uz
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Kanalga Telegram’da o‘tish

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Ko'proq ko'rsatish
1 720
Obunachilar
-124 soatlar
-47 kunlar
-1430 kunlar
Postlar arxiv
እዬዬ አልባ ሞቴ ለራሴ አዝኜ ሳልጨርስ ባዘንኩብሽ ቀን ሳልተክዝ በሬን ሳልዘጋ ለእዬዬ ሳልደበር ተበድዬ አዬ. . . በብርዳም ኮተታም ዓለም ቁር ከውስጥሽ ሲፋለም ጨለማ ጮሆ ሲንጫረር ዝምታሽ ታሞ ሲጫፈር ክፍተትሽ ከፍቶ ሲዛባ ዛቢያሽ ከራሱ ሲቃባ ማን ነበረ ያለበሰሽ - ያንን ጸዓዳ ጋቢ እርምሽንም ባታወጪ - ከድንኳኑ እንድታድሪ ብርዱን ችለሽ እንድትበሪ ለቅሶኛውን እንድትመስዪ አዪ. . . የኔም ተራ ደረሰና ስወድቅልሽ ከወና ስንከባለል ዝምታ ጋር እነጋንጩርን ሳናግር እነጽልመትን ስጋግር ከነ ጋኔንም ስበደር ማን ነበረ ያሰከረኝ - በዚህ የሃቅ አረቄ በወጉ እንኳ ሳላዝን - ከለቅሶ ቀድሞ ሳቄ ድሮስ መቼ ለ'ኔ አውቄ ብርቄ. . . ለራሴ አዝኜ ሳልጨርስ ባዘንኩብሽ ቀን ሳልተክዝ በሬን ሳልዘጋ ለእዬዬ ሳልደበር ተበድዬ አዬ አዬ . . . ይኸው ክፉ ቀን መጥቶ ደጄም አደረ ተዘግቶ ሞት ቢሞላው መንገዱን እኔስ ሞትኩኝ የምለው አንቺ ውስጥ ሞቼ እንደሆን ድብን. . . #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ @poeticsaturdays @artsmailinglist

የናፈቅኩሽ ቀን ናፈቀኝ

Hello Tibeb community, Due to the current situation of the Corona virus, the application deadline for Tibeb Be Adebabay has b
Hello Tibeb community, Due to the current situation of the Corona virus, the application deadline for Tibeb Be Adebabay has been postponed for two weeks! Which means you will have more #time ⏰⏳to work on your applications! 📝 Work on your ideas and apply before April 2, 2020! Find out more: http://bit.ly/2Id4yQk Apply: https://bit.ly/2SMzU6o Call us on +251 98 332 031 #tibebbeadebabay #TBA2020 #Tibeb #AddisAbaba #ArtinAddis

የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ቫይረስን በማስመልከት በተቻለ መጠን ሰዎች በአንድ ቦታ መሰባሰብን መቀነስ እንዳለብን አሳስቧል። በዚህም መሠረት በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን የብሔራዊ የሥነ-ግ
+1
የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ቫይረስን በማስመልከት በተቻለ መጠን ሰዎች በአንድ ቦታ መሰባሰብን መቀነስ እንዳለብን አሳስቧል። በዚህም መሠረት በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን የብሔራዊ የሥነ-ግጥም ግጥሚያ(ውድድር) ላልተወሰነ ጊዜ ለማራዘም ተገደናል። ከሚመለከተው መንግሥታዊ አካል "ሕዝባዊ መሰባሰቦችን" ማድረግ እንደሚቻል ሲነገር ውድድሩን የምናደርግ መሆኑን እያሳወቅን ሁላችንም የግጥማዊ ቅዳሜ ቤተሰቦች በያለንበት ደኅና እንድንሆን ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን። Relying on recommendations from the Ethiopian government due to the spread of COVID-19 in Ethiopia, we have decided to postpone the 1st Annual Ethiopia National Poetry slam until a later time in which it is safer to have large, public gatherings. We will rely on guidance from public health officials about when we may reschedule so that everyone in our Poetic Saturdays family can remain as safe as possible. We look forward to rescheduling our very first National Poetry Slam so that a National Champion may be crowned! Stay safe out there, you beautiful people!

በኢንስታ ግራም ካሜራችሁ 👆 ይህን በማንበብ ብቻ የኢንስታግራም ገጻችንን ተቀላቀሉ

Follow me on Instagram! Username: gitem_sitem https://www.instagram.com/gitem_sitem?r=nametag
Follow me on Instagram! Username: gitem_sitem https://www.instagram.com/gitem_sitem?r=nametag

Morning Tibeb community, the second week to submit your applications since it's opened! 🤩🤩 We are excited to receive them! 🗃 So here is the link to the application form https://bit.ly/2SMzU6o for those who apply online. We will send tips and suggestions through the week! Good luck!

ላንቺ #ሰይፈተማም #poeticsaturdays #ግጥምሲጥም ከሰውነትሽ በላይ - ሰው ለመሆንሽ ክብር ዘንባባ እንኳን ባልዘነጥፍ - ቄጤማ ፊትሽ ባልከምር ከመንገድሽ ጋሬጣውን ባልመነጥር እንቅፋት አልሆንብሽም - እንደው ሌላው ሌላው ቢቀር ላንቺ የሚገባሽ እንዲገባሽ - መስመሮቼን አነጻለሁ በለከፈሽ እንዳይከፋሽ - መልካም አፎች እጣራለሁ ባንቀመጥ በእኩል ሚዛን - የሰው ነገር ቢሆን ግራ እስከማይሽ እተጋለሁ - ውጅንብሩ እንዲጠራ ላንቺ መሞቱን እየረሳ ሰው - ቀኑ ላይ ቀመር ሲያበዛ የህይወት መስመር ተስታ- በጾታ ዳስ ስንገዛ ዓለምሽ ተንቃ ሳይ - መከበርሽ ተወዛውዛ ሳንካ አልባ ምድር ስዬ - ብራ ቀንሽን ላወዛ ቀስቃሽ አለሁሽ ለፋፊ - እንዳትታዪ በዋዛ ላንቺ አቅሜን የማልለካብሽ - እንደሰው ላይሽ ሰው ሆኜ እራሴን የማነጻልሽ - ከመንገድ ሳይሽ ሰክኜ ለራሴ ስል የማግዝሽ - ከወንድ ጉራ መንኜ የምነቃ በጥበብሽ - የነቁ ቃላት ሰንኜ ላንቺ እንደ ራስሽ ስትኖሪ - የምትችይውን ይውቁ በሴትነት ምሽግ ከትተው - አቅምሽን እንዳይንቁ ብርሃን ይሁን መንገድሽ የሚመራሽም ልብሽ የምትመሪውም እራስሽ የልብሽ ብርሃን ፈክቶ - ድቅድቃችን ላይ ያብራ ቀስቃሽ ነኝ ያለው ሁላ - ተቀስቅሶ ይጠራ ተቀስቅሶ ይጣራ ተቀስቅሶ እንዲበራ የተፈጥሮ አካል ሆነሽ - እሱም ተፈጥሮን ይኑራ ነጻ አውጥተሽው ደሞ - ነጻ ይሁን ከአጥሩ ነጻ አውጥተሽው ደሞ- ባንቺው ይኩራ እንዳገሩ ላንቺ እምር እንዳሉ - ላንቺ ይሁኑ ቀናት ሁሉ ሰይፈ ተማም 2012

.........ለጀግኒት........... አንቺ ጀግኒት የጀግና ሰው ዘውድ አንቺ ውድ ሰው የውድ ሰው ልጅት አንቺ የእንቁ ፍልቃቂ የወርቅ ሰው ውበት የተኖረልሽ የሚኖርልሽ የተኮራብሽ የሚኮራብሽ አንቺ የአንቺ የእሷ የእሱ የእኔ መከታ እመቤቲቱ ስለ ነፃነትሽ አባትሽ በእናትሽ እዝጎይታ ክንዱ የጠነከረው እንደልብሽ ውለሽ በሀገርሽ ቋንቋ ደስታሽን ከሀዘንሽ እንድተርኪበት ሸማሽ ጃኖ እንዲሆን እንድትቆነጂበት ሲያሻሽ ጥጡን ፈትለሽ ሲልሽ ጠጅ ጥለሽ ጎጆ ታሞቂበት ሞቶልሻል፡፡ ግን ደግሞ ብትልፈሰፈሺ ብትፈሪና ትቢትሽ ቢበዛ የሞተልሽ ጀግና ይፋረድሻል፡፡ ስንፍናሽ ከላቀ ተራራው ያኮርፍሻል ወንዙ ያለቅስብሻል፡፡ ተነሺ ካባ ልበሺ ታሪክ ታጠቂ ጉራን አውልቂ ስንፍናን ናቂ ታሪክ አቅልሚ ክብር ጠምጥሚ ሀገርን አልሚ ልህቀት ቅሰሚ ኑሪ ክበሪ ጠ ን ክ ሪ፡፡ ውድ ኢትዮጲያዊቷ ኑሪ ክበሪ እንኳን አደረሰሽ፡፡ 👑👑👑👑👑 መልካም አድዋ ተፃፈ:- በርብቃ ሲሳይ 2010 @getem @getem @getem

See you then. Get your tickets @FeministFront
See you then. Get your tickets @FeministFront

ስንል ጥቅም ጥቅም ፍቅርን ጥርቅምቅም ስንል ፍቅር ፍቅር ጥቅማችን ላይ ቅርቅር አቤቱ አድለነ ጥቅማጥቅም ያለው ፍቅር አዘግነነ #ጥቅር #ሰይፈተማም

ተዘዋውሯል! በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት የሀገራዊ የግጥም ውድድራችንን ወደ መጋቢት 11 አዘዋውረነዋል። ያኔ እንገናኝ! POSTPONED! Due to scheduling concerns, we have d
+1
ተዘዋውሯል! በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት የሀገራዊ የግጥም ውድድራችንን ወደ መጋቢት 11 አዘዋውረነዋል። ያኔ እንገናኝ! POSTPONED! Due to scheduling concerns, we have decided to postpone the National Poetry Slam to March 20th! See you there!

ማን ያውቃል?🙇‍♂️ በ ቶማስ አድማሱ @Mmiinnuu . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል? ለመውለድ ያቀደ ገና ከመውደዱ የምሩን ይሞታል? ማን ያውቃል? ባይኔ መኃሉ ላይ ካይኔ ጥቁሩ ላይ ብሌኔን ታቅፈሽ በዓለም ሌላ ላላይ ላንቺ እየዘመርኩ ሆንኩኝ ማኅሌታይ። .... እተረከዝሽ ስር ላንቺ ስል ወረድሁ/ኝ ትተሺኝ ብትበርሪ መልአክ ነች አልሁ/ኝ ማን ያውቃል እውነትን ፤ እውነትም ማን ያውቃል? ማን ነው የሚጸና ከሃቅ እና ከቃል?? ማን ያውቃል? እጄን ይዘሽ ከእጅሽ ሆኜ በመሃሉ ከብደሽ ላይኔ ሌላው አንሶ ቀልሎ ሁሉ በሳቀብን ስናሽካካ የረታንን ስንጥለው ባረፍድ እንኳ እንዳይስቁ አጣት ብለው ታቅፈኝ ይሆን ፤አውቃት ይሆን፤ አያት ይሆን? ቀን መቃዠት አንቺን ማለም ሌሊት ሲሆን ማን ያውቃል ? መገጣጠም እንጂ አሁን አለ "እውነት"? የቱ ነው ሃቅ ሚሆን ከህልም እና ቅዠት? የቱ ነው የሚያም ከእውነት ማጣት እና የውሸት ከማግኘት? ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል? ማን ያውቃል?

በከፍታ መብረር ከመሬት ያርቃል ብለው የመከሩ ፡ ሠጎን እና ዶሮ ተመሬት አደሩ ። ሁለቱም ልክ ነው ያለችው ሦረኔ ትንሹን ተራምዳ፡ ትንሹን በራ ነው ፡ ሠማይ እን ምድርን የምታሥታርቀው ፡ በሠማዩ ነጥታ በምድሩ ጠቆረች ፡ ባለ ሁለት መልኳ በመዘነቋ ነው ጅግራ የተባለች ። የጅግራም ትርጉሙ ፡ ከጃችን ሥያሜ "ጅ" እየጎተተ ከታች ካለው እግር ... ግንን እየሣበ ...

ትሑት ምህላ ========= አቤቱ ጌታ ሆይ ፣ የኢትዮጵያውያንን እምነት የግሪክን ጥበብ መሻት የአይሁድን ምልክት ጥማት የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት- ልክፍት የሱፊን ተደሞ የዜንን አርምሞ የተመሥ
ትሑት ምህላ ========= አቤቱ ጌታ ሆይ ፣ የኢትዮጵያውያንን እምነት የግሪክን ጥበብ መሻት የአይሁድን ምልክት ጥማት የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት- ልክፍት የሱፊን ተደሞ የዜንን አርምሞ የተመሥጦ መገለጥን ምትሐት ፣ ......አጣምረህ ለነብሴ ሥጣት! በዚህ፣ኃይሏ ግርማ እንደ ጨለማ ፣ ቀለም ድንበርን ታሥማማ.....። አሜን። ዲበኩሉ ጌታ ሰኔ ፳ ፳፻፰ ዓ.ም -----------//---------- የምድር ዘላለም ድንቅ መፅሀፍ ነው በተገኘበት ይነበብ!! ያነበበ ብዙ ያተርፋል # @sufafel @sufafel @sufafel

​​Abstract Utter silence I listen Whooshing sound of cars Some how it makes me calm The moon lighting the darkness Some how it heals Some how the beauty Puts me in trance Some how it is easier To bare my soul To people I barely know It is okay to be bare And sometimes it is okay To wallow in pain I want to live here Here is just me Here is just me alone Here is my home Do we have a meaning? Do you have a meaning? Do I? We work, sleep and eat Wake up to do it all again What if this is hell? What if hell is just like a broken Record Repitition of the same thing over and over Suddenly you wouldn't know when it will be over I say all this while I am sober When you pause Only eyes can see Ears can hear Fears dissapear life reappear And you exist I crave this pause The one that closed the door Is my shadow who likes to to oppose He is in control I suppose Somehow they misunderstood It is he who is talking Not me It is he who you seeing Not me "Me" is a misconstruction Made by the perception of what I think is others perception of me I really don't know what "Me" is I don't know "I" As soon as the word "I" exist We perish This abstract mind Science couldn't decode History couldn't record This isn't my mind speaking This isn't my body your witnessing Just the formation of DNA Manifestation of information That lived for decade -Anima #Existence

ክብልል.aac1.66 MB

Ethiopian hiphop music remix https://youtu.be/yTtoOjyqIhI