uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 758
Obunachilar
+324 soatlar
+97 kunlar
+4630 kunlar
Postlar arxiv
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ ። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመቱ ዓመታዊ ታ
+9
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል  ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ ።    የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመቱ ዓመታዊ  ታላቅ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ገ/ሥላሴ በላይ የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ ዋና አስተዳዳሪ፣ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው እና ሌሎችም የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት፣ የሰንበት ት/ት ቤት አገልጋዮችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል እንኳን አደረሳችሁ!!!
በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል እንኳን አደረሳችሁ!!!

ሰላም እብል ኪያከ መልዐከ፤ ሩኀሩኅ ልብ ለኵሉ እንተኢኮንከ ድሩከ ሚካኤል ሊቅየ ለለዕቤለከ፤ ኅብአኒ በጽላሎትከ ነግሀ ወሠርከ፤ እስመ እምንዕስየ እፈርሕ ሀከከ። ለሁሉ የምትራራ ጌታዬ ቅዱስ ሚካኤል
ሰላም እብል ኪያከ መልዐከ፤ ሩኀሩኅ ልብ ለኵሉ እንተኢኮንከ ድሩከ ሚካኤል ሊቅየ ለለዕቤለከ፤ ኅብአኒ በጽላሎትከ ነግሀ ወሠርከ፤ እስመ እምንዕስየ እፈርሕ ሀከከ። ለሁሉ የምትራራ ጌታዬ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ እኔን ወዳጅህን በረድኤትህ ጥላ ከጧት እስከ ማታ ከክፉ ነገር ሁሉ ሠውረኝ ከልጅነቴ ጀምሮ ፀብንና ክርክርን እፈራለሁና። ትንብልናሁ ወአስተብቊዖቱ ለቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት የሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን። የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።

“በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤..." ትን ዳን. 12፥1 በነገው እለት ኅዳር 12 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ
“በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤..."             ትን ዳን. 12፥1 በነገው እለት ኅዳር 12 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል እርስዎም በክብረ በዓሉ ላይ እንዲገኙ የከበረ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!! ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን!!!

🌹🌹🌹🌹🌹ሥርዐተ ማኅሌት ዘኅዳር ቅዱስ ሚካኤል🌹🌹🌹🌹🌹 በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
+6
🌹🌹🌹🌹🌹ሥርዐተ ማኅሌት ዘኅዳር ቅዱስ ሚካኤል🌹🌹🌹🌹🌹 በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የተከበራችሁ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ለማዕከላውያን (እድሜያቸው ከ13-18) ለሚሆኑ የዲጅታል ሰሌዳ መጽሔት በአዲስ መልክ ህዳር 12 ቀን ስለሚጀምር ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ቤተሰብ ይሁ
የተከበራችሁ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ለማዕከላውያን (እድሜያቸው ከ13-18) ለሚሆኑ የዲጅታል ሰሌዳ መጽሔት በአዲስ መልክ ህዳር 12 ቀን ስለሚጀምር ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ቤተሰብ ይሁኑ ይከታተሉ🙏 https://t.me/+Czq3A7Y-zIwxNTk0       እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይባርክ።

ጥቅምት 30/2018 በሚሊኒየም አዳራሽ ከነበረው የምርቃት መርሐግብር የሰንበት ት/ቤታችን ተመራቂዎች እና የመርሐ ግብሩ አቅራቢዎች በጥቂቱ ማስታወሻ
+9
ጥቅምት 30/2018 በሚሊኒየም አዳራሽ ከነበረው የምርቃት መርሐግብር የሰንበት ት/ቤታችን ተመራቂዎች እና የመርሐ ግብሩ አቅራቢዎች በጥቂቱ ማስታወሻ

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ሰይፉ አየለ አባት አርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል የምትችሉ አባላት መኖሪያ ቤታቸው ቦሌ አራብሳ አካባቢ በመሄድ ወይም በስልክ ቁጥር +251910846228 በመደወል  እንድናጽናናቸው ይሁን። የአባታችንን ነፍስ ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

"ተመየጢ እግዝእትየ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ። ወኢትጐንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ። ዘያመጽእ አልቦ በላዕሌኪ ሁከተ። ለወልድኪ ዘየኃሥሦ ይእዜሰ ሞተ። በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ።"🌹🌹 🌹"እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ መልአከ እግዚአብሔር ለአረጋዊ ጻድቅ ቅዱስ ዮሴፍ እንደነገረው በአንቺ ላይ መከራን የሚያመጣው ጠፍቷልና ልጅሽን የሚፈልገውም ጨካኝ ኄሮድስ እነሆ ሞቷልና ቤት እንደሌለውም በግብፅ አትዘግይ። ወደ ሀገርሽ ናዝሬትም ተመለሺ።"🌹                  (ሰቆቃወ ድንግል)

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ ጋር ወደ ግብጽ ሀገር ተሰዳ ስትመለስ ቁስቋም በምትባል ሀገር ገብታ ያረፈችበት በዓል ኅዳር 6 ነው፡፡ ጌታችን 3 ዓመት ከ6 ወር የግብጽ ስደት በኋላ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ ጋር ወደ ግብጽ ሀገር ተሰዳ ስትመለስ ቁስቋም በምትባል ሀገር ገብታ ያረፈችበት በዓል ኅዳር 6 ነው፡፡ ጌታችን 3 ዓመት ከ6 ወር የግብጽ ስደት በኋላ ወደ እስራኤል እንደሚመለስ  ሆሴዕ በትንቢት መነጽርነት ተመልክቶ “ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት ” ብሎ ተናግሯል           ሆሴ 11÷1 «ተመየጢ ተመየጢ ሱላማጢስ ...ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ » መኃ 7፥1 እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ሃገራችን ኢትዮጵያን ቅድስት ቤተክርስቲያንን እና ሕዝቧን ይባርክልን ይጠብቅልን ዘንድ አሳስቢን። አሜን።     🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️      🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ በሁላችንም ላይ ይደር።