JUSTIN APOLOGETICS]
ፍኖተ- ከእስልምናና ከሌሎች ቤተ እምነቶች ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ መስጫ “ #አንድ ጌታ #አንድ ሃይማኖት #አንዲት ጥምቀት፤” — ኤፌሶን 4፥5 አስተያየት ካሎት @Againest_hereticss_bot ላይ ያድርሱን
Ko'proq ko'rsatish509
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-27 kunlar
-730 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
ALL IN ONE[APK]
📚Nicene and post Nicene father's all.series :
📚 a marvelous 37-volume work containing the writings of numerous early fathers of the church, including polycarp Ignatius, Justin Martyr, Irenaeus, Theophilus, Tertullian, Origen, Clement, Hippolytus, and many others.
📕 #ANF:01-09
📕 #NPNF Series1: 101-114
📕 #lNPNF1Extras: “More Fathers” NPNF1 portion: (Augustin, Chrysostom)
📗 #NPNFSeries 2:202-214
📗 #NPNF2Extras: “More Fathers” NPNF2 portion
📚#BIBLE_VERSION:Brenton,LXX(greek english) kjv 2testament greek(LXX OT+ tischendorf8 NT), Byzantine and 71 other bible versions.
📝COMMENTARY: Catena(thomas Aquinas), Chrysostom,Lightfoot, luthr, barenes and others
📖DICTIONARY:Hebrew greek, strong Hebrew and greek,Concord...........etc
©@JUSTIN_APOLOGETICS
👍 1❤ 1🔥 1
ከልጅሽ ሌላ ባለመድኃኒት አልሻም፡፡ ከጸሎትሽም ረዳትነት በቀር ደግሞ ኃጢአቴን የሚያስተሠርይልኝ አልፈልግም፡፡ ንጽሕት ሆይ ከርኩሰቴም ከዕዳ በደሌም ሁሉ ንጹሕ አድርጊኝ፡፡ ከሥጋና ከነፍስ ቁስሌም ፈውሽኝ፡፡
፳፪. ለደዌ መድኃኒት ይሹለታል፤ ለቁስልም አቃቂር መልካሙን ቅመም ይፈልጉለታል፤ የኃጢአት ቁስል ግን ያለ ልጅሽ ፈቃድ አይጠገንም፡፡
አርጋኖን ዘሃሙስ ¹:₂₁_₂₂
©@JUSTIN_APOLOGETICS
❤ 7
“For whosoever does not confess that Jesus Christ has come in the flesh, is antichrist;”( 1 John iv. 3 . ) and whosoever does not confess the testimony of the cross,[ 230 ] is of the devil; and whosoever perverts the oracles of the Lord to his own lusts, and says that there is neither a resurrection nor a judgment, he is the first-born of Satan.
ማንም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ የማያምን ፀረ ክርስቶስ ነው። ማን በመስቀል ላይ መከራ መቀበሉን የማያምን ዲያብሎስ ነው።ማንም የክርስቶስን ትምህርት ለራሱ እንዲመችው የሚያጣምም እና የትንሣዔና የመጨረሻ ፍርድ የለም የሚል ይህም የሰይጣን የበኩር ልጅ ነው።
📚፦Polycarp : Epistle to the Philippians
Chapter VII[7]
❤ 6👍 2
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
ብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ዐረፉ
ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ ዶ/ር በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።
በረከታቸው ይደርብን።
"በአፈፃፀም ደረጃ በወንጌል የተፈፀሙ ታሪኮች ዛሬ አፈፃፀማቸው ከዚያን ጊዜ ለየት ያሉ አሉና። ለአብነትም ክርስቶስ የጾመው ከመፈተኑ አስቀድሞ ነበር። እኛ ደግሞ ከትንሳኤ በፊት እንጾማለን።
የጾሙን የጊዜ ርዝመት በተመለከተ ቀናቱ[40] ናቸው። የፆሙን ዘመን በተመለከተ ግን ልዩነት አለ። ለእኛ ጾሙ ከክርስቶስ ጋር ለመሞታችን አምሳል ነው። ጾማችንን #ለትንሳኤው በዓል ለማዘጋጀት የምናነፃበት የምንቀድስበት መሣሪያ ነው። እንዲሁም ጌታችን ለአርባ ቀናት በተከታታይ ጾመ። #እርሱ_እግዚአብሔር ነውና። እኛ ግን ስንጾም በተከታታይ ሳይሆን እስከተወሰነ ሰዓት እየፆምን እንደ አቅማችን እናደርጋለን። ምንም እንኳ አንዳንዶች ለጾም ካላቸው ፅኑ ፍቅርና ቅንዓት የተነሳ ጾማቸውን ረዘም ላሉ ሰዓታትና ቀናት ቢያራዝሙም።
እንደገናም ለደቀመዛሙርቱ ምሥጢረ ቁርባንን የሰጣቸው ከደርብ ፎቅ ላይና ከእራት በኋላ ከስቅለቱ አንድ ቀን አስቀድሞ ነበር። እኛ ግን ምሥጢረ ቁርባንን የምንፈፅመው በቤተክርስቲያን ከምግብ በፊትና እና ከትንሳኤ በኋላ ነው። እርሱ ያደረጋቸው ነገሮች ከእኛ እና እኛ ከምናደርጋቸው የተለዩ አይደሉም። ሆኖም ግን #አፈፃፀማቸውን በተመለከተ ከጊዜና ከሁኔታዎች ጋር ፍፁም የሆነ ተመሳሳይነት እና አንድነት የሌለባቸው ነገሮች አሉ።ሆኖም ለእኛ የተላለፉልንን ማድረግና መፈፀም ለሚገባን ነገሮች #አርአያና_መሠረት እንዲሆኑ ነው።"
📚 SELECT ORATIONS
OF SAINT GREGORY NAZIANZEN,: on mystery of baptism
❤ 5👍 2
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
ዜና ሻሸመኔ
‘’ዛፍ ላይ ወጥቼ ነው ምደውልላችሁ’’ - የሻሸመኔ ምእመን
ሕገ ወጥ ቡድኑ የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን በመንግሥት የጸጥታ ኃይል ታግዞ ከሰበረ በኋላ በርካታ ምእመናን ወደ አልታወቀ ቦታ እየታፈሱ እየተወሰዱ መሆኑን የከተማው ዓይን እማኞች ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን አድርሰውናል።
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን አሳልፈን አንሰጥም ባለው ምእመን ላይ የከተማው ሚሊሻ፣ፖሊስና ልዩ ኃይል በቅንጅት ተኩስ በመክፈትም በርካታ ምእመናን እንዳቆሰሉና የቆሰሉትን ሳይቀር ወደ ፖሊስ ጣቢያ እያስገቡም ይገኛሉ።
እንደመረጃ ሰጭዎቻችን ከሆነ በአይሱዙ መኪና ካህናትና ምእመናንን ከየቤቱ እያሰሱ በማፈስ ወደ አልታወቀ ቦታ እየወሰዷቸው ነው ብለዋል።
በአሁኑ ሰዓት ምእመናን በኃይል ከቤተ ክርስቲያን እንዲወጡ በመደረጉ ተበታትነው እየተሳደዱ ይገኛሉ ያሉት መረጃ ሰጫችን ይህንንም መረጃ "ዛፍ ላይ ወጥቼ ነው ምደውልላችሁ" በማለት ያለውን የደኅንነት ስጋት ገልጸውልናል።
የከተማው ኦርቶዶክሳውያን ቤተ ክርስቲያናቸውን አሳልፈው እንደማይሰጡ ሲታወቅ ሕገ ወጥ ቡድኑ ደጋፊዎች የሌላ ቤተ እምነት ተከታዮችን በማስተባበር መስቀል ሲያስሩና ነጠላ ሲያለብሱ እንደነበር የዓይን እማኛችን ተናግረዋል።