዕትነት አለፉ፡፡ **ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ /1929-1922ዓ.ም./ የተቃጠለውን ቤ.ክ. አሳነፁ፥ የውኃ ታንከር ከምድር በታች አስቆፍረው በደንጊያና በኖሩ አሠሩ፡፡ ከ8ት ዓመታት በኋላ ከሚያዝያ 13-15/ 1928ዓ.ም. ግን ጠላት ጣሊያን በጦር አውሮፕላን ሁኖ ገዳሙንና የውኃ ገንዳውን በቦንብ ደበደበ፥ 28 መነኰሳትንም ፈጀ (የቦንቡ ቀለሃ አሁንም በገዳሙ ወፍጮ ቤት ይገኛል)፡፡ ነገር ግን አውሮፕላኖቹ ጥቃቱን አድርሰው ሲመለሱ በአበው ጸሎት፥ በጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ተዓምር አድራጊነት 2ቱን አውሮፕላኖች አንዱን ዋለንታ ላይ፤ ሁለተኛውን ማርዘነብ ላይ ከስክሰዋቸዋል፤ ስብርሪያቸው አሁንም ድረስ አለ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

Yo Ab: ... ስለ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም የቀጠለ #የገዳሙ_አመሠራረት *ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደነ መልከጼዴቅና ነቢያት የክርስቶስን መወለድ የሚጠብቁ መናንያን የነበሩበት ነው፤ ለዚሁም ማስረጃ ክርስቶስ በተወለደ ዕለት ቶራ(ሚዳቋ) ‹‹ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም፥ ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን፥ ዮም ተወልደ መድኀኔ ዓለም›› (የብርሃን አምላክ ዛሬ ተወለደ) በማለት ስትቦርቅ የታየበት ነው፡፡ /የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ/ *ይህ ገዳም በዚህ ሁኔታ የስውራንና የባሕታውያን መኖሪያ ሁኖ እስከ 4ኛው ክፍለ ዘመን ከቆየ በኋላ፤ በአብርሃ ወአጽብሃና በጳጳሱ ከሣቴ ብርሃን በአካባቢው በሚያልፉ ጊዜ (ቀድሞ ወደ ግብጽና ሱዳና የሚኬደው በዚሁ አካባቢ ተደርጎ ነበር)፤ ለጳጳሱ ድባ ተራራ ላይ (አሁን ገዳሙ የሚገኝበት ተራራ) ታላቅ የብርሃን ምሰሶ ዐምድ ሲወርድ፤ አወራረዱም ከላይ አንድ፥ ከታች ደግሞ ሦስት ሁኖ ያያሉ፤ ያትንም ለነገሥታቱ ነግረዋቸው ወደ ቦታው ያመራሉ፤ ከተራራው ግርጌ ሲደርሱ ይህ ቦታ መንፈሰ እግዚአብሔር የሰፈነበት የተቀደሰ ቦታ ነውና እኛም ጫማችንን ሠራዊቱም ትጥቃቸውን ፈትተው መግባት አለብን ብለው ለነገሥታቱ ነገሯቸው፤ ነገሥታቱም ከነሠራዊታቸው ጫማቸውን አውልቀው፥ ዝናርና ትጥቃቸውን ፈትተው፥ ጎራዴና ጦራቸውን አስቀምጠው፥ ባርኔጣቸውን አውልቀው፥ ከፈረስና ከበቅሎ ላይ ወርደው ወደ ተራረው ጕዞ ጀምረዋል፡፡ ይህ ቦታ ዛሬ ግዝት በር የሚባል ሲሆን (በየካቲት 27፣ ሐምሌ 27፣ ሰሙነ ሕማማትና፣ ቀብር ካልሆነ በቀር) 7ት ቀናት እዚሁ ቦታ ላይ ተቀምጦ ነገሥታቱ ከነሠራዊታቸው ያደረጉትን ሥርዐት (በባዶ እግር፣ ….) ነው ወደ ገዳሙ ተራራ ላይ የሚወጣው፡፡ ወደ ተራረውም እንደደረሱ ብርሃኑ ቢሰወርባቸው ለ7ት ቀን ሱባኤ ይዘው ምሥጢሩ ተገልጦላቸው ሚዳቋም ምልክት ሰጥታቸዋለች፤ ወዲያውም ቦታውን ባርከው፥ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፥ ነዋሪ መነኰሳትን አስቀምጠው፥ ለገዳሙ መተዳደሪይ ርስት ጉልት ጎልተው፥ ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት ብለው ገድመው፥ የብርሃን ዐምድ ያዩበት ነውና የገዳሙን ስም ‹‹ምቅዋመ ሥላሴ›› ብለው ሰይመው ተመልሰዋል፤ ኋላ ግን ገዳሙ ስሙ ‹‹መካነ ሥላሴ›› በሚል ስያሜም ሲጠራ ቆይቷል፡ በ14ኛው ክፍለ ዘመን የጌታችን መስቀል የቅዱሳን አእፅምትና ሌሎችም ንዋያተ ቅድሳት ለ3ት ቀናት ውለው አድረውበታል፤ የብርሃን ነጸብራቅም ታይቷል፡፡ **በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተነሡት ጻድቁ ዓምደ ሥላሴ ደግሞ በተለያየ ዘመን ጠፍ የነበረውን ይህንን ገዳም አስፋፍተውና እንደ መሶብ አስባርከው እስካሁን ድረስ ሥርዐቱን እንደጠበቀ ቆይቷል፡፡ እርሳቸውም 104ዓመታትን ከኖሩ በኋላ የካቲት 27 ዐርፈው በዚሁ በገዳማቸው አጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ **ይህ ገዳም የትምህርትና የጥበብ ማዕከልም በመኾኑ ከሕዝብ እስከ ካህናት፤ ከመሳፍንት እስከ ነገሥታት፤ ከመነኰሳት እስከ ጳጳሳት፤ ቅዱሳንና ጻድቃን መናኻሪያቸው አድርገውታል፤ (ለአብነትም ከነገሥታት ዐፄ ፋሲል፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ይጠቀሳሉ) *** ዐፄ ቴዎድሮስ የተወለዱት በማኅበረ ሥላሴ አካባቢ ዳዋ በሚባል መንደር ሲሆን፤ በሕፃንነታቸው ቸንከር ተክለ ሃይማኖት ገብተው ሲማሩ እስላሞች ቤተ ክርስቲያኑን አቃጥለውና ተማሪዎቹን ሲገድሉ እርሳቸው አምልጠው፤ ወደ ታላቁ ገዳም ገብተው ከታለቁ ምሁር ባሕታዊ ከአባ ገብረ መሢሕ (በኢየሩሳሌምና በግብጽ ገዳማት የኖሩና ዐረብኛና ፈረንሣይኛን የሚያውቁ) ዘንድ ተማሩ፤ በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ፡፡ የአባታቸው ልጅ የደንቢያ ቋራና መተማ ገዢ ደጃዝማች ክንፉ ጸሎት በአባቶች ሊያስደርጉ ወደ ማኅበረ ሥላሴ ሲመጡ ዐፄ ቴዎድሮስም ጸሎተ ማርያም አስደርሰው ‹‹ስሞት ግን ዐፅሜን ከዐፅማችሁ ጋር ደምሩልኝ›› ብለው ገዳሙን ለቀው ደጃች ክንፉን ተከትለዋቸው ሄዱ፤ …… ሚያዝያ 5/1860ዓ.ም. ዐፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ ካረፉ በኋላና በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ተቀብረው 3ት ዐመት ከተቈጠረ በኋላ በኑዛዜያቸው መሠረት ልጃቸው ራስ መሸሻና የመቅደላ ካህናትና ሕዝብ የንጉሣችንን የዐፄ ቴዎድሮስን ዐፅም በታላቁ ማኅበረ ሥላሴ አምጠተው በክብር አሳረፉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/   #የገዳሙ_መነኰሳት_ሥርዐት *** ገዳሙ ሥርዐተ አበው እጅጉን የሚጠበቅበት፥ ፍቅር እንደ ሸማ የተለበሰበት፥ ምግባረ ትሩፋት የሚዘወተርበት ገዳም ነው፡፡ ለአብነትም፤ **በገዳሙ የሚገኙ መነኰሳት እንደ ዮሐንስ ወገባቸውን በዝናር የሚታጠቁና በዚያ በበርሐ እያረሱና ከፍተኛ ቊጥር ያላቸውን ከብቶች እየጠበቁ፤ ነፍሳቸውን ለሥላሴ አደራ ሰጥተው የሚኖሩ ናቸው፡፡ *የገዳሙ መደበኛ (ከዓመት እስከ ዓመት) ምግብ ከብዙ እህሎች የተቀያየጠው ‹‹መኰሬታ›› (ዳቤ) ሲሆን፤ በተለያዩ ሃገራችን ከምናውቀው መኰሬታ (ዳቤ) ይለያል፤ መኰሬታው የሚጋገረው በድንጋይ ወፍጮ በእጅ በክርትፉ ደቅቆ ሲሆን ፈጽሞ ዱቄት ያልሆነ፥ ያልላመና ወፍጮ ያልነካው ነው፡፡ በዓለም ለሚኖር ሰው ለመመገብ ይከብዳል፡፡ **መጠጣቸው ውኃ ሲሆን አልፎ አልፎ በበዓላ ከኑግ(ከሱፍ) የሚሠራ ጭልቃን ይጠጣሉ፡፡ አብዛኞች የሚመገቡትና የሚጠጡት በቀን ውሎ አንዴ ነው፡፡ ***ሥጋ ትህርምት ነው (ፈጽሞ አይበላም)፤ በዓመት 3ት ቀን (ልደት ጥምቀትና ትንሣኤ) ብቻ ነው የሚበላው፡፡ የመገርመው ግን ገዳሙ ሰፊ መሬት ስላለው በከብት ብዛት (በሃገራችን ግንባር ቀደም ነው)፡፡ እንጀራ መብላት የሚፈልግና የታመመ መነኰስ ካለ ከገዳሙ ጋር አንድነት ወዳለው ወደ ዋታሆ አቦ በመሄድ ነው እንጀራ የሚበላው፡፡ * መነኰሳቱ ለዓመት ከሚሰጣቸው ልብስ ውጪ በራሳቸው አሰፍተውና ገዝተው መልበስ አይችሉም፤ * ቁሪት (የግል ንብረት) አይፈቀድም፤ ማለትም መነኰሳቱ ከሚቆነንላቸው (ከሚሰጣቸው) መኮሪታና ጭልቃ ውጭ ማንኛውንም ተጨማሪ ምግብና መጠጥ (የሚወርድ ውኃም ቢኾን) መመገብና መጠጣት፤ በቤታቸው መርፌም ቢኾን ያለ መጋቢው ፈቃድ ማስቀመጥም ኾነ መጠቀም አይፈቀድም፤ * ማንኛውም ወደ ገዳሙ የሚሄድ ሰው (በየካቲት 27 በጻድቁ ዓምደ ሥላሴ፣ በጥርና በሐምሌ 7 የቅድስት ሥለሴ ክብረ በዓል ቀንና ለቀብር ካልኾነ በስተቀር) ለ፯ት ቀናት የግዝት በር ላይ ደጅ መጥናት ግድ ይለዋል፡፡ **በማኅበረ ሥላሴ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ስለሆነ፤ ወገን፥ ወገን፤ ተለይ፥ ተለይ፤ አጎዶ፥ አጎዶ፤ ጉዞ፥ ጉዞ፤ ሰፈር፥ ሰፈር ሲባሉ በየወገኑና በየጾታው እንዲሁም ወደ ሚታዘዙበት ቦታ ይሄዳሉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የገዳሙ_መፍለስ_መነሳት_መጥፋት_መልማት -ገዳሙ በጠረፍ አካባቢ ከመኖሩ ጋር በተያያዘ ፤ለበርካታ ጊዜያት በየዘመናቱ መቃጠል፣ መዘረፍና የቦንብ ድብደባ ደርሶበታል፤ መናኞች በሰይፍ ተሰይፈውበታል፡፡ ዋና ዋናዎቹን ብናነሣ፤ *አብርሐ ወአጽብሐ ያሠሩትን ቤ/ክ ዮዲት ጉዲት (842-888ዓ.ም.) አቃጠለችው፥ ንዋያተ ቅድሳቱንና ንብረቱን ዘረፈች፡፡ **ዮዲት ያፈረሰችውን በንጉሥ ዐምደ ጽዮን(1268-1277ዓ.ም.) ቤ/ክ መልሶ ተሠራ፡፡ *በእስላም የቱርክ መንግሥት ይረዳ በነበረው ወራሪው አሕመድ ግራኝ /1541-1545ዓ.ም./ ብዙ መነኰሳት ተጨፈጨፉ፥ ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ እንደገና በዐፄ ሠርፀ ድንግል /1553-1587ዓ.ም./ ተቋቋመ፡፡ *በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፡፡ /ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ) *በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን እንግሊዞች የገዳሙን ንብረት መዘበሩ፡፡

/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ ፨ ታቦቱ_ሥላሴ፥ ፨ ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ፥ ፨ የገዳሙ ስም ማኅበረ ሥላሴ፡፡ ፨ በየቀኑ በሁሉም ቤክ በቅዳሴ ላይ ስሙ የሚነሳው ገናናው ገዳም (ብዙዎች ግን የማያውቁት)፡፡ ፨ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ድንቅናዕፁብ ገዳም፡፡ ፨ ገዳሙን ያጠፉ አውሮፕላኖችን በጸሎት የከሰከሱ አባቶች የሚገኙበት የበርካታ ትምህቶችና የጥበብ ማዕክል፤ …. ኢትዮጵያውያን ሁሉ ቢያንስ አንዴ ሊያዩት የሚገባ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ገዳም!!!፡፡ ፨ በዚህች በየካቲት 27 እለት ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወመነኰሳት (ለአቡነ ክፍለ ማርያም፥ ለአቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘቋራ፥ ለ፯ቱ ዘሥላሴ በመባል ለሚጠሩ ቅዱሳን፣ ለዐርከ ሥሉስ /የአርኬና የመልክአ ቊርባን ደራሲ/፤ ….) የኾኑትና ፤ ጽድቃቸውና ቃልኪዳናቸው እንደ ምድር አሸዋ የበዛው፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለመቊጠር የሚያስቸግረው ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ ልደታቸውም እረፍታቸውም ነው፡፡ - እኒህ ጻድቅ የተወለዱት በጎጃም(ሸዋም የሚሉ አሉ) ሲኾን፤ የተወለዱትም ሆነ 104ዓመታት ከኖሩ በኋላ ያረፉበት ቀን በመድኀኔ ዓለም ወርኀዊ በዓል በየካቲት 27 ነው፡፡ - ጻድቁ በተለያዩ ገዳማት በአርድእትነትና ሥርዐተ አበው በማጥናትና በመተግበር ከቆዩ በኋላ፤ ምንኩስናን ከአቡነ ተንሥአ ክርስቶስ ዘትግራይ ተቀብለዋል፤ ኋላም ወደ ታላቁ ገዳም ገዳመ ዋሊ (ገዳመ ዋልድባ) ገብተው ከቆዩ በኋላ ወደ ገዳመ አስቄጥስ በመሄድ ለ18 ዓመታት ከቆዩ በኋላ በስተመጨረሻ ምናኔያቸውን በማኅበረ ሥላሴ አድርገዋል፡፡ * በ1616ዓ.ም. ሱስንዮስ 8,000 ክርስቲያኖችን የካቶሊክን ካልተቀበላችሁ ብሎ ጠዳ ላይ በሰየፈ ጊዜ ሳይፈሩና ሳይፍሩ ለሃይማኖታቸው ከተከራከሩና ጠበቃ ከኾኑት መካከል ግንባር ቀደሙ ናቸው፡፡ (ሌሎችም ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ እኅተ ጴጥሮስ፣ ፍቅርተ ጴጥሮስ፣ ሐራ ድንግል ምዕመነ ድንግል አብረው ይጠቀሳሉ)፡፡ እነዚህም ቅዱሳን ሐዘናቸውን ወደ ፈጣሪያቸው በማድረሳቸው ሱስንዮስ ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ (ተቀሰፈ)፡፡ -  የሱስንዮስ ልጅ ፋሲልም አባቴን ይፈውሱልኝ ብሎ መልእክትን ላከ፤ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና አባ ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ ማርያም ተገኝተው ካቶሊክነቱን ከተወ እሺ ብለው 3ት ሱባኤ ጸልየው ፈወሱት፤ ሱስንዮስም ንሥሐ ገብቶ ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ፡፡ በሰኔ 21 1624ዓ.ም. ‹‹የእስክንድርያ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይመለስ፥ የሮም ካቶሊክ ሃይማኖት ይፍለስ፥ ልጄ ፋሲል ይንገሥ›› ብለው አዋጅ ነገሩ፤ ልጃቸው ፋሲልንም ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ቅብዓ መንግሥት (አፈዋተ መንግሥት) ቀብተው አነገሡት፤ ንጉሡም ለገዳሙ የእርሻ መሬት የሚሆን ጣቁሳ ላይ 44ት ጉልት ጐለተ፥ የገዳሙንም ስም ‹‹ማኅበረ ሥላሴ›› ብሎ ሰየመው፡፡ - ታላቁ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ቀድሞም ከእርሳቸው በፊት የነበረ ቢኾንም፤ በተለያዩ ዘመናት በጠላት የጠፋ ስለነበረ ዳግመኛ ያስፋፉትና እንደ መሶብ ያስባረኩት ናቸው፤ - ከወለዷቸው አንዱ ዐርከ ሥሉስ ከደረሳቸው አንዱ በኾነው በመልክአ ቊርባን ላይ፤ ‹‹ሰላም ለክሙ ጻድቃነ ዛቲ ዕለት ኵልክሙ፤ ዕድ ወአንስት በበአስማቲክሙ፡፡ ቅዱሳነ ሰማይ ወምድር ማኅበረ ሥላሴ አንትሙ፤ ዝክሩነ በጸሎትክሙ በእንተ ማርያም እሙ፤ ተማኅጸነ ለክርስቶስ ሥጋሁ ወደሙ፡፡ በማለት የደረሱለት ሲኾን፤ በዚህም በየቀኑ በቅዳሴ ላይ ከቊርባን በፊት የማኅበሩን ስም የማይጠራ ቤተ ክርስቲያን የለም፡፡ ፨ ብፁዕ አባ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ንብረቱ ገዳም ውስተ ሀቌሁ ቅንአቱ ዘአዲም ያስተጋብእ ጽድቀ ዘእምኵሎሙ ቅዱሳን በጾም ወበጸሎት ሀለወ በክብር ወበሰላም፡፡ /መሐረነ አብ/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (#የሺዎች_ማኅበር)፤ ፨ ምቅዋመ ሥላሴ፡፡ ፨ስለ ገዳሙ አጠቃላይ ሁኔታ፤ *ገዳሙ የሚገኘው በሀገራችን በመተማ በረሃ ደቡባዊ ክፍል፥ ከጎንደር በስተምዕራብ አቅጣጫ (132 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ) ሲሆን፤ ከአ.አ. 901ኪ.ሜ. ርቀት ላይ፤ ከደረቅ ዐባይ ቀበሌ በ4ት ሰዓት የእግር ጕዞ ይገኛል፡፡ የጣቁሳ የቋራና የሱዳን በረሓማው አከባቢዎችም ያዋስኑታል፡፡ *ከፀሐዩ ሐሩር ማየልና ከቆላነቱ የተነሣ ‹‹በደንጊያው ላይ ተልባ ያስቆላል›› እየተባለ የሚነገርለት ነው፡፡ የተለያዩ ዕፅዋትና አራዊት የሚገኙበትም ሲሆን ቦታው በብሔራዊ ደረጃ ጥብቅ ደን ነው፡፡ * የገዳሙ ይዞታ ከ19ሺህ 186 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሲሆን፤ በቦታ ስፋት የሚመስለው ዋልድባ (ዋሊ) ብቻ ነው፡፡ በዚህም ከሃገራችን ገዳማት 2ቱ ታላላቅ ገዳማት እጅግ በጣም ሰፋፊ ይዞታ ያላቸው ገዳማት ናቸው፡፡ * ገዳሙ በ፪ት ትላልቅ ወንዞች (በገንዳ ውኃና ሸንፋ ወንዝ) የተከበበ ነው፡፡ *ገዳሙ በሚገኝበት በረሃ ውስጥ 4ት ተራሮች(አምባዎች) ይገኛሉ፡፡ እነርሱም፤ ድባ(የማኅበረ ሥላሴ ገዳም ያለበት)፣ ከርከመች፣ ኩክቢና ጎርማስ ይባላሉ፡፡ *ገዳሙን በርቀት ሆነው የሚያዋስኑት ታላላቅ ገዳማትም፤ በሰሜን አቅጣጫ ደምጫ፥ በደቡብ ጋንጫ(ዋታሆ አቦ) ናቸው፡፡ *በገዳሙና በአካባቢው ከሚገኙት የተለያዩ ዕጽዋት መካከል (ሰርኪን፥ ሲና፥ የዕጣን ዛፍ/ዋልያ/፥ መቀር፥ ወርካ፥ ክርክራ፥ ሽመል) እና ሌሎችም ልዩ ልዩ ዕጽዋት የሚገኙበት ሲኾን፤ ከዱር አራዊት መካከልም (አንበሳ፥ ነብር፥ አጋዘን፥ ቶራ/ሚዳቋ/፥ ድኩላ፥ አሳማ፥ ጉሬዛ፥ ዝንጀሮ፥ ቀይ ጦጣ፥ የተለያዩ የእባብና የዘንዶ ዝርያዎች) ይገኙበታል፡፡

፨ ቅዱስነትዎ እንኳን አደረስዎ ፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundayS
፨ ቅዱስነትዎ እንኳን አደረስዎ ፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958