cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

طالب العلم

በአላህ ፍቃድ በዚህ ነፃ መድረክ ማንኛውም ሰው ከዲናችን ጋር ተያያዥ ጉዳዮችን መማርና ማስተማር ይችላል።የምናውቀውን በማሳወቅና የማናውቀውን በመማር ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ።በዋናነትም የሰለፊያ መሻይኾች ትምህርቶችንን እናስተላልፋለን። جزاكم الله خير ወደ ግሩፑ መቀላቀል የሚፈልግ @ebnumuslim01

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
179
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

የዙልሒጃ አስር ቀናቶች 〰〰〰〰〰〰〰〰 ♦️አዲስ ወቅታዊ ምክር 📝በነዚህ ውድ ቀናቶች፦ ▪️የሰዎች መዘናጋት ▪️ግንዛቤን ማስፋት ▪️ከረመዷን ይበልጣሉን? 【ክፍል፦ ①】 🏷 ኢንሻአላህ ይቀጥላል…… http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
Hammasini ko'rsatish...
① የዙልሂጃ 10 ውድ ቀናቶች.mp34.64 MB
Photo unavailableShow in Telegram
🍁አንድ ቀን ከምትወዷቸው ሰዎችጋ ጓደኝነታችሁ ካበቃ ፍቅራቸውን በልባቹህ ውስጥ አኑሩት! #ሚስጥራቸውንም,ታሪካቸውንም.. ደብቁላቸው! 🌸#ምክኒያቱም፦ ጓደኝነት ማለት #መልካም_ስነ_ምግባር ማለት ነው:: ✔️መልካምነት አብሮ በመኖር ውስጥ ብቻ ሳይሆን አብሮ ባለመኖር ውስጥም መልካም መሆን! ርቀውም ቀርበውም ያው መልካሞች'መልካም ናቸውና!! ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy
Hammasini ko'rsatish...
📌ድብልቅልቁ የትምህርት ዓለም ዋይታ በእውነተኛው የኢስላም ብርሃን ሲፈታ📌 📝 ተከታታይ ፅሁፍ 👉ክፍል አንድ👈 بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيم ብዙ ወገኖች እንዲህ በማለት ይጠይቃሉ ፦ ግን እንዴት የወንድና የሴት መደባለቅ ወንጀል ሊሆን ይችላል❓❗ በመጀመሪያ ወንድም እህቶቼ አላህ ሐቅን የምናይበትና የምንቀበልበት ልባዊ ብርሃን ይስጠን !!! በማስከተልም አላህ ልዕለ ሃያሉ አምላክ ይህንን አስከፊ ድርጊት በመከልከል እንዲህ ይለናል ፦ {{ "وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعًا فَاسْأَلُوهُنَّ مِنْ وَرَاءِ حِجَاب" }} { "ዕቃ (መዋስን) በጠየቃችኋቸው ጊዜ ከሒጃብ (ከግርዶሽ) ኋላ ሆናችሁ ጠይቋቸው።" } ውዱ የአላህ ነብይም ( ﷺ ) እንዲህ በማለት ያስጠነቅቁናል ፦ (( "عَنْ عُقْبَةَ بْنِ عَامِرٍ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ إِيَّاكُمْ وَالدُّخُولَ عَلَى النِّسَاءِ فَقَالَ رَجُلٌ مِنْ الْأَنْصَارِ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَفَرَأَيْتَ الْحَمْوَ قَالَ الْحَمْوُ الْمَوْتُ " )) (( " አደራችሁን "አጂነቢይ" (ለትዳር የተፈቀዱ ሴቶች) ባሉበት መግባትን ተጠንቀቁ። " )) በዚህም ጊዜ አንድ የመዲና ሰው " የባል ቅርብ ዘመድ ቢሆንስ? " በማለት ጠየቃቸው። እርሳቸውም :– (( " የባል ቅርብ ዘመድማ የባሰውን ሞት ነው። " )) በማለት የሴትና ወንድ መደባለቅ አስከፊ መዘዝ እንዳለው አመላከቱ። አሁንም ግልፅ አልሆነልንም አላህና መልዕክተኛው ለምንድን ነው❓ እንዲህ በከባዱ የከለከሉት ? የሚሉ ወገኖች አሉ❗ በመጀመሪያ ደረጃ ግልፅ ያልሆነልን ነገር ሁሉ ትክክል አይደለም ማለት አይደለም። ምክንያቱም ፦ አላህና መልዕክተኛው አንድን ፍርድ ወይም ውሳኔ ሲያሳልፉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የመተግበር ግዴታ አለብንና። ታላቁ አምላክ አላህም እንዲህ ይለናል፦ {{ " وَمَا كَانَ لِمُؤْمِنٍ وَلَا مُؤْمِنَةٍ إِذَا قَضَى اللَّهُ وَرَسُولُهُ أَمْرًا أَنْ يَكُونَ لَهُمُ الْخِيَرَةُ مِنْ أَمْرِهِمْ وَمَنْ يَعْصِ اللَّهَ وَرَسُولَهُ فَقَدْ ضَلَّ ضَلَالًا مُبِينًا" }} 【(الأحزاب (36)】 (( " አላህና መልዕክተኛው የሆነ ነገርን በፈረዱ ጊዜ ለወንድና ለሴት አማኞች በጉዳያቸው ላይ ምርጫ ሊኖራቸው አይገባም። አላህንና መልህክተኛውን የሚያምፅ በርግጥም ግልፅ የሆነ ጥመትን ጠሟል" )) 【አል– አሕዛብ (36)】 የአላህና የመልዕክተኛው ውሳኔ ውስጥ ጥልቅ የሆነ ጥበብ አለው። ስለዚህም ብዙ ጊዜ ለመቀበል እንቸገርና ስንልፈሰፈስ እንታያለን። ለዚህም ነው አላህ እንዲህ በማለት የእውቀትን ሚስጥር የነገረን ፦ {{ " وَمَا يَعْلَمُ تَأْوِيلَهُ إِلَّا اللَّهُ وَالرَّاسِخُونَ فِي الْعِلْمِ يَقُولُونَ آَمَنَّا بِهِ كُلٌّ مِنْ عِنْدِ رَبِّنَا وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّا أُولُو الْأَلْبَاب} 【 آل عمران (7) 】 (( " ትክክለኛውን ትርጉም አላህ ብቻ እንጂ ሌላ ማንም አያውቀውም። በዕውቀትም የጠለቁት በርሱ አምነናል ሁሉም ከጌታችን ዘንድ ነው ይላሉ። የአእምሮ ባልተቤቶች እንጂ ሌላው አይገሰጽም " )) አላህ ከተገሳጮች ያድርገን❗ ስለዚህም ነው፤ አላህ በወሰነው ውሳኔ ውስጥ ጥልቅ ጥበብ አለ የምንለው ፤ ስለሆነም አላህን ለመፍራት ቁርጠኛ እንሁን የቻልነውን ያህል ሁሉ ስለ እውነተኛው ‼ እደግመዋለሁ❗ ስለ እውነተኛው "ኢስላም" እንወቅ በማስከተልም እንደድንቆቹ ሰሐባዎች ሰምተናል እንታዘዛለን እንበል ! አላህ ይርዳን !!! እንግዲህ ወንድም እህቶቼ ከዚህም በበለጠ ምክንያቱ በተሰወረብንና ባላወቅነውም ጉዳይ ላይ አላህና መልክተኛውን መታዘዝ ግድ ከሆነብን ምነው ታዲያ❓ ምክንያቱ እጅግ በጣም ተብራርቶ በተነገረን የኢኽቲላጥ እና የአመፅ አይነቶች አይነት በአይነቱ በተለያዩ ማማለያዎች ቀርበውልን ቀን በቀን እየተጋትናቸው "ሰብር" ማድረጋችን ?! ሳንጎዳስ ቀርተን ይሆን ?! ወይስ እስልምናን ጠቅመንበት ነው ?! ወይንስ እንደኩፋሮች የማይቻለውን የአላህ ቅጣት አይመጣብንም ብለን ተማምነን ነው ❓❗ 👉 በትንሹም ቢሆን ነካ ላደረገን እንኳን ብርክ ብርክ ብሎን ፣ ድንፋታችን ቀዝቅዞ ፣ መላው ጠፍቶንና ግር ብሎን ገና ከዓዚዙ ሳንታረቅ ??? አሁንስ መቼ ተማርን❓ መቼ ተመከርን❓መቼስ ተቀጣን❓ እንደውም ይባስ ብለን ለዚህ ሁሉ ቅጣቱና ማስፈራሪያው ትልቁ መንስኤ የሆነውን የኢኽቲላጥ ትምህርት መቼ እንደ ሚጀምር በመጠባበቅ ጭንቀት ውጦናል። ብዙ ነገር እየሰማን ነዉ። የኛ ነገር ያሳዝናል መጨረሻችን ምን ይሆን? የአዛኞች ሁሉ አዛኝ የሆንከው አምላክ ሆይ እዘንልን ! ግን ይህ ሁሉ ሲሆን መካሪ ፣ ገሳጭ ፣ አስጠንቃቂ ጠፍቶ ነዉን ? እሱንስ ተውት ሆድ ይፍጀው ብለን ግን አንተወውም። ስለ እውነተኛና አስመሳይ መካሪዎች ልዩነት ከሆነ ደግሞ በአላህ ፈቃድ በቀጣይ በምናቀርበው ተከታታይ ጽሁፍ አላህ ግልፅ አድርጎ እንዲያሳየን በማለት እየለመንኩት… 👉 እስቲ እኔስ ለዚህ ፅሁፍ ምን አነሳሳኝ? 1ኛ· አላህ ጥራት የተገባው አምላክ (( " ከናንተ ውስጥ ወደ መልካም ነገር የሚጣሩና ከመጥፎ ነገር የሚከለክሉ ይኑሩ" )) በማለቱ እና ከስጋትም ለመዳን ስል … {{ " وَلْتَكُنْ مِنْكُمْ أُمَّةٌ يَدْعُونَ إِلَى الْخَيْرِ وَيَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنْكَرِ وَأُولَئِكَ هُمُ الْمُفْلِحُون " }} 【(آل عمران (104)】 (( " ከናንተ ወደ በጎ ነገር የሚጣሩ ከመጥፎ ነገር የሚከለክሉ ህዝቦች ይኑሩ የሚድኑ ህዝቦች እነኚህ ናቸው። " )) 【አል–ዒምራን (104)】 2ኛ· በተጨማሪም በመልካም ባለማዘዛቸውና ከመጥፎ ባለመከልከላቸው የተነሳ በነብያቶች አንደበት የተረገሙ በመሆናቸው … {{ " لُعِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ بَنِي إِسْرَائِيلَ عَلَى لِسَانِ دَاوُودَ وَعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ ذَلِكَ بِمَا عَصَوْا وَكَانُوا يَعْتَدُونَ} 【 (المائدة (78)】 (( " ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት በዳውድና በመርየም ልጅ በዒሳ አንደበት ተረገሙ። ይህም ትዕዛዝን በመጣሳቸውና ወሰንን የሚያልፉ በመሆናቸው ነው። " )) 【አል ማኢዳ (78)】 3ኛ· የሰው ልጆች ከመልካም ነገር ርቀው በመጥፎ ነገር ላይ ሲዘወትሩ ለጥፋት የተዘጋጁ ህዝቦች እንደሚሆኑና አስከፊ ለሆኑ አደጋዎችም ተጋላጭ ስለሚሆኑ … አላህ ካለ በቀጣዩ የምናየው ይሆናል ፦ እኔም ለናሙና ያህል እንደ መግቢያ ይህን ካልኳችሁ ወደ ዋናው መልዕክቴ ልመለስና አንድ ብዬ ስጀምር ፦ 👉 የኢኽትላጥ ትምህርት የእውነት ጉዳት የለውምን ??? 👈 በአላህ ፍቃድ ክፍል ሁለት ይቀጥላል ፦ ✍Umu_teymiyah
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
🍁#ድቅድቅ ባለ ጨለማ ውስጥ ትልቅ ብርሃን አለ። ጨለማው ወንጀላችን ሲሆን ብርሃኑ ኢስቲግፋር ከልብ ተፀፅቶ መመለስ ከዛም #የአል_ረህማንን እዝነት ማግኘት ነው። 🍁አል_ረህማንም ወደ ብርሃን ሲጠራን #እዲህ_ይላል፦‹ባሪያዎቼ ሆይ! በየእለቱ በቀንና በሌሊት ወንጀል ትፈጽማላችሁ እኔ ሁሉንም ወንጀል እምራለሁ። እናም ወንጀላችንን ማረን በሉኝ እምራችኋለሁ።›› ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy
Hammasini ko'rsatish...
ሱረቱል ካህፍ ቃሪዕ ኻሊድ አል-ጀሊል 👇👇👇👇👇 https://t.me/Alselfiy
Hammasini ko'rsatish...
018.mp324.11 MB
Photo unavailableShow in Telegram
اللهم صل وسلم على نبينا وحبيبنا ورسولنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين وسلم تسليما كثيرا صل الله عليه وسلم
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላምሽ እየናፈቀን ቀናቶች ሳምንቶች ወራቶቹ ወድመው አመቻቶች እየቆጠርን ዛሬም ነገም ተስፋ አለን ትድኛለሽ ብለን! ተስፋችንም ሁሉን አስተዳዳሪና አስተናባሪ ሁሉን ፈጣሪ የሰላም ባለቤት የሆነው የላቀው ጌታች አሏህ ነው። ያረብ....ታመና በጥና...! እንባችንም ደርቆ ሆዳችንም ነፍሮ ለብችኖም ደምቶ ቁስልን በቁስል ይዘን ይሄው ባንተው እዝነት ዛሬ ላይ ደረስን....ያረብ....ያሰላም.....ሰላምህን ያአሏህ እኛ በዳዮችን ይክሳል ብለንምንጮህበት አካል አይንረንም ሊኖረንም አይችልም إلا انت! አጥፊዎችን አጥፍተህ ለተበዲዮች ፍርድህን ሰላምህን ፍትህህን አውርድልን! ጌታችን ሆይ..! እንደ ሰው ልጅ ክፋትማ አንዳችም በምድእ ላይ ምትንቀሳቀስ ነገር ባችኖረች ነበር ....አንተ ግን ቻይ አዛኝ ነህና....እዘንልን!
Hammasini ko'rsatish...
🚫ከሚሰግድ ሰው አጠገብ ሆነን አናውራ!🚫 አሏህን ከማክበር አንዱ የዲን ህግጋትን ማክበር ነው በተለይም አሏህን ከሰው ልጆች ጋር የሚያገናኝ የሆነውን ሰላትን ማክበር ለአሏህና ለዲኑ ያለንን ክብር ከሚያሳዩ ነገሮች መሃል አንዱ ነው‼️ ሰላት ከሚሰግድ ሰው አጠገብ ሆነን ድምጽን ጮኽ አድርጎ ማውራት የሰጋጁን ሃሳብ የሚሰርቅ ነገር ማድረግ ጌታውን ከሚያከብር ሰው የማይጠበቅ ተግባር ነው። ብዙዎቻችን እናውቃለን ግን እንተገብረውም! ብዙዎቻችን አዛን ሲባል ማለትና ማድረግ የሚኖርብንን እናውቃለን ግን. አናደርገውም። (إلا من رحيم ربي) አሏህ ይዘንልን ቀልባችንን የተገራች ቀልብ ያድርግልን አሚን! ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy https://t.me/Alselfiy
Hammasini ko'rsatish...
በሰለፎች መንገድ

💎«رَبَّنَا آتِنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً وَهَيِّئْ لَنَا مِنْ أَمْرِنَا رَشَدًا ♻️« ጌታችን ሆይ! ከአንተ ዘንድ እዝነትን ስጠን፤ ለእኛም ከነገራችን ቅንን አዘጋጅልን‼️ ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ

https://t.me/Alselefiy

ለአስተያየትዎ

https://t.me/Alselefiygoldenislamicgroup

እንደ ታዘዝከው ቀጥ በል/በይ ! የሰው ልጂ እንደፈለገው ልቅና ገደብ አልባ መሆን የለበትም የታዘዘውን መታዘዝ የተከለከለውን መከልከል ያስፈልጋል ፡፡ በአንድ ነገር ላይ ከታዘዝን ወይም ከተከለከልን አሚን ብሎ መቀበልና ቀጥ ብሎ መተግበር ግዴታ ነው ፡፡ አላህ በተከበረው ቃሉ ምን ይለናል ፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ وَلَا تَطْغَوْا ۚ إِنَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም (ቀጥ ይበሉ)፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና፡፡ ♻ ♻ ♻ https://t.me/Alselfiy
Hammasini ko'rsatish...
በሰለፎች መንገድ

💎«رَبَّنَا آتِنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً وَهَيِّئْ لَنَا مِنْ أَمْرِنَا رَشَدًا ♻️« ጌታችን ሆይ! ከአንተ ዘንድ እዝነትን ስጠን፤ ለእኛም ከነገራችን ቅንን አዘጋጅልን‼️ ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ

https://t.me/Alselefiy

ለአስተያየትዎ

https://t.me/Alselefiygoldenislamicgroup

ክፍል 2 የሀጅ ና ኡምራ ት/ት ደርሶች👂👆https://t.me/ustazAbdalmajid
Hammasini ko'rsatish...
AUD-20150906-WA0084.mp37.69 MB
AUD-20150908-WA0034.mp37.68 MB
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.