uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 408 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 577-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 192-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 408 obunachiga ega bo‘ldi.

12 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 76 ga, so‘nggi 24 soatda esa 7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.12% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.38% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 871 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 446 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 23 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 408
Obunachilar
+724 soatlar
+347 kunlar
+7630 kunlar
Postlar arxiv
#ጾመ_ገሃድ/#የገናና_የጥምቀት_ጾም/ (በብዙዎች ዘንድ የተጠየቀ) #አስቸኳይ_ለሌሎችም_ማድረስን_አትርሱ_shareeeeee_ #ገሃድ_ ማለት አግሀደ (ገለጠ፥ አሳየ) ካለው የተገኘ ሲሆን መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። ጾመ ገሀድ በልደትና በጥምቀት ዋዜማ የሚጾም ጾም ሲሆን ከ፯ቱ አጽዋማት አንዱ ነው። #ጋድ_ ማለት ደግሞ እጅ መንሻ፣ ስጦታ አንደማለት ነው። ጋዳ ካለው የተወሰደ ሲሆን ይህም ማለት ማክሰኞ ተጹሞ ለረቡዕ፥ ረቡዕ ተጹሞ ለኀሙስ፥ .... የሚሰጥ ስጦታ እንደማለት ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም (ጋዳ ዖፍ/ድጓ/፥ ጋዳ ያበውኡ ቁርባን- ቁርባንን እጅ መንሻ ይመጣሉ/ዝማሬ/) እንዲል፨ #አንድም_ ለልማዱ ጾም የሚጾመው በእለቱ ሲሆን የጋድ ጾም ግን በዋዜማው ያለው እለት ተጹሞ የእለቱ አለት የሚበለበት ስለሆነ ተውላጠ ጾም እንደማለት ጋድ ተባለ። #አንድም_ ጋድ_ የጠፍር ሰም ነው፤ ይኸውም ቁመቱ ከሁለት ክንድ የማይበልጥ የጠፍር ዐይነት ሲሆን አገልግሎቱም ላም ሲታለብ እግሮቿን ወድሮ ማሰሪያ ነው፤ ጋዱን ስጭን አንዲሉ፤ ታዲያ ከገሃድ ጾም ጋራ ምን ያመሳስለዋል ቢሉ ለምሳሌ ረቡዕ ቢውል ማክሰኞ ተጹሞ ለረቡዕ ተውላጥ(ለውጥ) በመስጠቱ ጾም ያልነበረ ማክሰኞን ልክ እንደላሟ እግር ከረቡዕ ጋራ አጣምሮ፥ ወድሮ፥ አንድ የሚያደርግ የጾም ዕለት ስለሆነ ጋድ ተባለ። #አንድም_ጋድ_ ማለት የማይዳሰስ፥ የማይታይ፣ ረቂቅ፥ ስውር አምላክ ከሚታይ ከሚዳሰስ ሥጋ ጋራ አንድ ሆነ፥ ተሳሰረ (እግዚአብሔር ቃል ከትስብዕት ጋራ ተሳሰረ፥ ተዋሐደ) ሲሉ ጋድ ብለውታል። /እንደ ላይ ቤት ትርጓሜ/፨ ይኸውም፤ ጥምቀት ማክሰኞ ሲውል ዋይዜማው ሰኞ እስከ ምሽት 12 ሰዐት ይጾማል፤ ጥምቀት ረቡዕ ሲውል ዋይዜማው ማክሰኞ እስከ ምሽት 12 ሰዐት ይጾማል፤ ጥምቀት ኀሙስ ሲውል ዋይዜማው ረቡዕ እስከ ምሽት 12 ሰዐት፤ ማክሰኞ እስከ 6(9) ሰዐት ይጾማል፤ ጥምቀት ዐርብ ሲውል ዋይዜማው ኀሙስ እስከ ምሽት 12 ሰዐት ይጾማል፤ #ጥምቀት_ቅዳሜ_ሲውል_ዋይዜማው_ዐርብ_እስከ_ምሽት_12_ሰዐት_ኀሙስ_እስከ_6(9)_ሰዐት ይጾማል፤ ጥምቀት እሑድ ሲውል ዋይዜማው ቅዳሜ እስከ 6 ሰዐት፤ ዐርብ እስከ ምሽት 12 ሰዐት ይጾማል፤ **ጥምቀት ሰኞ ሲውል ዋይዜማው እሑድ እስከ ምሽት ጠዋት 3 ሰዐት፤ ቅዳሜ እስከ 6 ሰዐት ይጾማል፤ #የጾሙ_ቀመር፤ ለጥምቀት ቀን ስጦታ(ልዋጭ) የሚሆን 12 ሰዐት መጾም ነው። ዋይዜማው ረቡዕና ዐርብ ላይ ሲውል ረቡዕና ዐርብ ራሳቸው እስከ 9 ሰዐት ጾም ስለሆኑ እስከ ምሽቱ 12 ሰዐት ተጹመው ዋይዜማቸው ማክሰኞና ኀሙስ እስከ 6(9) ሰዐት ይጾማል። ጥምቀት የሚውልበት ቀን ጥምቀተ ባሕሩ እስኪባረክ እስከ 3 ሰዐት ድረስ ይጾማል፤ ድምሩ 12 ሰዐት ይሆናል፨ #በባሕረ ሐሳብ ቀመርም ጥምቀት የዋለበትን ቀን ደግሞ የሚውለው ከ8 ዓመታት በኃዋላ ነው፨ (ማብራሪያውን ለሰጡን ለአራቱ ጉባኤያት መምህርና ለቅኔው ማዕበል፥ ለቅኔው ፈጣሪ ለሊቁ ከሃሊ በቃሉ መድኀኔ ዓለም ይስጥልን)

#ጌታ_ለምን_በሠላሳ_ዘመኑ_ተጠመቀ? 1. በሕገ ኦሪት መሠረት ለካህናት አገልግሎት መመረጥ የሚቻለው በ፴ ዘመን እንደነበረ ሁሉ እርሱም የሊቀ ካህናትን ተግባር፣የመምህርነቱንና የአዳኝነቱን ሥራ በ፴ ዘመኑ በጥምቀት ጀመረ፡፡ 2. አዳም እንደ ሠላሳ ዘመን ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በአርባ ቀኑ ልጅነትን ተሰጥቶት ኋላም በኃጢአት ምክንያት ያጣውን ልጅነት ይመልስለት ዘንድ ነው፡፡ #የጥምቀት_ጥቅም_በጥምቀት_የሚገኝ_ጸጋ) ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ እንወለዳለን፡- ድህነትን እናገኛለን፡- የኃጢአት ሥርየትን እናገኛለን፡- ….. ፪...፫…፬…፭…. #በጥር_11_በጥምቀት_በዓል_የምንረጨውና_የምንጠመቀው_ጥምቀት_ለቡራኬ_ነው፡፡

(ሥርዐተ ማኅሌቱን ሁላችሁም ትጠቀሙበት ዘንድ በሁሉም አድባራት/ጥምቀተ ባሕር/ የሚቆመውን የየአድባራቱን ይትበሃል አዘጋጅተነዋል፤ መልካም በዓል፡፡ #ዘመነ_አስተርእዮ “አስተርእዮ” ቃሉ የግእዝ ሲሆን ተርእየ (ታየ፣ ተገለጠ) ካለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጕሙም በገሀድ መታየት በይፋ መገለጥ ማለት ነው፡፡ በጽርዕ ቋንቋም ኤጲፋኒ(Epiphany) ይባላል፡፡ ዘመነ አስተርእዮ ከጥምቀት በዓል (ጥር 11) አንስቶ አስከ ጾመ ነነዌ ድረስ ያለው ጊዜ ነው፡፡ አስተርእዮ የተባለበት ምክንያትም የማይታየው የአምላክ አካልና ባሕርይ ከሚታየው የሰው አካልና ባሕርይ ጋር ተዋሕዶ የተገለጠበትና ማንነቱ በገሀድ (በዮርዳኖስ ባሕር) የታወቀበት፥ ምሥጢረ ሥላሴም የተገለጠበት ወቅት ስለሆነ ዘመነ አስተርእዮ ተባለ፡፡ በዚህ ዘመን የሚውሉ ማንኛውም በዓላት የአስተርእዮ በዓል ይባላሉ፤ ለምሳሌ ጥር 21 እመቤታችን በዓለ ዕረፍቷ ሆኖ ሳለ ‹‹የአስተርእዮ ማርያም›› ይባላል፡፡ #በዓለ_ጥምቀት_የጥምቀት_በዓል የጥምቀት በዓል በየዓመቱ ጥር 11 ዕለት ይውላል በዓሉ የሚጀምረውም ከጥር 10 ዕለት ጀምሮ ሲሆን፤ ኦሪት ለወንጌል አምሳል፣ መርገፍ እንደሆነች፤ በዘመነ ብሉይ የተሠሩ አጽዋማትና በዓላትም በዘመነ ሐዲስ ለተሠሩ አጽዋማትና በዓላተ አምሳል መርገፍ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያተ በብሉይ ይከበር በነበረው በበዓለ መጸለት(ዳስ በዓል) በዓለ ጥምቀት ገብቶበታል፡፡ ይኸውም እንደምን ነው ቢሉ በመጸለት ቀድሞ ካህናተ ኦሪት ለ7ት ቀናት ታቦት ይዘው ወንዝ ወርደው ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ሕዝቡ እህል አከማችተው አባቶቻችን በኢያሱ መሪነት ውኃውን አቁሞ የዮርዳኖስን ወንዝ አሻገራቸው እያሉ ያስቡበት ነበር፤ በዘመነ ሐዲስ በጥምቀተ በዓልም ካህናተ ወንጌል ታቦት ይዘው፤ ወንዝ ወርደው /ውሃ ከትረው/ ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ጌታችን ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በእደ ዮሐንስ በማየ ዮርዳኖስ ተጠመቀ እያው ያስቡበታልና፡፡ /ዘሌ.23÷39-43፣ ኢያ. 3÷16/ #ለጥምቀት_በዓል_ምዕመናን_የምንይዘው_ዥንጉርጉር_በትር_ምሳሌው፣ ያዕቆብ ከወንድሙ ከኤሳው ሸሽቶ በአጐቱ በላባ ቤት ብዙ ዓመታት ስላገለገለ ለአገልግሎቱ ዥንጉርጉር ሆነው የሚወለዱት በጐች ለያዕቆብ እንዲደረግና ምልክት የሌለባቸውን ለላባ እንዲሰጠው አዘዘው፡፡ ያዕቆብም በጐቹ ምልክት ያለባቸው ሆነው እንዲወለዱ ዥንጉርጉር እንጨት ውኃ በሚጠጡበት ውስጥ ጨምሮ በጐቹም እንደበትሩ ዥንጉርጉር እንደወለዱ እናያለን፡፡ /ዘፍ. 30÷31/ ይህ ምሳሌ ነው፡፡ በጐቹ የምዕመናን ውኃው የጥምቀት አውራዎቹ የመምህራን አንድም የቀሳውስት የሚጸነሱት በትሩን እንጂ አውራውን እንደማይመስሉ ምዕመናንም ሥላሴን ይመስላሉ እንጂ ያስተማራቸውን መምህራንን ቀሳውስትን አይመስሉምና፤ እንጨቱ ዥንጉርጉር መሆኑ ጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው /አምላክ ወሰብእ/ ለመሆኑ ምሳሌ፤ ያዕቆብ የጌታ ላባ የዲያብሎስ ምሳሌ ነው፡፡ ምልክት ያላቸው ለያዕቆብ ምልክት የሌላቸው ለላባ እንደሆኑ ሀብተ ወልድ፥ ሕይወተ ልቡና ያላቸው ለጌታ፤ ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡና የሌላቸው ለዲያብሎስ የመሆናቸው ምሳሌ ነው፡፡ ምዕመናን ዥንጉርጉር በትር መያዛቸው ሰው የሆነ አምላክ /አምላከ ወሰብእ/ ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ በመሠረተልን ጥምቀት ተጠምቀን ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡናን አግኝተን የሥላሴ ልጆች መሆናችንን ለማሳየት ነው፡፡ #ጥምቀት_ አጥመቀ /አጠመቀ/ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም በገቢር መንከር፣ መድፈቅ፣መዝፈቅ፣ማጥመቅ፣ሲሆን በተገብሮ ደግሞ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጠመቅ፣ መላ አካልን በውኃ ውስጥ ማስገባት ማለት ነው፡፡ከዚህ በተጨማሪም አጠማመቅ፣ ጠመቃ፣ የማጥመቅና የመጠመቅ ሥራ፣ኀጽበት በጥሩ ውሃ የሚፈፀም፣ የበዓል ስም፤ ጌታችን የተጠመቀበት ዕለት ማለትም ነው፡፡ በብሉይና በሐዲስ ኪዳን የተለያዩ የጥምቀት ዓይነቶች አሉ እነርሱም፡- #ጥምቀት_በብሉይ_ኪዳን_ (የአይሁድ ጥምቀ፣ የኤሲያንስ ጥምቀትና የዮሐንስ ጥምቀት ነበሩ) #ጥምቀት_በሐዲስ_ኪዳን፤ ፩. #የጌታችን_ጥምቀት፤ #የጥምቀት_መሥራች_ማነው_በምንስ_ተመሠረተ? የጥምቀት መስራቹ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን አመሠራረቱም በትምህርት /ዮሐ.351/፣ በተግባር /ማር.19፣ ማቴ.313/ እና በትዕዛዝ /ማቴ.2813/ ነው፡፡ #ጥንተ_ጥምቀት_ጌታችን_መቼ_ተጠመቀ? ጥንተ ጥምቀት ማለት ጌታችን የተጠመቀበት ዕለት ማለት ሲሆን ጌታችን የተጠመቀውም ዓለም በተፈጠረ በ5531 ዓመተ ዓለም(በ31 ዓመተ ምሕረት)፤ በዘመነ ሉቃስ፤ በዕለተ ማክሰኞ፤ ጥር 11 ዕለት፤ ሌሊት በ10 ሰዓት ነው፡፡ በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ፍት.ነገሥ.አን.19፣ ድስቅ.29፣ ተረፈ.ቄርሎስ፣ ሉቃ.323/ #ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ_? ሀ. ምሥጢረ ሥላሴን ለመግለጥ ለ. ሰው /አዳም/ በበደል ምክንያት ያጣውን ልጅነት ለመመለስ ሐ. የአዳምና የሔዋንን ዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ ‹‹የዕዳችንን ደብዳቤ ደመሰሰልን›› /ቆላ. 2$14/፣ ወሠጠጠ መጽሐፈ እዳሆሙ ለአዳም ወለሔዋን (ለአዳምና ለሔዋን የዕዳ ደብዳቤያቸውን ቀደደላቸው) /ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ ቊ.9/ ሠ. ትንቢተ ነቢያትን ለመፈፀም /መዝ.76$16/ ረ. በእርሱ ጥምቀት የእኛን ለመባረክ ሰ. የእግዚአብሔር ልጅ እንድንሆን /ገላ.3$26፣ገላ.4$4፣ሮሜ.8$14፣ዮሐ.1÷13፣1ኛ.ዮሐ.3÷1/ #ጌታችን_ለምን_በዮርዳኖስ_ተጠመቀ? ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው፤ ትንቢቱን(/መዝ.113$1-8/)፣ ምሳሌውን(ዮርዳኖስ ከላይ ነቅዑ /ምንጩ/ አንድ ነው ዝቅ ብሎ ለሁለት ‹‹ዮር›› እና ‹‹ዳኖስ›› ተብሎ ይከፈላ….፣ ፣ዘፍ.14$14-20፣ መጽሐፈ ነገስት ካልእ 6$1 አንድምታ ና መጽ.ነገሥት ካልዕ 5$16 ምሥጢሩን (በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የአዳምንና የልጆቹን ደብዳቤ ለመደምሰስ/ቆላ.2$14፣ ኤፌ.2$15፣ ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ ቊ.1/፡፡) ለመፈጸም ነው፡፡ #ጌታችን_ለምን_በውኃ_ተጠመቀ?  ትንቢቱ፡- ሀ. ‹‹ጥሩ ውሃንም እረጫችኋለሁ እናንተም ከርኵሰታችሁ ትነፃላችሁ›› ጥሩ ውሃ የተባለ የጥምቀት ውሃ ነው፡፡ /ት.ሕዝ.36$25/ ለ. ‹‹አቤቱ ውኖች አዩህ ውኖች አይተው ፈሩ›› /መዝ.76$16/ ሐ. ድሆችና ምስኪኖች ውኃ ይሻሉ /ኢሳ.41$17/ መ. ‹‹ወይቤ ኩሎሙ እለ ጸምዑ ይሑር ኀበ ማይ፣ እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ሂዱ›› /ት.ኢሳ. 55$1/  ምሳሌው፡- ዘፍ.1$2፣ አክሲማሮስ ዘሐሙስ #ጌታችን_ለምን_ወደ_ዮሐንስ_ሄደ_ለምንስ_በዮሐንስ_እጅ_ተጠመቀ? 1. ትህትናን ለማስተማር፡ 2. ለአብነትና ሥርዐትን ሊደነግልልን፡- #ጌታችን_በማን_ስም_ተጠመቀ? ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ሌላውን ሰው በአንተ ስም፣ በባሕርይ አባትህ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቃለሁ አንተን ግን በማን ስም /ምን እያልኩ/ አጠምቅሃለሁ አለው›› ጌታችንም ‹‹ወልዱ ለብሩክ ከሳቴ ብርሃን ተሣሀለነ …፣ እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዐት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለን$ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየአትት ኃጢአተ ዓለም፣ እነሆ የዓለምን ሀጢአት የምታስወግድ የእግዚአብሔር በግ /መስዋዕቱ/ እያልክ አጥምቀኝ›› አለው፡፡ /ዮሐ. 1÷30/

#የእግዚአብሔርን_የቃል_ኪዳን_ታቦት_ሌዋውያን_ካህናት_ተሸክመውት_ባያችሁት_ጊዜ_ከስፍራችሁ_ተነስታችሁ_ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ ‹‹#አነ_ውእቱ_ኖላዊ_ሔር_ (እውነተኛ ጠባቂ እኔ ነኝ)፡፡››፤ #መድኀኔ_ዓለም_ዘደብረ_ሰላም፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መለያ ዓርማ:: መድኀኔ ዓለም ዘደብረ ሰላም፤ ታላቁ ደብር ከዓመት ዓመት ውዳሴና ማኀሌት የማይቋረጥበት (የጥምቀት በዓል ተረኛ በሚሆንበት እንኳን ሳይቀር በጃንሜዳና በቤተክርስቲያንችን በ2ቱም ቦታ ላይ ማኅሌት የሚቆምበት ቅዳሴ የሚቀደስበት)፤ ውዳሴ ማርያም፣ ከስተተ አርያምና መስተጋብዕ በዜማ ከዓመት ዓመት የሚደርስበት........ ኦ ደብረ ሰላም ኢይተዓፀዉ አናቅጽኪ፤ ኢይጸልም ፀሐይኪ፤ ወኢየዓርብ ወርኅኪ፤ ....... ይበራህ ውዳሴኪ ወማኅሌትኪ፥ ወያፍርሁ ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር ምዕመንኪ፥ ይብዝሁ ወይተግሁ በሰላም ወበጥዒና ማኅበረ ካህናትኪ ....... -ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀ ኔዓለም (በደብረ ሰላም በውስጧ መድኅ ኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡) -አብርሂ አብርሂ ደብረ ሰላም፤ ብርሃንኪ መድኀኔ ዓለም፡፡ (ብርሃንሽ መድኀኔ ዓለም ነውና ደብረ ሰላም ሆይ አብሪ ድመቂ፡፡)

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቀሳውስትና ዲያቆናት (አስተዳዳሪዎቹ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ፍቅረማርያም ምሕረቱ የደብረ ሰላም አስተዳዳሪና መልአከ ሰላም/ኋላ ሊቀ ሥልጣናት/ ቆሞስ ወልደ ሳሙኤል የመንበረ ጸባዖት አስተዳዳሪ ና መልአከ ገነት የመናገሻ ሀነተ ጽጌ አስተዳዳሪ/ (መስቀል ሲያሳልሙ የሚታዩት መነኰስ አባት የታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም መጋቤ/ (ጥቁር ሰናፊር የለበሱት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች)

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ዲያቆናትና ደባትር መዘምራን

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት የጥምቀት ተሰላፊዎች-አስተባባሪዎች

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት የጥምቀት ተሰላፊዎች-የሕብረት-2

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት የጥምቀት ተሰላፊዎች-የሕብረት