ar
Feedback
᎛ᎇᎄʜ🌍ᎢᎏɎᎇᎱᵗʰ

᎛ᎇᎄʜ🌍ᎢᎏɎᎇᎱᵗʰ 

الذهاؚ إلى القناة على Telegram

ስለ቎ክኖሎጂ አዳዲስ መሚጃዎቜ እና ሶፍትዌር ዚሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ ዹቮክኖሎጂ ነው ኹዘመኑ ጋር አብሚው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

إ؞هار المزيد

📈 ن؞رة تحليلية على قناة تيليجرام ᎛ᎇᎄʜ🌍ᎢᎏɎᎇᎱᵗʰ 

تُعد قناة ᎛ᎇᎄʜ🌍ᎢᎏɎᎇᎱᵗʰ  (@computer_android_tricks) لاعؚاً ن؎طاً. يضم المجتمع حالياً 11 983 م؎تركاً، محتلاً المرتؚة 17 269 في ف؊ة التعليم والمرتؚة 2 838 في منطقة Ethiopia.

📊 م؀؎رات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في МевіЎПЌП، حقق الم؎روع نمواً سريعاً وجمع 11 983 م؎تركاً.

ؚحسؚ آخر الؚيانات ؚتاريخ 04 مارس, 2026، تحاف؞ القناة على ن؎اط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء ؚمقدار -107، وفي آخر 24 ساعة ؚمقدار 0، مع ؚقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يؚلغ متوسط تفاعل الجمهور 0‎%. وخلال أول 24 ساعة من الن؎ر يحصد المحتوى عادةً N/A‎% من ردود الفعل نسؚةً إلى إجمالي الم؎تركين.
  • وصول المن؎ورات: يحصل كل من؎ور على متوسط 0 م؎اهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 م؎اهدة.
  • التفاعلات والاستجاؚة: يتفاعل الجمهور ؚانت؞ام؛ متوسط التفاعلات لكل من؎ور يؚلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف الم؀لف القناة ؚأنها مساحة للتعؚير عن الآراء الذاتية:
“ስለ቎ክኖሎጂ አዳዲስ መሚጃዎቜ እና ሶፍትዌር ዚሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ ዹቮክኖሎጂ ነው ኹዘመኑ ጋር አብሚው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

ؚفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث الؚيانات ؚتاريخ 05 مارس, 2026) تحاف؞ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُ؞هر التحليلات تفاعلاً ن؎طاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن ف؊ة التعليم.

11 983
الم؎تركون
لا توجد ؚيانات24 ساعات
-337 أيام
-10730 أيام
أر؎يف الم؎اركات
ኢትዮ ቎ሌኮም በሚሰጣ቞ው ዚአገልግሎት ዘርፎቜ ላይ ኹነገ ጀምሮ ማሻሻያ እንደሚያደርግ አስታወቀ። ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ታምሩ በሰጡት መግለጫ፥ ዜጎቜ እንቅስቃሎያ቞ውን
ኢትዮ ቎ሌኮም በሚሰጣ቞ው ዚአገልግሎት ዘርፎቜ ላይ ኹነገ ጀምሮ ማሻሻያ እንደሚያደርግ አስታወቀ። ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬሕይወት ታምሩ በሰጡት መግለጫ፥ ዜጎቜ እንቅስቃሎያ቞ውን በመገደብ በቀታ቞ው እንዲቆዩ በማድሚግ ዚኮሮና ቫይሚስ ስርጭትን ለመቀነስ በሚያስቜል መልኩ ማሻሻያ እንደሚደሚግ ተናግሚዋል። በዚህም “በቀትዎ ይቆዩ” ዚሞባይል ጥቅል አገልግሎት፣ ዚተለያዩ ድሚ ገጟቜን በነጻ መጎብኘት ዚሚያስቜል አገልግሎት እንዲሁም ዚቅድመ ክፍያ ሞባይል አዹር ሰአት ዚቆይታ ጊዜን ዚሚያራዝም አገልግሎት ኹነገ ጀምሮ ተግባራዊ ይደሹጋል ነው ያሉት። ይህን ተኚትሎም በቀትዎ ይቆዩ ዚሞባይል ድምጜ ጥቅል አገልግሎት ደንበኞቜ በ5 ብር 30 ደቂቃ ዹሃገር ውስጥ ዚድምጜ ጥሪ 20 ነጻ ዹአጭር ዹፅሁፍ መልዕክት መጠቀም ይቜላሉ። በተጚማሪም በቀትዎ ይቆዩ ዚሞባይል ኢንተርኔት ጥቅል አገልግሎት በ5 ብር 100 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እንዲሁም 20 ነጻ ዹአጭር ዹሃገር ውስጥ ዹፅሁፍ መልክት እንዲሁም በ10 ብር 250 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እና 20 ነጻ ዹሃገር ውስጥ አጭር ዹፅሁፍ መልዕክት መጠቀም ይቜላሉ ተብሏል። ኹዚህ ባለፈም በቀትዎ ይቆዩ ዚሞባይል ኢንተርኔት እና ድምጜ ጥቅል አገልግሎት ደግሞ ደንበኞቜ፥ በ15 ብር 300 ሜጋ ባይት ኢንተርኔት እና 30 ደቂቃ ዹሃገር ውስጥ ዚድምጜ ጥሪ ኹ20 ነጻ ዹሃገር ውስጥ አጭር ዹፅሁፍ መልዕክት ጋር። ደንበኞቜ እነዚህን አገልግሎቶቜ ኚማለዳው 12 ሰዓት እስኚ ቀኑ 10 ሰዓት ድሚስ መጠቀም ዚሚቜሉ ሲሆን፥ ኹተጠቀሰው ሰዓት ውጭ ግን በነበሹው መደበኛ ታሪፍ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል። (FBC) ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኢትዮጵያ በ- #ኮሮና_ቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 82 መድሚሱን ዚጀና ሚንስትር ተናገሚ። ባለፋት 24 ሰዓታት ለ447 ሰዎቜ ዚላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ8 ሰዎቜ ላይ ዚኮሮና ቫይሚስ ተገኝቶባ቞ዋል
በኢትዮጵያ በ- #ኮሮና_ቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 82 መድሚሱን ዚጀና ሚንስትር ተናገሚ። ባለፋት 24 ሰዓታት ለ447 ሰዎቜ ዚላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ8 ሰዎቜ ላይ ዚኮሮና ቫይሚስ ተገኝቶባ቞ዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#በኢትዮጵያ ተጚማሪ 8 ሰዎቜ ዚኮሮና ቫይሚስ ተገኘባ቞ው በኢትዮጵያ ተጚማሪ ስምንት ሰዎቜ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ዚኢፌዎሪ ዚጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ። ሚኒስ቎ሩ በሰጠው መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት 447 ሰዎቜ ዚላቊራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቾው በስምንቱ ሰዎቜ ላይ ቫይሚሱ ተገኝቷል።   ይህንንም ተኚትሎ በሀገሪቱ ቫይሚሱ ዚተገኘባ቞ው ሰዎቜ ቁጥር 82 መድሚሱን ነው ሚኒስ቎ሩ ያስታወቀው።    

አጫጭር አለም አቀፍ መሚጃዎቜ ፊ 📌በአፍሪካ 14 ሺህ 400 ሰዎቜ በቫይሚሱ ሲያዙ ኹ700 በላይ ሰዎቜ ሰዎቜ ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል። 2,800 በላይ ሰዎቜ ደግሞ ኚኚቫይሚሱ አገግመዋል። 📌ዚአ
አጫጭር አለም አቀፍ መሚጃዎቜ ፊ 📌በአፍሪካ 14 ሺህ 400 ሰዎቜ በቫይሚሱ ሲያዙ ኹ700 በላይ ሰዎቜ ሰዎቜ ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል። 2,800 በላይ ሰዎቜ ደግሞ ኚኚቫይሚሱ አገግመዋል።   📌ዚአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ማድሚግ በቅርቡ በሁሉም ስፍራዎቜ ዚሚለመድ ነገር መሆኑን ዹዓለም ጀና ድርጅት ቃል አቀባይ ዎቪድ ናቊሮ አስታወቁ። 📌መላው ዓለም በኮሮናቫይሚስ በተጚነቀበት ወቅት ሕይወት በኒካራግዋ እምብዛም አልተቀዚሚም። ዚእግር ኳስ ጚዋታዎቜ፣ ፌስቲቫሎቜም እዚተካሄዱ ነው። 📌በዩናይትድ ኪንግደም ዹሚገኙ ቀብር አስፈጻሚዎቜ ለሜያጭም ሆነ አገልግሎት ለመስጠት አስክሬን መሾፈኛ ወይም 'ቊዲ ባግ' ክምቜት እንደሌላ቞ው ለቢቢሲ ተናገሩ። 📌ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያ በኮሮናቫይሚስ ክፉኛ ልትጠቃ ትቜላልቜ ሲሉ አስጠነቀቁ። በሩሲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ቫይሚሱ ሪፖርት ኹተደሹገ በኋላ አገሪቱ በአንድ ቀን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ኹፍተኛ ቁጥር ማስመዝገቧን ተኚትሎ ፑቲን አስጠንቅቀዋል። 📌ዚአፍሪካ ሕብሚት ኹዓለም አቀፉ ማህበሚሰብ ድጋፍ ዚሚያስተባብሩ ልዩ ልዑካን መድቧል። ዚሕብሚቱ ሊቀ መንበር ሲሪል ራማፎሳፀ ኮሮናቫይሚስ ዚአህጉሪቱን ምጣኔ ኃብት እንዳያላሜቀው አስፈላጊው እርምጃ ሁሉ ዚሚወሰድበት ጊዜ ነው ብለዋል። 📌በኢኳዶር በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ዚሞቱ ሰዎቜ አስክሬን በዚመንገዱ እዚተጣለ ነው። በኢኳዶሯ ትልቋ ኹተማ ጉዓያኪል ነዋሪዎቜ በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ዚሞቱ ዘመዶቻ቞ውን ሳይቀብሩ ለቀናት መቆዚት ግድ ሆኖባ቞ዋል። (BBC , CNN ) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ዚዶክተር ሊያ ዚዛሬ ኮቪዲ19 ሪፖርት አስደንጋጭ ነው።!! ኮሮናቫይሚስ ኢትዮጰያ ኚገባ በኋላ ሪፖርት ሲደሚግ ተጓዥ ወይንም ቫይሚሱ ካለባ቞ው ሰዎቜ ጋር ንኪኪ ዚነበራ቞ውን ሰዎቜ ነበር በብዛት ሪፖርት
ዚዶክተር ሊያ ዚዛሬ ኮቪዲ19 ሪፖርት አስደንጋጭ ነው።!! ኮሮናቫይሚስ ኢትዮጰያ ኚገባ በኋላ ሪፖርት ሲደሚግ ተጓዥ ወይንም ቫይሚሱ ካለባ቞ው ሰዎቜ ጋር ንኪኪ ዚነበራ቞ውን ሰዎቜ ነበር በብዛት ሪፖርት ሲደሚግ ዚነበሩት ዛሬ ዚጀና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ሪፖርት ያደሚጉልን ዚኮቪዲ 19 ኚተገኘባ቞ው ሶስት ሰዎቾ ውስጥ ሁለቱ ወንድ ዚአዲስ አበባ ታማሚዎቜ ምንም ዹውጭ ሀገሹወ ጉዞ ያልነበራ቞ውና ቫይሚሱ ካለባ቞ው ሰው ጋር ንኪኪ ዹሌላቾው በማለት ነግሹውናል ።ታዲያ ሰዎቹ ኚዚት ያዛ቞ው? ኹማን ነው ዚተገባባ቞ው ? ዚሚሉት ጥያቄዎቜ በጣም ወሳኝ ናቾው ። በተጚማሪም ዚዛሬው ሪፖርት ዹጉዞ ታሪክ ሳይኖሚን በቫይሚሱ ኚተያዘ ጋርም ሰው ሳንነካካ በሌላ ነገር ኮሮናቫይሚስ እዚተያዘ ነው ብለን እንድንጠይቅ ይገፋናል። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ ተጚማሪ ሊስት ግለሰቊቜ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ተሚጋገጠ። ዚጀና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት 14 ሰዎቜ ደግሞ ኚቫይሚሱ አገግመዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ለ247 ግለሰ
በኢትዮጵያ ተጚማሪ ሊስት ግለሰቊቜ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ተሚጋገጠ። ዚጀና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት 14 ሰዎቜ ደግሞ ኚቫይሚሱ አገግመዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ለ247 ግለሰቊቜ ዚላቊራቶሪ ምርመራ መደሹጉን ጠቅሰው፥ ኹዚህ ውስጥ ሶስቱ ግለሰቊቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው መሚጋገጡን ሚኒስትሯ ተናግሚዋል። አሁን ላይም በአጠቃላይ በኢትትዮጵያ በቫይሚሱ ዹተጠቁ ሰዎቜ ቁጥር 74 ደርሷል። ➡ሶስቱም ግለሰቊቜ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ዹውጭ ሀገር ዹጉዞ ታሪክ ዚላ቞ውም። ➡ሶስቱም ዚአዲስ አበባ ኹተማ ነዋሪ መሆናቾው ነው ዚተገለጞው። ➡ኚግለሰቊቹ መካኚል ሁለቱ ወንዶቜ ሲሆኑፀሁለቱም ኚበሜታው ኚተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳላ቞ው ገና አልተሚጋገጠም። ➡አንዷ ዹ23 ዓመት እድሜ ያላትና ኚበሜታው ኚተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳላት መሚጋገጡን መግለጫው አመላክቷል። ይህን ተኚትሎም በኢትዮጵያ ዚኮሮና ቫይሚስ ዚተገኘባ቞ው ሰዎቜ ቁጥር 74 ደርሷል። በሌላ ዜና ቫይሚሱ እንዳለባ቞ው ኚተሚገጠባ቞ው ግለሰቊቜ መካካል ተጚማሪ አራት ግለሰቊቜ ኚበሜታው ያገገሙ ሲሆንፀይህን ተኚትሎም በአጠቃለይ ኚበሜታው ያገገሙ ሰዎቜ ቁጥር ወደ 14 ኹፍ ብሏል።በኢትዮጵያ እስካሁን ለ4 ሺህ 110 ሰዎቜ ዚኮሮና ቫይሚስ ዚላቊራቶሪ ምርመራ ተደርጎላ቞ዋል። (FBC) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ሀሰተኛ መሹጃ ዚሚያሰራጩ ለህግ ይቀርባሉ! በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም በ቎ሌግራም እና በፌስቡክ፣ ላይ ሀሰተኛ መሚጃዎቜን ዚሚያሰራጩ ግለሰቊቜን ባንኩ ተኚታትሎ ለህግ ለማቅሚብ እዚሰራ መሆኑን ገልጿል
ሀሰተኛ መሹጃ ዚሚያሰራጩ ለህግ ይቀርባሉ! በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም በ቎ሌግራም እና በፌስቡክ፣ ላይ ሀሰተኛ መሚጃዎቜን ዚሚያሰራጩ ግለሰቊቜን ባንኩ ተኚታትሎ ለህግ ለማቅሚብ እዚሰራ መሆኑን ገልጿል። ኹሰሞኑን ንግድ ባንክ ኮሮና ቫይሚስን በማስመልኚት እስኚ ሚያዚያ 30 ዹሚቆይ ዚሚያሞልም ዚጥያቄ እና መልስ ውድድር አዘጋጀ ዹሚሉ አጭበርባሪዎቜ መበራኚታ቞ው ይታወቃል።

በዓለም ዙሪያ በ COVID-19 ዹተጠቁ ሰዎቜ ቁጥር ወደ 2ሚሊዹን ተጠግቷል፡፡ እስካሁን 1.8 ሚልዹን በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ ተጠቅተው 113ሺ በላይ ሚሆኑት ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል ፡፡ ኹ 421
በዓለም ዙሪያ በ COVID-19 ዹተጠቁ ሰዎቜ ቁጥር ወደ 2ሚሊዹን ተጠግቷል፡፡ እስካሁን 1.8 ሚልዹን በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ ተጠቅተው 113ሺ በላይ ሚሆኑት ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል ፡፡ ኹ 421ሺ በላይ ሰዎቜ ኚቫይሚሱ እንደዳኑ ተገልፇል፡፡ በቫይሚሱ እጅጉን ኚተጠቁት ሀገራት መሀኹል አሜሪካ ግንባር ቀደም ስትሆን አጠቃላይ እስካሁን ኹ 550ሺ በላይ ሰዎቜ በአሜሪካ ዚቫይሚሱ ተጠቂ ሆነዋል፡፡ 21ሺ 6መቶ በላይ ሰዎቜ ለህልፈተ ህይወት ሲዳሚጉ ኹ 31ሺ 2መቶ በላይ ሚሆኑት አገግመዋል፡፡ በኢትዮጵያም በዛሬው ዕለት ዚተገለፁትን 2 ግለሰቊቜ ጚምሮ በአጠቃላይ እስካሁን 71ሰወቜ በ ቫይሚሱ ዚተያዙ መሆናቾው ተገልጿል፡፡ 3ሰዎቜ በቫይሚሱ ምክንያት ለህልፈተ ህይወት መዳሚጋ቞ው ይታወሳል፡፡ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ኚማርቜ 27 ጀምሮ ኚዱባይ ዹነበሹው በሚራ ሙሉበሙሉ ቆሟል!! በኢትዮጲያ አዹር መንገድም በኢምሬትስ አዹር መንገድም! ዶ/ር ሊያ ታደሰ

#Ethiopia : ኚዱባይና ኚሳውዲ አሚቢያ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያውያን ለበሜታ በሚያጋልጥ ሁኔታ እዚተባሚሩ መሆናቾው ኚባድ ስጋት ላይ ጥሎናል"--- ዚጀና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ። ዜጎቹ ያ
#Ethiopia : ኚዱባይና ኚሳውዲ አሚቢያ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያውያን ለበሜታ በሚያጋልጥ ሁኔታ እዚተባሚሩ መሆናቾው ኚባድ ስጋት ላይ ጥሎናል"--- ዚጀና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ። ዜጎቹ ያለ ምንም ዚጀና ምርመራ ዚሚመጡ መሆናቾው ደግሞ አደጋውን እንደሚያኚብደው ሚኒስትሯ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ ገልፀዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በጣም ኹፍተኛ ጥንቃቄና ዝግጅት እዚተደሚገ መሆኑን ተናግሚዋል። በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት ኚሳውዲ አሚቢያ ወደ አገራ቞ው ዚሚመለሱት ኹ3ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ምንም አይነት ዚጀና ምርመራ ሳይደርግላ቞ው ዚሚመለሱና ዚቆይታ቞ው ጊዜም ጥንቃቄ ዚተሞላበት ባለመሆኑ ትልቅ ስጋት ላይ ጥሎናል ብለዋል፡፡ Via #eliasmeseret

ዚብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን ኚኮሮናቫይሚስ አገግመው ኚሆስፒታል ወጡ፡፡ በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ሆስፒታል ገብተው ህክምና ሲኚታተሉ ዚቆዩት ዚብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን አ
ዚብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን ኚኮሮናቫይሚስ አገግመው ኚሆስፒታል ወጡ፡፡ በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ሆስፒታል ገብተው ህክምና ሲኚታተሉ ዚቆዩት ዚብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን አገግመው መውጣታ቞ው ተነግሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን ኚኮሮና ቫይሚስ ጋር በተያያዘ ባሳለፍነው ሳምንት በግል ዶክተራ቞ው ምክር ሆስፒታል መግባታ቞ው ይታወሳል። (FBC) 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Ethiopia : በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ዚተመሚመሩ ሰዎቜ 3863 ሰዎቜ መሆናቾው መግለጫው ያመለክታል። ▪በ24 ሰዐት ውስጥ 286 ሰዎቜ ተመርምሹዋል ኹዛም ውስጥ 2 ሰው በቫይሚሱ መያዛ቞ው ተሚጋግጠዋል። ▪በአጠቃላይ በቫይሚሱ ተይዘው 56 ሰዎቜ ህክምና እዚተደሚገላ቞ው። ▪ በኮቪድ-19 ሶስት ሰዎቜ ሞተዋል ▪ ሁለት ሰዎቜ ወደ ሀገራ቞ው ተመልሰዋል ▪ አስር ሰዎቜ ኚበሜታው አገግመዋል ዶ/ር ሊያ ታደሰ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ ሁለት ተጚማሪ ሰዎቜ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ዚጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ። ባለፉት 24 ሰዓታት ዚላቊራቶሪ ምርመራ ኹተደሹገላቾው 286 ግለሰቊቜ መካኚል ነው ሁለቱ ዚኮሮናቫይሚስ እንደ
በኢትዮጵያ ሁለት ተጚማሪ ሰዎቜ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ዚጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ። ባለፉት 24 ሰዓታት ዚላቊራቶሪ ምርመራ ኹተደሹገላቾው 286 ግለሰቊቜ መካኚል ነው ሁለቱ ዚኮሮናቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው ዹተሹጋገጠው ብለዋል ዚጀና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ። ይህን ተኚትሎም በኢትዮጵያ ቫይሚሱ ዚተገኘባ቞ው ሰዎቜ ቁጥር 71 ደርሷል። ዚጀና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት፥ ዛሬ ቫይሚሱ ዚተገኘባ቞ው ሁለቱም ግለሰቊቜ ኢትዮጵያዊያን መሆናቾውን አስታውቀዋል። ሁለቱም ሎቶቜ ሲሆኑ፥ አንዷ ዹ24 ዓመት እድሜ ያላትና ኚአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውሳኔ በፊት ኚዱባይ ዚተመለሰቜ መሆኗን መግለጫው አመላክቷል። ሌላኛዋ ግለሰብ ዹ35 ዓመት እድሜ ያላትና ኚቱርክ ወደ ኢትዮጵያ መጥታ በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ክትትል ስታደርግ ዚነበሚቜ ናት። እስካሁን ባለው ሂደት በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ለ3 ሺህ 863 ሰዎቜ ዚላቊራቶሪ ምርመራ መኹናወኑም በመግለጫው ተጠቁሟል። ቫይሚሱ ኚተገኘባ቞ው ግለሰቊቜ መካኚል 56ቱ ዹህክምና ክትትል እያደሚጉ ይገኛሉ። አሁን ላይ በጜኑ ህሙማን ክፍል ክትትል ዹሚደሹግላቾው ህሙማን አለመኖራ቞ውም በመግለጫው ተመላክቷል። ቫይሚሱ እንዳለባ቞ው ኚተሚጋጋጠባ቞ው ግለሰቊቜ መካኚል ሶስት ሰዎቜ በቫይሚሱ ህይወታ቞ው ማለፉ ዚሚታወስ ነው። Via #FBC 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Google #Apple ግዙፍ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቹ አፕል እና ጉግል ኮሮናቫይሚስ ካለበት ሰው ጋር ንክኪ ላደሹጉ ሰዎቜ ጥቆማ ዚሚሰጥ መሣሪያ እዚሠሩ መሆኑ ተነግሯል:: መሣሪያው አንድ ሰው በቫይሚሱ
#Google #Apple ግዙፍ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቹ አፕል እና ጉግል ኮሮናቫይሚስ ካለበት ሰው ጋር ንክኪ ላደሹጉ ሰዎቜ ጥቆማ ዚሚሰጥ መሣሪያ እዚሠሩ መሆኑ ተነግሯል:: መሣሪያው አንድ ሰው በቫይሚሱ ኚተያዘ ግለሰብ ጋር ዚቅርብ ግንኙነት ካደሚገ ለግለሰቡ መሹጃ ዚሚሰጥ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ መሣሪያው ኚጥቃሞ በተጚማሪ በበሜታው ኚተያዙ ሰዎቜ ጋር ንክኪ ያላ቞ውን ሰዎቜ ለማሰስ ጥቅም ላይ ለሚውሉ ሌሎቜ መተግበሪያዎቜ ዹመሹጃ ግብዓት እንደሚሰጥም ተገልጿል። መሣሪያውን መጠቀም ዹሚፈልጉ ሰዎቜ ማንነታ቞ውን ሳያሳውቁ መመዝገብ ዚሚቜሉ ሲሆን ቫይሚሱ ኚያዛ቞ው ሰዎቜ ጋር ንክኪ ማድሚግ አለማድሚጋ቞ው ዚሚጣራውም ዚስልካ቞ውን ብሉቱዝ በመጠቀም ነው። መሣሪያውን ዹሚጠቀም ሰው ካገኛ቞ው ሰዎቜ መካኚል ኮቪድ-19 ዚተገኘባ቞ው ግለሰቊቜ ካሉፀ መሣሪያው ዚማስጠንቀቂያ መልዕክት ይልካል። አፕል እና ጉግል በጥምሚት ባወጡት መግለጫፀ መሣሪያው ዚተጠቃሚዎቜን ዚግላዊነት መብት እንደማይጋፋ ተነግሯል፡፡ ምንጭ፡- BBC ~ INSA 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በኢትዮጵያ ተጚማሪ አራት ግለሰቊቜ ዚኮሮና ቫይሚስ ተገኘባ቞ውፀ 10 ግለሰቊቜ ደግሞ ኹህመሙ አገግመዋል በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ዚላቊራቶሪ ምርመራ ኹተደሹገላቾው 345 ግለሰቊቜ መካኚል አራቱ ዚኮሮና ቫይሚስ እንደተገኘባ቞ው መሚጋገጡን ዚጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በመላው ዓለም በኮሮና ቫይሚስ ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኹ102 ሺ አለፈ። ጣልያን በቫይሚሱ ኹ18ሺ 800 በላይ ሰዎቜ ዚሞቱባት ዚመጀመርያዋ ሀገር ስትሆን አሜሪካ ኹ18 ሺ በላይ ዜጎቿን ያጣቜ ሁለተኛዋ
#በመላው ዓለም በኮሮና ቫይሚስ ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኹ102 ሺ አለፈ። ጣልያን በቫይሚሱ ኹ18ሺ 800 በላይ ሰዎቜ ዚሞቱባት ዚመጀመርያዋ ሀገር ስትሆን አሜሪካ ኹ18 ሺ በላይ ዜጎቿን ያጣቜ ሁለተኛዋ ሀገር ሆናለቜ። ስፔንም እንዲሁ ኹ15ሺ 700 በላይ ዜጎቜ ዚሞቱባት 3ኛዋ ሀገር ስትሆን ፈርንሳይም ኹ13 ሺ በላይ ዜጎቿን በሞት አጥታለቜ። በአፍሪካም እንዲሁ በቱኒዝያ 25 ሰዎቜ፣ በደቡብ አፍሪካ 24 ሰዎቜ እንዲሁም ኒጀር ደግሞ 11 ሰዎቜን በኮሮና ቫይሚስ ምክንያት አጥተዋል። በኛም ሀገር በኮሮና ቫይሚስ ምክንያት 3 ሰዎቜን ህይወታ቞ው ማለፉ ይታወቃ። 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ በሜታ ምክንያት ህይወታ቞ው ያለፈው ዹ3ኛ ሰው... 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ዚኮሮና ቫይሚስ ኹተቀሰቀሰ 100 ቀን ሞላው‌ 📌ዚኮሮና ቫይሚስ ኚቻይናዋ ውሀን ኹተማ ኹተቀሰቀሰ በሁወላ ብዙ ዹአለም ሀገራትን እያካለለ እነሆ 100 ቀን ሞላው። 📌በነዚህ 100 ቀናት ኹ 1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ ሲጠቁ ኹ 94 ሺ በላይ ሰዎቜ ለሞት ተዳርገዋል። 📌አሜሪካ ኹ 400 ሺ በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ ሲጠቃባት ኹ14 ሺ ሰው በላይ ሰዎቜ ሞተውባታል 📌በጣሊያንም ኹ 16 ሺ በላይ ሰዎቜ ሞተውባታል 📌በሀገራቜንም 65 ሰዎቜ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሲሆን 2 ሰዎቜም በቫይሚሱ ምክንያት ህይወታ቞ውን አጥተዋል። 📌እባካቜሁ ዚጀና ባለሙያዎቜ ዚሚሉትን እንተግብር። እ ን ራ ራ ቅ እጃቜንን በሳሙና እንታጠብ። እናልፈዋልን አትጠራጠሩ‌ ግን ሳትሚበሹ ተጠንቀቁ። መዘናጋት ዋጋ ያስኚፍለናል።

#COVID_19 UPDATE ⬆ በኢትዮጵያ ያለውን ዹCOVID-19 ወቅታዊ ሁኔታ ዝርዝር መሹጃ ይመልኚቱ 👇👇👇 https://telegra.ph/CIVID-19-UPDATE-04-10 ━━━━━━━━━━━
#COVID_19 UPDATE ⬆ በኢትዮጵያ ያለውን ዹCOVID-19 ወቅታዊ ሁኔታ ዝርዝር መሹጃ ይመልኚቱ 👇👇👇 https://telegra.ph/CIVID-19-UPDATE-04-10 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

Corona virus update #COVID-19 as on April. 9 18: 30 GMT 📌 ዹተሹጋገጠ ዹ ቫይሚሱ ተጠቂዎቜ 1,577,783 📌 ዚሟ቟ቜ ቁጥር 93,673 📌 ያገገሙ (ዚተሻላ቞ው) #348,319 📌 ዛሬ በዩኀስኀ ዹተመዘገበ ዚሟቜ ቁጥር 1,326 📌 በዩኀስኀ ዹተመዘገበ ጠቅላላ ዚሟቜ ቁጥር 16,114 📌 አዲስ ኬዝ 20,527 📌 ጠቅላላ በዩኀስኀ ያሉ ዚቫይሚሱ ተጠቂዎቜ 455,454 📌 ዛሬ በጣልያን ዹተመዘገበ ዚሟቜ ቁጥር 610 📌 በጣልያን ዹተመዘገበ ጠቅላላ ዚሟቜ ቁጥር 18,279 📌 አዲስ ኬዝ 4,204 📌 ጠቅላላ በጣሊያን ያሉ ዚቫይሚሱ ተጠቂዎቜ 143,626 📌 ዛሬ በስፔን ዹተመዘገበ ዚሟቜ ቁጥር 446 📌 በስፔን ዹተመዘገበ ጠቅላላ ዚሟቜ ቁጥር 15,238 📌 አዲስ ኬዝ 4,226 📌 ጠቅላላ በስፔን ያሉ ዚቫይሚሱ ተጠቂዎቜ 152,446 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━