የታዋቂ ሰዎች ንግግር
Kanalga Telegram’da o‘tish
አለም ላይ የምናቃቸው የታላላቅ ሰዎች ንግግር ይቀርባል #share share እውነተኛ የጠቢባን ንግግር 🇪🇹😂😂😂😂😂😂🇪🇹 ♎️♊️♋️♐️♍️♒️♑️♈️🔱🔯♓️💢➗💠💡💤💨💦🕐🌟⭐️
Ko'proq ko'rsatish1 453
Obunachilar
-124 soatlar
-37 kunlar
-530 kunlar
Postlar arxiv
1 454
SkillMoney
Complete tasks and manage your rewards.
https://t.me/SkillMoney01_bot/earn?startapp=ref_C800CFE8
1 454
SkillMoney
Complete tasks and manage your rewards.
https://t.me/SkillMoney01_bot/earn?startapp=ref_C800CFE8
1 454
በአንድ ትምህርት ቤት መምህርቷ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበ ተማሪ ጫማ ሽልማት ለመስጠት ቃል ትገባና ፈተናው ተካሄደ ። በፈተናው ሁሉም ልጆች ተመሳሳይ ውጤት አስመዘገቡና ለሁሉም ጫማ መስጠት ስለማይቻል መምህርቷ አብሰለሰለች። ከዛም አንድ ሃሳብ መጣላት ፦ ለተማሪዎቹ ቁራጭ ወረቀት ሰጠቻቸው እና ስማቸውን በላዩ ላይ እንዲፅፉ እና በዕጣ እንዲለዩ ስማቸው የወጣለትም ጫማ እንድወስድ ወሰነች ። ሁሉም ጽፈው እንደጨረሱ መምህርቷ የሰበሰበችውን ወረቀት በኩባያ ውስጥ ነቀነቀቻቸውና በሁሉም ፊት አንድ ወረቀት መዘዘች። ወረቀቱን ስትከፍት መሎና ይላል ...ሁሉም ደስ አላቸው ። መሎናም በደስታ ተሞልታ ሽልማቱን ተቀበለች። መሎና እነዛን ጫማዎች በጣም ትፈልጋቸው ነበር ። በተቀደደው ባረጀው ጫማዋ በጣም ተሰላችታ ነበር ። አባቷ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል ...እናቷ ድሃና ረዳት የሌላት ስለነበረች ይህ ሽልማት ለሷ ትልቅ ትርጉም ነበረው።
ታርኩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ነገር ታዲያ እዚህ ጋር ነው ያለው ፦
መምህርቷ በኩባያ ውስጥ ያሉትን ሌሎች ወረቀትን ቀስ እያለች አንድበአንድ ስትመለከት እያንዳንዱ ልጅ በወረቀት ላይ የጻፈው የመሎናን ስም ነበር ።
✅ልባችን ንጹህ ስሆን ለኔ ማለትን ትተን ለኛ ማለት እንጀምራለን
✅ልጆች ንፁህ ነጭ ወረቀት ናቸው ጥላቻን ፣ ዘረኝነት አንስበካቸው
✅ፍቅርን መተሳሰብን እንዝራባቸው፣ ያኔ አለምን የተሻለ ቦታ ማድረግ እንችላለን ።
"ከቲክቶክ አለም የተወሰደ"
የልጆችን አይነት ልብ ይስጠን 🙏
<<መልካም ምሽት👋>>
@tebibangegr
1 454
ኢትዮጵያ ውስጥ ላይመለሱ የጠፉ ነገሮች:-
➤ ለህዝብና ለሃገር የሚያስብ ታማኝና ቅን መሪ
➤ የፈለግከው የሃገሪቱ ክፍል እንደ ልብህ ተንቀሳቅሶ መስራት
➤ ወጣቶች በሃገራቸው ላይ የነበራቸው ተስፋ
➤ በወር ደሞዝህ ሳትሳቀቅ ከወር ወር መቆየት
➤ በቀን ሶስት ግዜ መብላት
➤ ደስ የሚሉ የክረምት የልጅነት ጊዜያቶች
➤ ክረምት ት/ቤት ሲዘጋ ቤተሰብ ጋር ገጠር መሄድ
➤ በልጅነታችን የፈለግነው የሰፈራችን ቤት እየገባን ምሳና ቁርሳችንን እየበላን የምንውልበት
➤ የሰው ልጅ ዋጋ ከገንዘብ በላይ ነበር 😭😭
➤ ተምሮ ስራ መያዝ
➤ የአውዳመት ድባብ ፣ ቡና መጠጣት
📌 የቀረ ካለ ጨምሩበት....
መልካም ጊዜ እመኝላቹሃለሁ
💚💛❤️
1 454
ዳኛ ዑመር በጅግጅጋ ከተማ በታላቅ እና ደማቅ አቀባበል ተቀብለዋል።
በአቀባበሉ ላይ የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ ከንቲባው፣ የወጣቶች ሚኒስትር፣ የባምቤዳ ኃይል፣ የባህልና የሙዚቃ ቡድኖች እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
@tebibangegr
1 454
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘገበ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ነበር።
ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ/ም
1 454
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ! 🚨
ሰሞኑን በቴሌግራም ላይ እጅግ አደገኛ የሆነ የአካውንት ጠለፋ እና የማጭበርበር ድርጊት እየተፈጸመ ይገኛል።
በጣም ፀያፍ የሆኑ ምስሎችን እና ቪዲዮዎችን እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ ከስራቸው ሊንክ (Link) ያያይዛሉ።ሊንኩ የሚላክላችሁ ከማታውቁት ሰው ብቻ ሳይሆን፣ አካውንታቸው በተጠለፈ የቅርብ ጓደኞቻችሁ ወይም ዘመዶቻችሁ ስም ሊሆን ይችላል።
ከዚያ ሊንኩን ልክ እንደነካችሁት የእናንተም የቴሌግራም አካውንት ወዲያውኑ በሰከንዶች ውስጥ ይጠቃል፣ ከቁጥጥራችሁ ውጪ ይሆናል። ከዚያም በእናንተ ስም ለሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ቫይረስ ይልካል።
⚠️ስለዚህ ከማንኛውም ሰው (የምታውቁትም ይሁን የማታውቁት) የሚላክላችሁን ማናቸውንም አይነት ሊንክ በፍጹም አትንኩ! አትክፈቱ!
እባካችሁ ይህንን መረጃ ለምትወዷቸው ሰዎች ሁሉ በማጋራት ከጠላፊዎች ይታደጓቸው።
SHARE
@tebibangegr
1 454
አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ከዚህ ዓለም ድካም አረፈች
አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ባደረባት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች።
የአርቲስት ሰላማዊት ደስታ የሽኝት ፕሮግራም በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ዛሬ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ቤተሰቦቿ፣ ዘመዶቿ፣ ጓደኞቿና የሙያ አጋሮቿ በተገኙበት የሚከናወን ሲሆን የቀብር ስነስርአቱ ከቀኑ 7:00 ሰዓት በማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
1 454
የህይወት አርቲቡርቲ፥ ቅጥ ያጣ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት፥ ሰው ሰራሽ የኑሮ ውድነት፥ የዘረኝነት እንቶፈንቶ፥ የሃይማኖት አክራሪነት ለደቆሰው ለዚህ ህዝብ ደስታውን ስለሚደሰትበት መንገድ ቅድመ-ሁኔታ አታውጡለት።
ይህ ህዝብ ለአርሰናል አይደለም ማልያ በሬ ቢጥልለትም አሻሮ ከሰራው የውስጡ ብሶት ሊሸሽ ኳስ ስር ተሸሽጎ ውስጡ የሚያመነጭለትን dopamine ያጣጥምበት
በህይወቱ ሲያማርር፥ ኑሮ ከተባለ የማይገፋ ቋጥኝ ጋር ጡጫ ሲጋጠም፥ የቀለብና የቤት ኪራዩን ሊያገኝ ሲንደፋደፍ ምን አግዘኸዋል?ለየትኛው ብሶቱ ለማንኛው ጭንቀቱ መፍትሄ ዘይደህለት ነው ዛሬ በፌሽታው ቀን የደስታው ኬላ የምትሆንበት? እርሙን መደሰቻ አጥቶ በግራ የማይገታ የኑሮ ሰበዝ፥ በቀኝ የተተበተበ የዘረኝነት ትብታብ፥ ከፊቱ ድንግርግሩ የወጣ መፃኢ ተስፋ፥ ከኋላው ያልተቋጨ ሃገራዊ ስንክሳር እያግተለተለ በመሆንና ባለመሆን ለሚዋዥቅ ለዚህ ምስኪን ህዝብ ለምን ለደስታው ደረሰኝ ካልቆረጥኩልህ ትላለህ???
አርሰናልን ደገፈ ማለት ለተፈናቀሉ ወገኖቹ ስሜት አልባ ነው ማለት ይሆን እንዴ? በዋንጫው ስኬት አቅሉን እስኪስት አበደ ማለት ለሃገሩ ስሜት አልባና ባንዳ ትውልድ ተፈጠረ ማለትስ ነው?
አርሰናል ዋንጫ በልቷል አንተስ ቁርስህን በላህ?🙄🙄🙄 ላም ጥያቄ😏😏😏 ህይወት እስከ ምግብ መኖር እስከ እህል ድረስ ብቻ የሚመስላቸው አጋሰሶች ሃሳብ ነው።
ይሄ ህዝብ ደስታውን በዊድም ባገኘ🤲🤲🤲 በመከራው መመከሩ ሳያንስ፥ በስቃዩ መሳቀቁ ሳይጎድለው፥ በችጋር መከትከቱ፥ በአሳር መንከራተቱ ዕጣፈንታው እኮ አይደለም። በቃ ኢትዮጵያዊ by hook or by crook ይሳቅልኝ
ከጋራ ድል ይልቅ ለጋራ ሀዘን የታጨ፥ ከጋራ ስኬት ይልቅ ለወል ውድቀት ተላልፎ የተሰጠ ህዝቤ ለሳቅና ፌሽታው አርሰናል ምክንያት ከሆነ ከ"ያርግለት" በቀር ምንስ ሊባል🙏🙏🙏
አጉል ጥራዝ አትንጠቁ፥ ከልክ በላይ አትወቁ፥ ጦርነቱን ያልጀመረ ህዝብ የውጭ ኳስ ላይ ለምን ፈነጠዘ ተብሎ ሙሾ አይደረደርለትም።
የኑሮ ውድነቱን የፈጠረው በኢትዮጵያ የሚገኝ የአርሰናል ደጋፊ ይመስል በሰው ደስታ ተዝካር አትፍጠሩ።
አርሰናልን ስንከተል ያለፍነውን ስርጓጉጥ፥ የተሻገርነውን የሰቀቀን ድልድይ፥ የተጫነብንን ቋጥኝ፥ የተፎገርነውን ፉገራ እኛው ባለቤቶቹ በዘመናት ቁጥር ስር የሆንነውን ስለምናውቅ የሆንነው ላይ ያልነበራችሁ የደስታችን ትራፊኮች ተዉን እንለፍበት🤲🤲🤲
የሰው ልጅ passion የሚባል ነገር አለው የኔ passion ኳስ መመልከት ነው ያንተን passion የመተቸት መብት የለኝም፤ እኔ የሚመቸኝ የግድ እንዲመችህ አላስገድድህም።
ብዙ የተባልንበት፥ ልጅነቴን የተዋደቅኩለት፥ ከእኩዮቼ የተሟገትኩለት፥ እራቴን ያልበላሁለት፥ ጅማቴ እስኪገተር የጮህኩለት የኔው አርሰናል ዋንጫውን በክብር አንስቷል
የፈረንጅ ሃገር ኳስ፥ ነጫጭባ ለሚራገጠው፥ አርሰናል ቁርስ አይገዛልህም ጂኒ ጃንካችሁን ተዉትና ሰዉን ለምርጫው ተዉት። የውጭ ሙዚቃን ሆነ ፊልም ስታሳድዱ ልክ የውጭ ኳስ ስንደግፍ ስህተት🤣🤣🤣🤣 ሄችሄችሄችሄች
"ለመደሰት ምክንያት ባይኖረን እንኳን ሰበብ እየፈጠርን እንደሰትበት" ፍሊስ...ፍሊስ🤲🤲
1 454
ትዳርን የምገድሉ 18 ነገሮችን እኔሆ
1. ስንፍና ትዳርን ያፈርሳል።
2. ጥርጣሬ ትዳርን ያፈርሳል።
3. እምነት ማጣት ትዳርን ያፈርሳል።
4. እርስ በርስ አለመከባበር ትዳርን ያፈርሳል።
5. ይቅር አለማለት፣ ቂም፣ ጥላቻ፣ ክፋትና ቁጣ ትዳርን ያፈርሳሉ።
6.አላስፈላጊ ክርክር ትዳርን ያፈርሳል።
7. ከትዳር አጋርህ ምስጢር መደበቅ ትዳርን ያፈርሳል።
8. ማንኛውም ዓይነት ክህደት (በገንዘብ፣ በስሜት፣ በሥነ-ልቦና ወይም በሌላ) ትዳርን ያፈርሳል።
9. ውሸት ትዳርን በቀላሉ ያፈርሳል፤ በሁሉም ነገር ለትዳር አጋርህ ቅን ሁን።
10. ከትዳር አጋርህ ይልቅ ከወላጆችህ/ቤተሰብህ ጋር ብዙ መቀራረብ ትዳርን ያፈርሳል።
11. የግብረ ሥጋ ግንኙነት እጥረት፣ ወይም አለመደሰት ትዳርን ያፈርሳል።
12. ብዙ እና ጥንቃቄ የሌለው ንግግር ትዳርን ያፈርሳል።
13. ከትዳር አጋርህ ጋር ትንሽ ጊዜ ማሳለፍ ትዳርን ያፈርሳል።
14. ገንዘብ፣ ያለ እቅድ ግዢና የገንዘብ ዲሲፕሊን ማጣት ትዳርን ያፈርሳል።
15. የትዳር አጋርህን ድክመት ለወላጆች ወይም ለእህት ወንድሞች ማጋለጥ ትዳርን ያፈርሳል።
16. በመንፈሳዊ ሕይወት ጽኑ አለመሆንና አብሮ አለመጸለይ ትዳርን ብቻ ሳይሆን ሕይወትንም ይጎዳል።
17. ማማረር ፣ ተግሣጽና እና እርማት አለመቀበል ትዳርን ያፈርሳል።
18. የእግዚአብሔርን ቃል አለማወቅና አለመታዘዝ ትዳርን ያፈርሳል።
1 454
ጧት
------
ራሱን ጎዝጉዞ
ራሱን አንጥፎ
ራሱ ላይ አድሮ
ሰው በጧት ይነቃል
ተስፋና ብልቱን
አንድ ላይ ገትሮ
-----------
የመፀሀፍ ርዕስ: የቀንድ አውጣ ኑሮ!
ይስማዕከ ወርቁ
1 454
ዳስ ጣል (አንሳው)
ዳስ ጣል ልቤ፣ ለውስጤ ሀዘን ለቅሶ
ሰው አይችልህ ደርሶ
አለ ጊዜ፣ ገና ነው እያልኩት
እራሴን በደልሁት
ለካ እንዲህ ነው ማለቅ፣ እህ እያሉ ነዶ
ሀገር የሞተበት፣ የት ያለቅሳል ሄዶ?
ዳስ ጣል
ዳስ ጣል
ዳስ ጣል ልቤ
ለውስጤ አዘን ለቅሶ
ሰው አይችልህ ደርሶ
አለ ጊዜ፣ ገና ነው እያልኩት
እራሴን በደልሁት
ለካ እንዲህ ነው ማለቅ፣ እህ እያሉ ነዶ
ሀገር የሞተበት፣ የት ያለቅሳል ሄዶ?
ዳስ ጣል
ዳስ ጣል
አክሱም ላሊበላን፣ በአንድ አለት አጽንቶ
አልራመድ አለ፣ ሀገር ተለያይቶ
ምሰሶው ዘመመ፣ ጣራውም ያፈሳል
ሀገር የሞተበት፣ የት ሄዶ ያለቅሳል!
ባሳደገኝ ቅየ፣ ባደኩበት መንደር
ባይተዋር ሰው ሁኜ፣ እንደሌለው ሀገር
ያቆምኋትን ሰንደቅ፣ ተፈትኜ በእሳት
እንዴት አቀርቅሬ፣ ባንዲራዬን ላንሳት
አባይ ለዘዴው፣ በአፍ ይቀድማል
አምኖ መከዳት፣ እንዴት ያማል
ወርቅ ያበደረ ደርሶት አለት
እንዴት ይችላል ዝም ማለት
ከነገ ዛሬ፣ ይሻል ባልኩኝ
የራሴን ጩኸት፣ ተነጠቅኩኝ
ተጣላሁና ከወንዜ አድባር
እንዴት ልታረቅ፣ ከራሴ ጋር
አዲስ አበባ፣ አዶ ሸገሩ
እንኳን ሸገሩ
የሁሉ አይደል ወይ? ሞላው ሀገሩ
በፍቅር ጠርተው፣ ከዳር እስከ ዳር
መሃል ገቡና፣ አቆሙን ከዳር
ባቆዩት ሀገር፣ ጀግኖች በአንድነት
በአርበኝነት
እንዴት ይገፋ፣ ኢትዮጵያዊነት
ኧ . . . ኧ . . . ና ና
ባቆዩት ሀገር ፣ ጀግኖች በአንድነት
እንዴት ይገፋል፣ ኢትዮጵያዊነት
1 454
''ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም''
''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ''
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የቻናላችን ቤተሰቦች በሙሉ ፥ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት በዓል ይሁንልን አሜን።
@tebibangegr
1 454
Repost from ETHIO IPTV
😂 ፆም ሊፈታ እንጂ ፤ ፆም ሊያዝ መሰላቸው እንዴ
🤔 በሬ 300ሺ ፣ በግ 35ሺ ፣ ዶሮ 3500
💥 በቂቤ አይፈታም እንዴ ካልበላቹ ትሞታላቹ አልተባልን እንደውም ስጋ ማብዛት በሽታ መሸመት ነው!!
😭 እኔ ከነጋዴው በላይ በዚ ዋጋ የሚገዛው አጋሰስ ህብረተሰብ ነው ደሜን ሚያፈላው!
@ETHIOIPTV1206
1 454
ከዛሬ 12 ሰአት ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ጭማሪ ተደርጓል‼️
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገዉ 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ባስተላለፈዉ የነዳጅ ዉጤቶች የዋጋ ግንባታ የአፈፃፀም ዉሳኔ መሠረት የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በየጊዜዉ እየተከለሰ ስራ ላይ እንዲዉል ሲደረግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት የአለም የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከመጋቢት 23/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የአዲስ አበባ ከተማ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዚህ በታች በተቀመጠው ሠንጠረዥ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ በመንግሥት የተወሰነ መሆኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።
