Addis Ababa City Manager Office
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 474
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kun
-2130 kun
Postlar arxiv
ገቢን በተመለከተ
ያለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ ገቢ ያገኘችበት ነው። ለአብነትም ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል። ከሬሚታንስ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ የተገኘ ሲሆን ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም በቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ ሪዘርቭ በ10 እጥፍ አድጓል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ግብርናን በተመለከተ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም በሁሉም መመዘኛዎች ከፍተኛ ለውጥ በፍጥነት ማስመዝገብ ችሏል። ለአብነትም ግብርና ብቻውን የ7 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል። በምርት ደረጃም ሩዝን ወስደን ብናይ ከነበረበት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 63 ኩንታል ማሳደግ የተቻለ ሲሆን የስንዴ ምርትንም ከለውጡ በፊት ከነበረበት 47 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 280 ሚሊዮን ኩንታል በአጠረ ጊዜ ውስጥ አሳድግነዋል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የእዳ ሽግሽግን በተመለከተ
ኢትዮጵያ አሁን ላይ እዳዋን ለመክፈል ምንም ችግር የለባትም። በሪፎርሙ አመካኝነት ከ4 አስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የእዳ ሽግሽግ ተደርጓል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም መንግስት አንድም ዶላር የንግድ ብድር አልወሰደም። ይህም እዳን ለመቆጣጠር ያለንን ጽኑ አቋም ያሳያል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ብዝሃ ዘርፍ ትብብርን በተመለከተ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ወደ ብዝሃ ዘርፍ እንዲሸጋገር የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ ሆኗል። መንግስት ከህዝብ ጋር ተሳስሮ ልማት እንዲያመጣ ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠውም ከለውጡ ወዲህ ነው። ለአብነትም መንግስትና ህዝብ ተሳስረው በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት 48 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል ችለዋል። ለዚህ ስኬት ደግሞ ከ25 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ሳይታክቱ በነጻ በየ ዓመቱ ወጥተው ችግኞችን መትከል ችለዋል። ይህም የመንግስትና ህዝብ ቅንጅትን በተግባር ያሳየ ነው።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከሳርቤት- መካኒሳ- ጀርመን እና ጋርመንት አደባባዮች - ፋሪ የኮሪደር ልማት ስራዎች ትናንት ማምሻውን ጎብኝተዋል::
በልደታ ክ/ከተማና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ውስጥ የተሰራው ይህ የኮሪደር ልማት 16.5 ኪሎ ሜትር ርዝመትና ስፋት አለው።
ከሳር ቤት ጀምሮ ካርል አቦ ማዞሪያ ፣ከመከኒሳ በጀርመንና ጋርመንት አደባባዮች አድርጎ ፉሪ ድረስ የሚዘልቀው ይህ የኮሪደር ልማት ስራ የአስፋልት መንገድ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የእግረኛ መንገድ፣ የህንፃ እድሳት፣ የሳይክል መጋለቢያ፣ ፕላዛዎች፣ ስፖርት ማዘውተርያ ስፍራዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት፣ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች/ የገበያ ማዕከላት፣ ታክሲ ተርሚናል፣ የአውቶብስና ታክሲ መጫኛና ማውረጃ፣ አረንጓዴ ስፍራዎች፣ ግሪነሪ ፓርኮች፣ አንፊ ቲያትሮች፣ ካፌዎች፣ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ነው::
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ አስተባባሪ ወ/ሮ አለምፀሃይ ሽፈራውና በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ፣ የክ/ከተሞች ዋና ስራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ የከተማና ከክ/ከተማ የተውጣጡ አመራሮች ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ስለ ፕሮጀክቶቹ ይዘት በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታና በአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ አስተባባሪ ወ/ሮ አለምፀሃይ ሽፈራው ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በምክር ቤት ዓባላት የተነሱ ጥያቄዎች፡
እየተካሄደ ባለው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች፡-
1.በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት ምን ታስቧል? በተለይም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች አካባቢ
2. የፕሪቶሪያውን ስምምነት ወደ ጎን በመተው የኢትዮጵያን ህዝብ ዳግም ወደ ጦርነት ለማስገባት እየተስራ ያለውን ሂደት አደብ ለማስገዛት ምን እየተሰራ ነው፤ የአሁናዊ የትግራይ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታስ እንዴት ይታያል?
3. የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤታማ እንዲሆን ምን እየተሰራ ነው፤ በዚህ አልካተትም የሚሉ አካላትን በተመለከተስ ምን ታስቧል?
4. የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሂደት እና የመጪው ጊዜ ተስፋ ላይ፤በተለይም ሀገራችን የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠቀም እየሰራች ያለችውን አስደናቂ ስራ ለህዝቡ ቢብራራ?
5. በቀጣይ የሚገነቡ የቤት ግንባታ ሂደቶችን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥ?
6.መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩል በህዝቡ ዘንድ እየተነሱ ያሉ ችግሮች ይሰማሉ፡፡ ለወደፊቱ መልካም አስተዳደርን የበለጠ ለማስፈን ምን ታስቧል?
7. የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል በተደረገው የመንግስት ሰራተኞችን የደመወዝ ጭማሪ መነሻ በማድረግ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪና የቤት ኪራይ እየተጨመረ ነውና ይህን ህገወጥ ተግባር በሚፈፅሙ አካላት ላይ ምን እርምጃ እየተወሰደ ነው?
8. ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለመደው ሁኔታ ነው የሚካሄደው ወይስ ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚሰጡ ምክር ሀሳቦችን አካቶ ነው ይህ ከሆነ ጊዜ አያጥርም ወይ ቢብራራ?
9. የዘንድሮው ምርጫ ሰላማዊ እና ፍትሀዊ እንዲሁም እክል እንዳያጋጥመው ምን እየተሰራ ነው?
10. የትምህርት ጥራት የበለጠ እንዲሻሻል ምን እየተሰራ ነው? የመምህራን ብቃትም እንዲሁ?
11. የባህር በር ጥያቄያችንን በሰላምና በሰጥቶ መቀበል ዘዴ ለማምጣት ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት እንዴት ይታያል?
12. የሻቢያን ትንኮሳ አለማቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ምን እየተሰራ ነው?
13. በአባይ ወንዝ ግድብ ምክንያት ከቦታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች ምን ታስቧል?
14. በቤኒሻንጉል ክልል ውስጥ የተጀመረው የወርቅና ሌሎም ማዕድናት ፕሮጀክቶችን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት ምን ታስቧል?
15. በቤኒሻንጉል ክልል ከማሼ ዞን ተፈቅዶ የነበረው የመንገድ ፕሮጀክት እስካሁን አልተጀመረም ምክንያቱ ቢብራራ?
16. በቀጣይ በአባይ ወንዝ ላይ ለምንገነባው ተጨማሪ ግንባታ ቢታሰብበት?
17. በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች በተካሄዱት ጦርነቶች የደረሱ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳቶችን ቢጠቅሱልን?
18. የፖለቲካና የህሌና እስረኞች እልባት ቢሰጠው?
19. በህግ ማስከበር ስም ለሚፈፀሙ የዘፈቀደ እስር ለቀጣዩ መርጫ አሉታዊ ሁኔታ እንዳያስከትል ምን ታስቧል?
20. የኑሮ ውድነትና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን ለማረጋጋት ምን ታስቧል?
21. ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት በዘላቂነት በሰላም ለመፍታት ምን ታስቧል?
22. ነፍጥ ካነሱ አካላት ጋር ያለውን አለመግባባት መሰላም ለመፍታት መንግስት ምን አስቧል?
23. የአሲዳማነት አፈርን ለማሻሻል ምን ታስቧል?
24. የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል ቢብራራ?
25. የመድሃኒት አቅርቦትን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት ምን አቅዷል?
26.ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም አኳያ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ የተያዘ እቅድ አለ ወይ ?
27. የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የራሳቸውን ገቢ ለማመንጨት እንዲችሉ ምን እየተሰራ ነው?
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ
የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ለማቅረብ ወደ አዲስ አበባ የመጡት MAPARA A JAZZ የተባሉና የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች አዲስ አበባ ውስጥ አፈናና ድብደባ ተፈጽሞብናል ብለው በፌስ ቡክ ገፃቸው ያሰራጩት መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ማረጋገጡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው Mapara A JAZZ የተባሉት ሙዚቀኞች ወደ አዲስ አበባ የመጡት የሙዚቃ ስራቸውን ለማቅረብ እንደሆነ ፖሊስ ባሰባሰበው መረጃ ማወቅ ተችሏል።
እነዚህ ግለሰቦች ስራቸውን ጨርሰው በሠላም ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ አፈናና ድብደባ ተፈፅሞብናል ብለው በፌስ ቡክ ገፃቸው ያሰራጩትን መረጃ መሰረት በማድረግ ፖሊስ ተገቢውን የማጣራት ተግባር አከናውኗል።
ተፈፅሞብናል ስላሉት ወንጀል ለፖሊስ መረጃ ደርሶ እንደሆነ ለማረጋገጥ በክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በፖሊስ ጣቢያዎች ተጠይቆ ምንም ዓይነት የቀረበ አቤቱታ ካለመገኘቱም ባሻገር በፖሊስ ምርመራ የተሰባሰቡ የተንቀሳቃሽ ምስል፣ የፎቶና የድምጽ ማስረጃዎች እንዲሁም ከአዘጋጁ ቅሩንፉድ ኢንተርቴይመንት ጭምር እንደተረጋገጠው ግለሠቦቹ ይህን የሀሠት መረጃ የለቀቁት ብዙ ተከታዮችን ለማግኘት ሆን ብለው መሆኑን ተረጋግጧል።
ግለሰቦቹ አፈናና ድብደባ ተፈጽሞብናል ያሉት አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ/ም ቢሆንም በማግስቱ ጥቅምት 15 በተጋበዙበት መድረክ ላይ ተገኝተው የሙዚቃ ስራቸውን ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገድ አቅርበው ማጠናቀቃቸው እና በሠላም ወደመጡበት ሀገር መመለሳቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እንዲሁም ከአዘጋጆቹ የተረጋገጠና ሲሆን የተሰራጨውም መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል።
ከተማችን አዲስ አበባ በአስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ሲሆን የከተማዋን ብሎም የሀገሪቱን መልካም ገፅታ ለማጉደፍ የሚደረጉ መሠል እንቅስቃሴዎችን ህብረተሰቡ በንቃት ሊከታተልና የመረጃዎቹን ትክክለኛነት ሊያጤን እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።
Addis Ababa Police
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ በሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት ፉሪ የኮሪደር ልማት ምርቃት ላይ ያስተላለፉት መልዕክት… See more
