uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 383 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 582-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 194-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 383 obunachiga ega bo‘ldi.

09 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 38 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.91% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.42% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 370 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 449 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 25 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 10 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 383
Obunachilar
-124 soatlar
-67 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
(‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫) #ጥምቀትን_በአዲስ_አበባ__በየትኛው_ጥምቀተ_ባሕር_ያከብራሉ_፤ #በአዲስ_አበባ_በ10ሩም #ክፍለ_ከተሞች_የሚገኙ #76ት #የጥምቀተ_ባሕር_ቦታዎችና_ወደ_ጥምቀተ_ባሕሩ_የሚወርዱትን_179 #ገዳማትና_አድባራት_እነሆ_ጽፈንላችኋል፡፡ (እኛ በአ.አ. ከሚገኙ 76ት ጥምቀት ባሕር መካከል፤ ብዙ ታቦታት የሚወርዱበትን የጃንሜዳን ፎቶ ለጥፈንላችኋል፤ እናንተም በየአካባቢያችሁ ያሉትን በ‹ኮሜንት› መጻፊያ ላይ ለጥፉልን፡፡) ፠ ፠ ፠ #በአራዳና_ጉለሌ_ክፍለ_ከተማ_ (7ት ጥምቀተ ባሕር) #፩ኛ) #በጃንሆይ_ሜዳ_ (በጃንሜዳ)፤ /በአዲስ አበባ ትልቁና የ12 አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት የሚያድሩበት) 1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤ 2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤ 3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ 4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤ 5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው) 6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤ 8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤ 9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤ 10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤ 11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ 12ኛ. ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡ #፪ኛ) #እንጦጦ_ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ 1ኛ. እንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤ.ክ. 2ኛ. እንጦጦ ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም #፫ኛ) #ሽሮ_ሜዳ_ወረዳ_01 ፥ #ቀበሌ_02_ 1ኛ. ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ #፬ኛ) #አዲሱ_ገበያ_ 1ኛ. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ 2ኛ. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለሃይማኖት #፭ኛ) #ወረዳ_3ና_4 (19 ቀበሌ) 1ኛ. መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም #፮ኛ) #ሸጎሌ_መንገድ_ 1ኛ. ጉለሌ(ሸጎሌ) ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. ድልበር መድኀኔ ዓለም #፯ኛ) #ወረዳ_7_ቀበሌ_15(ቤልኤር፤ ኳስ ሜዳ) 1ኛ. ቀበና ምሥራቀ ፀሐይ መድኀኔ ዓለም ፠ ፠ ፠ #በየካ_ክፍለ_ከተማ_ (14ት ጥምቀተ ባሕር) #፰ኛ) #ወረዳ_8(22 አካባቢ፤ ባልደራስ አጠገብ) 1ኛ. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል 3ኛ. ቀበና ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ኪዳነ ምሕረት #፱ኛ) #ወንድይራድ_ትምህርት_ቤት_አካባቢ_(ኮተቤ) 1ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ኮተቤ (ኋላ ሲ.ኤም.ሲ.) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል 3ኛ. መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና 4ኛ. ሲ.ኤም.ሲ. አቡነ ተክለ ሃይማኖት 5ኛ. ደብረ አራራት ቅዱስ አማኑኤል 6ኛ. ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ 7ኛ. ኮተቤ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲ኛ) #ዋሻ_ተክለ_ሃይማኖት_ጠበል_ቦታ 1ኛ. ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. አንቆርጫ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል #፲፩ኛ) #በግ_ተራ 1ኛ. ኮተቤ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት #፲፪ኛ) #ላምበረት_ቤተ_ክርስቲያኑ_አካባቢ 1ኛ. ላምበረት ደብረ ፀሐይ አቡነ አረጋዊ #፲፫ኛ) #ጉራራ_አካባቢ 1ኛ. ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲፬ኛ) #ወረዳ_10 #ከጉራራ_ከፍ_ብሎ_ፖሊስ_ሴንተር_አጠገብ 1ኛ. ደብረ መድሐኒት ዳንሴ መድኀኔዓለም 2ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል #፲፬ኛ) #ሎቄ_ቤተ_ክርስቲያን_አካባቢ 1ኛ. ሎቄ መ.ጸ. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፲፭ኛ) #ኬንያ_ኤምባሲ_ጀርባ_(በግ ተራ) 1ኛ. ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም #፲፮ኛ) #መሪ_አደባባይ 1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ 2ኛ. መሪ ደብረ ታቦር ቅዱስ ፋኑኤል #፲፯ኛ) #አባዶና_ካራ_አሎ_አርሴማ_ጠበል_አካባቢ_(ገበያው መሐል) 1ኛ. ካራ አሎ ደብረ ቀርሜሎስ መድኀኔ ዓለምና አቡነ ገሪማ 2ኛ. ካራ አሎ ቅድስት ሥላሴ 3ኛ. አባዶ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ 4ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲፰ኛ) #አባዶ_አካባቢ 1ኛ. አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል #፲፱ኛ) #አያት_አካባቢ 1ኛ. ጣፎ መ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አያት ደ/ክ ቅድስት ማርያም #፳ኛ) #አባዶ_ኮንዶሚንየም 1ኛ. አባዶ ጽርሐ አርያም ቅድስት ማርያም 2ኛ) ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ) ደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ 4ኛ) ደብረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም 5ኛ) አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 6ኛ. ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ 7ኛ. ኢያሪኮ ቅዱስ ገብርኤል ፠ ፠ ፠ #ልደታ_አዲስ_ከተማና_ቂርቆስ_ክፍላተ_ከተማ_ (5ት ጥምቀተ ባሕር) #፳፩ኛ) #ቂርቆስ_አካባቢ 1ኛ. ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ #፳፪ኛ) #ኦሎምፒያ_ቦሌ_ማተሚያ_ቤት_አካባቢ 1ኛ. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ 2ኛ. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ #፳፫ኛ) #ልደታ_ክፍለ_ከተማ_ሜትሮሎጂ_ጀርባ 1ኛ. ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ጎላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ቅዱስ ሚካኤል #፳፬ኛ) #ሳር_ቤት_ኮንዶሚንየም 1ኛ. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም #፳፭ኛ) #ቄራ_አካባቢ 1ኛ. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ፠ ፠ ፠ #ኮልፌ_ቀራንዮ_ክፍለ_ከተማ_(9ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፳፮ኛ) #መድኀኔ_ዓለም_ከፍተኛ_መሠናዶ_ትምህርት_ቤት_(ራስ ኀይሉ ሜዳ) 1ኛ. መርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል 2ኛ. ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል 4ኛ. ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ 5ኛ. ጠሮ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ #፳፯ኛ) #ሳንሱሲ_መናፈሻ_አጠገብ 1ኛ. አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አስኮ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 4ኛ. ፍኖተ ሎዛ ብርጭቆ ማርያም #፳፰ኛ) #ወረዳ_15_(አርሴማ ጠበል /አወልያ ትምህርት ቤት ጋር/) 1ኛ. ቃሎ ተራራ አቡነ ሀብተ ማርያም #፳፱ኛ) #ገዳመ_ኢየሱስ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅጽር_ግቢ_ውስጥ 1ኛ. ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ 3ኛ. ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ 4ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም 5ኛ. ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 6ኛ. መርካቶ ደብረ ገሊላ አማኑኤል 7ኛ. ገዳመ ኢየሱስ #፴ኛ) #ወረዳ_5_ #ጻድቃኔ_አካባቢ_ታቦት_ማደርያ 1ኛ. ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ገብረ ክርስቶስ 2ኛ. ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም 4ኛ. ጻድቃኔ ማርያም 5ኛ. ፈለገ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት 6ኛ. ወይራ ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና ዕጨጌ ዮሐንስ #፴፩ኛ) #ወረዳ_4_ #አየር_ጤና_ኪዳነ_ምሕረት_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ 1ኛ. አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም 3ኛ. ዓለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል

#ኢራንቡቲ_ጥምቀተ_ባሕር (#ሸንኮራ_ወንዝ_ዳርቻ) ፥ ምንጃር፡፡ #41_ታቦታት_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱበት፡፡ ከ600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረው፤ በአፄ ዘርዐ ያዕቆብ የተጀመረውና ታሪክ፣ ባህል፣
#ኢራንቡቲ_ጥምቀተ_ባሕር (#ሸንኮራ_ወንዝ_ዳርቻ) ፥ ምንጃር፡፡ #41_ታቦታት_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱበት፡፡ ከ600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረው፤ በአፄ ዘርዐ ያዕቆብ የተጀመረውና ታሪክ፣ ባህል፣ እምነትና የሀገር ወግ የሚንጸባረቁበት፤ የኢራንቡቲ ጥምቀተ ባሕር እስከዛሬም ድረስ በሃገራችን በኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል በደማቅ ከሚከበርባቸው ቦታዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ በበዓሉ ላይም እናቶች በእልልታ የታላቁን የደብረ ኤረር ተራርን አልፎ እስከሚያስተጋባ ድረስ ያደምቁታል፡፡ ከ41ዱ ታቦታት መካከል ጥቂቶቹ፤ ፠ ሸንኮራ ዮሐንስ ፠ ባልጪ አማኑኤል ፠ በሳ ሚካኤል ፠ ጅማ ገብርኤል ፠ ኢቲቻ ተክለ ሃይማኖት ፠ አረካ ዋርካ ይልፋታ ሥላሴ ፠ አክላል ኪዳነ ምህረት ፠ እንጆረራ አማኑኤል ፠ ወረቀት ሀገር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፠ ውሪ ጊዮርጊስ …. ይገኙበታል፡፡ (ምንጭ፤ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የጥር 7 ሥርዐተ ማኅሌት በመካነ ሥላሴ (ኋላ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ) ይህን ይመስላል፡፡ (የቤቱን ቀለም አካተን ሥርዐተ ማኅሌቱን አካተን ባለማዘጋጀታችን እንድናካትተው ለጠየቃችሁን ወደፊት አ
+4
የጥር 7 ሥርዐተ ማኅሌት በመካነ ሥላሴ (ኋላ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ) ይህን ይመስላል፡፡ (የቤቱን ቀለም አካተን ሥርዐተ ማኅሌቱን አካተን ባለማዘጋጀታችን እንድናካትተው ለጠየቃችሁን ወደፊት አካተን እናዘጋጀዋለን፡፡) /ፎቶውን ለዘገበለን ወንድማችን ቅድስት ሥላሴ በበረከት ይጎብኝልን፡፡) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት_ነው፡፡ ለጥር 7 ከዋይዜማው ጀምሮ የሚባለውን ሥርዐተ ማኅሌት ከወረብ ድምፅ ጋር አብረን አዘጋጅተነዋል፤ መልካም ሥርዐተ
+4
#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት_ነው፡፡ ለጥር 7 ከዋይዜማው ጀምሮ የሚባለውን ሥርዐተ ማኅሌት ከወረብ ድምፅ ጋር አብረን አዘጋጅተነዋል፤ መልካም ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ወረቦቹን በድምፅ ማጋኘት ከፈለጉ በቴልግራም ገጻችን (https://t.me/medihanaelem) ያገኛሉ፡፡

በቅድስት ሥላሴ የተሰየሙ ብዙ አድባራትና ገዳማት ቢኖሩም፤ የታሪክ ሙዳይ የኾኑ፥ ከዕድሜያቸው ብዛትና ከአመሠራረታቸው አንጻር በታሪክ አሻራ ላይ ያላቸው አስተዋጽዖ ከፍተኛ የኾኑ ፥ የታሪክ አሻራቸው ያንጸባረቀ፥ አሻራቸው የላቀ፥ እድሜያቸው የጎላ፤ 8ቱ ዐበይት ገዳማት (ቤ.ክ)፤ እንዲሁም በአ.አ. ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው አብያተ ክርስቲያናት፡፡ 1ኛ) #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ ከ2000ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ የብዙ ቅዱሳን (የአባ ዓምደ ሥላሴ፣ የአባ ክፍለ ማርያም፣ የ7ቱ ዘሥላሴ፣ የአባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ /የአርኬና የመልክዓ ቊርባን ደራሲ/፣ …….. ) መፍለቂያ፡፡ 2ኛ) #አሰቦት_ቅድስት_ሥላሴ፣ በ13ኛው ክ/ዘመን በታላቁ ጻድቅ በአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተመሠረተ፡፡ 3ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ሰሜን_ሸዋ_ደብረ_ብርሃን_ከተማ፤ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ዘመን የተመሠረተ፡፡ 4ኛ) #መካነ_ሥላሴ_ደቡብ_ወሎ_ወረኢሉ፤ በ1500ዓ.ም. በዓፄ ናዖድ የተመሠረተና በልጁ በዓፄ ልብነ ድንግል ሥራው የተጠናቀቀ፤ ባለ 16 መንበር በዕንቊና በወርቅ የታነጸ የነበረ፤ (ኋላ በግራኝ የፈረሰ፤ ጽላቱ በዓፄ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ቀድሞ መካነ ሥላሴ አሁን 4 ኪሎ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል የሚጠራው)፤ ደቡብ ወሎ ያለው መካነ ሥላሴ ግን ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና በቀድሞው ቅርጹ በባለ 16 መንበር ተደርጎ ካች አምና የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በመገንባት ላይ ይገኛል፤ (ለሕንፀታ ቤቱ ኹላችንንም ያብቃን)፡፡ 5ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ጎንደር_ከተማ፤ በጥር 26 ቀን 1683 ዓ.ም. በዓፄ አድያም ሰገድ የታነጸ፤ በጎንደር ከተማና ዙሪያ ከሚገኙ 44ቱ ታቦታተ ጎንደር በአሠራሩ ልዩ የኾነ፤ በ1880ዎቹ ድርቡሽ ጎንደር ከተማን ሲያጠፋ አብረው ከጠፉት 44ት አብያተ ክርስቲያናት በተዓምራት ሳይቃጣል የቀረ፤ የታላላቅ ሊቃወንት (የእነ ሊቁ ክፍለ ማርያም) መፍለቂያ፡፡ 6ኛ) #ናርጋ_ሥላሴ_ከጣና_ላይ_ገዳማት_አንዱና_ዋነኛው፡፡ 7ኛ) #ጨለቆት_ሥላሴ_ትግራይ፤ መቀለ አጠገብ፡፡ 8ኛ) #አዲስ_አበባ_መካነ_ሥላሴ_ ( #መንረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል እየተጠራ ያለ) (4 ኪሎ)፡፡ #በአዲስ_አበባ_የሚገኙ_የቅድስት_ሥላሴ_አብያተ_ክርስቲያናት (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት) 1ኛ. መካነ ሥላሴ (መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.)፤ (4 ኪሎ) 2ኛ. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ (ሽሮሜዳ) 3ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ (አያት መሪ) 4ኛ. ካራ አሎ ቅድስት ሥላሴ (ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ) 5ኛ. ጠሮ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ፤ (ኮልፌ ቀራንዮ) 6ኛ. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም (ጀሞ) 7ኛ. ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ (ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፥ ወረዳ 4) 8ኛ. ፈለገ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ (ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ) 9ኛ. ቂሊንጦ ቅድስት ሥላሴ (አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፥ ወረዳ 9) 10ኛ. ኤረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ (ጎሮ ሰፈር፥ ወረዳ 9) 11ኛ. መሪ ቅድስት ሥላሴ (መሪ አያት፥ ወረዳ 13) እንዲሁም በድርብነት 12ኛ. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (የሥላሴ ታቦት በድርብነት ይከበራል) (አዲሱ ገበያ) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ (ተጨማሪ ካሉ ከነፎቷቸው ጨምሩበት) #ለብቃ_ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣ #በለስ_ዋሻ_ኢየሱስ /ተጉለትና ቡልጋ/፥ #በአ.አ. #ገነተ_ኢየሱስና_ገነተ_ማርያም ቤ/ክ፤ (ፈረንሳይ) #በአ.አ #ገዳመ_ኢየሱስ (ኮልፌ 18) #በአ.አ #እንጦጦ_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ራጕኤልና_ኤልያስ (የኤልያስ ዕርገቱ) #በጎጃም_ደብረ_ኤልያስ ይከበራል፡፡ #ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡ ፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡ ፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡ እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡ #ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ (የዚህን ቅዱስ ነቢይ ታሪክ በደንብ ያንቡብት ብዙ ትምህርት ይቀስሙበታል) **በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን ✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡ ✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29 ✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡ ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡ ✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9 ✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡ ✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡ #ደመና_ደመና ….. #በሠረገላ_፤ ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤… ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤ ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤ በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤ አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡ #ዳግመኛም ዛሬ የአባቶችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/ #ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem