Ted Art
Kanalga Telegram’da o‘tish
499
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
499
ይህ ስራ ከ 5 ዓመት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ በትዕዛዝ የሰራሁት ስራ ነው። ይህን ከመጠዬቄ በፊት ከፎቶ ሰርቼ አላውቅም ነበርና ስራልኝ ተብዬ ስጠየቅ ባይመጣልኝስ ብዬ ፈርቼ ነበር ሆኖም በድፍረት ተቀበልኩት ከዛም እንዲህ ሲመጣልኝ በጣም ነበር ደስ ያለኝ😊
499
የእንጦጦ : ፓሊ : ኮሌጅ : ሥነ - ጥበብ : ትምህርት : ክፍል : ማስተማር : ከጀመረበት : ጊዜ : ( 1999 ዓ.ም. ) አንስቶ : ከመደበኛው : የመማር : ማስተማር : ሂደት : በተጓዳኝ : በሥነ - ጥበብ : ዘርፉ : አንጋፋ : ባለሙያዎችን : በመጋበዝ : የሕይወትና : የሥራ : ልምዳቸውን : ይካፈላል ፤ እነሆ : የዚህ : ወር : እንግዳችን ...
በኢትዮጽያ : የጠልሰም : ሥዕል : ጥበብ : አንጋፋው : ሠዓሊ : ሔኖክ : መልካምዘር : ይሁን ፣ ሥራዎቹን : በኢትዮጵያ : በተደጋጋሚ : ጊዜ ፣ በተለያዩ : ዓለማትም : የሥዕል : ትርዒቱን : ያቀረበና ፣ የተለያዩ : ወርክሾፓችን : የተካፈለ : ሲሆን ፤ የፊታችን : ረቡዕ : ሚያዝያ : 30, 2016 ዓ.ም. ከ 8: 00 ሰዓት : ጀምሮ : የሕይወት : ልምዱን : እና : አጠቃላይ : ስለ : ጠልሰም : ጥበብ : ምንነት ፣ ፍልስፍናና : አሰራር ፤ እንዲሁም : ስለ፡ ትምህርት ፡ ሥርዓታችን : የምንወያይ : ሲሆን ፤.. በተጨማሪም : በቅርቡ : በሻርጃህ : አርት : ፋውንዴሽንና : ሙዝዬም : ( SHARJAH ART FOUNDATION, MUSEUM ) የተከፈተውና : እየታየ : ባለው : ሥራዎቹና ፡ ሁነቱ : ዙሪያ : ውይይት : እናደርጋለን ፠
499
Repost from Event Addis Media
በእይታ ላይ የሚገኙ የሥዕል አውደርዕዮች
-የሠዓሊ መሐሪ ተሾመ ፣ የሠዓሊ ሙሉ ለገሰ፣ የሠዓሊ አሌክሳንደር ታደሰ የሥዕል ስራዎች የቀረበበት በጊዜ እይታ የተሰኘ የሥነጥበብ አውደርዕይ ከሚያዝያ 12 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወሎ ሰፈር ዳኒ ፕላዛ በሚገኘው አውሮራ የሥዕል ማሳያ ውስጥ በእይታ ላይ ይገኛል።
-የአኑማ ሀይሉ "ታሪክ እና ከዋክብት " የተሰኘው የሥነጥበብ አውደርዕይ ከሚያዝያ 17 2016 ዓ.ም ጀምሮ ቦሌ ዓለም ሲኒማ ጀርባ በሚገኘው አትሞስፌር ውስጥ በእይታ ላይ ይገኛል ።ይህ አውደርዕይ እስከ ግንቦት 2 2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ነው።
-የሠዓሊ ወርቅነህ ብዙ "ፅድቅና ኩነኔ" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ከሚያዝያ 17 2016 ዓ.ም ጀምሮ አትላስ በሚገኘው ኢትዮ ሜትሮፖሊታን የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ ቀርቧል።አውደርዕዩም ለሳምንታት በእይታ ላይ ይቆያል።
-የሠዓሊ ሰላማዊት ገ/ፃዲቅ ሥዕል ስራዎች የሚቀርቡበት "የቅጠሎች ሹክሽኩታ" የሥዕል አውደርዕይ ከሚያዝያ 18 2016 ዓ.ም ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ውስጥ በእይታ ላይ ይገኛል።ይህ የሥዕል አወድርዕይ እስከ ግንቦት 2 2016 ዓ.ም ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪ: https://t.me/EventAddis1
