uz
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Kanalga Telegram’da o‘tish

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  analitikasi

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 11 983 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 17 269-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 838-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 11 983 obunachiga ega bo‘ldi.

04 Mart, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -107 ga, so‘nggi 24 soatda esa 0 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 0% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining N/A% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 0 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 0 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 05 Mart, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

11 983
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-337 kunlar
-10730 kunlar
Postlar arxiv
ኢትዮ ቴሌኮም በሚሰጣቸው የአገልግሎት ዘርፎች ላይ ከነገ ጀምሮ ማሻሻያ እንደሚያደርግ አስታወቀ። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ታምሩ በሰጡት መግለጫ፥ ዜጎች እንቅስቃሴያቸውን
ኢትዮ ቴሌኮም በሚሰጣቸው የአገልግሎት ዘርፎች ላይ ከነገ ጀምሮ ማሻሻያ እንደሚያደርግ አስታወቀ። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ታምሩ በሰጡት መግለጫ፥ ዜጎች እንቅስቃሴያቸውን በመገደብ በቤታቸው እንዲቆዩ በማድረግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ በሚያስችል መልኩ ማሻሻያ እንደሚደረግ ተናግረዋል። በዚህም “በቤትዎ ይቆዩ” የሞባይል ጥቅል አገልግሎት፣ የተለያዩ ድረ ገጾችን በነጻ መጎብኘት የሚያስችል አገልግሎት እንዲሁም የቅድመ ክፍያ ሞባይል አየር ሰአት የቆይታ ጊዜን የሚያራዝም አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ነው ያሉት። ይህን ተከትሎም በቤትዎ ይቆዩ የሞባይል ድምጽ ጥቅል አገልግሎት ደንበኞች በ5 ብር 30 ደቂቃ የሃገር ውስጥ የድምጽ ጥሪ 20 ነጻ የአጭር የፅሁፍ መልዕክት መጠቀም ይችላሉ። በተጨማሪም በቤትዎ ይቆዩ የሞባይል ኢንተርኔት ጥቅል አገልግሎት በ5 ብር 100 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እንዲሁም 20 ነጻ የአጭር የሃገር ውስጥ የፅሁፍ መልክት እንዲሁም በ10 ብር 250 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እና 20 ነጻ የሃገር ውስጥ አጭር የፅሁፍ መልዕክት መጠቀም ይችላሉ ተብሏል። ከዚህ ባለፈም በቤትዎ ይቆዩ የሞባይል ኢንተርኔት እና ድምጽ ጥቅል አገልግሎት ደግሞ ደንበኞች፥ በ15 ብር 300 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እና 30 ደቂቃ የሃገር ውስጥ የድምጽ ጥሪ ከ20 ነጻ የሃገር ውስጥ አጭር የፅሁፍ መልዕክት ጋር። ደንበኞች እነዚህን አገልግሎቶች ከማለዳው 12 ሰዓት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ መጠቀም የሚችሉ ሲሆን፥ ከተጠቀሰው ሰዓት ውጭ ግን በነበረው መደበኛ ታሪፍ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል። (FBC) ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኢትዮጵያ በ- #ኮሮና_ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 82 መድረሱን የጤና ሚንስትር ተናገረ። ባለፋት 24 ሰዓታት ለ447 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ8 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል
በኢትዮጵያ በ- #ኮሮና_ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 82 መድረሱን የጤና ሚንስትር ተናገረ። ባለፋት 24 ሰዓታት ለ447 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ8 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#በኢትዮጵያ ተጨማሪ 8 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው በኢትዮጵያ ተጨማሪ ስምንት ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት 447 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸው በስምንቱ ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።   ይህንንም ተከትሎ በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 82 መድረሱን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።    

አጫጭር አለም አቀፍ መረጃዎች ፦ 📌በአፍሪካ 14 ሺህ 400 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ700 በላይ ሰዎች ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል። 2,800 በላይ ሰዎች ደግሞ ከከቫይረሱ አገግመዋል። 📌የአ
አጫጭር አለም አቀፍ መረጃዎች ፦ 📌በአፍሪካ 14 ሺህ 400 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ700 በላይ ሰዎች ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል። 2,800 በላይ ሰዎች ደግሞ ከከቫይረሱ አገግመዋል።   📌የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ በቅርቡ በሁሉም ስፍራዎች የሚለመድ ነገር መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ቃል አቀባይ ዴቪድ ናቦሮ አስታወቁ። 📌መላው ዓለም በኮሮናቫይረስ በተጨነቀበት ወቅት ሕይወት በኒካራግዋ እምብዛም አልተቀየረም። የእግር ኳስ ጨዋታዎች፣ ፌስቲቫሎችም እየተካሄዱ ነው። 📌በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ ቀብር አስፈጻሚዎች ለሽያጭም ሆነ አገልግሎት ለመስጠት አስክሬን መሸፈኛ ወይም 'ቦዲ ባግ' ክምችት እንደሌላቸው ለቢቢሲ ተናገሩ። 📌ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያ በኮሮናቫይረስ ክፉኛ ልትጠቃ ትችላልች ሲሉ አስጠነቀቁ። በሩሲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ቫይረሱ ሪፖርት ከተደረገ በኋላ አገሪቱ በአንድ ቀን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ከፍተኛ ቁጥር ማስመዝገቧን ተከትሎ ፑቲን አስጠንቅቀዋል። 📌የአፍሪካ ሕብረት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ የሚያስተባብሩ ልዩ ልዑካን መድቧል። የሕብረቱ ሊቀ መንበር ሲሪል ራማፎሳ፤ ኮሮናቫይረስ የአህጉሪቱን ምጣኔ ኃብት እንዳያላሽቀው አስፈላጊው እርምጃ ሁሉ የሚወሰድበት ጊዜ ነው ብለዋል። 📌በኢኳዶር በኮሮናቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች አስክሬን በየመንገዱ እየተጣለ ነው። በኢኳዶሯ ትልቋ ከተማ ጉዓያኪል ነዋሪዎች በኮሮናቫይረስ ምክንያት የሞቱ ዘመዶቻቸውን ሳይቀብሩ ለቀናት መቆየት ግድ ሆኖባቸዋል። (BBC , CNN ) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

የዶክተር ሊያ የዛሬ ኮቪዲ19 ሪፖርት አስደንጋጭ ነው።!! ኮሮናቫይረስ ኢትዮጰያ ከገባ በኋላ ሪፖርት ሲደረግ ተጓዥ ወይንም ቫይረሱ ካለባቸው ሰዎች ጋር ንኪኪ የነበራቸውን ሰዎች ነበር በብዛት ሪፖርት
የዶክተር ሊያ የዛሬ ኮቪዲ19 ሪፖርት አስደንጋጭ ነው።!! ኮሮናቫይረስ ኢትዮጰያ ከገባ በኋላ ሪፖርት ሲደረግ ተጓዥ ወይንም ቫይረሱ ካለባቸው ሰዎች ጋር ንኪኪ የነበራቸውን ሰዎች ነበር በብዛት ሪፖርት ሲደረግ የነበሩት ዛሬ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ሪፖርት ያደረጉልን የኮቪዲ 19 ከተገኘባቸው ሶስት ሰዎቸ ውስጥ ሁለቱ ወንድ የአዲስ አበባ ታማሚዎች ምንም የውጭ ሀገረወ ጉዞ ያልነበራቸውና ቫይረሱ ካለባቸው ሰው ጋር ንኪኪ የሌላቸው በማለት ነግረውናል ።ታዲያ ሰዎቹ ከየት ያዛቸው? ከማን ነው የተገባባቸው ? የሚሉት ጥያቄዎች በጣም ወሳኝ ናቸው ። በተጨማሪም የዛሬው ሪፖርት የጉዞ ታሪክ ሳይኖረን በቫይረሱ ከተያዘ ጋርም ሰው ሳንነካካ በሌላ ነገር ኮሮናቫይረስ እየተያዘ ነው ብለን እንድንጠይቅ ይገፋናል። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ ተጨማሪ ሦስት ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ። የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት 14 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ለ247 ግለሰ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ ሦስት ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ። የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት 14 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ለ247 ግለሰቦች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉን ጠቅሰው፥ ከዚህ ውስጥ ሶስቱ ግለሰቦች በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን ሚኒስትሯ ተናግረዋል። አሁን ላይም በአጠቃላይ በኢትትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 74 ደርሷል። ➡️ሶስቱም ግለሰቦች ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላቸውም። ➡️ሶስቱም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ መሆናቸው ነው የተገለጸው። ➡️ከግለሰቦቹ መካከል ሁለቱ ወንዶች ሲሆኑ፤ሁለቱም ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳላቸው ገና አልተረጋገጠም። ➡️አንዷ የ23 ዓመት እድሜ ያላትና ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳላት መረጋገጡን መግለጫው አመላክቷል። ይህን ተከትሎም በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 74 ደርሷል። በሌላ ዜና ቫይረሱ እንዳለባቸው ከተረገጠባቸው ግለሰቦች መካካል ተጨማሪ አራት ግለሰቦች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን፤ይህን ተከትሎም በአጠቃለይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ወደ 14 ከፍ ብሏል።በኢትዮጵያ እስካሁን ለ4 ሺህ 110 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸዋል። (FBC) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ ለህግ ይቀርባሉ! በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም በቴሌግራም እና በፌስቡክ፣ ላይ ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦችን ባንኩ ተከታትሎ ለህግ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ገልጿል
ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ ለህግ ይቀርባሉ! በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም በቴሌግራም እና በፌስቡክ፣ ላይ ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦችን ባንኩ ተከታትሎ ለህግ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። ከሰሞኑን ንግድ ባንክ ኮሮና ቫይረስን በማስመልከት እስከ ሚያዚያ 30 የሚቆይ የሚያሸልም የጥያቄ እና መልስ ውድድር አዘጋጀ የሚሉ አጭበርባሪዎች መበራከታቸው ይታወቃል።

በዓለም ዙሪያ በ COVID-19 የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ወደ 2ሚሊየን ተጠግቷል፡፡ እስካሁን 1.8 ሚልየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው 113ሺ በላይ ሚሆኑት ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል ፡፡ ከ 421
በዓለም ዙሪያ በ COVID-19 የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ወደ 2ሚሊየን ተጠግቷል፡፡ እስካሁን 1.8 ሚልየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው 113ሺ በላይ ሚሆኑት ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል ፡፡ ከ 421ሺ በላይ ሰዎች ከቫይረሱ እንደዳኑ ተገልፇል፡፡ በቫይረሱ እጅጉን ከተጠቁት ሀገራት መሀከል አሜሪካ ግንባር ቀደም ስትሆን አጠቃላይ እስካሁን ከ 550ሺ በላይ ሰዎች በአሜሪካ የቫይረሱ ተጠቂ ሆነዋል፡፡ 21ሺ 6መቶ በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት ሲዳረጉ ከ 31ሺ 2መቶ በላይ ሚሆኑት አገግመዋል፡፡ በኢትዮጵያም በዛሬው ዕለት የተገለፁትን 2 ግለሰቦች ጨምሮ በአጠቃላይ እስካሁን 71ሰወች በ ቫይረሱ የተያዙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ 3ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸው ይታወሳል፡፡ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ከማርች 27 ጀምሮ ከዱባይ የነበረው በረራ ሙሉበሙሉ ቆሟል!! በኢትዮጲያ አየር መንገድም በኢምሬትስ አየር መንገድም! ዶ/ር ሊያ ታደሰ

#Ethiopia : ከዱባይና ከሳውዲ አረቢያ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያውያን ለበሽታ በሚያጋልጥ ሁኔታ እየተባረሩ መሆናቸው ከባድ ስጋት ላይ ጥሎናል"--- የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ። ዜጎቹ ያ
#Ethiopia : ከዱባይና ከሳውዲ አረቢያ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያውያን ለበሽታ በሚያጋልጥ ሁኔታ እየተባረሩ መሆናቸው ከባድ ስጋት ላይ ጥሎናል"--- የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ። ዜጎቹ ያለ ምንም የጤና ምርመራ የሚመጡ መሆናቸው ደግሞ አደጋውን እንደሚያከብደው ሚኒስትሯ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ ገልፀዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በጣም ከፍተኛ ጥንቃቄና ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት ከሳውዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የሚመለሱት ከ3ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ምንም አይነት የጤና ምርመራ ሳይደርግላቸው የሚመለሱና የቆይታቸው ጊዜም ጥንቃቄ የተሞላበት ባለመሆኑ ትልቅ ስጋት ላይ ጥሎናል ብለዋል፡፡ Via #eliasmeseret

የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ከኮሮናቫይረስ አገግመው ከሆስፒታል ወጡ፡፡ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሆስፒታል ገብተው ህክምና ሲከታተሉ የቆዩት የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን አ
የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ከኮሮናቫይረስ አገግመው ከሆስፒታል ወጡ፡፡ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሆስፒታል ገብተው ህክምና ሲከታተሉ የቆዩት የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን አገግመው መውጣታቸው ተነግሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ባሳለፍነው ሳምንት በግል ዶክተራቸው ምክር ሆስፒታል መግባታቸው ይታወሳል። (FBC) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Ethiopia : በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የተመረመሩ ሰዎች 3863 ሰዎች መሆናቸው መግለጫው ያመለክታል። ▪️በ24 ሰዐት ውስጥ 286 ሰዎች ተመርምረዋል ከዛም ውስጥ 2 ሰው በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጠዋል። ▪️በአጠቃላይ በቫይረሱ ተይዘው 56 ሰዎች ህክምና እየተደረገላቸው። ▪️ በኮቪድ-19 ሶስት ሰዎች ሞተዋል ▪️ ሁለት ሰዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ▪️ አስር ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል ዶ/ር ሊያ ታደሰ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ ሁለት ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ባለፉት 24 ሰዓታት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 286 ግለሰቦች መካከል ነው ሁለቱ የኮሮናቫይረስ እንደ
በኢትዮጵያ ሁለት ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ባለፉት 24 ሰዓታት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 286 ግለሰቦች መካከል ነው ሁለቱ የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የተረጋገጠው ብለዋል የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ። ይህን ተከትሎም በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 71 ደርሷል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት፥ ዛሬ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሁለቱም ግለሰቦች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን አስታውቀዋል። ሁለቱም ሴቶች ሲሆኑ፥ አንዷ የ24 ዓመት እድሜ ያላትና ከአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውሳኔ በፊት ከዱባይ የተመለሰች መሆኗን መግለጫው አመላክቷል። ሌላኛዋ ግለሰብ የ35 ዓመት እድሜ ያላትና ከቱርክ ወደ ኢትዮጵያ መጥታ በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ክትትል ስታደርግ የነበረች ናት። እስካሁን ባለው ሂደት በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ለ3 ሺህ 863 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መከናወኑም በመግለጫው ተጠቁሟል። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ግለሰቦች መካከል 56ቱ የህክምና ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ። አሁን ላይ በጽኑ ህሙማን ክፍል ክትትል የሚደረግላቸው ህሙማን አለመኖራቸውም በመግለጫው ተመላክቷል። ቫይረሱ እንዳለባቸው ከተረጋጋጠባቸው ግለሰቦች መካከል ሶስት ሰዎች በቫይረሱ ህይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው። Via #FBC 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Google #Apple ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ አፕል እና ጉግል ኮሮናቫይረስ ካለበት ሰው ጋር ንክኪ ላደረጉ ሰዎች ጥቆማ የሚሰጥ መሣሪያ እየሠሩ መሆኑ ተነግሯል:: መሣሪያው አንድ ሰው በቫይረሱ
#Google #Apple ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ አፕል እና ጉግል ኮሮናቫይረስ ካለበት ሰው ጋር ንክኪ ላደረጉ ሰዎች ጥቆማ የሚሰጥ መሣሪያ እየሠሩ መሆኑ ተነግሯል:: መሣሪያው አንድ ሰው በቫይረሱ ከተያዘ ግለሰብ ጋር የቅርብ ግንኙነት ካደረገ ለግለሰቡ መረጃ የሚሰጥ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ መሣሪያው ከጥቃሞ በተጨማሪ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎች ለማሰስ ጥቅም ላይ ለሚውሉ ሌሎች መተግበሪያዎች የመረጃ ግብዓት እንደሚሰጥም ተገልጿል። መሣሪያውን መጠቀም የሚፈልጉ ሰዎች ማንነታቸውን ሳያሳውቁ መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን ቫይረሱ ከያዛቸው ሰዎች ጋር ንክኪ ማድረግ አለማድረጋቸው የሚጣራውም የስልካቸውን ብሉቱዝ በመጠቀም ነው። መሣሪያውን የሚጠቀም ሰው ካገኛቸው ሰዎች መካከል ኮቪድ-19 የተገኘባቸው ግለሰቦች ካሉ፤ መሣሪያው የማስጠንቀቂያ መልዕክት ይልካል። አፕል እና ጉግል በጥምረት ባወጡት መግለጫ፤ መሣሪያው የተጠቃሚዎችን የግላዊነት መብት እንደማይጋፋ ተነግሯል፡፡ ምንጭ፡- BBC ~ INSA 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በኢትዮጵያ ተጨማሪ አራት ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው፤ 10 ግለሰቦች ደግሞ ከህመሙ አገግመዋል በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 345 ግለሰቦች መካከል አራቱ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ102 ሺ አለፈ። ጣልያን በቫይረሱ ከ18ሺ 800 በላይ ሰዎች የሞቱባት የመጀመርያዋ ሀገር ስትሆን አሜሪካ ከ18 ሺ በላይ ዜጎቿን ያጣች ሁለተኛዋ
#በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ102 ሺ አለፈ። ጣልያን በቫይረሱ ከ18ሺ 800 በላይ ሰዎች የሞቱባት የመጀመርያዋ ሀገር ስትሆን አሜሪካ ከ18 ሺ በላይ ዜጎቿን ያጣች ሁለተኛዋ ሀገር ሆናለች። ስፔንም እንዲሁ ከ15ሺ 700 በላይ ዜጎች የሞቱባት 3ኛዋ ሀገር ስትሆን ፈርንሳይም ከ13 ሺ በላይ ዜጎቿን በሞት አጥታለች። በአፍሪካም እንዲሁ በቱኒዝያ 25 ሰዎች፣ በደቡብ አፍሪካ 24 ሰዎች እንዲሁም ኒጀር ደግሞ 11 ሰዎችን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት አጥተዋል። በኛም ሀገር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት 3 ሰዎችን ህይወታቸው ማለፉ ይታወቃ። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈው የ3ኛ ሰው... 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

የኮሮና ቫይረስ ከተቀሰቀሰ 100 ቀን ሞላው‼️ 📌የኮሮና ቫይረስ ከቻይናዋ ውሀን ከተማ ከተቀሰቀሰ በሁወላ ብዙ የአለም ሀገራትን እያካለለ እነሆ 100 ቀን ሞላው። 📌በነዚህ 100 ቀናት ከ 1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲጠቁ ከ 94 ሺ በላይ ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል። 📌አሜሪካ ከ 400 ሺ በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲጠቃባት ከ14 ሺ ሰው በላይ ሰዎች ሞተውባታል 📌በጣሊያንም ከ 16 ሺ በላይ ሰዎች ሞተውባታል 📌በሀገራችንም 65 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን 2 ሰዎችም በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን አጥተዋል። 📌እባካችሁ የጤና ባለሙያዎች የሚሉትን እንተግብር። እ ን ራ ራ ቅ እጃችንን በሳሙና እንታጠብ። እናልፈዋልን አትጠራጠሩ‼️ ግን ሳትረበሹ ተጠንቀቁ። መዘናጋት ዋጋ ያስከፍለናል።

#COVID_19 UPDATE ⬆️ በኢትዮጵያ ያለውን የCOVID-19 ወቅታዊ ሁኔታ ዝርዝር መረጃ ይመልከቱ 👇👇👇 https://telegra.ph/CIVID-19-UPDATE-04-10 ━━━━━━━━━━━
#COVID_19 UPDATE ⬆️ በኢትዮጵያ ያለውን የCOVID-19 ወቅታዊ ሁኔታ ዝርዝር መረጃ ይመልከቱ 👇👇👇 https://telegra.ph/CIVID-19-UPDATE-04-10 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

Corona virus update #COVID-19 as on April. 9 18: 30 GMT 📌 የተረጋገጠ የ ቫይረሱ ተጠቂዎች 1,577,783 📌 የሟቾች ቁጥር 93,673 📌 ያገገሙ (የተሻላቸው) #348,319 📌 ዛሬ በዩኤስኤ የተመዘገበ የሟች ቁጥር 1,326 📌 በዩኤስኤ የተመዘገበ ጠቅላላ የሟች ቁጥር 16,114 📌 አዲስ ኬዝ 20,527 📌 ጠቅላላ በዩኤስኤ ያሉ የቫይረሱ ተጠቂዎች 455,454 📌 ዛሬ በጣልያን የተመዘገበ የሟች ቁጥር 610 📌 በጣልያን የተመዘገበ ጠቅላላ የሟች ቁጥር 18,279 📌 አዲስ ኬዝ 4,204 📌 ጠቅላላ በጣሊያን ያሉ የቫይረሱ ተጠቂዎች 143,626 📌 ዛሬ በስፔን የተመዘገበ የሟች ቁጥር 446 📌 በስፔን የተመዘገበ ጠቅላላ የሟች ቁጥር 15,238 📌 አዲስ ኬዝ 4,226 📌 ጠቅላላ በስፔን ያሉ የቫይረሱ ተጠቂዎች 152,446 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━