ወደ አላህ የምትመለሱበትን ቀን ፍሩ!!!
በአላህና በመጨረሻው ቀን አምኖ የሚኖር ሰው አኗኗርና የማያምን ሰው አኗኗር ይለያያል።
ለዛ ነው ጌታችን አላህ
{ተሰነቁ ከስንቅ ሁሉ በላጩ አላህን መፍራት ነው።} ሲል አማኞችን ያነቃቃው። ጭንቀቱን የአኼራ ጭንቀት ያደረገ አላህ የአኼራንም የዱንያውንም ጭንቀት ይበቃዋል። አላህ ዘንድ ያለው በላጭና በቂ ነው ፣ በአላህ ላመኑና በሱ ብቻ ለተመኩ።
• በአላህ የማያምነው በዱንያ ስግብግብነት የታሰረው ፣ በስልጣን ጥማት መከራው የሚያየው ፣ ሙስሊሙን ከሙስሊም ፣ወንድምን ከውንድሙ የሚያናክሰው የአመኔ ዱንያን ወዳዱ እስረኛማ ነገራቶችን የሚለካው ግላዊ በሆነው ጥቅም ነው።
تبا له ولأمثاله
ዱንያ ወዳድ የሆኑትን እስረኞች አላህ እንድህ ሲል ነበር የገለፃቸው።
﴿وَقالوا إِن هِيَ إِلّا حَياتُنَا الدُّنيا وَما نَحنُ بِمَبعوثينَ﴾ [الأنعام: ٢٩]
{እሷ የዱንያ ህይወት እንጂ ሌላ አይደለችም እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም አሉ።} ጌታችን አላህ መቀስቀስን የሚቃወሙትን ሰዎች ምሎ ትቀሰቀሳላችሁ በላቸው የሰራችሁት ይነገራችኋል ይህም
ለአላህ ቀላል ነው በላቸው ብሏል። የሰው ልጅ አገኘሁ ፣ ጎለበትኩ ፣ ጠነከርኩ ብሎ በጌታው ላይ አመፀኛ ይሆናል። ለአላህ አይከብድም እንጂ ቢከብድ ኖሮ የሚከብደው ሰማይ ምድርን መፍጠር ነበር ነገር ግን ብዙዎች አያውቁም አይገነዘቡም አይገባቸውም።
• አንተ የሰው ልጅ ሆይ! እናትህ መሀፀን ሆነህ የሚንከባከብህን ጌታ ትክዳለህን!!?
• ከናትህ መሀፀን እንድትወጣ መንገዱን ያገራልህን ታምፃለህን!!?
• በምድር ላይ ስትኖር አንተን ያጠነከረህ ያጎበተህ ስትታመም የሚያሽርህ ፣ ስትራብ የሚመግብህ ፣ ስትጠማ የሚያጠጣህ ፣ ነውርህን የሸፍንልህ ፣ የአእምሮ ባለቤት ያደረገህ ፣ ከሰዎች መሀል መርጦ ብሩህ እምነት የሰጠህን ጌታ ታምፃለህን!!?
√ አብሽር ከፊትህ የሰራሃትን የምታገኝበት ቀን አለ። የስራ መዝገብህን የምትይዝበትን ቀን ትደርስበታለህ።
አስተውል
•√ አይን እኔ ሀራም ተመልክቻለሁ በምትልበት ቀን እንደት ትሆን ይሆን!
•√ ጆሮ እኔ ሀራምን ሰምቻለሁ አዳምጫለሁ በምትልበት ለት እንደት ትሆን ይሆን!
•√ እጅ እኔ ሀራምን ጨብጫለሁ ይዣለሁ በምትልበት እለት እንደት ትሆን ይሆን!
•√ እግር እኔ ወደ ሀራም ተጉዣለሁ በምይልበት እለት እንደት ትሆን ይሆን!?
ሞት በጀነት እና በጀሀነም መካከል በሚታረድበት ለት ሁኔታዎች በሚቀያየሩበት እለት እንደት እንሆን ይሆን!!!!! ሞት ከታረደ ቡኃላ ይጠራል እናንተ የጀነት ሰዎች ሆይ! ተደሰቱ ሞት የለም ፣የእሳት ሰዎች ሆይ ተሰቃዩ ሞት የለም ይባላል። እኔና አንተ ከየትኞቹ እንሆን ይሆን!?
• ማረፊያህን አውቀህ ነው? እንድህ የምትደሰተው የምትፈነጨው?
• በየትኛው መልካም ስራ ተማምነህ ይሆን ቸልተኛ የሆንከው!?
ሞት ላይ አምነው ለኖሩ አምነው ለሰሩ እንድህ ይባላሉ
አንቺ የተረጋጋሽ ነፍስ ሆይ የወደድሽ እና የተወደድሽ ስትሆኚ ወደ ጌታሽ ውጪ ትባላለች
ጀነቴም ግቢ ትባላለች!!!
ጌታዬ አንተ ከውድ ባሮችህ አድርገን!
✍ደቃቅ
📎
https://t.me/bilu_man12