cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
35 707
Obunachilar
+1424 soatlar
+447 kunlar
+87330 kunlar
Postlar arxiv
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶችን ጠለፋ በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ስጋት አድሮባቸዋል ተባለ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶች ጠለፋ መባባሱ ተገለጠ። በክልሉ ኮሬ ዞን ውስጥ «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ አስተማሪ የሆነ ቅጣት እንደማይሰጥ ያመለከቱት ወገኖች በአሁኑ ጊዜ ሴት ልጆች ወጥተው ለመግባት ስጋት እንደሆነባቸው ዳጉ ጆርናል ከዶቼ ቬለ ዘገባ ተመልክቷል። ስማቸው ያልተገለጸ አንድ አባት ከትምህርት ቤት የምትመለስ ልጃቸው በስድስት ወንዶች ከመንገድ መወሰዷን ነው የተናገሩት። ጉዳዩን በሕግ ለመፍታት ያደረጉት ጥረትም አለመሳካቱንም አመልክተዋል። በተጠቀሰው ዞን በያዝነው ግማሽ ዓመት ብቻ ተጠልፈዋል የተባሉ የ 24 ልጃገረዶች ሥም ዝርዝር ይፋ መደረጉን ተከትሎ ወላጆችና የህዝብ ተመራጮች በዞኑ የሕግ አካላት ላይ ጫና እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል። #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😢 9🤬 3👍 2😁 2💔 2🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶችን ጠለፋ በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ስጋት አድሮባቸዋል ተባለ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶች ጠለፋ መባባሱ ተገለጠ። በክልሉ ኮሬ ዞን ውስጥ «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ አስተማሪ የሆነ ቅጣት እንደማይሰጥ ያመለከቱት ወገኖች በአሁኑ ጊዜ ሴት ልጆች ወጥተው ለመግባት ስጋት እንደሆነባቸው ዳጉ ጆርናል ከዶቼ ቬለ ዘገባ ተመልክቷል። ስማቸው ያልተገለጸ አንድ አባት ከትምህርት ቤት የምትመለስ ልጃቸው በስድስት ወንዶች ከመንገድ መወሰዷን ነው የተናገሩት። ጉዳዩን በሕግ ለመፍታት ያደረጉት ጥረትም አለመሳካቱንም አመልክተዋል። በተጠቀሰው ዞን በያዝነው ግማሽ ዓመት ብቻ ተጠልፈዋል የተባሉ የ 24 ልጃገረዶች ሥም ዝርዝር ይፋ መደረጉን ተከትሎ ወላጆችና የህዝብ ተመራጮች በዞኑ የሕግ አካላት ላይ ጫና እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል። #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 5😢 5 1
"ታማሚው ስለማይድን የተሰበሰበውን ብር ሰይጣን አሳስቶን አጠፋነው. . ." ይህንን ያለው 9,000 ሰው ተሰብስቦ በሚመለከተው የቲክቶክ ሽምግልና ላይ ነው። ከሞተር ወድቆ ከወገብ በታች ለማይንቀሳቀሰው አለሙ ቢጫ የተባለ ታማሚ ግለሰብ የተለያዩ ታዋቂ ቲክቶከሮች የእርዳታ ገንዘብ ቢሰበስቡም ለታማሚው ብር ሳይደርስ ቀርቶ ታማሚው ባቀረበው ተማፅኖ ብሩን የሰበሰቡት ቲክቶከሮች የተወሰነ ብር ቢመልሱም ዋነኛው ወጣት ግን 350,000 ሺህ ብር አካባቢ ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም። ለዚህም የቀረበው ምክንያት " ታማሚው ስለማይድን ብሩን አጥፍቼዋለሁ . . . ቲክቶክ አካውንቴን ሸጬ እከፍላለሁ" ብሏል። Via: ስንታየሁ ኃይሉ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
🤬 81👍 16😁 11💔 7😢 6👎 4🤔 4 3
በቦኮሃራም የታገተችው ናይጄሪያዊት ተማሪ ከ10 ዓመት በኋላ ሦስት ልጆችን ወልዳ ነጻ ወጣች ከአስር ዓመት በፊት በቦኮሃራም ታጣቂዎች ታግተው ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዷ የሦስት ልጆች እናት ሆና በናይጄሪያ መንግሥት ወታደሮች ነጻ ወጣች።በአውሮፓውያኑ ሚያዝያ 2014 ቦርኖ ከምትባለው ከተማ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች 276 ተማሪ ሴቶችን ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤታቸው አፍነው መውሰዳቸው ይታወሳል። እነዚህ የቺቦክ ትምህርት ቤት ሴት ልጆች መታገት መላው ዓለምን አስደንግጦ በወቅቱ የአሜሪካ ቀዳማዊ እመቤት የነበሩትን ሚሼል ኦባማን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የማስለቀቅ ዘመቻ እንዲጀመር ምክንያት ሆኖ ነበር።ታፍነው ተወስደው ከነበሩት 280 ከሚጠጉት ልጃገረዶች መካከል አስካሁን ድረስ 100 የሚሆኑት በታጣቂዎቹ ቁጥጥር ስር ናቸው ወይም የደረሱበት አልታወቀም።ትናንት ሐሙስ ደግሞ የናይጄሪያ ሠራዊት ከአስር ዓመት በፊት ከታፈኑት ተማሪዎች መካከል አንዷን ከሦስት ልጆቿ ጋር ከታጣቂዎቹ ነጻ ማውታቱን አስታውቋል።ታጋቿ ሦስት ልጆቿ በተጨማሪም የአምስት ወራት ነፍሰ ጡር መሆኗን ሠራዊቱ ገልጿል። በቦኮ ሃራም ቡድን ታፍነው ከተወሰዱ ሴት ተማሪዎች መካከል አስካሁን ከ180 በላይ የሚሆኑት በሰሜን ምሥራቅ ናይጄሪያ ውስጥ ከምትገኘው ቦርኖ ግዛት የቡድኑ መደበቂያ ሳምቢሳ ጫካ በፀጥታ ኃይሎች ነጻ ወጥተዋል ወይም ከቡድኑ አምልጠዋል።አስካሁን ከቡድኑ ነጻ ከወጡ ልጃገረዶች መካከል አንዳንዶቹ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ ማርገዛቸው ወይም ልጅ መውለዳቸው ተዘግቧል።የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ጠልፈው የሚወስዷቸውን ተማሪዎች በወሲብ ባርነት ስር ያቆይዋቸዋል የሚሉ ዘገባዎች በተደጋጋሚ ሲወጡ መቆየታቸው ይታዋል። ወደ ቤታቸው ከተመለሱት መካከልም የተወሰኑት የናይጄሪያ ባለሥልጣናት የሚያስፈልጋቸውን እንክብካቤ እና ድጋፍ እንዳላደረጉላቸው በመግለጽ መንግሥትን ይታቻሉ።በናይጄሪያ ውስጥ አሁንም የጅምላ አፈና ተማሪዎችን እና ወላጆችን የሚያሳስብ ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል። የተለያዩ ወሮበላ ቡድኖች ተማሪዎችን ዒላማ በማድረግ ጠልፈው እየወሰዱ ማስለቀቂያ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው የተለመደ ነው።በሴቭ ዘ ችልድረን በጎ አድራጎት ድርጅት መረጃ መሠረት ከአውሮፓውያኑ 2014 አስከ 2022 ድረስ በናይጄሪያ ውስጥ ከ1,680 በላይ ተማሪዎች ታግተዋል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 39💔 20😢 9😁 4 2
Photo unavailableShow in Telegram
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
ቀላል በሚመስሉ ስህተቶች በ10 ሺዎች ለሞት መማገዳችን ማቆም አለበን - አቶ ጌታቸው ረዳ በታሪክ አጋጣሚ ህዝብን ለመምራትም ሆነ ለማደናገር እድል ያገኘን ሰዎች በምንፈፅማቸው ቀላል እሚመስሉ ስህተቶች በአስር ሺዎች ለሞት መማገዳችን ማቆም አለብን ሲሉ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በይፋዊ የፅህፈት ቤታቸው የፌስቡክ ገፅ ማጋራታቸዉን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል። በፅሑፋቸውም በአስር ሺዎች ለሞት መማገድ እንድናቆም ደግሞ ከሁሉም በላይ በየ30 ዓመቱ ከኋላችን እየተከተለ በሺዎች መስዋእትንት እንድንከፍልና በጥፋት ጫፍ ላይ እንድንደርስ እሚያደርገንን ነገር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ አለብን ብለዋል። ይህ እንዲሆን ከተፈለገ ደግሞ የፖለቲካ መንገዳችን እስከወድያኛው ሊቀየር ይገባዋል ለዚህም መስራት አለብንም ሲሉም ተደምጠዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሰሞኑን በርከት ያሉ ልጥፎች በፅህፈት ቤታቸው ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ በማጋራት ላይ እሚገኙት አቶ ጌታቸው በትናትናው ዕለትም በተመሳሳይ ውስጥህን ሳትፈትሽ በተለመደው መንገድ ለውጥ እንዲመጣ መጠበቅ ስህተት ነው ያሉ ሲሆን ችግሩ እንዲፈጠር አስተዋፅኦ ያደረገ አስተሳሰብና አረዳድ ይዘህ አጥጋቢ ምላሽ ለመስጠት እንደሚከብድ እሚረዳ አካሄድ ሊኖረን ግድ ይላልም ብለዋል። በሚሊዮን ሙሴ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 76🕊 10👎 9😁 5 2👏 1
በሸዋሮቢት ከተማ ከሚገኙ 20 የለስላሳ መጠጥ ማከፋፋያ ተቋማት ዉስጥ አራቱ ጊዜው ያለፈበት ምርት ሊያሰራጩ ሲሞክሩ ተያዙ የሸዋሮቢት ከተማ ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት የጊዜ ገደባቸው ያለፈባቸውን የተለያዮ ምርቶች ላይ እርምጃ የወሰደ ሲሆን  በ20 የንግድ ተቋማት ባደረጋቸው የፍተሻ ስራ አራቱ ጊዜው ያለፈበት መጠጦችን ሊያከፋፍሉ ሲሞክሩ መያዛቸው ተገልጿል፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተፈራ ሲያምረኝ  በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደገለጹት  የተያዙት መጠጦች  የለስላሳ ምርት የሚገኙበት ሲሆን  500 ሊትር  የሚሆን መጠን እንደተወገደም  ገልጸዋል፡፡ ህገ ወጥ ድርጊቶችንና የጊዜ ገደብ ያለፈባቸውን ምርቶች ወደ ተጠቃሚ ከመድረሳቸው በፊት በ20 የጅምላ አከፋፋዮች ላይ በተደረገ የአሰሳና ፍተሻ ስራ  የጁስና የለስላሳ መጠጦቹን  መሰብሰብ ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ጊዜያቸው አልፎ ከተገኙት ምርቶች ጋር ቸኮሌት እንደሚገኙበትም ተጠቁሟል፡፡ በመኆኑም  ማህበረሰቡም ጊዜው ያለፈባቸውን ምርቶች ከመጠቀም ራሱን እንዲጠብቅና  በቀጣይም ህገወጥ ድርጊቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር ጤናማ የንግድ ስርአት ለመዘርጋት ማኅበረሰቡም ከፍተኛ ርብርብ ሊያደርጉ እንደሚገባ  ገል  ጸው አሁንም የቁጥጥር ስራውን በተለያዩ  ተቋማት ላይ እያካሄዱ መሆኑንም  አቶ ተፈራ ሲያምረኝ ጨምረውም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡ በኤደን ሽመልስ #
Hammasini ko'rsatish...
👍 28👏 21 3
የአንድ አመት ልጁን ከእነ ህይወቷ ለመቅበር የሞከረው ወላጅ አባት በቁጥጥር ስር ዋለ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ  ኮሶል ቀጭን መንደር ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረው  ፀብ ምክንያት የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም ሙከራ ማድረጉን ፖሊስ አታውቋል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረ ጊዜያዊ ፀብ እናት  የአንድ ዓመት ሴት ህፃን ልጅ ጥላ በመጥፋቷ ወላጅ አባት ቲቲዮስ ኪያግላስ የተባለው ተጠርጣሪ የአንድ ዓመት ህፃን ልጁ እያለቀሰች ስታስቸግረዉ በሁኔታው ተበሳጭቶ የአንድ አመት ልጁን  በህይወት ለመቅበር ጉድጓድ  ሲያዘጋጅ የተመለከቱ የአከባቢው ነዋሪዎች  ለፖሊስ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጸዋል። ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪውን  ጉድጓድ እየቆፈረ እያለ በቁጥጥር  ስር እንዲውል በማድረግ ህፃኗን ጉዳት ሳይደርስባት መታደግ መቻሉንና በተጠርጣሪው ላይ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል። ፖሊስ የህፃኗን ወላጅ እናት አፈላልጎ ማስረከቡን የክልሉ  ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😢 45👍 17🤬 16🤔 10😱 4 3🤯 3
የሸኔ ታጣቂዎች የብርጌድ አመራር ነበር የተባለዉ ዋቅቶላ ወርቁ በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር ዋለ 👉🏼ታጣቂ ቡድኑ ወደ ሌሎች አከባቢዎች በመንቀሳቀስ አደረጃጀት ለመፍጠር ሙከራ እያደረገ መሆኑ ተነግሯል በምዕራብ ጉጂ ዞን የሚንቀሳቀሰው የሸኔ ታጣቂ ቡድን የብርጌድ አመራር ነበር የተባለዉ ዋቅቶላ ወርቁ በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ሀይሌ ለዳጉ ጆርናል ተናግረዋል። ግለሰቡ ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በሶዶ ከተማ ላይ መያዙን ኢንስፔክተሩ ገልጸዋል። ዋቅቶላ ወርቁ በቁጥጥር ስር የዋለዉ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት የፌደራል ፖሊስና ከደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ በሰሩት የክትትል ስራ መሆኑን አክለዋል። ግለሰቡ በምዕራብ ጉጂ ቡድኑ እየተበታተነ በመምጣቱ በመሸሽ ኤፍሬም ዘገየ እና ኬና ዋቆ ከተሰኙ ግብረአበሮቹ ጋር ወደ ሶዶ ከተማ መግባቱን ገልጸዋል። ቡድኑ ወደ ሌሎች አከባቢዎች በመንቀሳቀስ አደረጃጀት ለመፍጠር ሙከራ እያደረገ መሆኑን ከክልሉ ፖሊስ መረጃና ኢንተለጀንስ ዳሬክቶሬት የደረሰን መረጃ አመላክቷል። ግለሰቡም ወደ ሶዶ ከተማ የመጣበት ሌላኛዉ ምክኒያት ገንዘብና ቁሳቁስ ለማሰባሰብ ብሎም አባላትን ለማደራጀት በአርባምንጭ ከተማ በኩል በማድረግ ወደ ሶዶ መግባቱን ጠቅሰዋል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት ግብረአበሮች ዉስጥ አንዱ በእዛዉ በሶዶ ከተማ ነዋሪ እና የሸኔ ቡድን ደጋፊና አባል ነበርም ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ሀይሌ ጨምረዉ ዳጉ ጆርናል ተናግረዋል። #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 42👏 9 4😁 1
እስራኤል በኢራን እስፋሃን ከተማ በፈፀመችው ጥቃት የኒውክሌር ጣቢያ ላይ ጉዳይ አለመድረሱን ቴህራን አስታወቀች የኢራን አየር መከላከያ ሶስት ትናንሽ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በማዕከላዊ እስፋሃን ከተማ ላይ ከአየር እንዳወረደ አስታውቋል። የኢራን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ይህንን የዘገቡት የዩናይትድ ስቴትስ ብሮድካስተሮች ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣናትን ጠቅሰው ከሰአታት በፊትላ የእስራኤል ሚሳኤሎች በኢራን ጥቃት መፈፀማቸውን ተከትሎ ነው።የኢራን መንግስታዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ የአየር መከላከያ ስርዓቱ በንቃት ላይ መሆኑን በመግለፅ ዛሬ ረፋድ ድረስ ዋና ከተማይቱን ቴህራን እና ኢስፋሃንን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በረራዎች መቋረጣቸውን ዘግቧል። አደጋው ከደረሰ ከአራት ሰአት ተኩል በኋላ የአየር ክልል የተከፈተ ሲሆን በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል። የኢስፋሃን ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን ሁለተኛ ብርጋዴር ጄኔራል ሲያቫሽ ሚሃንዱስት ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደተናገሩት የአየር መከላከያ ስርዓቶች አጠራጣሪ ነገር ማሳየታቸውን ተከትሎ የተሰነዘረው ጥቃት ምንም አይነት ጉዳት አላደረሰም ብለዋል። ቀደም ሲል ኤቢሲ ኒውስ የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለስልጣንን ጠቅሶ እንደዘገበው እስራኤል ኢራን ውስጥ በሚገኝ ቦታ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መሰንዘሯን አስታውቋል። የአውሮፓ ህብረት ዋና ፀሀፊ ኡርሱላ ቮን ደር ሌየን እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ፈፅማለች የሚለውን ዘገባ ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ ተጨማሪ ውጥረት እንዳይከሰት ለመከላከል ጠይቀዋል።የቻይና መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊን ጂያን እንደተናገሩት ቤጂንግ “አግባብነት ያላቸውን ሪፖርቶች” አስተውላለች በማለት ውጥረቱን የበለጠ የሚያባብሱ ማንኛውንም እርምጃዎችን ትቃወማለች ሲሉ ገልፀዋል። የኦማን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢራብ ኢስፋሃን ከተማ ላይ የተፈፀመውን "የእስራኤል ጥቃት" በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል። ኦማን "በተጨማሪም የእስራኤልን ተደጋጋሚ ወታደራዊ ጥቃቶችን እንደምታወግዝ አስታውቃለች። የባህረ ሰላጤ ሀገር የሆነችው ኦማብ በኢራን እና በምዕራባውያን ሀገራት መካከል ለረዥም ጊዜ የሸምጋይነት ሚና ስትወጣ ቆይታለች። የኢራን መንግስት የዜና አውታር ፕረስ ቲቪ እንደዘገበው በኢስፋሃን ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው የኒውክሌር ጣቢያ ላይ ምንም አይነት ፍንዳታ ወይም ጉዳት በጥቃቱ አልደረሰም ብሏል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 49 7
Photo unavailableShow in Telegram
ከእኔ ጋር የፍቅር ጓደኛነት ለመቀጠል አልፈለገችም በማለት የግብረ-ስጋ ግንኙነት በመፈጸም አንገቷን አንቆ የገደለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ ከእኔ ጋር በፍቅር ጓደኝነት ለመቀጠል ፈቃደኛ አልሆነችም በሚል የ17 አመቷን የግል ተበዳይ አስገድዶ የግብረ-ስጋ ግንኙነት በመፈጸም ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገ ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጥቷል። አብዱ ኪያር ዩሱፍ የተባለው ተከሳሽ በጳጉሜን 01 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 6፡30 ሰዓት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰፈራ ቀርሳ ቢላ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የግት ተነዳይን አንገቷን አንቆ በመያዝ በአካባቢው ወደሚገኝ ካባ በሚወስዳት ጊዜ ላለመሄድ ስትታገለው ነበር። ግለሰቡ የግል ተበዳይ ጩኸት ስታሰማ በድጋሚ በልብስ ማሰሪያው ጨርቅ አንገቷን አጥብቆ በመያዝና እራስዋን እንዳትከላከል በማድረግ የግብረ-ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና አንገቷን በእጅ እና በልብስ የወገብ ማሰሪያ ጨርቅ በማነቅ ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል። በዚህም ግለሱቡ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶበት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 11ኛ ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቶ በክርክሩ ሂደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ እንደሌለው በመግለጹ ፍርድ ቤቱ ለሰራው ወንጀል በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 55👎 10🤬 9 2💔 2😁 1🤯 1
Photo unavailableShow in Telegram
እስራኤል በኢራን ላይ የሚሳኤልና ድሮን ጥቃት ፈጸመች እስራኤል ከሰሞኑ ከኢራን ለተፈጸመባት ጥቃት የአጸፋ ምላሽ በሚመስል መልኩ በኢራን ላይ በዛሬው እለት የሚሳኤልና ድሮን ጥቃቶች የአጸፋ እርምጃ መውሰዷ ተሰምቷል። ኢራን ባሳለፍነዉ ሚያዝያ 1 ቀን እስራኤል ሶሪያ በሚገኘው የኢራን ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ላይ ባደረሰችው ጥቃት 13 ዜጎቿ መገደላቸውን ተከትሎ በእስራኤል ላይ ባሳለፍነው ቅዳሜ 300 ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት ማድረሷ ይታወሳል። እስራኤል በዛሬዉ የአጸፋ ምላሿ ኢስፋሃን በተባለ የኢራን አካባቢ ባሉ ወታደራዊ ካምፖች ላይ ነዉ የድሮኖች ጥቃት የፈጸመችዉ። በአንጻሩ የኢራን መንግስት የተሰነዘረበትን ጥቃት የጸረ-ሚሳኤል መከላከያ በማስወንጨፍ ሦስት ድሮኖች መትቶ መጣሉን አስታዉቋል። ለኢራን ጥቃት የእስራኤል መንግስት አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ዝቶ እንደነበርም የሚታወስ ሲሆን የተለያዩ ሀገራት እስራኤል ጉዳዩን በሰከነ መንገድ እንድትይዝ ሲወተዉቱ ቆይተዋል። እስራኤልን በኢራን ላይ ያደረሰችዉን ጥቃት ተከትሎ የአየር በረራዎች ተስተጓጉለው እንደነበርና በአሁኑ ሰዓት በረራ መጀመሩ ተነግሯል። እንዲሁም አካባቢው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሱን የአልጃዚራ ዘግቧል። የሁለቱ አገራት የሰሞኑ ግጭትን ተከትሎ አገራት ዜጎቻቸውን ወደ እስራኤል እንዳይጓዙ  እያስጠነቀቁ ይገኛሉ። የሁለቱ አገራት የሰሞነኛ ፍጥጫ በቋፍ ላይ የነበረ ሲሆን ዉዝግባቸዉ ወደ ይፋዊና ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ የገባ መስሏል። እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ማደረሷ ቢዘገብም በተመሳሳይ ኢራቅ እና ሶሪያም የእስራኤል ቡጢ ያረፈባቸው ሀገረት ናቸዉ ሲል አልጀዚራ አስነብቧል። ሁለቱ ሀገራት ላይም ከባድ ፍንዳታዎች መከሰታቸዉ በዘገባው ተጠቅሷል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 48👎 21🕊 10😢 6😱 5 1🔥 1🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
በጃኔቫ ፤ በመንግስት ላይ የተቃዉሞ ድምጽ ያሰሙ ሰዎችን የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት አወገዘ በጃኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት፣ ማክሰኞ'ለት ለኢትዮጵያዊያን ተረጂዎች ገንዘብ ለማሰባሰብ ጄኔቫ ውስጥ በተካሄደው ዓለማቀፍ መርሃ ግብር ላይ የተወሰኑ ኢትዮጵያዊያን ተቃውሞና ጩኸት ማሰማታቸውን አውግዟል። አራቱ ትዉልደ ኢትዮጵያዊያን ሰዎች በጉባኤው ተገኝተዉ በኢትዮጵያ እየደረሱ ናቸዉ ያሏቸዉን ጉዳዮች በመጥቀስ በጭኸት ስብሰባውን አዉከዉ እንደነበር ዳጉ ጆርናል መዘገቡ አይዘነጋም። ፖሊስ ጩኸት ያሰሙትን ኢትዮጵያዊያን ይዞ ከአካባቢው እንዳራቃቸው ጽሕፈት ቤቱ ገልጧል። ጽሕፈት ቤቱ፣ ለድርቅ ተጎጂዎች ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ እርዳታ በሚያሰባስብበት መድረክ ላይ ጩኸት ማሰማት፣ የአገር ጠላትነት ፖለቲካ እንጂ የተቃውሞ ፖለቲካ አይደለም በማለት ተችቷል። የኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ፣ ባልተገባ ቦታ ጩኸት በማሰማት "አገር አዋራጅ" የኾነ ድርጊት የሚፈጽሙ ግለሰቦችን ሊቃወማቸው እንደሚገባም ጽሕፈት ቤቱ አሳስቧል። ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤቱ፣ በአገር ክብር ላይ እጃቸውን የሚዘረጉ ግለሰቦችን በሕግ አግባባብ የምጠይቅበትን አሠራር እከተላለሁ በማለትም አስጠንቅቋል። Via ዋዜማ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😁 73👍 40👎 23👏 4 2
Photo unavailableShow in Telegram
የፍልስጤም እግር ኳስ ማህበር በጋዛ ወረራ የተነሳ ፊፋ እስራኤልን እንዲያገል ጠየቀ 👉 የፍልስጤም የተባበሩት መንግስታት ሙሉ አባልነት ጥያቄ ላይ አርብ እለት ድምጽ ይሰጣል የፍልስጤም እግር ኳስ ማህበር (ፒ ኤፍ ኤ) ለዓለም እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ፊፋ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት በእስራኤል እግር ኳስ ማህበር ውስጥ ያሉ ባለስልጣናት "በጋዛ ውስጥ ለተፈጸመው የዘር ማጥፋት ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚሰጡ የሚያመለክቱ" የማህበራዊ ሚዲያ ጽሁፎችን አጋርቷል፡፡ "በጋዛ ውስጥ ያሉት ሁሉም የእግር ኳስ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል ወይም በከባድ ሁኔታ ተጎድተዋል፣ በእስራኤል ወረራ ወደ ማጎሪያ ካምፕ የተቀየረውን የአል-ያርሙክን ታሪካዊ ስታዲየም ጨምሮ ከአንድ በላይ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ጉፋትን በሰነድ በማስደገፉ ማቅረቡን" የፍልስጤም እግር ኳስ ማህበር ተናግሯል። የእስራኤል እግር ኳስ ማህበር በሊጋው ውስጥ የሚደርሰውን አድልዎ እና ዘረኝነት ላይ እርምጃ መውሰድ አልቻለም፣ይህም የፊፋ ህግጋትን አንቀጽ 3 በቀጥታ የሚጥስ ነው ሲል አክሏል።ከኢየሩሳሌም የመጣ አንድ የእስራኤል ቡድን “እስራኤል ውስጥ እጅግ ዘረኛ ቡድን እንዴት እንደሆነ በኩራት ይዘምራል። ለተቃዋሚ ቡድኖች በሚጫወቱት አረቦች ላይ እንደ ‘አሸባሪ’ ያሉ ፅሁፎችን ያሰማሉ” ሲል የፍልስጤም እግር ኳስ ማህበር ተናግሯል። በሌላ በኩል የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ቤጂንግ ፍልስጤም የተባበሩት መንግስታት ሙሉ አባል እንድትሆን ትደግፋለች ሲሉ ተደምጠዋል።ዋንግ ከኢንዶኔዥያ አቻቸው ጋር በጃካርታ ያደረጉትን ቆይታ ተከትሎ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ለፍልስጤም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባልነት እንደሚደግፉ አስታውቀዋል ሲል በቻይና መንግስት የሚደገፈው ዲጂታል የዜና ማሰራጫ ዘ ፔፐር ዘግቧል። ዋንግ በተጨማሪም እስራኤል በጋዛ ላይ ያካሄደችው ጦርነት ሰብአዊ አደጋ ፈጥሯል እና "ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው የተኩስ አቁም" በአስቸኳይ ተግባራዊ መሆን አለበት ማለታቸዉን የዜና ማሰራጫው ዘግቧል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አርብ እለት የፍልስጤም የተባበሩት መንግስታት ሙሉ አባልነት ጥያቄ ላይ ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህ እርምጃ ዩዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል ጠንካራ አጋርነትን ሊያግደው ይችላል ተብሎ ይጠበቃል ። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 57😁 10 5👏 3
Photo unavailableShow in Telegram
በአዲስ አበባ እግረኞች ላይ ከሚደርስ የትራፊክ አደጋ ዋነኛው መሻገሪያ መንገድ ዜብራ ላይ ነው ተባለ በአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪዎች በእግረኞች ላይ የትራፊክ አደጋ ከሚያደርሱባቸው መንገዶች ውስጥ አንዱና ዋነኛው የእግረኞች መሻገሪያ ዜብራ ላይ እንደሆነ የከተማ አስተዳደሩ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታውቋል ። ማኔጅመንቱ አሽከርካሪዎች ዘወትር በእግረኞች መሻገሪያ ዜብራ ላይ እግረኞች እስኪሻገሩ ቅድሚያ በመስጠት የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ የድርሻውን መወጣት እንደሚገባ አሳስቧል ። የማኔጅመንቱ የ6 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት እንደሚያመላክተው 198  ሰዎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል ። በትራፊክ አደጋው ህይወታቸው ካለፈ 198 ሰዎች መካከል 82 በመቶው የሚሆኑት እግረኞች ናቸው ተብሏል ። በተያያዘም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎችን ለመቀነስ በእግረኞች የመንገድ አጠቃቀም እና ቅጣት ዙሪያ ማኔጅመንቱ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ተወያይቶ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። በዕለቱ በተያዘው ዓመት የመጋቢት ወር ብቻ 2 ሺ 608 የሚሆኑ እግረኞች የመንገድ አጠቃቀም ህግን በመጣስ መቀጣታቸው ተጠቁሟል ። የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/ 2009 መሠረት በእግረኞች የሚፈፀሙ ጥፋቶች ላይ ቁጥጥር በማድረግ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወሳል ። በአበረ ስሜነህ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 18🤔 7🔥 1😢 1
ኬፕ ታውን ኤርፖርት የአፍሪካ ምርጥ አየር ማረፊያ ተብሎ ሲሰየም ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል በደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታውን የሚገኘው አየር ማረፊያ በደንበኞች ደረጃ አሰጣጥ ድርጅት ስካይትራክስ ባደረገው ጥናት የአህጉሪቱ ምርጥ አየር ማረፊያ ተብሎ ተሰይሟል።በአለም አቀፍ ደረጃ ኬፕ ታውን 54ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዝርዝሩ ላይ ያለው ቦታ አየር ማረፊያዉ የቀነሰበት ሲሆን በ 2020 23 ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ በአህጉራዊ ዝርዝሩ ውስጥ ሌሎች ሁለት የደቡብ አፍሪካ አየር ማረፊያዎች ደርባን እና ጆሃንስበርግ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን እንደ ቅደም ተከተላቸዉ ተቀምጠዋል።በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ የሚገኘው ቦሌ አየር ማረፊያ ከአፍሪካ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ የናይሮቢው ጆሞ ኬንያታ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 10ኛ ደረጃን አግኝቷል።በሌላ በኩል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ጎረቤት ሀገራት እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ በዱባይ አየር ማረፊያ ስራው በእጅጉ አስተጓጉሏል፡፡አውሎ ነፋሱ ማክሰኞ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችን በመምታቱ መንገዶችን እና  የአለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ክፍሎች በጎርፍ ተይዘዋል፡፡ድንገተኛ የጎርፍ አደጋዉ በኦማን 20 ሰዎችን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ደግሞ የአንድ ሰው ህይወት ነጥቋል፡፡ አንዳንድ በረራዎች ሐሙስ እለት ቢደረጉም የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ዋና የጉዞ ማዕከል ቢሆንም እምብዛም አገልግሎት እየሰጠ አይደለም፡፡የዓለማችን ሁለተኛዉ አውሮፕላን ማረፊያ ባለስልጣናት ሐሙስ እለት እንደተናገሩት በውጭ አገር አጓጓዦች በሚጠቀሙበት ተርሚናል 1 ወደ ውስጥ የሚደረጉ በረራዎችን መቀበል መጀመራቸውን፣ ነገር ግን ወደ ውጭ የሚደረጉ በረራዎች መጓተታቸውን ቀጥለዋል ሲሉ ተደምጠዋል።የዱባይ አውሮፕላን ማረፊያ ኃላፊ ፖል ግሪፊስ "አሁን በጣም ፈታኝ ጊዜ ነው፤ በህይወቱ ማንም ሰው እንደዚህ አይነት ሁኔታዎችን አይቶ አያውቅም" ብለዋል፡፡አየር ማረፊያው ለመድረስ በሚሞክሩ ሰዎች መጨናነቅ ምክንያት በዙሪያው ያሉት መንገዶች ተዘጋግተዋል።ረቡዕ እለት ብቻ ወደ 300 የሚጠጉ በረራዎች ሲሰረዙ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ዘግይተዋል ። የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በታሪክ ከፍተኛውን የዝናብ መጠን ተመዝግቦባታል፡፡የመንግስት የዜና ወኪል የዝናብ መረጃ መሰብሰብ ከጀመረበት ከ1949 ዓመት ጀምሮ ከተመዘገቡት ሁሉ የበለጠ ታሪካዊ የአየር ሁኔታ ክስተት ሲል ጠርቶታል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 30😁 11🤔 8😢 4
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ ወደ ህክምና ተቋማት መምጣታቸዉ የተረጋገጡ 460 የሄሞፊሊያ ታማሚዎች መኖራቸው ተገለፀ ከእናትወደ ልጅ የሚተላለፈው እና ወንድ ልጆችን የሚያጠቃው ሄሞፊሊያ ወይንም የደም አለመርጋት ችግር ያጋጠማቸው በኢትዮጵያ ውስጥ 460 ሰዎች መኖራቸውን የኢትዮጵያ የሄሞፊሊያ ሶሳይቲ አስታዉቋል፡፡ የኢትዮጵያ የሄሞፊሊያ ሶሳይቲ ፕሬዝዳንት አቶ ሳምሶን ኃይለማርያም ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በሽታው 99 በመቶ የሚያጠቃው ወንዶችን መሆኑን እና ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ከማስተላለፍ ባለፈ በሽታው አይጠቁም ብለዋል፡፡ህመሙ በዘር የሚተላለፍ ቢሆንም መነሻው ምክንያቱ በደም ውስጥ ደም እንዲረጋ ከሚያደርጉ ፕሮቲኖች አንዱ ሲጎል ነው፡፡ በዚህም ምክንያም ደም መርጋት ባለመቻሉ ደም ወደ ውስጥ እንዲፈስ በማድረጉ እና መገጣጠሚያዎችን እንዲያብጡ የሚያስከትል በሽታ መሆኑን ገልፀዋል፡፡በኢትዮጵያ የበሽታው ስርጭት የሚገመተው ከ5 እስከ 7 ሺ ሰዎች ቢሆንም ህመሙ ታውቆላቸው ህክምና እያገኙ ያሉ 460 ሰዎች ወይንም 4 በመቶ ብቻ ናቸው ፡፡በአለም ላይ ከ10ሺ ሰዎች አንዱ የሄሞፊሊያ ታማሚ እንደሆነ መረጃያዉ ያመላክታል፡፡ ምልክቶቹም በዘር የሚተላለፍ በሽታ እንደመሆኑ መጀመሪያ ሊታይ የሚችለው አራስ ልጅ ሲገረዝ በሚያጋጥመው ያለ ማቋረጥ ደም መፍሰስ ፤የመገጣጠሚያ ቦታዎች እብጠጥ እና ሌሎችም እንዳሉ ገልፀዋል፡፡ህክምናው በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እና በሌሎችም ሆስፒታሎች በደም ስር የሚሰጥ መድኃኒት ቢኖርም መድኃኒቱ ላይ ግን እጥረት እንዳለ እና እንደሚፈለገው መጠን እንዳልሆነ አቶ ሳምሶን ኃይለ ማርያም ጨምረው ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል፡፡ በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😢 18👍 13 2🙏 2
የኬንያ ፕሬዝዳንት ሩቶ ፣ድምጻዊ በርና ቦይና ደቡብ አፍሪካዊዉ የራግቢ ተጫዋች ሲያ ኮሊሲ በዓለም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ዉስጥ ተካተቱ አፍሮቤያት ድምጻዊ በርና ቦይ፣ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የራግቢ ቡድን አምበል ሲያ ኮሊሲ በታይም መፅሄት በአለም ከፍተኛ ተደማጭነት ካላቸው ሰዎች መካከል እውቅና ያገኙ አፍሪካውያን ቡድን ሶስቱ ግለሰቦች እየመሩ መሆናቸዉን አስታዉቋል። በርና ቦይ ዘላቂ ምልክት ያደረጉ በርካታ ሰዎች ያሉ ሲሆን የስራዉን ጥረት በርካቶች  ያደንቁለታል፡፡የግራሚ አሸናፊው ፈረንሣይ-ቤኒናዊ ድምጻዉ አንጄሊኬ ኪድጆ ናይጄሪያዊውን ሙዚቀኛ በርና ቦይን ታሪክ በመሠራት ላይ ያለ ሰዉ ሲል አወድሶታል። ሌላኛዉ  ግከሰብ ኮሊሲ ሲሆን በአመራርነቱ "በጥበብ እና በትህትና" እውቅና አግኝቷል፡፡ ደቡብ አፍሪካዊው ኮሜዲያን ትሬቨር ኖህ እንዳለው ኮሊሲ ባለፈው አመት ሀገሪቱን በሚያስደንቅ የራግቢ የአለም ዋንጫ በማሸነፍ በበርካታ ደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ አድቆት ከማግኘቱ ባለፈ ተስፋ የሰጠ ሲል አሞካሽቶታል። የኬንያ ፕሬዚደንት ሩቶ የአፍሪካን የአየር ንብረት ርምጃ በግንባር ቀደምነት በመምራት የተሰየሙ ሲሆን፣ የታይም ጋዜጠኛ ጀስቲን ወርላንድ ግን ሀገራቸው ላይ እየከበዱ ያሉትን በርካታ ፈተናዎች መፍታት አለባቸው ብሏል።ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመጣችው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ጁሊያን ሉሴንጅ ጾታዊ እና ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን በመቅረፍ እና በአገሯ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ በማነሳሳት ረገድም ክብር ተሰጥቷታል። በኬንያ ትልቁ ሰ ፈር ኪቤራ ውስጥ እንደ ድህነት እና ትምህርት ያሉ ጉዳዮችን ሲፈታ የነበረውን ኬኔዲ ኦዴዴ የተባለውን የማህበራዊ ስራ ፈጣሪ ታይም መጽሄት ስሙን አስፍሮታል፡፡አመታዊው የታይም 100 ዝርዝር ባለፈው አመት በዓለም ላይ ተጽእኖ ለፈጠሩ ግለሰቦች ትኩረት ይሰጣል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 15 2👏 2
🔥 5👍 3 3
በአዲስ አበባ ከተማ ከአየር ብክለት ጋር ተያይዞ በየዓመቱ ከ2 ሺህ በላይ ሰዎች ህይወት እንደሚያልፍ ተነገረ በአዲስ አበባ ከተማ ከጊዜ ወደ ጊዜ የአየር ብክለት መጠን እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በየአመቱ 2 ሺህ አራት መቶ የሚሆኑ ሰዎች ለህልፈት ይዳረጋሉ ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።በባለስልጣኑ  የአየር ንብረት ለውጥና አማራጭ ኢነርጂ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰይድ አብደላ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከማገዶ በሚወጣ ጭስ፣ ቆሻሻን በአግባቡ ባለማስወገድ እንዲሁም ከአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚወጡ ፍሳሾች እና በሌሎች ምክንያቶች  ሳቢያ የአየር ብክለት ይከሰታል ብለዋል። ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ ጭስ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚስተዋለው የአየር ብክለት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ  አቶ ሰይድ ተናግረዋል።ይህ ሁኔታ ከአካባቢ ብክለት ባለፈ በሰዎች ጤና ላይ ሞትን የማስከተል እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ለጉዳዮ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀዋል።አዲስ አበባንም ከብክለት የፀዳች ፣ለነዋሪዎቿና ለእንግዶቿ ምቹ እንድትሆን ለማድረግ ከተሽከርካሪ የሚወጣ ጭስን ለመከላከል የሚያስችለው መመሪያ እንዲፀድቅ እየተደረገ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፓርት ብክለትን ለመቆጣጠር  የወጣው መመሪያ እንዲፀድቅ ለፍትህ ቢሮ ተልኳል ሲሉ የተናገሩት አቶ ሰይድ  መመሪያው ተሽከርካሪዎች  በተቀመጠው የልቀት መጠን ስታንዳርድ  መሰረት እንዲያሽከረክሩ ያስገድዳል ብለዋል።አያይዘውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ  ከትራንስፓርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር እንዲሁም ከደረጃዎች ባለስልጣን ጋር በጋራ በመሆን ስታንዳርዱ  እንዲዘጋጅ  አድርጓ። የመመሪያውን ተፈፃሚነት በሚመለከትአንድ አሽከርካሪ ስታንዳርዱን ጠብቆ ስለማሽከርከሩ  ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተጠቅሷል።በዚህም ትናንሽ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ መለስተኛና ሌሎች መኪኖች   እንደክብደታቸው  እና አይነታቸው የሚለቁት የጭስ መጠን በአግባቡ የሚለካ ይሆናል ሲሉ አቶ ሰይድ አብደላ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጨምረዉ ተናግረዋል፡፡ በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 19👎 8😁 6🤔 3😱 1
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
ዩናይትድ ስቴትስ የቀድሞ የማላዊ ባለስልጣናትን በሙስና ክስ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ አገደች አራት የቀድሞ የማላዊ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሙስና ወንጀል ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ ተጥሎባቸዋል።እነሱም የቀድሞ የፖሊስ አዛዥ ጆርጅ ካይንጃ፣ የቀድሞ የህግ አማካሪ እና የፍትህ ፀሀፊ ሬይኔክ ማትምባ፣ የቀድሞ የህዝብ ግዥ እና የንብረት ማስወገድ ዳይሬክተር ጆን ሱዚ-ባንዳ እና የቀድሞ የፖሊስ አገልግሎት ጠበቃ ሚዋቢ ካሉባ ናቸዉ። አራቱ በዩናይትድ ስቴትስ ዲፓርትመንት ስማቸዉ የተጠቀሱት ግለሰቦች "በአጠቃላይ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመግባት ብቁ አይደሉም፣ ምክንያቱም በከፍተኛ ሙስና ውስጥ በመሳተፋቸው"ነዉ ተብሏል።እገዳው በቀድሞ ባለስልጣናት የትዳር አጋሮች ላይም የጸና ነዉ ተብሏል፡፡ የታገዱት ባለስልጣናት “ለማላዊ ፖሊስ አገልግሎት የመንግስት ግዥ ውል ለመስጠት ከአንድ የግል ነጋዴ ጉቦ እና ሌሎች ዋጋ ያላቸውን ንብረቶች በመቀበል ህዝባዊ ሀብትን አላግባብ ተጠቅመዋል” ብሏል።የቀድሞ ባለሥልጣናቱም ከብሪታኒያው ነጋዴ ዙኔት ሳትታር ጋር በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፀረ-ዘረፋ አካል የተከሰሱ ከ80 በላይ ታዋቂ የማላዊ ዜጎች ስም ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ በኋላ በማላዊ ክስ ቀርቦባቸዋል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 10👎 1 1
ከአላማጣ እና ከሌሎች የራያ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ነዋሪዎች፤ በቆቦ ኢንዱስትሪ መንደር እንዲጠለሉ መደረጋቸው ተነገረ በአማራ እና የትግራይ ክልሎች “የወሰን ይገባኛል” ጥያቄዎች ከሚነሱባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው የራያ አካባቢ ባለፉት ቀናት ውጊያ መካሄዱን ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለው ቆቦ ከተማ መግባታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ተፈናቃዮቹ በአሁኑ ወቅት ከቆቦ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ የኢንዱስትሪ መንደር በጊዜያዊነት እንዲጠለሉ መደረጋቸውንም አስታውቀዋል። በአወዛጋቢዎቹ የራያ አካባቢዎች ውጊያ የተቀሰቀሰው፤ ከአካባቢው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ባለፈው ቅዳሜ እና እሁድ በማይጨው እና መኾኒ ከተማዎች ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ መሆኑን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። ከሰላማዊ ሰልፎቹ  በኋላ በሪ ተኽላይ እና ገርጃለ በተባሉ አካባቢዎች፤ በትግራይ ኃይሎች እና በአማራ ክልል ታጣቂዎች መካከል “ከባድ የተኩስ ልውውጥ” ሲደረግ እንደነበር እማኞቹ አስረድተዋል። የአላማጣ ከተማ ከሰኞ አመሻሽ ጀምሮ በመከላከያ ሰራዊት እና በፌደራል ፖሊስ አባላት ቁጥጥር ስር ከገባ በኋላ በከተማይቱ መረጋጋት መታየቱን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው የአላማጣ ነዋሪዎች አመልክተዋል። በትላንትናው እና በዛሬው ዕለት መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት ቢቀጥልም፤ የህዝብ አገልግሎት ሰጪዎች እና ተቋማት ግን አሁንም ዝግ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።  የመንግስት ሰራተኞች በጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ስራ ገበታ ለመመለስ መቸገራቸውን እና የተወሰኑትም ከተማይቱን ለቅቀው መሄዳቸውን ነዋሪዎቹ አክለዋል። በአላማጣ ከተማ የነበሩ የስራ ኃላፊዎች፤ ከትላንት በስቲያ ከሰዓት በአጎራባች ወደምትገኘው ቆቦ ከተማ መግባታቸውን የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ አበራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።  Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 16🕊 6👎 1😁 1
Photo unavailableShow in Telegram
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.