የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Kanalga Telegram’da o‘tish
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Ko'proq ko'rsatish2 616
Obunachilar
+524 soatlar
+127 kunlar
+3030 kunlar
Postlar arxiv
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የተሰማቸውን የኀዘን መልእክት አስተላለፉ።
⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ወረዳ በአረርቲ ከተማ በደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲስ እየተሰራ ባለው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመወጣጫ መሰላል ተደርምሶ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን በመግለጽ ! በአደጋው በሞተ ሥጋ ለተለዩን ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስን በአደጋው የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሁሉ ምሕረትን በመለመን ለተጎጂ ቤተሰቦችና ለመላው ምዕመናን መጽናናትን ይስጥልን በማለት አባታዊ የኃዘን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል !!!
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት
ምንጭ:- EOTC ሕዝብ ግንኙነት
መስከረም 21
ብዙኃን ማርያም
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡
በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡
ጉባዔ_ኒቅያ
በ325ዓ.ም አርዮስ የሚባል መናፍቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአርዮስ ክህደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡
በዚህም መሠረት ከሚያዝያ 21 ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ 2348 (ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ዐርባ ስምንት) ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡
ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ (2348) መካከል (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ 318 ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት 318ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው /ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡
318ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም ፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "#ብዙኃን_ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡
2. ዕፀ መስቀል
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
‹‹… መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ አይሁድ ክህዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ፤ … መስቀል ኀይላችን፣ ጽንዓችን፣ ቤዛችን፣ የነፍሳችን መዳኛ ነው፡፡ አይሁድ ይክዱታል፤ እኛ ግን እናምንበታለን፡፡ ያመነውም እኛ በመስቀሉ ኀይል እንድናለን፤ ድነናልም››
እንኳን ለበዓለ መስቀል በሰላም አደረሳችሁ
እጸ መስቀል
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ::
ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት።
ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡
ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡
ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡
መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት
የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ
እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ
* ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች
1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)
2.ቅንድብመቀንደብ
3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ እንዲሁም 4.አላስፈላጊ ሜካፕ .....
5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ ተግባራትን አትጠቀሙ።
* መገኛሰዓት:- የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ከቀኑ 6:00 ጎላ ጊቢ እንድትገኙ ይሁን።
መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ
እንኳን ሐመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ
* ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች
1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)
2.ቅንድብመቀንደብ
3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ እንዲሁም 4.አላስፈላጊ ሜካፕ .....
5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ ተግባራትን አትጠቀሙ።
* መገኛሰዓት:- የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ከቀኑ 6:00 ጎላ ጊቢ እንድትገኙ ይሁን።
መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
