Endod + እንዶድ +
前往频道在 Telegram
www.endod.net በአስተውሎት ንጽህና፣ በአብሮነት መድህን፣ ከተፈጥሮ በተቀዳ ጽናት ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ሆኖ መገኘት መቻል እና ሌሎችን ማስቻልን መነሻው አድርጎ ወደ ወድ አድማጮቹ በFM Addis 97.1 የሚደርስ የራድዮ መሰናዶ ነው።
显示更多1 226
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
1 226
"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት" -2 | ዘጸዓት ያልሰመረልን እኛ? ስደት እና ዳፋዎቹ
ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ እናንተ የሚያደርሱት መሰናዶ ገዢ ሐሳብ ነው። በ እንዶድ ምዕራፍ ፫ - ሐ : ክፍል ወደ እናንተ የሚደርሰው ይህ መሰናዶ እኛን እና ስደትን ወደ ኋላ የምንቃኝበት ሸጋ መሰናዶ ነው።
ባልደረባችን ተሻለ ከበደ አዘጋጅቶታል፤ ጠርሲዳ ከበደ መሰናዶውን እያጋፈረች አብራችኹ ታመሻለች፤ ሜሪ መኮንን እናንተን ታስተናግዳለች።
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!
1 226
የሕይወትዎን ጣዕም ያጎደሉ አንዳንድ አካላዊ የጤና አለመመቸቶች ከ'ይቅር'-ባይነት ጋር ሊያያዙ እንደሚችሉ አስበው ያውቃሉ?
ይህ መሰናዶ በዚህ ዙሪያ ሸጋ ሐሳቦችን ሸክፏል!
https://youtu.be/7OCg_c0i1Co
1 226
"እኛ" እና "ነገረ-ዘጸዓት"
ዛሬ ምሽት 2:00 በ FM Addis 97.1 የእንዶድ ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች ተሻለ ከበደ እና ጠርሲዳ ከበደ ወደ እናንተ የሚያደርሱት መሰናዶ ገዢ ሐሳብ ነው። በ እንዶድ ምዕራፍ ፫ - ሐ : ክፍል 8 ወደ እናንተ የሚደርሰው ይህ መሰናዶ እኛን እና ስደትን ወደ ኋላ የምንቃኝበት ሸጋ መሰናዶ ነው።
ባልደረባችን ተሻለ ከበደ አዘጋጅቶታል፤ ጠርሲዳ ከበደ መሰናዶውን እያጋፈረች አብራችኹ ታመሻለች፤ ጸጋ ካሕሳይ እናንተን ያስተናግዳል።
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!
1 226
"ከትልቁ እስር ቤት መፈታት!"
በእርግጥ ይቅርባይነት ስንል ምን ማለታችን ነው?
ይቅር ማለት ጥቅሙ ምንድን ነው? (ከአካላዊ ጤናችን ጋር በቀጥታ እንደሚገናኝ አስበውት ያውቃሉ?)
ለዓመታት የተሸከምነውን የበደል ቁርሾ እንዴት ማራገፍ እንችላለን!(ተግባራዊ ልምምዶች)
እንደማህበረሰብ ይቅርባይ መሆን ያሉት ትሩፋቶችስ?
ዳዊት አርዓያ ከሥነ-ልቦና ባለሙያዋ ሔለን ገ/ኪዳን ጋር ያደረጉትን ሸጋ ቆይታ ተጋበዙልን።
እንዶድ፤ ከ'ኛው ለ'ኛው!
Subscribe በማድረግም ቤተሰብም ሁኑን!
https://youtu.be/veuv1LBM59o
1 226
ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "የገዛ መልኬ... "
በቅርቡ "የሰው መልክ" የተሰኘ ተቀዳሚ የግጥም
መድብሉን የሰጠን ወጣቱ ገጣሚ በረከት ተስፋዬን ይዘን የነፍስ ወከፍ መልካችንን እናስስ ዘንድ እንጋብዛችኋለን!
ዛሬ ዛሬ የዓለም መልክ እና ቅርፅ እንዲህ ላለ ስር የሰደደ ብቸኝነት አብዝቶ የሚያንደረድር ነው፤ አኗኗራችን ልፊያ እና ግፊያ ያታክታል!
ታዲያ በእርግጥ እንዲህ ባለው ጊዜ ጤናማ ወዳጅነት መመስረት እንችል ይሆን? ኑ አብረን እንጠይቅ!
የብዙቻችኹን የጽሑፍ መልዕክቶች መነሻ በማድረግ መለስ ብለን ወደ ምዕራፍ ፪ አቅንተን ባልደረባችን መኮንን ሞገሴ አዘጋጅቶት ወደናንተ ያደረስነው የእንዶድ ምዕራፍ 2 ቀዳሚ ተከታታይ መሰናዶ ሰው እና ሰው 5ኛ ክፍል "መተላለፎቻችን" ለዛሬ እንዲስማማ ተጠናቅሯል።
አዎ "ሰው | ዛሬ | ዓለም" አይደል ይህ ተከታታይ መሰናዷችን? እርስ በርስ እየተላለፍን ብቸኝነት እየጸናብንም አይደል? መሰናዶውን ያደመጣችሁት ብትደግሙት አብዝታችሁ የምትወዱት፤ ያላዳመጣችኹትም የምታተርፉበት እንደሆነ በመሉ ልብ እንነግራችኋለን።
ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ፤ ጸጋ ካሕሳይ እና ጠሪሲዳ ከበደ እያስተናገድናችኹ እናመሻለን፤ አብረን እንዝለቅ!
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ
1 226
ሰው | ዛሬ | ዓለም -፮ : "መተላለፎቻችን... "
ብቸኝነት ይሰማዎታል? ሰዎች መሀል ብንሆንም ብቻችንን እንደሆንን ማሰብ ጀምረን ይሆን?
ዛሬ ዛሬ የዓለም መልክ እና ቅርፅ እንዲህ ላለ ስር የሰደደ ብቸኝነት አብዝቶ የሚያንደረድር ነው፤ አኗኗራችን ልፊያ እና ግፊያ ያታክታል!
ታዲያ በእርግጥ እንዲህ ባለው ጊዜ ጤናማ ወዳጅነት መመስረት እንችል ይሆን? ኑ አብረን እንጠይቅ!
የብዙቻችኹን የጽሑፍ መልዕክቶች መነሻ በማድረግ መለስ ብለን ወደ ምዕራፍ ፪ አቅንተን ባልደረባችን መኮንን ሞገሴ አዘጋጅቶት ወደናንተ ያደረስነው የእንዶድ ምዕራፍ 2 ቀዳሚ ተከታታይ መሰናዶ ሰው እና ሰው 5ኛ ክፍል "መተላለፎቻችን" ለዛሬ እንዲስማማ ተጠናቅሯል።
አዎ "ሰው | ዛሬ | ዓለም" አይደል ይህ ተከታታይ መሰናዷችን? እርስ በርስ እየተላለፍን ብቸኝነት እየጸናብንም አይደል? መሰናዶውን ያደመጣችሁት ብትደግሙት አብዝታችሁ የምትወዱት፤ ያላዳመጣችኹትም የምታተርፉበት እንደሆነ በመሉ ልብ እንነግራችኋለን።
ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ፤ ጸጋ ካሕሳይ እና ጠሪሲዳ ከበደ እያስተናገድናችኹ እናመሻለን፤ አብረን እንዝለቅ!
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ
1 226
እነሆ የእንዶድ 3ኛ ምዕራፍ 3ኛ ተከታታይ መሰናዶ: "ሰው፣ ዛሬ፣ ዓለም"
ክፍል ፬: አላፊ
በዚህ ተከታታይ መሰናዶ የምንኖርባትን ዓለም የተረዳንበትን መንገድ አብረን እንቃኛለን፤ ለተሻለ መረዳትም ዙሪያ-ገባችንን እናስሳለን!
ምሽት 2:00 ላይ በFM Addis 97.1 እንገናኝ!
ሀና ተረፈ(ሃኒቻ) እንግዶችን ሆና ታመሻለች፤ መኮንን ሞገሴ እና ፀጋ ካህሳይ ይጠብቋችኋል!
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!
1 226
መቅደላ መኩሪያ ከእንዶድ ጋር ያደረገውን ሸጋ ቆይታ አድምጠዋል? እንግዲያው ስለ ምስጋና፣ ይቅርባይነት እና አድናቆት የሰጠንን ግሩም ቆይታ ተጋበዙልን!
https://youtu.be/sjmBAP3k9YM
1 226
በዚሕች በየቀኑ በምትቀያየር ዲጅታል ዓለም ውስጥ መረጃ በነጠላ ሕይወታችን ውስጥ ያለው ዋጋ ከቶውኑ የሚያጠያይቅ አይደለም።
እርስዎስ ስለ የተዛባ መረጃ (Misinformation) እና የተሳሳተ መረጃ(Disinformation) ምን ያሕል ያውቃሉ?
የእንዶድ ምዕራፍ ሶስት፤ ሶስተኛ ተከታታይ መሰናዶ በዚህ ረገድ በር ከፋች የሆኑ ሀሳቦች ይዟል፤ መኮንን ሞገሴ፣ ተሻለ ከበደ እና ጸጋ ካሕሳይ አብረዋችኹ ያመሻሉ!
ዛሬ ምሽት 2:00 ላይ በአንጋፋው FM Addis 97.1 እንገናኝ!
ኑ! ለተሻለ ነገ አ'ብ'ረን እናዋጣ!
1 226
ሸጋ ቆይታ! ከእንዶድ ምዕራፍ-1
ከግጥም እና ዜማ ደራሲው፣ ጸሐፊው፣ ፕሮዲውሰሩ እና ሙዚቀኛው ዓለምአየሁ ደመቀ ጋር ያደረግነውን ውብ ውይይት ተጋበዙልንማ!
https://youtu.be/-kDRY30kJJU
1 226
ከሰውመሆን ይስማው ጋር ያደረግነውን ውብ ቆይታ ተጋበዙልን!
https://youtube.com/playlist?list=PLTqdaZz7JE0VnFuPDOp-8ysEbbHPGcGSC&si=D9gve7155IfEkMA6
1 226
የፊታችን ሰኞ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያ እና የእስልምና እምነት ምዕመናን በየሃይማኖታቸው ትልቅ ስፍራ ያሏቸውን ሁለት ታላላቅ ጾሞች ይጀምራሉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በአዋጅ ከሚጾሙት 7ቱ አጽዋማት አንዱና ትልቁ የሆነውን ጾመ ኢየሱስ ፣ ጾመ ሁዳዴ ፣ አርባ ጾም በመባል የሚታወቀውን ዐብይ ጾም ይጀምራሉ።
በሂጅራ አቆጣጠር ዘጠነኛው ወር እና በሙስሊሞች ዘንድ የጾም፣ ጸሎት ወር የሆነውም ፡ ረመዳን በዚሁ ቀን በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ይጀመራል።
ይሕን በማስመልከት ባሳለፍነው መጋቢት 13 2015 ዓ.ም ያደረስናችኹን ጾም ፡ ለአካል፣ ለዓዕምሮ፣ ለነፍስ መሰናዶ በድጋሚ ወደ እናንተ እናደርሳለን!
