uz
Feedback
Endod + እንዶድ +

Endod + እንዶድ +

Kanalga Telegram’da o‘tish

www.endod.net በአስተውሎት ንጽህና፣ በአብሮነት መድህን፣ ከተፈጥሮ በተቀዳ ጽናት ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ሆኖ መገኘት መቻል እና ሌሎችን ማስቻልን መነሻው አድርጎ ወደ ወድ አድማጮቹ በFM Addis 97.1 የሚደርስ የራድዮ መሰናዶ ነው።

Ko'proq ko'rsatish
1 226
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
photo content

"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት" -2 | ዘጸዓት ያልሰመረልን እኛ? ስደት እና ዳፋዎቹ ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ
"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት" -2 | ዘጸዓት ያልሰመረልን እኛ? ስደት እና ዳፋዎቹ ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ እናንተ የሚያደርሱት መሰናዶ ገዢ ሐሳብ ነው። በ እንዶድ ምዕራፍ ፫ - ሐ : ክፍል ወደ እናንተ የሚደርሰው ይህ መሰናዶ እኛን እና ስደትን ወደ ኋላ የምንቃኝበት ሸጋ መሰናዶ ነው። ባልደረባችን ተሻለ ከበደ አዘጋጅቶታል፤ ጠርሲዳ ከበደ መሰናዶውን እያጋፈረች አብራችኹ ታመሻለች፤ ሜሪ መኮንን እናንተን ታስተናግዳለች። ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!

የሕይወትዎን ጣዕም ያጎደሉ አንዳንድ አካላዊ የጤና አለመመቸቶች ከ'ይቅር'-ባይነት ጋር ሊያያዙ እንደሚችሉ አስበው ያውቃሉ? ይህ መሰናዶ በዚህ ዙሪያ ሸጋ ሐሳቦችን ሸክፏል! https://youtu.be/7OCg_c0i1Co

ተጋበዙልን! https://youtu.be/jeQHeXr44dA

"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት" ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ እናንተ የሚያደርሱት መሰናዶ ገዢ ሐሳብ ነው። በ እን
"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት" ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ እናንተ የሚያደርሱት መሰናዶ ገዢ ሐሳብ ነው። በ እንዶድ ምዕራፍ ፫ - ሐ : ክፍል 8 ወደ እናንተ የሚደርሰው ይህ መሰናዶ እኛን እና ስደትን ወደ ኋላ የምንቃኝበት ሸጋ መሰናዶ ነው። ባልደረባችን ተሻለ ከበደ አዘጋጅቶታል፤ ጠርሲዳ ከበደ መሰናዶውን እያጋፈረች አብራችኹ ታመሻለች፤ ጸጋ ካሕሳይ እናንተን ያስተናግዳል። ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!

"ከትልቁ እስር ቤት መፈታት!" በእርግጥ ይቅርባይነት ስንል ምን ማለታችን ነው? ይቅር ማለት ጥቅሙ ምንድን ነው? (ከአካላዊ ጤናችን ጋር በቀጥታ እንደሚገናኝ አስበውት ያውቃሉ?) ለዓመታት የተሸከምነውን የበደል ቁርሾ እንዴት ማራገፍ እንችላለን!(ተግባራዊ ልምምዶች) እንደማህበረሰብ ይቅርባይ መሆን ያሉት ትሩፋቶችስ? ዳዊት አርዓያ ከሥነ-ልቦና ባለሙያዋ ሔለን ገ/ኪዳን ጋር ያደረጉትን ሸጋ ቆይታ ተጋበዙልን። እንዶድ፤ ከ'ኛው ለ'ኛው! Subscribe በማድረግም ቤተሰብም ሁኑን! https://youtu.be/veuv1LBM59o

ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "የገዛ መልኬ... " በቅርቡ "የሰው መልክ" የተሰኘ ተቀዳሚ የግጥም መድብሉን የሰጠን ወጣቱ ገጣሚ በረከት ተስፋዬን ይዘን የነፍስ ወከፍ መልካችንን እናስስ ዘንድ እንጋ
ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "የገዛ መልኬ... " በቅርቡ "የሰው መልክ" የተሰኘ ተቀዳሚ የግጥም መድብሉን የሰጠን ወጣቱ ገጣሚ በረከት ተስፋዬን ይዘን የነፍስ ወከፍ መልካችንን እናስስ ዘንድ እንጋብዛችኋለን! ዛሬ ዛሬ የዓለም መልክ እና ቅርፅ እንዲህ ላለ ስር የሰደደ ብቸኝነት አብዝቶ የሚያንደረድር ነው፤ አኗኗራችን ልፊያ እና ግፊያ ያታክታል! ታዲያ በእርግጥ እንዲህ ባለው ጊዜ ጤናማ ወዳጅነት መመስረት እንችል ይሆን? ኑ አብረን እንጠይቅ! የብዙቻችኹን የጽሑፍ መልዕክቶች መነሻ በማድረግ መለስ ብለን ወደ ምዕራፍ ፪ አቅንተን ባልደረባችን መኮንን ሞገሴ አዘጋጅቶት ወደናንተ ያደረስነው የእንዶድ ምዕራፍ 2 ቀዳሚ ተከታታይ መሰናዶ ሰው እና ሰው 5ኛ ክፍል "መተላለፎቻችን" ለዛሬ እንዲስማማ ተጠናቅሯል። አዎ "ሰው | ዛሬ | ዓለም" አይደል ይህ ተከታታይ መሰናዷችን? እርስ በርስ እየተላለፍን ብቸኝነት እየጸናብንም አይደል? መሰናዶውን ያደመጣችሁት ብትደግሙት አብዝታችሁ የምትወዱት፤ ያላዳመጣችኹትም የምታተርፉበት እንደሆነ በመሉ ልብ እንነግራችኋለን። ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ፤ ጸጋ ካሕሳይ እና ጠሪሲዳ ከበደ እያስተናገድናችኹ እናመሻለን፤ አብረን እንዝለቅ! ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ

ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "መተላለፎቻችን... " ብቸኝነት ይሰማዎታል? ሰዎች መሀል ብንሆንም ብቻችንን እንደሆንን ማሰብ ጀምረን ይሆን? ዛሬ ዛሬ የዓለም መልክ እና ቅርፅ እንዲህ ላለ ስር የሰደ
ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "መተላለፎቻችን... " ብቸኝነት ይሰማዎታል? ሰዎች መሀል ብንሆንም ብቻችንን እንደሆንን ማሰብ ጀምረን ይሆን? ዛሬ ዛሬ የዓለም መልክ እና ቅርፅ እንዲህ ላለ ስር የሰደደ ብቸኝነት አብዝቶ የሚያንደረድር ነው፤ አኗኗራችን ልፊያ እና ግፊያ ያታክታል! ታዲያ በእርግጥ እንዲህ ባለው ጊዜ ጤናማ ወዳጅነት መመስረት እንችል ይሆን? ኑ አብረን እንጠይቅ! የብዙቻችኹን የጽሑፍ መልዕክቶች መነሻ በማድረግ መለስ ብለን ወደ ምዕራፍ ፪ አቅንተን ባልደረባችን መኮንን ሞገሴ አዘጋጅቶት ወደናንተ ያደረስነው የእንዶድ ምዕራፍ 2 ቀዳሚ ተከታታይ መሰናዶ ሰው እና ሰው 5ኛ ክፍል "መተላለፎቻችን" ለዛሬ እንዲስማማ ተጠናቅሯል። አዎ "ሰው | ዛሬ | ዓለም" አይደል ይህ ተከታታይ መሰናዷችን? እርስ በርስ እየተላለፍን ብቸኝነት እየጸናብንም አይደል? መሰናዶውን ያደመጣችሁት ብትደግሙት አብዝታችሁ የምትወዱት፤ ያላዳመጣችኹትም የምታተርፉበት እንደሆነ በመሉ ልብ እንነግራችኋለን። ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ፤ ጸጋ ካሕሳይ እና ጠሪሲዳ ከበደ እያስተናገድናችኹ እናመሻለን፤ አብረን እንዝለቅ! ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ

photo content

እነሆ የእንዶድ 3ኛ ምዕራፍ 3ኛ ተከታታይ መሰናዶ: "ሰው፣ ዛሬ፣ ዓለም" ክፍል ፬: አላፊ በዚህ ተከታታይ መሰናዶ የምንኖርባትን ዓለም የተረዳንበትን መንገድ አብረን እንቃኛለን፤ ለተሻለ መረዳትም ዙ
እነሆ የእንዶድ 3ኛ ምዕራፍ 3ኛ ተከታታይ መሰናዶ: "ሰው፣ ዛሬ፣ ዓለም"   ክፍል ፬: አላፊ በዚህ ተከታታይ መሰናዶ የምንኖርባትን ዓለም የተረዳንበትን መንገድ አብረን እንቃኛለን፤ ለተሻለ መረዳትም ዙሪያ-ገባችንን እናስሳለን! ምሽት 2:00 ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ! ሀና ተረፈ(ሃኒቻ) እንግዶችን ሆና ታመሻለች፤ መኮንን ሞገሴ  እና ፀጋ ካህሳይ ይጠብቋችኋል! ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!

መቅደላ መኩሪያ ከእንዶድ ጋር ያደረገውን ሸጋ ቆይታ አድምጠዋል? እንግዲያው ስለ ምስጋና፣ ይቅርባይነት እና አድናቆት የሰጠንን ግሩም ቆይታ ተጋበዙልን! https://youtu.be/sjmBAP3k9YM

photo content

ለምሽታችኹ! https://youtu.be/sjmBAP3k9YM

በዚሕች በየቀኑ በምትቀያየር ዲጅታል ዓለም ውስጥ መረጃ በነጠላ ሕይወታችን ውስጥ ያለው ዋጋ ከቶውኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። እርስዎስ ስለ የተዛባ መረጃ (Misinformation) እና የተሳሳተ መረጃ
በዚሕች በየቀኑ በምትቀያየር ዲጅታል ዓለም ውስጥ መረጃ በነጠላ ሕይወታችን ውስጥ ያለው ዋጋ ከቶውኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። እርስዎስ ስለ የተዛባ መረጃ (Misinformation) እና የተሳሳተ መረጃ(Disinformation) ምን ያሕል ያውቃሉ? የእንዶድ ምዕራፍ ሶስት፤ ሶስተኛ ተከታታይ መሰናዶ በዚህ ረገድ በር ከፋች የሆኑ ሀሳቦች ይዟል፤ መኮንን ሞገሴ፣ ተሻለ ከበደ እና ጸጋ ካሕሳይ አብረዋችኹ ያመሻሉ! ዛሬ ምሽት 2:00 ላይ በአንጋፋው FM Addis 97.1 እንገናኝ! ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!

ሸጋ ቆይታ! ከእንዶድ ምዕራፍ-1 ከግጥም እና ዜማ ደራሲው፣ ጸሐፊው፣ ፕሮዲውሰሩ እና ሙዚቀኛው ዓለምአየሁ ደመቀ ጋር ያደረግነውን ውብ ውይይት ተጋበዙልንማ! https://youtu.be/-kDRY30kJJU

ከሰውመሆን ይስማው ጋር ያደረግነውን ውብ ቆይታ ተጋበዙልን! https://youtube.com/playlist?list=PLTqdaZz7JE0VnFuPDOp-8ysEbbHPGcGSC&si=D9gve7155IfEkMA6

የፊታችን ሰኞ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያ እና የእስልምና እምነት ምዕመናን በየሃይማኖታቸው ትልቅ ስፍራ ያሏቸውን ሁለት ታላላቅ ጾሞች ይጀምራሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
የፊታችን ሰኞ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያ እና የእስልምና እምነት ምዕመናን በየሃይማኖታቸው ትልቅ ስፍራ ያሏቸውን ሁለት ታላላቅ ጾሞች ይጀምራሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በአዋጅ ከሚጾሙት 7ቱ አጽዋማት አንዱና ትልቁ የሆነውን ጾመ ኢየሱስ ፣ ጾመ ሁዳዴ ፣ አርባ ጾም በመባል የሚታወቀውን ዐብይ ጾም ይጀምራሉ። በሂጅራ አቆጣጠር ዘጠነኛው ወር እና በሙስሊሞች ዘንድ የጾም፣ ጸሎት ወር የሆነውም ፡ ረመዳን በዚሁ ቀን በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ይጀመራል። ይሕን በማስመልከት ባሳለፍነው መጋቢት 13 2015 ዓ.ም ያደረስናችኹን ጾም ፡ ለአካል፣ ለዓዕምሮ፣ ለነፍስ መሰናዶ በድጋሚ ወደ እናንተ እናደርሳለን!