uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 380 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 573-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 194-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 380 obunachiga ega bo‘ldi.

06 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 32 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.44% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.50% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 449 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 461 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 20 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 07 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 380
Obunachilar
-424 soatlar
-257 kunlar
+3230 kunlar
Postlar arxiv
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 2027ኛ ዓመት የልደት በዓል አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ #ፎቶው_ላይ_የምትመለከቷቸው_አብያተ_ክርስቲያናት፤ 1)፠፠ #መናገሻ_ጋራ_ልደታ_ለማርያም፤ በአፄ ይስሐቅ ዘመን የተመሠረተች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመስቀላቸው የባረኳት፣ ግማደ መስቀሉ ያረፈባት፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተጠቀሰች ገዳም፡፡ 2)፠፠ #ጎንደር_መካነ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም_ቤተ_ክርስቲያን፡፡ * ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዷ የኾነች፤ አጸዷ ውጡ ውጡ የማያሰኝ ፍጹም መንፈስን፣ ነፍስንና ሥጋን የመመሰጥ ኃይል ያለው ቦታ ነው፡፡ * በስዕለት ሰሚነቷ የአፄ ዮስጦስንም ስዕለት ስለሰማቻቸው፤ አድረሺኝ (ቢያደርሰኝ ቢያደርሳችሁ እየተባለ ዛሬ ሞላው ጎንደር በፍልሰታ ማብቂያ የአድርሺኝ ስዕለቱን እንዲያወጣ መሠረት የኾነች ቤተ ክርስቲያን፡፡ * የ4ቱ ጕኤያት (መጻሕፍተ ትርጓሜያት፤ ብሉያት፣ ሐዲሳት፣ ሊቃወንትና መነኮሳት) ማስመስከሪያ የነበረች፤ አሁንም ይህንን ጕባኤ ለማስጀመር በሒደት ላይ የምትገኝ፡፡ * የታች ቤት ትርጓሜ ጀማሪና መምህር የኾኑት ሊቁ ዐራት ዐይና መምህር ኤስድሮስ ጕባኤ ከፍተው አትሮኖስ ዘርግተው ወንበር ተክለው ያስተማሩባት፤ ውዳሴ ማርያም ዘኀሙስ ‹‹ዳዊት ከቤተ ልሔም ውኃ ምንጭ ይጠጣ ዘንድ ፈለገ… የሚለውን ሲያትቱ ይህችው የቤተ ልሔም ውኃ እንደ ጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ማርያም ጠበል ነች፤ ያቺ የቤተ ልሔም ውኃ ጽምአ ዳዊትን ታረካ ነበርና (አርክታለች)፤ ይህች የልደታ ጠበል ምዕመናንን ከጤና ጽምእ ታረካለችና ትፈውሳለችና፤…. እያሉ ያነሷት፡፡ ዛሬም ድረስ ይህች የልደታ ጠበል በፈዋሽነቷ የታወቀችና ብዙ ሕሙማንን የሚፈወሱባት ናት፡፡ * በርካታ ለሃራችንና ለዓለማችን ትላልቅ ሥራን የሠሩ ሊቃውንትን ያፈራች፡፡ * የጎንደር ልደታ በደርቡሽ ጎንደር ስትቃጠልና ስትፈራርስ የመጀመሪያ ቤተ ክርስቲያኗም ፈርሷል (የመጀመሪያው ፎቶ የሚያሳየው ደርቡሾች ካፈረሱት የተረፉት አምዶችን ነው)፡፡ 3) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ማኅደረ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም፤ በ1916ዓ.ም. የተመሠረተች፡፡ 4) ፠፠ #መቀሌ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 5) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ደብረ_ዕንቊ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 6) ፠፠ #ሚዛን_አማን_ቅድስት_ልደታ__ቤ.ክ. 7) ፠፠ኢሉባቦር__ጮራ__ደብረ__ብርሃን__ቅዱስ__ሚካኤል__ወልደታ__ቤ.ክ. /#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 2027ኛ ዓመት የልደት በዓል አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ #ፎቶው_ላይ_የምትመለከቷቸው_አብያተ_ክርስቲያናት፤ 1)፠፠ #መናገሻ_ጋራ_ልደታ_ለማርያም፤ በአፄ ይስሐቅ ዘመን የተመሠረተች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመስቀላቸው የባረኳት፣ ግማደ መስቀሉ ያረፈባት፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተጠቀሰች ገዳም፡፡ 2)፠፠ #ጎንደር_መካነ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም_ቤተ_ክርስቲያን፡፡ * ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዷ የኾነች፤ አጸዷ ውጡ ውጡ የማያሰኝ ፍጹም መንፈስን፣ ነፍስንና ሥጋን የመመሰጥ ኃይል ያለው ቦታ ነው፡፡ * በስዕለት ሰሚነቷ የአፄ ዮስጦስንም ስዕለት ስለሰማቻቸው፤ አድረሺኝ (ቢያደርሰኝ ቢያደርሳችሁ እየተባለ ዛሬ ሞላው ጎንደር በፍልሰታ ማብቂያ የአድርሺኝ ስዕለቱን እንዲያወጣ መሠረት የኾነች ቤተ ክርስቲያን፡፡ * የ4ቱ ጕኤያት (መጻሕፍተ ትርጓሜያት፤ ብሉያት፣ ሐዲሳት፣ ሊቃወንትና መነኮሳት) ማስመስከሪያ የነበረች፤ አሁንም ይህንን ጕባኤ ለማስጀመር በሒደት ላይ የምትገኝ፡፡ * የታች ቤት ትርጓሜ ጀማሪና መምህር የኾኑት ሊቁ ዐራት ዐይና መምህር ኤስድሮስ ጕባኤ ከፍተው አትሮኖስ ዘርግተው ወንበር ተክለው ያስተማሩባት፤ ውዳሴ ማርያም ዘኀሙስ ‹‹ዳዊት ከቤተ ልሔም ውኃ ምንጭ ይጠጣ ዘንድ ፈለገ… የሚለውን ሲያትቱ ይህችው የቤተ ልሔም ውኃ እንደ ጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ማርያም ጠበል ነች፤ ያቺ የቤተ ልሔም ውኃ ጽምአ ዳዊትን ታረካ ነበርና (አርክታለች)፤ ይህች የልደታ ጠበል ምዕመናንን ከጤና ጽምእ ታረካለችና ትፈውሳለችና፤…. እያሉ ያነሷት፡፡ ዛሬም ድረስ ይህች የልደታ ጠበል በፈዋሽነቷ የታወቀችና ብዙ ሕሙማንን የሚፈወሱባት ናት፡፡ * በርካታ ለሃራችንና ለዓለማችን ትላልቅ ሥራን የሠሩ ሊቃውንትን ያፈራች፡፡ * የጎንደር ልደታ በደርቡሽ ጎንደር ስትቃጠልና ስትፈራርስ የመጀመሪያ ቤተ ክርስቲያኗም ፈርሷል (የመጀመሪያው ፎቶ የሚያሳየው ደርቡሾች ካፈረሱት የተረፉት አምዶችን ነው)፡፡ 3) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ማኅደረ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም፤ በ1916ዓ.ም. የተመሠረተች፡፡ 4) ፠፠ #መቀሌ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 5) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ደብረ_ዕንቊ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 6) ፠፠ #ሚዛን_አማን_ቅድስት_ልደታ__ቤ.ክ. 7) ፠፠ኢሉባቦር__ጮራ__ደብረ__ብርሃን__ቅዱስ__ሚካኤል__ወልደታ__ቤ.ክ. /#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

፠ ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ሲያርፍ የ70 ዓመት አረጋዊ ነበረ፡፡ ከ30 ዓመታት በላይ በዘለቀ መዋዕለ ስብከቱ ለዓለም ሁሉ የምስራች የሚሆን የወንጌልን ቃል ከመጻፉ ባሻገር ከሐዋርያዊ ተልዕኳቸው የተነሣ ብርሃናተ ዓለም ከተባሉ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በብዙ አህጉረ ስብከት ተዘዋውሮ በማስተማሩና ይልቁንም የጥንት ግሪክ ሥልጣኔ ተስፋፍቶባትና የሮማ ሥርወ መንግሥት ቁልፍ የፓለቲካና የንግድ መዲና በነበረችው እስክንድርያ በሰማዕትነት እስካረፈባት ቅጽበት ድረስ በአንደበቱም በሕይወቱም በክብሩና በመከራው ሁሉ በማስተማር አይሁድን ከይሁዲነት ወደ ክርስቲያንነት ፥ አረማውያንን ከአምልኮ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሰ እንዲሁም በጸሎታቸው የሚጠብቁ፥ በትሩፋታቸው የጽድቅን ዋጋ የሚያሰጡ የባሕታውያን አባት አባ ጳውሊን፣ የመነኰሳት አባት አባ እንጦንስን፣ አባ ጳኩሚስ እና አባ ሰራብዮንን፤ መናፍቃንን ተከራክረው የረቱ ፥ ሃይማኖትን ያቀኑ ቅዱስ እለእስክንድሮስን ፥ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊን ፥ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያን፥ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪትና ቅዱስ ዲዮስቆሮስን የመሳሰሉ ኦሮቶዶክሳውያን ሊቃውንትንና እስከ ዛሬም መከራ ሳይበግራቸው፥ ሞትና ግርፋታቸውን እንደ ክብር ቈጥረው፥ በሃይማኖታቸው ፀንተው የሚኖሩ የጸኑ ምእመናንን ያፈራች አንፀባራቂ ስም ያላት ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን ያቋቋመ ሐዋርያ በመሆኑ ዳግመኛም ከ4ኛ ክ/ዘ/ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን እስከ አቡነ ቄርሎስ 20ኛ ክ/ዘ/ ድረስ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በክህነት የመገቡ 111 ጳጳሳት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ያቋቋማት የዚህችው ቤተክርስቲያን ፍሬዎች በመሆናቸውና ትምህርታችን ከትምህርታቸው ፥ ሥርዐታችን ከሥርዓታቸው የተስማማ ፥ የተግባባ በመሆኑ “ማርቆስ አባታችን ፥ እስክንድርያ እናታችን” ማለት በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ የተለመደ ነበር፥ ታሪክ ነውና ዛሬም ቢሆን ቤተክርስቲያናችን ሙሉ በሙሉ ከግብጽ ቤተክርስቲያን ጥገኝነት ተላቃ በኢትዮጵያውያን ጳጳሳት ብትመራም ይህ እውነታ ግን የሚዘነጋ አይደለም፡፡ /#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem ምንጭ፤ በመምህር ኅሩይ ኤርምያስ ለለቩርዝቡርግ ቅዱስ ማርቆስ ሰ/ት/ቤት ዓመታዊ በዓል የተዘጋጀ ታኅሣስ ፳፻ወ፬ ዓ.ም. “የአጤ ኃይለ ሥላሴ ታሪክ” ከሚለው መጽሐፋቸው ገጽ 1132 ላይ ፠ በፎቶ የምትመለከቷቸው አብያተ ክርስቲያናት፤ * ሰላ ድንጋይ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአፄ ምኒልክና የተሠራና የአቡነ ማቴዎስ መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ በልዩ አሠራር በ42 ቆመ ብእሲ (ዐምድ) የታነጸ፡፡ * መናገሻ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአቡነ ማቴዎስ የተሠራና መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ ውጭው ክብ ውስጡ ግን ከሌሎች ክብ አብያተ ክርስቲያናት ልዩና ድንቅ በሆነ አሠራርና ሥዕላት የተሞላ፡፡ * ጎጃም ደብረ ማርቆስ፤ * መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ፤ አፄ ኀይለ ሥላሴ ከቤተ መንግሥታቸው ላይ ቦታ ቀንሰው ያነጹት ቤ.ክ.፡፡

#ቅዱስ_ማርቆስ_ወንጌላዊ_ሚያዝያ_፴ ማርቆስ የሚለው ስም 3ት ፍቺዎች አሉት ንብ፣ አንበሳና ካህን:: ሀ) *ንብ የሚለው ፍቺ የተሰጠው ንብ አበባ ካለው ተክል ሁሉ ቀስማ ማር እንድትሠራ እርሱም ቀድሞ ከጌታ ኋላም ከጌታ የተማርኩት ይበቃኛል ሳይል ከሐዋርያት ተምሮ ደገኛይቱን ወንጌልን በማስተማሩና በመጻፉ ነው፤ ለ) *አንበሳ መባሉ አንበሳ እንስሳት አራዊትን በክርኑ እንዲሰብር፤ በግብጽ ይመለኩ የነበሩ በእንስሳ አምሳል የተሠሩ ጣዖታትን በወንጌል ቃል ኃይልነት በማጥፋቱ ነው፡፡ ሐ. *ካህን የሚለው ትርጕም ደግሞ በሐዋ. 14፥13 “ወአምጽኡ ማሬ ዘድዮስ” ተብሎ ከተመዘገበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ የተወረሰ ነው:: ፠ ማርቆስ ከመባሉ በፊት ዮሐንስ ይባል የነበረ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድዕት ነው፤ ሐዋ. 12፥12፡፡ አባቱ አርስጦቦሎስ እናቱ ማርያም ይባላሉ፡፡ እናቱ ማርያም በጌታ ትምህርት አምነው ሲከተሉትና ሲያገለግሉት ከነበሩት ደጋግ ሴቶች አንዷ ስትሆን ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ቤቷን ለወንጌል አገልግሎት ሰጥታ ሐዋርያት በዚያ ተሰብስበው ለጸሎት ይተጉ ነበር፥ ጌታ ባረገ በ10ኛው ቀን (በተነሣ በ50ኛው ቀን) ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ሳሉ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትም በዚሁ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ውስጥ ነው፡፡ ሐዋ. 2፥1 ፤ 12፥12፡፡ ፠ የራሱን ሀገረ ስብከት ይዞ ማስተማር ከመጀመሩ በፊት ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያትን እየተከተለ ይማር ፥ በተልእኮም ይራዳቸው ነበር:: ከቅዱስ ጳውሎስ መጠራት በኋላ ጳውሎስንና አጎቱ በርናባስን ተከትሎ በአንጾኪያ ፤ ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትሎ በሮም አስተምሯል፤ እነርሱም በመልእክቶቻቸው “ማርቆስ ሰላም ይላችኋል” እያሉ አንስተውታል:: ሐዋ. 12፥25፣ ቈላ. 4፥10፣ 1ኛ ጴጥ. 5፥13 ፠ በሮም ተልእኮው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ ከፍጹምነት መድረሱን ዐውቆ ጵጵስና ሾሞ ከሀገረ ስብከቱ ግብጽን ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጠው፡፡ እርሱም ሊያስተምር ሄዶ ወደከተማ ሊገባ ሲቃረብ የጫማው ጠፍር ተበጥሶበት አንያኖስ ወደሚባል ጫማ ሰፊ ሄደና ስፋልኝ ብሎ ሰጠው። አንያኖስ ጫማውን ተቀብሎ ሲሰፋ መስፊያው እጁን ወግቶት “ኢስ ታኦስ” ብሎ ጮኸ “አሐዱ እግዚአብሔር” ማለት ነው፤ የጠራኸውን ታውቀዋለህን? አለው፥ ሲሉ ሰምቼ እንጂ ያስተማረኝስ የለም አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ፈቃደኛነቱን አይቶ አስተማረው አንያኖስም ከነቤተሰቦቹ አምኖ ተጠመቀ:: ፠ ከዚህ በኋላ አንያኖስን አስከትሎ በከተማ እየተዘዋወረ ያስተምር ጀመረ፤ ሕዝቡም ትምህርቱን ሰምተው ፥ ተአምራቱን አይተው አመኑ፥ ተጠመቁ፤ አብያተ ጣዖታቱንም አፈራርሰው አብያተ ክርስቲያናትን ሠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የጣዖታቱ አገልጋዮች የለመዱት ቢቀርባቸው በጠላትነት ተነሡበት:: ምእመናኑ ተሰብስበው አባታችን እንድትለየን አንሻም፤ ነገር ግን ገነውተ ጣዖታቱ በጠላትነት ተነሥተውብሀልና ቁጣቸው እስኪበርድ ጥቂት ጊዜ ወደ ሌላ ሥፍራ ሄደህ ቆይ አሉት:: አንያኖስን ኤጲስቆጶስ ልጆቹን ቄስና ዲያቆን አድርጎ ሾሞላቸው፤ በባርቃና በሌሎች 5 አውራጃዎች እየሰበከ ቅዱስ ጴጥሮስን ለመጠየቅ ወደሮም ሄደ፤ በዚያ ሆኖ በስብከቱ ያመኑ የእስክንድርያ ምእመናን የተማሩትን እንዳይዘነጉ የማርቆስ ወንጌል ተብሎ የሚታወቀውን ወንጌል በሮማይስጥ ቋንቋ ጽፎ ልኮላቸዋል:: ዘመኑ ጌታ ካረገ 11ኛው ሲፈጸም 12ኛው ሲጀመር ፥ ቀላውዴዎስ ቄሳር በነገሠ በ4ኛው ዓመት /45-46ዓ.ም. ባለው ጊዜ/ ነው:: ፠ ከጥቂት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ግብጽ ተመለሰ፥ ምእመናኑ በቊጥር በዝተው፥ በእምነት ጐልምሰው አግኝቷተቸው ደስ ብሎት እያስተማራቸው አብሯቸው ጥቂት ጊዜ ቆየ:: በዓለ ትንሣኤን በሚያከብሩበት ቀን አምልኮ ጣዖት ከስሞ አምልኮተ እግዚአብሔር በመስፋፋቱ ምቀኝነት ያደረባቸው ጣዖታውያን ሊጣሉት መጡ፤ ምእመናኑ አባታችን ሽሽ አሉት፤ እንግዲህስ በጌታዬና በአምላኬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ወንጌል ክብር መከራ ልቀበል እንጂ ልሸሽ አይገባኝም፥ አልሸሽም አለ፡፡ እንደ ላም በአንገቱ ገመድ አስረው በረሀ ለበረሀ ሲጐትቱት ዋሉ ፥ ሥጋው በእሾህ በጋሬጣ ተቀረደደ፡፡ ወደጌታ ቢያመለክት፤ ስለተቀበልኸው መከራ ክብርህን ከ12ቱ ደቀመዛሙርቴ ክብር አንድ አድርጌልሀለሁ፤ በስምህ የተማፀነኝንም እምርልሀለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገብቶለት ነፍሱን በቃለ አቅርንት፥ በይባቤ መላእክት አሳርጓታል:: በሞቱ ያልረኩት ጣዖታውያኑ ከሞተም በኋላ ሥጋውን ለማቃጠል ሽተው እንጨት ሰበሰቡ የሚያቀጣጥልላቸውን ዝፍትም በከመሩት እንጨት ላይ አርከፈከፉ፤ ጌታ ግን ይህን እንዲያደርጉ ዕድል አልሰጣቸውም ድንገት ታላቅ ነጐድጓድ ሆነ ፥ የተከማቹበት ሥፍራ ተናወጸ፥ የፀሐይም ብርሃን ተሠወረባቸው፤ በዚህ ጊዜ ምን መጣብን ብለው ማቃጠሉን ትተው ሸሽተዋል፡፡ ኋላ ግን ምእመናን በመብረቅ ጸዳል ተከብቦ አግኝተው በክብር ሥጋውን በአሌክሳንድርያ ቀብረውታል:: ፠ በዚህ ቦታ ተቀብሮ ለብዙ ዘመን ከቆየ በኋላ በ820 ዓ.ም ሁለት የቬኑስ ነጋድያን አጽሙን በድብቅ ከተቀበረበት አስወጥተው ወደ ቬነስ ወሰዱት፤ በዚህ ከተማ በሚገኘው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አኑረውት ቦታው የበላይ ቅዱስ ሆኖ በክብር ይኖር ነበር። ስለሆነም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰጣት በየጊዜው ከመጠየቅ አልቦዘነችም ነበር፡፡ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም የሮማው ርዕሰ ሊቀ ጳጳስ ጳውሎስ 6ኛ ስለፈቀዱ፤ ቅዱሱ ባረፈ በ1900 ፥ በተወሰደ በ1140 ዓመት አጽሙ ሰኔ 17 ቀን 1960 ዓ.ም. ፈልሶ ወደ ጥንተ ቦታው ለመመለስ በቃ፡፡ ሲመለስም ጃንሆይም በስፍራው ተገኝተዋል፡፡ /#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ማርቆስ የሚለው ስም 3ት ፍቺዎች አሉት ንብ፣ አንበሳና ካህን:: ሀ) *ንብ የሚለው ፍቺ የተሰጠው ንብ አበባ ካለው ተክል ሁሉ ቀስማ ማር እንድትሠራ እርሱም ቀድሞ ከጌታ ኋላም ከጌታ የተማርኩት ይበቃኛል ሳይል ከሐዋርያት ተምሮ ደገኛይቱን ወንጌልን በማስተማሩና በመጻፉ ነው፤ ለ) *አንበሳ መባሉ አንበሳ እንስሳት አራዊትን በክርኑ እንዲሰብር፤ በግብጽ ይመለኩ የነበሩ በእንስሳ አምሳል የተሠሩ ጣዖታትን በወንጌል ቃል ኃይልነት በማጥፋቱ ነው፡፡ ሐ. *ካህን የሚለው ትርጕም ደግሞ በሐዋ. 14፥13 “ወአምጽኡ ማሬ ዘድዮስ” ተብሎ ከተመዘገበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ የተወረሰ ነው:: ፠ ማርቆስ ከመባሉ በፊት ዮሐንስ ይባል የነበረ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድዕት ነው፤ ሐዋ. 12፥12፡፡ አባቱ አርስጦቦሎስ እናቱ ማርያም ይባላሉ፡፡ እናቱ ማርያም በጌታ ትምህርት አምነው ሲከተሉትና ሲያገለግሉት ከነበሩት ደጋግ ሴቶች አንዷ ስትሆን ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ቤቷን ለወንጌል አገልግሎት ሰጥታ ሐዋርያት በዚያ ተሰብስበው ለጸሎት ይተጉ ነበር፥ ጌታ ባረገ በ10ኛው ቀን (በተነሣ በ50ኛው ቀን) ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ሳሉ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትም በዚሁ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ውስጥ ነው፡፡ ሐዋ. 2፥1 ፤ 12፥12፡፡ ፠ የራሱን ሀገረ ስብከት ይዞ ማስተማር ከመጀመሩ በፊት ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያትን እየተከተለ ይማር ፥ በተልእኮም ይራዳቸው ነበር:: ከቅዱስ ጳውሎስ መጠራት በኋላ ጳውሎስንና አጎቱ በርናባስን ተከትሎ በአንጾኪያ ፤ ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትሎ በሮም አስተምሯል፤ እነርሱም በመልእክቶቻቸው “ማርቆስ ሰላም ይላችኋል” እያሉ አንስተውታል:: ሐዋ. 12፥25፣ ቈላ. 4፥10፣ 1ኛ ጴጥ. 5፥13 ፠ በሮም ተልእኮው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ ከፍጹምነት መድረሱን ዐውቆ ጵጵስና ሾሞ ከሀገረ ስብከቱ ግብጽን ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጠው፡፡ እርሱም ሊያስተምር ሄዶ ወደከተማ ሊገባ ሲቃረብ የጫማው ጠፍር ተበጥሶበት አንያኖስ ወደሚባል ጫማ ሰፊ ሄደና ስፋልኝ ብሎ ሰጠው። አንያኖስ ጫማውን ተቀብሎ ሲሰፋ መስፊያው እጁን ወግቶት “ኢስ ታኦስ” ብሎ ጮኸ “አሐዱ እግዚአብሔር” ማለት ነው፤ የጠራኸውን ታውቀዋለህን? አለው፥ ሲሉ ሰምቼ እንጂ ያስተማረኝስ የለም አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ፈቃደኛነቱን አይቶ አስተማረው አንያኖስም ከነቤተሰቦቹ አምኖ ተጠመቀ:: ፠ ከዚህ በኋላ አንያኖስን አስከትሎ በከተማ እየተዘዋወረ ያስተምር ጀመረ፤ ሕዝቡም ትምህርቱን ሰምተው ፥ ተአምራቱን አይተው አመኑ፥ ተጠመቁ፤ አብያተ ጣዖታቱንም አፈራርሰው አብያተ ክርስቲያናትን ሠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የጣዖታቱ አገልጋዮች የለመዱት ቢቀርባቸው በጠላትነት ተነሡበት:: ምእመናኑ ተሰብስበው አባታችን እንድትለየን አንሻም፤ ነገር ግን ገነውተ ጣዖታቱ በጠላትነት ተነሥተውብሀልና ቁጣቸው እስኪበርድ ጥቂት ጊዜ ወደ ሌላ ሥፍራ ሄደህ ቆይ አሉት:: አንያኖስን ኤጲስቆጶስ ልጆቹን ቄስና ዲያቆን አድርጎ ሾሞላቸው፤ በባርቃና በሌሎች 5 አውራጃዎች እየሰበከ ቅዱስ ጴጥሮስን ለመጠየቅ ወደሮም ሄደ፤ በዚያ ሆኖ በስብከቱ ያመኑ የእስክንድርያ ምእመናን የተማሩትን እንዳይዘነጉ የማርቆስ ወንጌል ተብሎ የሚታወቀውን ወንጌል በሮማይስጥ ቋንቋ ጽፎ ልኮላቸዋል:: ዘመኑ ጌታ ካረገ 11ኛው ሲፈጸም 12ኛው ሲጀመር ፥ ቀላውዴዎስ ቄሳር በነገሠ በ4ኛው ዓመት /45-46ዓ.ም. ባለው ጊዜ/ ነው:: ፠ ከጥቂት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ግብጽ ተመለሰ፥ ምእመናኑ በቊጥር በዝተው፥ በእምነት ጐልምሰው አግኝቷተቸው ደስ ብሎት እያስተማራቸው አብሯቸው ጥቂት ጊዜ ቆየ:: በዓለ ትንሣኤን በሚያከብሩበት ቀን አምልኮ ጣዖት ከስሞ አምልኮተ እግዚአብሔር በመስፋፋቱ ምቀኝነት ያደረባቸው ጣዖታውያን ሊጣሉት መጡ፤ ምእመናኑ አባታችን ሽሽ አሉት፤ እንግዲህስ በጌታዬና በአምላኬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ወንጌል ክብር መከራ ልቀበል እንጂ ልሸሽ አይገባኝም፥ አልሸሽም አለ፡፡ እንደ ላም በአንገቱ ገመድ አስረው በረሀ ለበረሀ ሲጐትቱት ዋሉ ፥ ሥጋው በእሾህ በጋሬጣ ተቀረደደ፡፡ ወደጌታ ቢያመለክት፤ ስለተቀበልኸው መከራ ክብርህን ከ12ቱ ደቀመዛሙርቴ ክብር አንድ አድርጌልሀለሁ፤ በስምህ የተማፀነኝንም እምርልሀለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገብቶለት ነፍሱን በቃለ አቅርንት፥ በይባቤ መላእክት አሳርጓታል:: በሞቱ ያልረኩት ጣዖታውያኑ ከሞተም በኋላ ሥጋውን ለማቃጠል ሽተው እንጨት ሰበሰቡ የሚያቀጣጥልላቸውን ዝፍትም በከመሩት እንጨት ላይ አርከፈከፉ፤ ጌታ ግን ይህን እንዲያደርጉ ዕድል አልሰጣቸውም ድንገት ታላቅ ነጐድጓድ ሆነ ፥ የተከማቹበት ሥፍራ ተናወጸ፥ የፀሐይም ብርሃን ተሠወረባቸው፤ በዚህ ጊዜ ምን መጣብን ብለው ማቃጠሉን ትተው ሸሽተዋል፡፡ ኋላ ግን ምእመናን በመብረቅ ጸዳል ተከብቦ አግኝተው በክብር ሥጋውን በአሌክሳንድርያ ቀብረውታል:: ፠ በዚህ ቦታ ተቀብሮ ለብዙ ዘመን ከቆየ በኋላ በ820 ዓ.ም ሁለት የቬኑስ ነጋድያን አጽሙን በድብቅ ከተቀበረበት አስወጥተው ወደ ቬነስ ወሰዱት፤ በዚህ ከተማ በሚገኘው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አኑረውት ቦታው የበላይ ቅዱስ ሆኖ በክብር ይኖር ነበር። ስለሆነም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰጣት በየጊዜው ከመጠየቅ አልቦዘነችም ነበር፡፡ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም የሮማው ርዕሰ ሊቀ ጳጳስ ጳውሎስ 6ኛ ስለፈቀዱ፤ ቅዱሱ ባረፈ በ1900 ፥ በተወሰደ በ1140 ዓመት አጽሙ ሰኔ 17 ቀን 1960 ዓ.ም. ፈልሶ ወደ ጥንተ ቦታው ለመመለስ በቃ፡፡ ሲመለስም ጃንሆይም በስፍራው ተገኝተዋል፡፡ ፠ ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ሲያርፍ የ70 ዓመት አረጋዊ ነበረ፡፡ ከ30 ዓመታት በላይ በዘለቀ መዋዕለ ስብከቱ ለዓለም ሁሉ የምስራች የሚሆን የወንጌልን ቃል ከመጻፉ ባሻገር ከሐዋርያዊ ተልዕኳቸው የተነሣ ብርሃናተ ዓለም ከተባሉ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በብዙ አህጉረ ስብከት ተዘዋውሮ በማስተማሩና ይልቁንም የጥንት ግሪክ ሥልጣኔ ተስፋፍቶባትና የሮማ ሥርወ መንግሥት ቁልፍ የፓለቲካና የንግድ መዲና በነበረችው እስክንድርያ በሰማዕትነት እስካረፈባት ቅጽበት ድረስ በአንደበቱም በሕይወቱም በክብሩና በመከራው ሁሉ በማስተማር አይሁድን ከይሁዲነት ወደ ክርስቲያንነት ፥ አረማውያንን ከአምልኮ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሰ እንዲሁም በጸሎታቸው የሚጠብቁ፥ በትሩፋታቸው የጽድቅን ዋጋ የሚያሰጡ የባሕታውያን አባት አባ ጳውሊን፣ የመነኰሳት አባት አባ እንጦንስን፣ አባ ጳኩሚስ እና አባ ሰራብዮንን፤ መናፍቃንን ተከራክረው የረቱ ፥ ሃይማኖትን ያቀኑ ቅዱስ እለእስክንድሮስን ፥ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊን ፥ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያን፥ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪትና ቅዱስ ዲዮስቆሮስን የመሳሰሉ ኦሮቶዶክሳውያን ሊቃውንትንና እስከ ዛሬም መከራ ሳይበግራቸው፥ ሞትና ግርፋታቸውን እንደ ክብር ቈጥረው፥ በሃይማኖታቸው ፀንተው የሚኖሩ የጸኑ ምእመናንን ያፈራች አንፀባራቂ ስም ያላት ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን ያቋቋመ ሐዋርያ በመሆኑ ዳግመኛም ከ4ኛ ክ/ዘ/ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን እስከ አቡነ ቄርሎስ 20ኛ ክ/ዘ/ ድረስ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በክህነት የመገቡ 111 ጳጳሳት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ያቋቋማት የዚህችው ቤተክርስቲያን ፍሬዎች በመሆናቸውና

ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳ
+3
ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳሙን ደበደበ፤ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ የተሠራውንም የውኃ ታንከር መታ፡፡ ወዲያው የገዳሙ አበው ኀይልነ ሥላሴ፥ ወጸወንነ ሥላሴ፥ በሥመ ሥላሴ እደቀጠቅጥ ከይሴ፡፡ …. ጸሎት ወደ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና ወደ ቅድስት ሥላሴ አቀረቡ፡፡ በጸሎታቸው ተአምራትም ወዲያው 2ቱም አውሮፕላኖች ከገዳሙ ክልል ሳይወጡ ወድቀው ተከሰከሱ፤ ዶግ ዐምድ ሆኑ፡፡ ዛሬ ለታሪክ መዘክርነት፤ የጻድቁንን የአበውን ተአምራት ለማስታወሻነት በገዳሙ ግዝት በር ላይ የአውሮፕላኖቹ ስብርባሪዎች ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳ
+3
ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳሙን ደበደበ፤ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ የተሠራውንም የውኃ ታንከር መታ፡፡ ወዲያው የገዳሙ አበው ኀይልነ ሥላሴ፥ ወጸወንነ ሥላሴ፥ በሥመ ሥላሴ እደቀጠቅጥ ከይሴ፡፡ …. ጸሎት ወደ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና ወደ ቅድስት ሥላሴ አቀረቡ፡፡ በጸሎታቸው ተአምራትም ወዲያው 2ቱም አውሮፕላኖች ከገዳሙ ክልል ሳይወጡ ወድቀው ተከሰከሱ፤ ዶግ ዐምድ ሆኑ፡፡ ዛሬ ለታሪክ መዘክርነት፤ የጻድቁንን የአበውን ተአምራት ለማስታወሻነት በገዳሙ ግዝት በር ላይ የአውሮፕላኖቹ ስብርባሪዎች ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳ
+3
ሚያዝያ 27ት የድል ቀንን ስናስብ፤ የማይረሳው የማኅበረ ሥላሴ አበው ተአምር፡፡ ጣሊያን በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደለመደው በታላቁ ገዳማችን ማኅበረ ሥላሴ ላይ 2ት የጦር አውሮፕላኖችን ልኮ ገዳሙን ደበደበ፤ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ የተሠራውንም የውኃ ታንከር መታ፡፡ ወዲያው የገዳሙ አበው ኀይልነ ሥላሴ፥ ወጸወንነ ሥላሴ፥ በሥመ ሥላሴ እደቀጠቅጥ ከይሴ፡፡ …. ጸሎት ወደ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና ወደ ቅድስት ሥላሴ አቀረቡ፡፡ በጸሎታቸው ተአምራትም ወዲያው 2ቱም አውሮፕላኖች ከገዳሙ ክልል ሳይወጡ ወድቀው ተከሰከሱ፤ ዶግ ዐምድ ሆኑ፡፡ ዛሬ ለታሪክ መዘክርነት፤ የጻድቁንን የአበውን ተአምራት ለማስታወሻነት በገዳሙ ግዝት በር ላይ የአውሮፕላኖቹ ስብርባሪዎች ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ፠ ፋሺስት ኢጣልያ አዲስ አበባን ሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም በዛሬዋ እለት አዲስ አበባን ያዘ፡፡ በአርበኞችና በሕዝቡ ታላቅ ተጋድሎ ሚያዝያ 27 ቀን 1933ዓ.ም ደግሞ ድሉ ተበሰረ፡፡ ፠ ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ከስደት መልስ መናገሻ ከተማቸው ሚያዝያ27 ቀን ገብተው የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከማውለብለባቸው አራት ወር ግድም በፊት ጥር 12 ቀን ሱዳን ድንበርን ተሻግረው ኢትዮጵያ ገብተው ያውለበለቡት ኦሜድላ ላይ ነበር ፡፡ #በጣሊያን_ወረራ_ወቅት_አስተዋጽዖ_ካደረጉት_መካከል_ዐበይቶቹ_ገዳማትና_አድባራት፤ #ከካህናት፡፡ ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል፤  ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡  እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460,770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746,800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤  300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤  2,000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣  በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡ ፠ይህንን እኩይ ተግሯን በግንባር ቀደምትነት የተፋለሟት፤ ዐበይቶቹም፤ ፠ የ፳ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕታት #ብፁዕ_አቡነ_ጴጥሮስ_(ሐምሌ 22/1929 ዓ.ም. መሐል አ.አ ላይ በስምንት ጥይት ያረፉት)ና #ብፁዕ_አቡነ_ሚካኤል_ (ኅዳር 24 ቀን 1929 ዓ.ም በኢሉባቦር ጎሬ ላይ በግፍ የተገደሉት) ፠ ‹‹በተንቤንና በአሸንጌ ሐይቅ ጦርነት›› በታኅሣሥ 18 ቀን 1928 ዓ.ም ከሞሶሎኒ ጋር ኢትዮጵያውያን ዘመናዊ ባልሆኑ መሣሪያዎች ድል ያደረጉት፤ ጦር አዛዣችን የነበሩት ልዑል ራስ ካሳ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጦር ድል በማድረጉ ፋሺስት የኬሚካል ጥቃት ፈጸመ፡፡ በዚያን ጊዜ ያለቁት 700,00 የሚደርሱ ናቸው፡፡ ፠ ጣሊያንን አውግዘው በታኅሣሥ 7/1928 ዓ.ም ሲሰየፉ፤ ከአንገታቸው ደም፥ ወተትና ውኃ የወጣው #ታላቁ_ሊቅ_አቡነ_ክፍሌ፡፡ ፠ በግንቦት 28/1929 ዓ.ም. ቊጥራቸው 2,200 የሚሆኑ በግፍ የተጨፈጨፉ #የደብረ_ሊባኖስ_መነኰሳት፡፡ ፠ በግንቦት 29/ 1929 ዓ.ም በቅዳሴ ላይ እንዳሉ የታረዱና ደመና የሸፈናቸው 43 #የአቡነ_ዜና_ማርቆስ_መነኰሳት፡፡ ፠ በሰኔ 12/ 1929 ዓ.ም በማስታኮት ላይ እያሉ የተገደሉ አስከሬናቸውን ሳይቀር በአካፋ የተሰቃየው 211 #የዝቋላ_መነኰሳት፡፡ ፠ በጥቅምት 17/1929 ዓ.ም የታረዱ 2116 የሆኑ #የደብረ_ዳሞ_መነኰሳት፡፡ ፠ በሰኔ 3/1929 ዓ.ም 60 የታረዱ #የምድረ_ከብድ_መነኰሳት፡፡ ፠ በሰኔ 15/ 1929 ዓ.ም የታረዱ፤ በዚህም አንበሶች ከጫካ ወጥተው ያለቀሱላቸው፤ 91 የሚሆኑ #የአሰቦት_መነኰሳት፡፡ ፠ በኅዳር 25/ 1929 ዓ.ም የታረዱ፤ ሲታረዱም ብርሃንም የወረደላቸው፤ 143 #የአዲስ_ዓለም_ካህናትና_መነኰሳት፡፡ ፠ በየካቲት 12/1929 ዓ.ም ከ30 ሺ በላይ በአካፋ ሳይቀር የተጨፈጨፉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፡፡ ፠ በመጋቢት 16/1929 ዓ.ም. ከላይ በቦንብ የውሃ ገንዳውን ጭምር፣ ከታች በመትረየስ የተፈጁት 515 #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም መነኰሳት፡፡ የበቁ አባቶችም በጸሎታቸውም አውሮፕላኗን የከሰከሷት፡፡ ፠ በመጋቢት 17/1929 ዓ.ም የታረዱ ብዛታቸው በውል ያልታወቁ #የደብረ_ዓባይ_ገዳም መነኰሳት፡፡ ፠ በሚያዝያ 18 ና ሚያዝያ 20/1929 ዓ.ም የታረዱ 363 #የመርጦ_ለማርያምና_የተድባበ_ማርያም ካህናትና መነኰሳት፡፡ ፠ በሐምሌ 29/1929 ዓ.ም. እየተለቀሙ እንዲታሰሩ ከተደረገ በኋላ ግማሾቹ የተሰፉትና ግማሾቹ ደግሞ በግዞት የተወሰዱት #የጎንደር_ሊቃውንት፡፡ ፠ በየካቲት 18/1929 ዓ.ም. የተሠዉት የአዲስ አበባ #የካ_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና ካህናት አባቶች፡፡ ፠ በየካቲት 20/1929 ዓ.ም #በአ.አ ከተማ ያሉ በተለያዩ ገዳማትና አድባራት የሚገኙ ታላላቅ ሊቃውንት ተለቅመው እንዲሰበሰቡ ከተደረገና ከተደበደቡ በኋላ እጅና እግራቸውን አስረው እሳት አጉርሰዋቸዋል፡፡ ፠ የትግራይ #ጨለቆት_ሥላሴ አገልጋዮችና (ርዕሰ ደብር የነበሩትን አስተዳዳሪውን ጨምሮ) አስረው ‹‹በሮማ ካቶሊክ ታምናላችው ወይስ በረሃብ ትሞታላችሁ?›› እያሉ በረሃብ አሠቃይተዋቸዋል፡፡ እምቢ ቢሏቸው ጽኑ ግርፋት ገርፈው ከለቀቋቸው በኋላ በመኪና ገጭተው ገድለዋቸዋል፡፡ ፠ #ይደመቆ_ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/ ፠ #አፈር_ባይኔ_ተክለ_ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/ ፠ #አክርሚት_ቅዱስ_ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/ ፠ #ጎበጥ_አገር_ገብርኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ እመ ምሕረት/ ፠ #አንኮበር_ቅድስት_ማርያም ቤ.ክ. ፠ #ደረፎ_ቅድስት_ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/ ፠ #ጎንቻ_መድኀኔ_ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/ ፠ #አንኮበር_ቅዱስ_ሚካኤል ቤ.ክ.፡፡ #ጀግናውና_የቅኔው_አዝመራ_አለቃ_መርሻ_ወልደ_ማርያም ፠ ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀገራችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤ *በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤ *ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤ **የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ ከ30,000 በላይ ሰማዕታት፤ *በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤ *በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤ *ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤ *በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤ *ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤ *ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡ *ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣ *350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡ **ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፠ ሕንፃውም ለ2 ዓመት በፍጥነት ከተሠራ በኋላ ሚያዚያ 27 ቀን 1942 ዓ.ም. ተሠርቶ ተጠናቅቆ ቅዳሴ በቤቱ ተከበረ፤ በዋይዜማው ሚያዚያ 26 ቀን ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኑ ቡራኬ ሥነ ሥርዓትና የሰዓታት ጸሎት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ሲካሄድ አደረ፡፡ ታቦቱም ከቤተ ሳይዳ (የካቲት 12) ሆስፒታል ግቢ ወጥቶ አዲስ ወደተሠራው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ገባ፡፡ ንጋት ላይ ልክ 12 ሰዓት ተኩል ላይ አፄ ኃ/ሥላሴ እቴጌ መነንና ንጉሣውያን ቤተሰቦች እንደደረሱ እና ብዙ ምዕመናን በተሰበሰቡበት የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት ተጀመረ፡፡ በዕለቱም የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት የተመራው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ፣ አቡነ ቴዎፍሎስና፣ አቡነ ጢሞቴዎስ ነበር፡፡ ከቅዳሴውም በኋላ የገዳሙ አስተዳዳሪ የነበሩት አባ ሃና የታቦቱን የስደትና የመመለስ ታሪክ የሚገልጽ፤ ስብከት ለ15 ደቂቃ ካሰሙ በኋላ በስደት ሀገር ሲዘመር የነበረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ መዝሙር ተዘመረ፡፡ በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ የቡራኬ ጸሎት አድርገው ናዝዘው፣ ሠርሆተ ሕዝብ ካደረጉ በኋላ፣ ታቦቱ ወጥቶ ሥርዓተ ዑደት ተደርጐ የበዓሉ ፍጻሜ ሆነ፡፡ ፠ የቤተ ክርስቲያኑ (የገዳሙ) ቅዱሳት ስዕላት፤ ቤተ ክርስቲያኑ ተመርቆ አገልግሎት ከጀመረ ከ8 ዓመታት በኋላ በውጭ ሀገር ሰዓሊ ከ1950 ዓ.ም እስከ 1954 ዓ.ም. በነበረው ጊዜ የተሣሉ ናቸው፡፡ ፠ ገዳሙ እንደታላላቅ ገዳማት ማኅሌት አይቆምበትም የከበሮና የጸናጽል ድምፅም አይሰማበትም፡፡ ታቦቱ የሚነግሠውም በዓመት አንዴ ሚያዝያ 27ት ብቻ ነው፡፡ #የገዳሙ_መተዳደሪያ፤ ፠ ገዳሙ በተመሠረተበት ጊዜ ራሱን እንዲችል ለማድረግ አባ ሃና በገንዘብና ከግል ርስታቸው 1 ጋሻ መሬት በመስጠት እንዲረዳበት ሰጥተዋል፡፡ ንጉሣውያን ቤተሰቦችም አክሲዬን በመግዛት ይህን ገዳም ረድተዋል፡፡ ገዳሙ ራሱ የካህናት ኑሮ እንዲሻሻል ለማድረግ የሥጋጃ ሥራ በመክፈል ጥረት አድርጓል፡፡ ፠ ገና ከመሠረቱ አንስቶ ልዩ የሚያደርገው አገልግሎቱ በአብዛኛው በአማርኛ ቋንቋ መከናወኑ ነው፡፡ እንዲሁም የማታ ስብከት መርሐ ግብር በማዘጋጀት በቀዳሚነት የሚጠቀስና ዛሬም ድረስ ተጠናክሮ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ፠ በሰሙነ ሕማማት የሚካሄደው አጠቃላይ መርሐ ግብር (በተለይም መልክአ ሕማማቱ እንደ ዋልድባ ገዳም ሰሙኑን በአራራይ ዜማ መባሉ) በብዙዎች ላይ ትዝታን የሚያመጣ ነው፡፡ ፠ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የኬክ ቤትና የመካከለኛ ክሊኒክ ባለቤት ነው በቤተክርስቲያኑ #ተምሮ_ማስተማር_ሰንበት_ትምህርት_ቤት (ማኅበር) ፠ ተምሮ ማስተማር በኢትዮጵያ ቀደምት ሰንበት ትምህርት ቤት ነው፡፡ ፠ ሰንበት ትምህርት ቤቱን የሚመራው ሰብሳቢው ከገዳሙ የሚወከል ነው፡፡ ፠ በአሁን ወቅት ከሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተለየ መልኩ መስማት ለተሳናቸው ትምህርት ያስተምራል፡፡ ፠ በሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤቶች ከተለመደው የተከታታይ ትምህርት የተለያ የአብነት ትምህርት ቤትን መሠረት ያደረገ ሥርዐተ ትምህርትና ትምህርት ይሰጣል፡፡ ፠ ዓይነ ሥውራንን ታሳቢ ያደረገና በብሬል የተዘጋጁ መጻሕፍትን ጭምር የያዘ የተደራጀ ቤተ መጻሕፍት አለ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ምስካየ_ኅዙናን ( #ዴ_ሡልጣን_) (#ቤተ_ሳይዳ) መድኀኔ ዓለም ገዳም፡፡ #የሚያዝያ_27_የድል_ቀን_መታሰቢያ_ቤተ ክርስቲያንና #ተምሮ_ማስተማር_ሰንበት_ትምህርት_ቤት (ማኅበር) ፠ ከ1895-ሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. ዴር ሡልጣን (የንጉሥ ገዳም) ገዳም በሚል ስያሜ፡፡ ፠ ከሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. - ነሐሴ 23 ቀን 1933 ዓ.ም. ‹‹በስደት ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን›› እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡ ፠ ከሚያዚያ 27 ቀን 1940 ዓ.ም. እስካሁን፤ ምስካዬ ኅዙናን ገዳም እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ ምስካየ ኅዙናን፤ የስሙም ትርጓሜ ለተበደሉትና ላዘኑት ማረጋጊያ ማጽናኛ ማለት ነው፡፡ ምስካየ አመስከይ ተጠጋ አስጠጋ ከሚለው የተገኝ ሲሆን ያዘኑ የተከዙ የተጨነቁ መጠጊያ ለማለት ነው፡፡ ፠ ከግራኝ መሐመድ ወረራ በኋላ እስከ አፄ ዮሐንስና ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ድረስ በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳሞቻችንን በቋሚነት የሚረዳቸው ባለመኖሩ አብዛኞቹን የግሪክ የአርመንና የግብጽ አብያተ ክርስቲያን ወሰዷቸው፤ አፄ ምኒልክ በ1895 ዓ.ም. ለኢየሩሳሌም ገዳማት የሚተዳደሩበት ቦታ ገዝተው ሕንፃ ሠርተው ሲሰጡ፤ መምህር ፈቃደ እግዚእ የተባሉ መነኵሴን በኢየሩሳሌም አለቅነት ሹመውና ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው እንዲሄዱ አድርገዋል፤ በወቅቱ የትራንስፖርት አቅርቦት ባለመኖሩ እስከ ጂቡቲ ድረስ በእግር ከዛ በኋላ በመርከብ ተጕዘው ኢየሩሳሌም ደርሰዋል፡፡ ታቦተ ሕጉም በዴር ሡልጣን መድኀኔ ዓለም ገዳም (የንጉሥ ገዳም) ለ34 ዓመታት ሲቀደስበት፥ ሲወደስበት ኖሯል፡፡ ፠ በ1928 ዓ.ም. ጣሊያን ኃይሏን አጠናክራ ሽንፈቷን ለመበቀል ኢትዮጵያን ስትወርር፤ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ቅዳሜ ሚያዚያ 24 ቀን 1928 ዓ.ም. ወደ ጅቡቲ በባቡር፤ ከዚያም በእንግሊዝ የጦር መርከብ ሚያዚያ 26 ቀን ከጅቡቲ ተነስተው ሚያዚያ 30 ቀን ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ደረሱ፡፡ በሰኔ ወር 1928 ዓ.ም. ደግሞ በእንግሊዝ የጦር መርከብ ተሳፍረው ከኢየሩሳሌም ወደ እንግሊዝ ሀገር በSouthhampton ወደብ አድርገው ወደ ለንደን ከተማ በባቡር ተጉዘው Waterloo station ደረሱ፡፡ ለጥቂት ቀናት ከሰነበቱ በኋላ፤ ስዊዘርላድ ውስጥ ጄኔቫ በሚገኘው፣ የመንግሥታቱ ማኅበር ስብሰባ ላይ ሰኔ 23 ቀን 1928 ዓ.ም. የኢጣሊያ መንግሥት በሀገራችንና ሕዝባችን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ በመዘርዘር አስረዱ፤ ነገር ግን ለአቤቱታቸው የመንግሥታቱ ማኅበር ምንም ዓይነት አቋምና እርምጃ አለመውሰዱ እንዳሳዘናቸው ‹‹እግዚአብሔርና ታሪክ ፍርዳችሁን ሲያስታውሱት ይኖራሉ›› በማለት ልብን የሚነካ ታሪካዊና ትንቢታዊ ንግግር አድርገው ወደ ኢንግላንድ ተመልሰው በ‹‹ባዝ›› ከተማ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የስደት ኑሯቸውን ቀጠሉ፡፡ ፠ ንጉሡም በማኅበሩ ላይ ተስፋ በመቁረጥ፤ ፊታቸውን ወደ አባቶቻቸው አምላክ በማዞር በጾምና በጸሎት ለመማፀን በማሰብ፤ እንዲሁም የሃይማኖት ችግር እንዳያገኘን የሚያድጉ ልጆቻችን የሃይማኖታቸውን መሠረት እንዳይለቁ በማለት በብፁዕ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ፈቃድ ቀደም ሲል በአፄ ምኒሊክ ወደ ኢየሩሳሌም ዴር ሱልጣን ገዳም ተልኮ አገልግሎት እየሰጠ የነበረውን ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ከኢየሩሳለም ወደ እንግሊዝ እንዲላክላቸው፤ በጥር ወር 1929 ዓ.ም. አባ ሃና ጂማን ከእንግሊዝ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌም ላኳቸው፤ አባ ሃና ጂማማ ታቦቱን ከሌሎች 4 መነኮሳት (መምህር ገ/ኢየሱስ፣ አባ ማርቆስ፣ አባ ኃይሌ ቡሩክ እና አባ ገ/ማርያም) ጋር በመሆን ወደ እንግሊዝ ይዘው ተመለሱ፡፡ ጽላቱም ንጉሡ በሚኖሩበት ቤት ሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. ባዝ ከተማ ደርሶ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ፡፡ በዚህ ቤትም ስደተኞቹ የጸሎትና የቊርባን ሥርዓትን እየፈጸሙ፤ የሚማሩበትና የሚጽናኑበት ሆኖ ቆየ፤ ስሙም ‹‹በስደት ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን›› እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡ ፠ በዓለም ጦርነት ኢጣልያ ከጀርመን ጎን ስትሰለፍ፤ እንግሊዝ አፄ ኀይለ ሥላሴን ለመርዳት ወሰነች፡፡ በሰኔ 17 ቀን 1932 ዓ.ም. ንጉሡን ወደ ግብጽ ከዚያም ወደ ሱዳን በመውሰድ፤ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ለሚደረገው የጦር ዘመቻ ዝግጅት እንዲጀመር አደረገች፡፡ በሱዳን የነበሩ ብዙ ስደተኛ ኢትዮጵያን እንዲሁም ሌሎች ከኢትዮጵያ በመምጣት በካርቱም አስፈላጊውን የጦር፣ ልምምድና ዝግጅት ከተደረገ በኋላ፤ ከእንግሊዞች ጋር በመሆን ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ጦርነቱ ተጀመረ፡፡ አፄ ኀይለ ሥላሴም ሱዳን ከደረሱ ከ7 ወራት በኋላ ጥር 12 ቀን 1933 ዓ.ም. ከሱዳን ወደ ሃገራቸው ኢትዮጵያ ግዛት በመግባት ኦሜድላ ላይ የኢትዮጵያን ባንዲራ ሰቀሉ፡፡ ከዚያም በጎጃም ደብረ ማርቆስ አድርገው ወደ መሐል ሀገር (በወጡ በ5 ዓመታቸው ሚያዚያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም.) ወደ መናገሻ ከተማቸው አዲስ አበባ በመግባት በቤተ መንግሥታቸው ባንዲራችንን ሰቀሉ፡፡ ፠ በነሐሴ 23 ቀን 1933 ዓ.ም. እቴጌ መነን ወደ አዲስ አበባ በተመለሱ ቀንም አባ ኃይሌ ቡሩክ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ተመልሰው በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ የስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ) የጸሎት ቤት ተከፍቶለት እያጠኑና እየጠበቁ ከቆዩ በኋላ፤ ለተበደሉትና ላዘኑት ማረጋጊያ ፥ ለሕሙማን መጽናኛ እንዲሆን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ተብሎ ተሰይሞ በቀድሞ ቤተ ሳይዳ ቀዳማዊ ኃይለ ሥለሴ ሆስፒታል /አሁን የካቲት 12 ሆስፒታል/ ተብሎ በሚጠራው ግቢ በሚያዚያ 27 ቀን 1935 ዓ.ም. ውስጥ ተተከለ፡፡ ፠ ሕመምተኛው በጸሎት በመፈወስ፤ ከሩቅም ሆነ ከቅርብ የሚሳለመው ሕዝብ ቊጥር እየተበራከተ በመምጣቱ ሕዝቡ ይበልጥ እንዲሳብና የቅዳሴ ፍቅር እንዲያድርበት በማለት በአባ ሐና መሪነት፥ በአባ ኃይሌ ቡሩክ ኃላፊነት ሌሎች አገልጋዮች ተቀጥረው ጸሎትና ቅዳሴው ጠቅላላው ሥነ ሥርዐቱ ሁሉ በስደት ሀገር አገልግሎት ይሰጥበት በነበረው በአማርኛ ተደረገ፤ ይህ ነገርም በመደበኛነት የቤተክርስቲያን ልሳኗ ግእዝ ከመሆኑ አንጻር በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥም ሆነ ውጭ ባሉት አባቶች ቅሬታ አስነሣ፡፡ ፠ ከአምስት ዓመት በኋላ ቀ/ኃ/ሥላሴ ቤተ ክርስቲያኑ አሁን በሚገኝበት ቦታ ላይ እንዲሠራ ሚያዚያ 27 ቀን 1940 ዓ.ም. የመሠረተ ድንጋይ አኖሩ፡፡ ቦታው ሲመረጥ በአካባቢው ያሉ ት/ቤቶችን (የተፈሪ መነኰንን፣ የእቴጌ መነን፣ የቀ/ኀ/ሥ ዩኒቨርሲቲ /አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን/)ከግምት ውስጥ በማስገባት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን በጸሎትና ትምህርተ ሃይማኖታቸውን እንዲጠብቁ ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡

#በአዲስ_አበባ_ገዳማትና_አድባራት_የሚታዩት #ብልሃተኛ_ወይስ_በላተኛ_አስተዳዳሪዎች፡፡ *** በአዲስ አበባ በሚገኙ አድባራትና ገዳማት ቀደም ብሎ ብልሃተኛ የሆኑ፤ ትምህርት የተማሩ፤ ያወቁ፤ በማስተዋል መንገድ የሚራመዱ፤ መጻሕፍትን የመረመሩ፤ ለሰውም ለእግዚአብሔርም የሚመቹ፤ የቤተ ክርስቲያኔ ጥቅም ከሚነካ እኔ ልጎዳ የሚሉ ተመርጠው ነበር የሚሾሙት፡፡ የሚሾሙትም በቃለ ዐዋዲው መሠረት፤ ** ሰባካ ጕባኤን በማጠናከር ስብከተ ወንጌልን ሊያስፋፉ፤ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ሊያጠናክሩ፣ ሰንበት ትምህርት ቤትን ሊያጠናክሩና ሊያስፋፉ ነው፡፡ ፠፠ ዛሬ ዛሬ ግን በጣት ከሚቈጠሩ አስተዳዳሪዎች በቀር፤ ሌሎች እንደ እነርሱ ሙሰኞችና ለሥራቸው ደጋፊ ከሆኑ 5ት ከለባት ጋር በመተባበር ስምንና ልብስን ከማንዠርገግ፤ በሙስና ቤተ ክርስቲያንን ከመዝረፍ፤ የሚቃወሟቸውን የሰበካ ጕባኤ አባላት፣ ሊቃውንትና ሰንበት ትምህርት ቤት ከማባረርና ከማፍረስ፤ ቤተ ክርስቲያናችንና እምነታችንን የሚያሰድብ ሥራ ከመሥራት፤ የሚያጸይፍና የሚያዋርድ ሥራን ከመፈጸም፤ በሙስናና በቅሌት ከመዘፈቅ የራቀ አስተዳዳሪ በአዲስ አበባ ላይ ማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ መጥቷል፡፡ ፠ በተለያዩ አድባራት በልማት ስም ሕንፃና ሱቅ ሊሠሩ ሲሯሯጡ ለካህናትና ለደብረ አስበው እንዳይመስልህ፤ ጥሩ ሥራ ሊሠራ ነው እያሉ ከሰበካ ጕባኤ አባላት ጀምሮ ጥሩንባ የሚነፉ፥ የሚያቶሰቱሱ ጀሌዎቻቸውም ለቤተ ክርስቲያን አስበው እንዳይመስልህ፤ ኋላ ከሚሠራው ሕንፃ ላይ በነፃ ይሰጥሃል ተብሎ ቃል ተገብቶለት ነው፡፡ እንደነዚህ የልማት አርበኛ ነን የሚሉትን አስተዳዳሪዎችም ቤተ ክርስቲያናችን ወደ ቤቶችና ልማት አስተዳደር መመርያ፤ መንግሥት ደግሞ ወደ ከተማ ልማት ቢወስዷቸው ለእንርሱም ለሕዝባችንም ጥቅም ይሰጣሉ፡፡ መጀመሪያ ምዕመኑን መች በቅጡ አስተማሩትና ነው ሕንፃና አዳራሽ ገንቢ የሆኑት!!!፡፡ (በእርግጠኝነት ብዙዎቻችሁ አንጀታችሁ ከሚያርበት ጉዳይ አንዱ እንደሚሆን አንጠራጠርም፡፡) ፠ ምዕመን ሆይ ንቃ፤ እንዲህ አይነቱን አስተዳዳሪ ፤ ‹‹ለቀጣፊ ገባዋል ጥፊ›› የሚለውን የአበው ተረት ብትፈጽምበት ለቤተ ክርስቲያንም እረፍት ለእነርሱም ትምህርት ነው፤ (አባቶች የሚያጠፋን በእግር ብረት እስከማሠር እንደሚደርሱ፤ የሰዓሊተ ምሕረት ምዕመናን ያን ዋሾ ቀጣፊና ሌባ አስተዳዳሪ እንዳስተማሩት አንተም በየደብርህ አስተምረው፡፡ (እኛም መረጃና ማስረጃ የማቅረቡን ሒደት እንቀጥላለን፡፡ ሌባ አስተዳዳሪ እጁን እስኪሰበስብ ድረስ) በሰሞኑ መነጋገሪያ ከሆኑት አንዱን እነሆ፤ ፠ ተከራዮችን ሲያስጨንቁ የተያዙት፤ ፠ ተከራዮችን አላግባብ ከንግድ ቦታዎቻቸው እንዲለቁ ያስጨነቁትና ፠ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁን የጣሱት፤ ፠ የገነተ ጽጌ (አራዳ) ቅዱስ ጊዮርጊስ አስተዳዳሪ መልአከ መንክራት ኀይሌ ኣብርሃ፣ በፖሊስ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ ፍ/ቤት ቀርበው በአንድ ሺሕ ብር ቅጣት መለቀቃቸው ታውቋል፡፡ • ተከራዮቹ፥ የአስተዳደሩን ብልሽትና ምዝበራ በማጋለጣቸው አለቃው የሚያሳድዷቸው ናቸው፤ • ከ47.5 ሚ ብር በላይ የታሪካዊው ደብር ገንዘብ፣ በግንባታ ስም በተደራጀ ስልት ተመዝብሯል፤ • አስተዳዳሪው፣ “ወረርሽኙን ለመከላከል” በሚል ሽፋን የጀበና ቡና ንግድ ላይ የተሰማሩ የአንድ ተከራይን ውል፣ ተመሳሳይ አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ሌሎች ዘጠኝ ተከራዮች ለይተው በቂም በቀል በማቋረጥ፣ በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ቁጥር 3/2012 ማስፈጸሚያ የሚኒስትሮች ም/ቤት ያወጣውን ደንብ ቁጥር 466/2012 አንቀጽ 17 በመጣሳቸው፣ ባለፈው ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 20 ቀን በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ በማግሥቱ ወደ ፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው፣ ጉዳያቸው በመዝገብ ቁጥር 191499 በታየበት ወቅት፣ አስተዳዳሪው ወንጀል መፈጸማቸውን አምነው በሰጡት የእምነት ክሕደት ቃል መሠረት ችሎቱ የጥፋተኝነት ብይን አሳልፎባቸዋል፤ የግራ ቀኙን የቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ በማዳመጥ በአንድ ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ወስኗል፤ ቅጣታቸውንም ፈጽመው ከኹለት ቀናት እስር በኋላ ወጥተዋል፡፡ በተከራዮች መካከል በአድልዎ ልዩነት በማድረግ በምዝበራቸው የሚቃወሟቸውንና የሚያጋልጧቸውን ለመበቀል የሞከሩበት እንደነበር በመረጃው ተመልክቷል፡፡ ፠ በደብሩ ሕንፃዎች ውስጥ ኪራይ ሳይከፍሉ ከአስተዳዳሪው ጋራ በመግባባት የሚኖሩ፣ በነፃ ይዘው ሲያበቁ ለሦስተኛ ወገን የሚያከራዩ ግለሰቦች መኖራቸውን እንዲሁም፣ ተከራዮች ቤቶቹን ከተከራዩ በኋላ በነፃ እንዲገለገሉባቸው በማድረግ፣ የደብሩን የፓርኪንግ ቦታ በማሳጣት የግንባታ ፕላኑን በሚጎዳ ኹኔታ መብቱንና ጥቅሙን የሚያሳጣ አመራር እየሰጡ እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡ ፠ በጠቅላላው፥ ከ47 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ፣ በተደራጀ ስልት በመመዝበሩ፣ በአሁኑ ወቅት የታሪካዊው ደብር የፋይናንስ ሀብት መሟጠጡንና አገልግሎቱን በአግባቡ ለማስፈጸም አክል ማጋጠሙን፣ የአስተዳደር ብልሽቱንና ምዝበራውን የሚቃወሙ የሰበካ ጉባኤ አባላት አጋልጠዋል፡፡ ይህም እንዲታረም በየጊዜው ጥያቄ የሚያነሡ አካላት፣ ያለአግባብ ከሥራቸው እንደሚባረሩና ጥቃትም እንደሚፈጸምባቸው ገልጸዋል፡፡ ፠ አለቃውንና ጸሐፊውን አግዶ ሕጋዊ የውጭ ኦዲተር በመሠየም፣ ባለፉት ዓመታት ሲደርስ የቆየው ጥፋት ተመርምሮ ርምጃ እንዲወሰድ፣ የሕንፃ ተቋራጩም ውላቸው ታግዶ ማጣራት እንዲደረግ፣ በአጠቃላይ የታሪካዊው የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብርን፣ ጊዜው ያለፈበት አስተዳደር፣ በመተዳደሪያ ደንቡ መሠረት በማስተካከል ችግሩ አፋጣኝ እልባት እንዲሰጠው አቤት ባዮቹ ጠይቀዋል፡፡ ፠**፠ መልአከ መንክራት ኀይሌ ኣብርሃ፣ #በ2002 ዓ.ም.፤ ከብሔረ ጽጌ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በምዝበራ እና በብልሹ አስተዳደር በካህናት እና ምእመናን ተቃውሞ ተባረሩ። #በ2006 ዓ.ም. ፤ ብሥራተ ገብርኤል በአስተዳዳሪነት በነበሩበት ጊዜ ሰበካ ጉባኤ አባላትን በግፍ በማባረር ጭምር ደብሩን በመመዝበር እና በሚሊዮን ለሚቆጠር የሊዝ እዳ አስታቅፈው በካህናት እና ምእመናን ተቃውሞ ተባርረው ወደ አራዳ ጊዮርጊስ ተዛወሩ። # ከ47.5 ሚሊዮን ብር በላይ የታሪካዊው አራዳ ጊዮርጊስ ደብር ገንዘብ፣ በግንባታ ስም በተደራጀ ስልት ተመዝብሯል፤ # የቤተክህነቱን አሠራር በመሪ ዕቅድ በመመራት የፋይናንስ እና የሰው ሀብት አስተዳደርን ለማዘመን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጀምሮ የነበረውን እንቅስቃሴ ጥቅመኛ የደብር አስተዳዳሪዎችን በማስተባበር እንዲጨናገፍ በግንባር ቀደምትነት ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ /…የሌሎችንም እጃቸው አላርፍ ያሉትና፤ በስመ ልማት የሌብነት ተግባር የሚፈጽሙትን የማጋለጥ ተግባር እንቀጥላለን፤ መረጃና ማስረጃ ለሰጣችሁን መድኀኔ ዓለም ይስጥልን፤ ወደፊትም መረጃና ማስረጃ ላኩልን የማጋለጥ ሥራውን እንቀጥላለን፤ ሌባ አስተዳደር እስኪጠፋ ድረስ፤ የሌባ አስተዳዳሪ እጁ እስኪሰበሰብ ድርስ፡፡) መልካመ ሰሙነ ፋሲካ፡፡

​​Дарья Мороз показала свою трагически погибшую мать. Марина Левтова, актриса и бывшая жена режиссёра Юрия Мороз, сегодня могла бы отмечать 61-летие, однако судьба распорядилась по-другому. В конце зимы 2000 года артистка погибла при трагических обстоятельствах. Она упала со снегохода и ударилась головой об дерево, актриса получила серьёзную травму и вскоре скончалась. Дарье Мороз на момент смерти матери, с которой она была очень близка, было всего 16 лет. Для неё случившееся стало главной трагедией в жизни. «У мамы сегодня день рождения. Память и любовь», — поделилась Дарьи под снимком своей красавицы-мамы.@vsenovostizvezd

ሌላኛዋ ቀጣፊ እኅተ ማርያም፤ የአልጋነሽ ዘሪሁን፡፡ በቅድስት አርሴማ የተነሣች ዋሾ ቀጣፊ ተያዘች፤ ወደ ጠበልም ተወሰደች፡፡ ፠ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፥ ደንበጫ ወረዳ፥ የወረዳ ወጀት ቀበሌ ከ3ት ዓመ
ሌላኛዋ ቀጣፊ እኅተ ማርያም፤ የአልጋነሽ ዘሪሁን፡፡ በቅድስት አርሴማ የተነሣች ዋሾ ቀጣፊ ተያዘች፤ ወደ ጠበልም ተወሰደች፡፡ ፠ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፥ ደንበጫ ወረዳ፥ የወረዳ ወጀት ቀበሌ ከ3ት ዓመት በፊት ጀምሮ ‹‹አርሴማ ተገልፃ እኔንም አርሴማ፥ ባሌንም ገብርኤል ብላ ሰይማናለች›› በማለት በሜሮን ያልከበረ ልብሰ ተክህኖ በመልበስ፤ መስቀል በመያዝ፤ እባርካለሁ፣ ኪዳን አደርሳለሁ፣ ቅዳሴ እቀድሳለሁ፣ 4ት ሕፃናትን ክርስትና አንስቻለሁ እያለች በመኖሪያ ቤቷ ስትስትና ስታስት ቆይታለች፡፡ ፠ አንዱን ጻድቅ ፥ አንዱን ኃጥእ በማለት ካህናትን ከሁለት በመክፈል ደጋፊ ስታፈራም ቆይታለች፡፡ ፠ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ከዚህ በፊት ለወረዳው መንግሥት የሕግ ክትትል እንዲደረግባት ደብዳቤ ቢጽፍም፤ የወረዳው መንግሥት ባልታወቀ ምክንያት በዝምታ አልፎታል፡፡ ከ3ት ዓመታት በኋላም ከትናናት በስቲያ በሚያዝያ 23/2012ዓ.ም. የአካባቢው ሰው ተመራርጦ ቤቷን በመፈተሽ ንዋየ ቅድሳቱን ወደ ቤተ ክርስቲያን፤ እርሷንም ወደ ጠበል ወስዷታል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ (https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Telegram kanali @finotehiwott statistikasi va tahlili