ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 323 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 647,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 194

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 323 名订阅者。

根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -87,过去 24 小时变化为 -13,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.89% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 240 次浏览,首日通常累积 1 515 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 323
订阅者
-1324 小时
-147
-8730
帖子存档
/ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/fino
/ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

፨ መንፈሳዊ ጉዞ ፨ ወደ ደብረ ከርቤ ዳግማዊ ጎልጎታ ገዳም /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/Fi
፨ መንፈሳዊ ጉዞ ፨ ወደ ደብረ ከርቤ ዳግማዊ ጎልጎታ ገዳም /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

ምኵራብ፤ ሦስተኛ ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡ በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡ በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም  ያስተምሩ ነበር፡፡ በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡ በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡ በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ የኢሳይያስን መጽሐፍ ምዕራፍ ፷፩ን አንብቧል፡፡  በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡ ፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16 ፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52 ፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1 ፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ ጌታችን ቤተ መቅደሱን የንግድ ማዕከል ያደረጉትን ዓይቶና አዝኖ ነጋዴዎቹን ከነመንጋቸው በጅራፍ እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡   /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

* በሠርፀ ድንግል የተሠራው ቤ/ክ ራሳቸውን አንሳር(አሸናፊዎች) በሚሉና የሱፊ እስልምና ተከታይ በሆኑት የሱዳን መሐዲስት ደርቡሾች በተደጋጋሚ 3ት ጊዜ ጥፋትን አደረሱበት፤ እነዚሁም -ከ1659-1674ዓ.ም. የመጀመሪያው ጥፋት፤ -በዐፄ ቴዎድሮስና በዐፄ ዮሐንስና ዘመን /በጥር 27 1877ዓ.ም. የጎንደርና የደምቢያውን ዘገረ ገዢ ዳኅና ፈንታን ገደሉ ገዳሙን አቃጠሉ፥ መነኰሳቱን ፈጁ/ -በ1880ዓ.ም. ጎንደር አካባቢ ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት አቃጠሉ -ጥር 10 1880ዓ.ም. ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተዋጉ፤ ልጃቸው ምንትዋብ ተማረከች አልሰልምም ብላ በረሃብ ሞተች፤ ባለቤቷ ደጃች ጀምበሬ ሞቱ፡፡ -ነሐሴ 23 1880ዓ.ም. ጎንደር ገብተው ከ44ቱ ደብራት 40ውን አቃጠሉ፤ -መስከረም 25 1881ዓ.ም. ጎንደርን አቃጠሉ፤ ቀሪዎቹን 3ት ደብራት ሠለስቱ ምዕትን ግምጃ ቤት ማርያምን አቃጠሉ፤ የግምጃ ቤት 9ኝ የመጻሕፍት መምህራንን (ዛሬ የምንገለገልበትን አንድምታ ከመምህር ኤስድሮስ በኋላ ያቀኑትን እነ መምህር ወልደ ሚካኤልን) በቤተክርስቲያኑ መውጫ በርላይ ከነተማሪዎቻቸው ሰየፏቸው፡፡ ጩጊ ማርያምንም አቃጠሉ፡፡ ….. ዐፄ ዮሐንስ እየመጡ መኾኑን ሲሰሙ ወደ መተማ ሸሹ፡፡ **ዐፄ ዮሐንስም ወደ ማኅበረ ሥላሴ በመግባት ገዳማውያኑን በማጽናናት፤ የብራና ተዓምረ ማርያምና ሌላም መብዓ በመስጠት በየካቲት 27/1881ዓ.ም ወደ መተማ ወርደው ተዋጉ፤ በውጊያው ግን ንጉሣችን ተመትተው ቆሰሉ፤ ጦሩም ንጉሡን ይዞ ወደ ማጠቢያ (ጻድቁ ልብስ ያጠቡበት በመሆኑ ይህን ስም አግኝቷል) ሸሸ፤ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ በመጋቢት 3/1881ዓ.ም. ደርሶ ንጉሣችንን ገደለ፤ ንጉሣችንን አናስነካም ያሉ በርካታ ካህናትና ምዕመናንም በሰማዕትነት አለፉ፡፡ **ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ /1929-1922ዓ.ም./ የተቃጠለውን ቤ.ክ. አሳነፁ፥ የውኃ ታንከር ከምድር በታች አስቆፍረው በደንጊያና በኖሩ አሠሩ፡፡ ከ8ት ዓመታት በኋላ ከሚያዝያ 13-15/ 1928ዓ.ም. ግን ጠላት ጣሊያን በጦር አውሮፕላን ሁኖ ገዳሙንና የውኃ ገንዳውን በቦንብ ደበደበ፥ 28 መነኰሳትንም ፈጀ (የቦንቡ ቀለሃ አሁንም በገዳሙ ወፍጮ ቤት ይገኛል)፡፡ ነገር ግን አውሮፕላኖቹ ጥቃቱን አድርሰው ሲመለሱ በአበው ጸሎት፥ በጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ተዓምር አድራጊነት 2ቱን አውሮፕላኖች አንዱን ዋለንታ ላይ፤ ሁለተኛውን ማርዘነብ ላይ ከስክሰዋቸዋል፤ ስብርሪያቸው አሁንም ድረስ አለ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

Yo Ab: ... ስለ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም የቀጠለ #የገዳሙ_አመሠራረት *ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደነ መልከጼዴቅና ነቢያት የክርስቶስን መወለድ የሚጠብቁ መናንያን የነበሩበት ነው፤ ለዚሁም ማስረጃ ክርስቶስ በተወለደ ዕለት ቶራ(ሚዳቋ) ‹‹ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም፥ ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን፥ ዮም ተወልደ መድኀኔ ዓለም›› (የብርሃን አምላክ ዛሬ ተወለደ) በማለት ስትቦርቅ የታየበት ነው፡፡ /የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ/ *ይህ ገዳም በዚህ ሁኔታ የስውራንና የባሕታውያን መኖሪያ ሁኖ እስከ 4ኛው ክፍለ ዘመን ከቆየ በኋላ፤ በአብርሃ ወአጽብሃና በጳጳሱ ከሣቴ ብርሃን በአካባቢው በሚያልፉ ጊዜ (ቀድሞ ወደ ግብጽና ሱዳና የሚኬደው በዚሁ አካባቢ ተደርጎ ነበር)፤ ለጳጳሱ ድባ ተራራ ላይ (አሁን ገዳሙ የሚገኝበት ተራራ) ታላቅ የብርሃን ምሰሶ ዐምድ ሲወርድ፤ አወራረዱም ከላይ አንድ፥ ከታች ደግሞ ሦስት ሁኖ ያያሉ፤ ያትንም ለነገሥታቱ ነግረዋቸው ወደ ቦታው ያመራሉ፤ ከተራራው ግርጌ ሲደርሱ ይህ ቦታ መንፈሰ እግዚአብሔር የሰፈነበት የተቀደሰ ቦታ ነውና እኛም ጫማችንን ሠራዊቱም ትጥቃቸውን ፈትተው መግባት አለብን ብለው ለነገሥታቱ ነገሯቸው፤ ነገሥታቱም ከነሠራዊታቸው ጫማቸውን አውልቀው፥ ዝናርና ትጥቃቸውን ፈትተው፥ ጎራዴና ጦራቸውን አስቀምጠው፥ ባርኔጣቸውን አውልቀው፥ ከፈረስና ከበቅሎ ላይ ወርደው ወደ ተራረው ጕዞ ጀምረዋል፡፡ ይህ ቦታ ዛሬ ግዝት በር የሚባል ሲሆን (በየካቲት 27፣ ሐምሌ 27፣ ሰሙነ ሕማማትና፣ ቀብር ካልሆነ በቀር) 7ት ቀናት እዚሁ ቦታ ላይ ተቀምጦ ነገሥታቱ ከነሠራዊታቸው ያደረጉትን ሥርዐት (በባዶ እግር፣ ….) ነው ወደ ገዳሙ ተራራ ላይ የሚወጣው፡፡ ወደ ተራረውም እንደደረሱ ብርሃኑ ቢሰወርባቸው ለ7ት ቀን ሱባኤ ይዘው ምሥጢሩ ተገልጦላቸው ሚዳቋም ምልክት ሰጥታቸዋለች፤ ወዲያውም ቦታውን ባርከው፥ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፥ ነዋሪ መነኰሳትን አስቀምጠው፥ ለገዳሙ መተዳደሪይ ርስት ጉልት ጎልተው፥ ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት ብለው ገድመው፥ የብርሃን ዐምድ ያዩበት ነውና የገዳሙን ስም ‹‹ምቅዋመ ሥላሴ›› ብለው ሰይመው ተመልሰዋል፤ ኋላ ግን ገዳሙ ስሙ ‹‹መካነ ሥላሴ›› በሚል ስያሜም ሲጠራ ቆይቷል፡ በ14ኛው ክፍለ ዘመን የጌታችን መስቀል የቅዱሳን አእፅምትና ሌሎችም ንዋያተ ቅድሳት ለ3ት ቀናት ውለው አድረውበታል፤ የብርሃን ነጸብራቅም ታይቷል፡፡ **በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተነሡት ጻድቁ ዓምደ ሥላሴ ደግሞ በተለያየ ዘመን ጠፍ የነበረውን ይህንን ገዳም አስፋፍተውና እንደ መሶብ አስባርከው እስካሁን ድረስ ሥርዐቱን እንደጠበቀ ቆይቷል፡፡ እርሳቸውም 104ዓመታትን ከኖሩ በኋላ የካቲት 27 ዐርፈው በዚሁ በገዳማቸው አጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ **ይህ ገዳም የትምህርትና የጥበብ ማዕከልም በመኾኑ ከሕዝብ እስከ ካህናት፤ ከመሳፍንት እስከ ነገሥታት፤ ከመነኰሳት እስከ ጳጳሳት፤ ቅዱሳንና ጻድቃን መናኻሪያቸው አድርገውታል፤ (ለአብነትም ከነገሥታት ዐፄ ፋሲል፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ይጠቀሳሉ) *** ዐፄ ቴዎድሮስ የተወለዱት በማኅበረ ሥላሴ አካባቢ ዳዋ በሚባል መንደር ሲሆን፤ በሕፃንነታቸው ቸንከር ተክለ ሃይማኖት ገብተው ሲማሩ እስላሞች ቤተ ክርስቲያኑን አቃጥለውና ተማሪዎቹን ሲገድሉ እርሳቸው አምልጠው፤ ወደ ታላቁ ገዳም ገብተው ከታለቁ ምሁር ባሕታዊ ከአባ ገብረ መሢሕ (በኢየሩሳሌምና በግብጽ ገዳማት የኖሩና ዐረብኛና ፈረንሣይኛን የሚያውቁ) ዘንድ ተማሩ፤ በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ፡፡ የአባታቸው ልጅ የደንቢያ ቋራና መተማ ገዢ ደጃዝማች ክንፉ ጸሎት በአባቶች ሊያስደርጉ ወደ ማኅበረ ሥላሴ ሲመጡ ዐፄ ቴዎድሮስም ጸሎተ ማርያም አስደርሰው ‹‹ስሞት ግን ዐፅሜን ከዐፅማችሁ ጋር ደምሩልኝ›› ብለው ገዳሙን ለቀው ደጃች ክንፉን ተከትለዋቸው ሄዱ፤ …… ሚያዝያ 5/1860ዓ.ም. ዐፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ ካረፉ በኋላና በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ተቀብረው 3ት ዐመት ከተቈጠረ በኋላ በኑዛዜያቸው መሠረት ልጃቸው ራስ መሸሻና የመቅደላ ካህናትና ሕዝብ የንጉሣችንን የዐፄ ቴዎድሮስን ዐፅም በታላቁ ማኅበረ ሥላሴ አምጠተው በክብር አሳረፉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/   #የገዳሙ_መነኰሳት_ሥርዐት *** ገዳሙ ሥርዐተ አበው እጅጉን የሚጠበቅበት፥ ፍቅር እንደ ሸማ የተለበሰበት፥ ምግባረ ትሩፋት የሚዘወተርበት ገዳም ነው፡፡ ለአብነትም፤ **በገዳሙ የሚገኙ መነኰሳት እንደ ዮሐንስ ወገባቸውን በዝናር የሚታጠቁና በዚያ በበርሐ እያረሱና ከፍተኛ ቊጥር ያላቸውን ከብቶች እየጠበቁ፤ ነፍሳቸውን ለሥላሴ አደራ ሰጥተው የሚኖሩ ናቸው፡፡ *የገዳሙ መደበኛ (ከዓመት እስከ ዓመት) ምግብ ከብዙ እህሎች የተቀያየጠው ‹‹መኰሬታ›› (ዳቤ) ሲሆን፤ በተለያዩ ሃገራችን ከምናውቀው መኰሬታ (ዳቤ) ይለያል፤ መኰሬታው የሚጋገረው በድንጋይ ወፍጮ በእጅ በክርትፉ ደቅቆ ሲሆን ፈጽሞ ዱቄት ያልሆነ፥ ያልላመና ወፍጮ ያልነካው ነው፡፡ በዓለም ለሚኖር ሰው ለመመገብ ይከብዳል፡፡ **መጠጣቸው ውኃ ሲሆን አልፎ አልፎ በበዓላ ከኑግ(ከሱፍ) የሚሠራ ጭልቃን ይጠጣሉ፡፡ አብዛኞች የሚመገቡትና የሚጠጡት በቀን ውሎ አንዴ ነው፡፡ ***ሥጋ ትህርምት ነው (ፈጽሞ አይበላም)፤ በዓመት 3ት ቀን (ልደት ጥምቀትና ትንሣኤ) ብቻ ነው የሚበላው፡፡ የመገርመው ግን ገዳሙ ሰፊ መሬት ስላለው በከብት ብዛት (በሃገራችን ግንባር ቀደም ነው)፡፡ እንጀራ መብላት የሚፈልግና የታመመ መነኰስ ካለ ከገዳሙ ጋር አንድነት ወዳለው ወደ ዋታሆ አቦ በመሄድ ነው እንጀራ የሚበላው፡፡ * መነኰሳቱ ለዓመት ከሚሰጣቸው ልብስ ውጪ በራሳቸው አሰፍተውና ገዝተው መልበስ አይችሉም፤ * ቁሪት (የግል ንብረት) አይፈቀድም፤ ማለትም መነኰሳቱ ከሚቆነንላቸው (ከሚሰጣቸው) መኮሪታና ጭልቃ ውጭ ማንኛውንም ተጨማሪ ምግብና መጠጥ (የሚወርድ ውኃም ቢኾን) መመገብና መጠጣት፤ በቤታቸው መርፌም ቢኾን ያለ መጋቢው ፈቃድ ማስቀመጥም ኾነ መጠቀም አይፈቀድም፤ * ማንኛውም ወደ ገዳሙ የሚሄድ ሰው (በየካቲት 27 በጻድቁ ዓምደ ሥላሴ፣ በጥርና በሐምሌ 7 የቅድስት ሥለሴ ክብረ በዓል ቀንና ለቀብር ካልኾነ በስተቀር) ለ፯ት ቀናት የግዝት በር ላይ ደጅ መጥናት ግድ ይለዋል፡፡ **በማኅበረ ሥላሴ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ስለሆነ፤ ወገን፥ ወገን፤ ተለይ፥ ተለይ፤ አጎዶ፥ አጎዶ፤ ጉዞ፥ ጉዞ፤ ሰፈር፥ ሰፈር ሲባሉ በየወገኑና በየጾታው እንዲሁም ወደ ሚታዘዙበት ቦታ ይሄዳሉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የገዳሙ_መፍለስ_መነሳት_መጥፋት_መልማት -ገዳሙ በጠረፍ አካባቢ ከመኖሩ ጋር በተያያዘ ፤ለበርካታ ጊዜያት በየዘመናቱ መቃጠል፣ መዘረፍና የቦንብ ድብደባ ደርሶበታል፤ መናኞች በሰይፍ ተሰይፈውበታል፡፡ ዋና ዋናዎቹን ብናነሣ፤ *አብርሐ ወአጽብሐ ያሠሩትን ቤ/ክ ዮዲት ጉዲት (842-888ዓ.ም.) አቃጠለችው፥ ንዋያተ ቅድሳቱንና ንብረቱን ዘረፈች፡፡ **ዮዲት ያፈረሰችውን በንጉሥ ዐምደ ጽዮን(1268-1277ዓ.ም.) ቤ/ክ መልሶ ተሠራ፡፡ *በእስላም የቱርክ መንግሥት ይረዳ በነበረው ወራሪው አሕመድ ግራኝ /1541-1545ዓ.ም./ ብዙ መነኰሳት ተጨፈጨፉ፥ ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ እንደገና በዐፄ ሠርፀ ድንግል /1553-1587ዓ.ም./ ተቋቋመ፡፡ *በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፡፡ /ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ) *በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን እንግሊዞች የገዳሙን ንብረት መዘበሩ፡፡

/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ ፨ ታቦቱ_ሥላሴ፥ ፨ ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ፥ ፨ የገዳሙ ስም ማኅበረ ሥላሴ፡፡ ፨ በየቀኑ በሁሉም ቤክ በቅዳሴ ላይ ስሙ የሚነሳው ገናናው ገዳም (ብዙዎች ግን የማያውቁት)፡፡ ፨ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ድንቅናዕፁብ ገዳም፡፡ ፨ ገዳሙን ያጠፉ አውሮፕላኖችን በጸሎት የከሰከሱ አባቶች የሚገኙበት የበርካታ ትምህቶችና የጥበብ ማዕክል፤ …. ኢትዮጵያውያን ሁሉ ቢያንስ አንዴ ሊያዩት የሚገባ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ገዳም!!!፡፡ ፨ በዚህች በየካቲት 27 እለት ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወመነኰሳት (ለአቡነ ክፍለ ማርያም፥ ለአቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘቋራ፥ ለ፯ቱ ዘሥላሴ በመባል ለሚጠሩ ቅዱሳን፣ ለዐርከ ሥሉስ /የአርኬና የመልክአ ቊርባን ደራሲ/፤ ….) የኾኑትና ፤ ጽድቃቸውና ቃልኪዳናቸው እንደ ምድር አሸዋ የበዛው፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለመቊጠር የሚያስቸግረው ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ ልደታቸውም እረፍታቸውም ነው፡፡ - እኒህ ጻድቅ የተወለዱት በጎጃም(ሸዋም የሚሉ አሉ) ሲኾን፤ የተወለዱትም ሆነ 104ዓመታት ከኖሩ በኋላ ያረፉበት ቀን በመድኀኔ ዓለም ወርኀዊ በዓል በየካቲት 27 ነው፡፡ - ጻድቁ በተለያዩ ገዳማት በአርድእትነትና ሥርዐተ አበው በማጥናትና በመተግበር ከቆዩ በኋላ፤ ምንኩስናን ከአቡነ ተንሥአ ክርስቶስ ዘትግራይ ተቀብለዋል፤ ኋላም ወደ ታላቁ ገዳም ገዳመ ዋሊ (ገዳመ ዋልድባ) ገብተው ከቆዩ በኋላ ወደ ገዳመ አስቄጥስ በመሄድ ለ18 ዓመታት ከቆዩ በኋላ በስተመጨረሻ ምናኔያቸውን በማኅበረ ሥላሴ አድርገዋል፡፡ * በ1616ዓ.ም. ሱስንዮስ 8,000 ክርስቲያኖችን የካቶሊክን ካልተቀበላችሁ ብሎ ጠዳ ላይ በሰየፈ ጊዜ ሳይፈሩና ሳይፍሩ ለሃይማኖታቸው ከተከራከሩና ጠበቃ ከኾኑት መካከል ግንባር ቀደሙ ናቸው፡፡ (ሌሎችም ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ እኅተ ጴጥሮስ፣ ፍቅርተ ጴጥሮስ፣ ሐራ ድንግል ምዕመነ ድንግል አብረው ይጠቀሳሉ)፡፡ እነዚህም ቅዱሳን ሐዘናቸውን ወደ ፈጣሪያቸው በማድረሳቸው ሱስንዮስ ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ (ተቀሰፈ)፡፡ -  የሱስንዮስ ልጅ ፋሲልም አባቴን ይፈውሱልኝ ብሎ መልእክትን ላከ፤ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና አባ ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ ማርያም ተገኝተው ካቶሊክነቱን ከተወ እሺ ብለው 3ት ሱባኤ ጸልየው ፈወሱት፤ ሱስንዮስም ንሥሐ ገብቶ ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ፡፡ በሰኔ 21 1624ዓ.ም. ‹‹የእስክንድርያ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይመለስ፥ የሮም ካቶሊክ ሃይማኖት ይፍለስ፥ ልጄ ፋሲል ይንገሥ›› ብለው አዋጅ ነገሩ፤ ልጃቸው ፋሲልንም ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ቅብዓ መንግሥት (አፈዋተ መንግሥት) ቀብተው አነገሡት፤ ንጉሡም ለገዳሙ የእርሻ መሬት የሚሆን ጣቁሳ ላይ 44ት ጉልት ጐለተ፥ የገዳሙንም ስም ‹‹ማኅበረ ሥላሴ›› ብሎ ሰየመው፡፡ - ታላቁ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ቀድሞም ከእርሳቸው በፊት የነበረ ቢኾንም፤ በተለያዩ ዘመናት በጠላት የጠፋ ስለነበረ ዳግመኛ ያስፋፉትና እንደ መሶብ ያስባረኩት ናቸው፤ - ከወለዷቸው አንዱ ዐርከ ሥሉስ ከደረሳቸው አንዱ በኾነው በመልክአ ቊርባን ላይ፤ ‹‹ሰላም ለክሙ ጻድቃነ ዛቲ ዕለት ኵልክሙ፤ ዕድ ወአንስት በበአስማቲክሙ፡፡ ቅዱሳነ ሰማይ ወምድር ማኅበረ ሥላሴ አንትሙ፤ ዝክሩነ በጸሎትክሙ በእንተ ማርያም እሙ፤ ተማኅጸነ ለክርስቶስ ሥጋሁ ወደሙ፡፡ በማለት የደረሱለት ሲኾን፤ በዚህም በየቀኑ በቅዳሴ ላይ ከቊርባን በፊት የማኅበሩን ስም የማይጠራ ቤተ ክርስቲያን የለም፡፡ ፨ ብፁዕ አባ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ንብረቱ ገዳም ውስተ ሀቌሁ ቅንአቱ ዘአዲም ያስተጋብእ ጽድቀ ዘእምኵሎሙ ቅዱሳን በጾም ወበጸሎት ሀለወ በክብር ወበሰላም፡፡ /መሐረነ አብ/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (#የሺዎች_ማኅበር)፤ ፨ ምቅዋመ ሥላሴ፡፡ ፨ስለ ገዳሙ አጠቃላይ ሁኔታ፤ *ገዳሙ የሚገኘው በሀገራችን በመተማ በረሃ ደቡባዊ ክፍል፥ ከጎንደር በስተምዕራብ አቅጣጫ (132 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ) ሲሆን፤ ከአ.አ. 901ኪ.ሜ. ርቀት ላይ፤ ከደረቅ ዐባይ ቀበሌ በ4ት ሰዓት የእግር ጕዞ ይገኛል፡፡ የጣቁሳ የቋራና የሱዳን በረሓማው አከባቢዎችም ያዋስኑታል፡፡ *ከፀሐዩ ሐሩር ማየልና ከቆላነቱ የተነሣ ‹‹በደንጊያው ላይ ተልባ ያስቆላል›› እየተባለ የሚነገርለት ነው፡፡ የተለያዩ ዕፅዋትና አራዊት የሚገኙበትም ሲሆን ቦታው በብሔራዊ ደረጃ ጥብቅ ደን ነው፡፡ * የገዳሙ ይዞታ ከ19ሺህ 186 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሲሆን፤ በቦታ ስፋት የሚመስለው ዋልድባ (ዋሊ) ብቻ ነው፡፡ በዚህም ከሃገራችን ገዳማት 2ቱ ታላላቅ ገዳማት እጅግ በጣም ሰፋፊ ይዞታ ያላቸው ገዳማት ናቸው፡፡ * ገዳሙ በ፪ት ትላልቅ ወንዞች (በገንዳ ውኃና ሸንፋ ወንዝ) የተከበበ ነው፡፡ *ገዳሙ በሚገኝበት በረሃ ውስጥ 4ት ተራሮች(አምባዎች) ይገኛሉ፡፡ እነርሱም፤ ድባ(የማኅበረ ሥላሴ ገዳም ያለበት)፣ ከርከመች፣ ኩክቢና ጎርማስ ይባላሉ፡፡ *ገዳሙን በርቀት ሆነው የሚያዋስኑት ታላላቅ ገዳማትም፤ በሰሜን አቅጣጫ ደምጫ፥ በደቡብ ጋንጫ(ዋታሆ አቦ) ናቸው፡፡ *በገዳሙና በአካባቢው ከሚገኙት የተለያዩ ዕጽዋት መካከል (ሰርኪን፥ ሲና፥ የዕጣን ዛፍ/ዋልያ/፥ መቀር፥ ወርካ፥ ክርክራ፥ ሽመል) እና ሌሎችም ልዩ ልዩ ዕጽዋት የሚገኙበት ሲኾን፤ ከዱር አራዊት መካከልም (አንበሳ፥ ነብር፥ አጋዘን፥ ቶራ/ሚዳቋ/፥ ድኩላ፥ አሳማ፥ ጉሬዛ፥ ዝንጀሮ፥ ቀይ ጦጣ፥ የተለያዩ የእባብና የዘንዶ ዝርያዎች) ይገኙበታል፡፡

፨ ቅዱስነትዎ እንኳን አደረስዎ ፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundayS
፨ ቅዱስነትዎ እንኳን አደረስዎ ፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958