uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 610
Obunachilar
+524 soatlar
+127 kunlar
+3030 kunlar
Postlar arxiv
ውድ የተከበራችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት እንዲሁም የአጥቢያችን ምዕመናን በሙሉ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯   በትላንትናው ዕለት ማለትም በ18/02/18 ዓ.ም በደብራችን የመንፈስ ቅዱስ ክብረ በዓልና በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ አላግባብ ጽሑፍና ማንም ባልፈቀደው መልኩ  ህግን በጣሰ መሠረት በደብራችን የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ/ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ   የትችት ጽሑፍ በሶሻል ሚዲያ ባስተላለፈው ዲ/ን  ከሳቴ ብርሃን ዙሪያ  እንደ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ ቤት መረጃ እያሰባሰብን እንዲሁም በግለሰቡ ላይ ማጣራት ያለብንን ጉዳዮች እየተከታተልን ሲሆን  ጽሁፉ ን እና ግላዊ ሃሳባቸውን ባስተላለፉት ግለሰብ ላይም የቤተ ክርስቲያኒቷ ህግ በሚያዘው  መሠረት የማጣራት እና እንዲጠየቅ የማድረግ ስራ ለመስራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እያደረግን መሆኑን ለክቡራን  አባላቶቻችን እና ወዳጆቻችን ለማሳሰብ እንወዳለን !!!     የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጽ/ቤት

'' ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ዘሠረጸ እም አብ ንስግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበ በነቢያት''     በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረጸ ከአብና ከወልድ ጋር በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን፤ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረው ነው። መንፈስ ቅዱስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ጰራቅሊጦስ:- ናዛዚ ፣ መጽንዒ፣ መስተፍሥሒ ፣ የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው። ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ''እናንተ  ግን  ከላይ ኃይል እስክትለብሱ  ድረስ  በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ'' ብሎ ለሐዋርያቱ በሰጣቸው ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሳ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ ድንገት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት መላው የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎችም በሁሉም ላይ አረፉባቸው በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በተለያዩ በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ ተናገሩ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጎለመሱ፤ ጥቡዓን ሆኑ፣ ፍርሃት ከውስጣቸው ተወግዶ መንፈሳዊ ድፍረት አግኝተዋል፤  ጽኑዓን ኾነዋል፤ ሰማያዊ ሀብት ዕውቀትና ጸጋን ታድለዋል። በዚህ ዕለት ሐዋርያት በተገለጠላቸው ቋንቋ ሲያስተምሩ ተቃዋሚ አይሁዳውያን  ''ጉሽ  ጠጅ  ጠጥተው  ሰክረው የሆነ ያልሆነውን ይቀባጥራሉ''  እያሉ ሐዋርያትን አሟቸው ቅዱስ ጴጥሮስም  ሰክረዋል  የምትሉ  እናንተ እንደምትሉት  አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ  ሰዓቱም ገና ጠዋት  ሦስት  ሰዓት  ነው    ይልቁኑ እናንተ በተንኮል ሰቅላችሁ የገደላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መሆኑን  በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ከክፋታቸው ተመልሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመኑ በዚያች ብቻ ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ተመልሰዋል ዕለቱም የቤተክርስቲያን የልደት ቀን ይባላል።   ከሶስቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ወር በገባ በ18 በዓሉ ሲሆን በአዲስ አበባ በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ዋና ደብሩ ሁልጊዜም በዓሉ ይታሰባል። ከዚያ በተጨማሪም በበዓለ ሃምሳ መንፈስቅዱስ የወረደበት ዕለት በታላቅ ድምቀት በየዓመቱ ይከበራል። ከሶስቱ አካላት አንዱ የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ጠብቆት አይለየን አሜን።

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ ድንግል አዘክሪ  ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን /2/  ካንቺ መወለዱን አዘክሪ  በቤተልሔም አዘክሪ  በጨርቅ መጠቅለሉን አዘክሪ  መኝታው ግርግም አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በዚያ በብርድ ወራት አዘክሪ  የገበሩለትን አዘክሪ  የአድግና የላም አዘክሪ  እስትንፋሣቸውን አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በግብጽ በረሃ አዘክሪ  መሠደድሽን አዘክሪ  የአሸዋውን ግለት አዘክሪ  ርሃቡና ጥሙን አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በመቃብሩ ዘንድ አዘክሪ  ባነባሽው እንባ አዘክሪ  አሳስቢ ድንግል ሆይ አዘክሪ  ገነት እንድንገባ አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ ድንግል አዘክሪ  ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን /2/  ካንቺ መወለዱን አዘክሪ  በቤተልሔም አዘክሪ  በጨርቅ መጠቅለሉን አዘክሪ  መኝታው ግርግም አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በዚያ በብርድ ወራት አዘክሪ  የገበሩለትን አዘክሪ  የአድግና የላም አዘክሪ  እስትንፋሣቸውን አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በግብጽ በረሃ አዘክሪ  መሠደድሽን አዘክሪ  የአሸዋውን ግለት አዘክሪ  ርሃቡና ጥሙን አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን  በመቃብሩ ዘንድ አዘክሪ  ባነባሽው እንባ አዘክሪ  አሳስቢ ድንግል ሆይ አዘክሪ  ገነት እንድንገባ አዘክሪ  ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል ጥቅምት 14/2018ዓ.ም በፎቶ (4)
+8
የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል ጥቅምት 14/2018ዓ.ም በፎቶ (4)

የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል ጥቅምት 14/2018ዓ.ም በፎቶ
+9
የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል ጥቅምት 14/2018ዓ.ም በፎቶ

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅ/ሚ/ቤ/ክ የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ከዚህ በታች ባሉት ክፍት የስራ መደቦች   አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። የሥራ ቦታ ፡-  የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት 1.የሥራው ዓይነት፡- ጊዜያዊ የሕንጻ አስተዳደር ተፈላጊ ችሎታ:-  በማንኛውም የት/ት መስክ ዲፕሎማ እና ከዛ በላይ ያለው/ያላት     ብዛት:-1 2.የሥራው ዓይነት :-ጊዜያዊ የቤተ መጻህፍት ክፍል ኃላፊ ተፈላጊ ችሎታ:-  በስነ-መለኮት ወይም በማንኛውም ት/ት ዘርፍ ዲግሪ  ያለው/ያላት    ብዛት:-1                          3.የሥራው ዓይነት :-ጽዳት       ተፈላጊ ችሎታ:- 8ኛ ክፍል እና ከዛ በላይ               ብዛት:- 1 መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን   ለሁሉም የሥራ ዓይነቶች ደሞዝ በስምምነት     የሰ/ት/ቤት አገልጋይ የሆኑ ይበረታታሉ    የማመልከቻ ጊዜ:- ከዛሬ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 (አስር) ቀናት ለበለጠ መረጃ:- የሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ ወይም በስልክ ቁጥር..         +251983753030         +251911458862