Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Kanalga Telegram’da o‘tish
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Ko'proq ko'rsatish1 610
Obunachilar
+124 soatlar
+47 kun
-130 kun
Postlar arxiv
Markaz Al-Hudah qhur'aan aliilisiyyih fanteena dooqasse barteenitih taxx...
https://youtube.com/watch?v=4TX852gBBfU&si=X2Jb1zwdMpaH5BUj
Repost from Kassis Faage
Yi toobokoy gad ankacisaanam Khaatimah umaane ellecaboh umaanel sinam taceem maay taaxigen?
Num elle suginnaan caalatal raba ceelalloh Makiinal gad fakka heeh gexak sugek too num raba wak maca axcuk rabe leeh gad abak rabam raq mali. Kaaduk Num elle rabe caalatal ugutaah Qhiyaamah ayro gad abak uguttek maca takkale hay Yalli wohuk amaan neh yacayuh
A Sheek Yalli kaah racmatay xiibitta iyyah anu innih rooci kak yewqe uddur Recorderil yaabisak sugen gaditte gabbaaqak rabe mara ubleh iyya! tah dubuk isih ankacise mara tekkek isih ankacissa isi garil yan mara edde ankacsissa hee mari anninnak tanih hinnay inkinnah Miixiyal Yallih gino inkih kah taabbennah sabab yakke maray rabeenik wadir keenil gexak raqta umaane yessemeggeh caba anninnak tanih!
Qhalbi teelllek ta Sheek ankacissek wadir gad ankacisak maraqta!
⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Kassisfaage
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
📌 ጥቅል ጥቆማ
ሙታንን በቤት ውስጥ መቅበር
አስገዳጅ ሁኔታ በሌለበት በቤት (በግል ግቢ) ውስጥ ሟችን መቅበር አብዛኛዎቹ የፊቅህ ሊቃውንት ዘንድ የተጠላ ነው፤ የተወሰኑት ጭራሽ እርም አድርገውታል። ሆኖም ከሚቀበረው ሰው ማንነት አንፃር የሺርክ መንገድን ለመዝጋት መከልከሉ ጥርጥር የለውም።
መልእክተኛችን ﷺ በቤታቸው የተቀበሩት ነብያት በሞቱበት ቦታ መቀበራቸው በልዩ ድንጋጌ የተወደደ እንደሆነ የሚያሳይ ሐዲሥ በመኖሩ ነው። በዚህ ላይ የሳቸው ቀብር በተገለጠ የመቃብር ስፍራ ቢሆን ለባእድ አምልኮ እንዳይጋለጥ ስለተሰጋም ነው።
በመስጂድ ውስጥ መቀበር
መስጂዶች ለሰላትና ለተያያዥ የአምልኮ ተግባራት እንዲውሉ ወቅፍ የተደረጉ በመሆናቸው በግቢያቸውም ይሁን በውስጣዊ ግንባታቸው ውስጥ ማንንም መቅበር አይቻልም። ይህን ማድረግ ከወቅፍ ንብረት እንደመዝረፍ ይቆጠራል፤ ቀብሩ ለሺርክ ተግባራት እንዲጋለጥም በር ይከፍታል።
የመልእክተኛችን ﷺ ቀብር ከመስጂዳቸው ጋር የተቀላቀለው ከጊዜ በኋላ መስጂዱ ሲስፋፋ በወቅቱ የነበሩ አስተዳደሮች በወሰዱት እርምጃ ነው። በሰሓቦች ዘመን መስጂዱ በተለያዩ አቅጣጫዎች ከመስፋፋቱ ጋር በቀብሩ በኩል ግን ምንም አልተነካም ነበር።
ስለሆነም ከጥንት ጀምሮ ታላላቅ የኢስላም ስብእናዎች ሲሞቱ ሙስሊሞች በሚቀበሩት የመቃብር ስፍራ እንጂ በቤታቸው ወይም በመስጂድ ውስጥ አይቀበሩም ነበር።
©: ሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
መቃብር ላይ ቤት/ ዶሪሕ መገንባት
~
በኢትዮጵያም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታዋቂ ሰዎች መቃብር ላይ የተገነቡ ህልቆ መሳፍርት ዶሪሆች አሉ። ይሄ ተግባር አላዋቂ ሰዎች መቃብሮቹን እንዲያመልኳቸው በር ከፍቷል። ይሄ ደግሞ ችግሩ ተከስቶ ሲታይ ብቻ ሳይሆን ስጋት ሲኖር ራሱ ቀድመን በጥብቅ ልንተዋወስበት የሚገባ ጉዳይ ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል:-
اللَّهُمَّ لَا تَجْعَلْ قَبْرِي وَثَنًا يُعْبَدُ اشْتَدَّ غَضَبُ اللَّهِ عَلَى قَوْمٍ اتَّخَذُوا قُبُورَ أَنْبِيَائِهِمْ مَسَاجِدَ
{ጌታዬ ሆይ! ቀብሬን የሚመለክ ጣኦት አታድርገው። የነብዮቻቸውን መቃብር የአምልኮት ቦታዎች አድርገው የያዙ ሰዎች ላይ የአላህ እርግማን በረታ!} [ሚሽካቱል መሷቢሕ፡ 750]
ይህን ያሉት እነዚያዎቹ የሰሩት ጥፋት በሳቸው ቀብር ላይ እንዳይደገም ስለሰጉ ለማስጠንቀቅ ነው። ይሄ ባይሆን ኖሮ ቀብራቸው ውጭ ላይ በግላጭ ይሆን እንደነበር እናታችን ዓኢሻ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ተናግራለች። [ቡኻሪ፡ 1390] [ሙስሊም፡ 529]
ሶሐቦች አደራቸውን ተወጥተዋል። የነብዩ ﷺ ቀብር የአምልኮት ቦታ እንዳይሆን በመስጋት ከሞቱበት ቤት ከጓዳቸው ቀብረዋቸዋል። ኢማም ኢብኑ ተይሚያ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦ “የነብዩ ﷺ ቀብር ምድር ላይ ካሉ ቀብሮች ሁሉ በላጭ ነው። ሆኖም ግን መመላለሻ ተደርጎ እንዳይያዝ ከልክለዋል። ስለዚህ ከሳቸው ቀብር ውጭ ያለው ማንም ይሁን ምን ይበልጥ ለክልከላ የተገባ ነው።” [አልኢቅቲዷእ፡ 2/172]
አንዳንዶች ግን የነብዩን ﷺ ኑዛዜ ጥሰው፣ አደራቸውን በልተው፣ አጥብቀው የከለከሉትን ጉዳይ በተቃራኒው አጥብቀው ያዘዙት በሚመስል ሁኔታ በታላላቅ ሰዎችና በሱፊያ ቁንጮዎች መቃብር ላይ ምን የመሳሰለ ቤት ይገነባሉ። ከዚያም የተለያዩ ሺርኮችን ለመፈፀም ቀብራቸው ዘንድ ይመላለሳሉ። ኢስላም ማለት የመቃብር አምልኮት ማለት እስከሚመስል ድረስ የሙስሊሙ አለም በዶሪሕ ተጥለቅልቋል።
በሶሪያ ደማስቆ ከተማ ውስጥ ብቻ መቶ ዘጠና አራት ዶሪሖች አሉ። ግብፅ ውስጥ ከስድስት ሺህ በላይ የሚመለኩ ዶሪሖች አሉ። በዒራቅ፣ በሱዳን፣ በሊቢያ፣ በህንድ፣ በፓኪስታን፣ በአፍጋኒስታን፣ በየመን፣ ... በሌሎችም የሙስሊም ሃገራት ያለው ነገር የከፋ እንጂ የተሻለ አይደለም።
የበለጠ የሚያሸማቅቀው ደግሞ ቀላል የማይባሉ ዶሪሖች ከነ ጭራሹ ቀብርም ሆነ የተቀበረ ነገር የሌላቸው ባዶ መሆናቸው ነው። ለምሳሌ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት ነው ተብሎ ካይሮ ውስጥ እርድ የሚፈፀምበት፣ ስለት የሚቀረብበት፣ ጠዋፍ የሚደረግበት፣ ሌሎችም ዘግናኝ የሺርክ ተግባራት የሚፈፀሙበት ዶሪሕ አለ። በተመሳሳይ ሶሪያ ውስጥ ደማስቆና ሐለብ (አሌፖ) ከተማ አቅራቢያ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። ምን ይሄ ብቻ! ዒራቅ ውስጥ ከርበላእና ነጀፍ ከተሞች ውስጥ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። በ“እ $ራኤል” ስር ባለችው በፍልስጤማዊቷ የዐስቀላን ከተማም የሑሰይን ዶሪሕ ይገኛል። ይህ ሁሉ እንግዲህ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት የሚባል ነው። ለመሆኑ ሑሰይን ስንት ጭንቅላት ነው የነበራቸው?
የዐሊይ ልጅ ዘይነብ የሞተችው መዲና የተቀበረችውም በቂዕ ነው። ነገር ግን ሶሪያ ደማስቆ ውስጥ እና ግብፅ ካይሮ ውስጥ በስሟ የተገነባ ዶሪሕ አለ። ግብፅ አሌክሳንድሪያ ከተማ ውስጥ የአቡ ደርዳእ ዶሪሕ አለ። ዓሊሞች ግን እርግጠኛ ሆነው እዚያ እንዳልተቀበሩ ይናገራሉ። ዐብዱረሕማን ብኑ ዐውፍ የተቀበሩት መዲና በቂዕ ውስጥ ነው። በዒራቋ የበስራ ከተማ ግን በስማቸው የተገነባ ዶሪሕ አለ። የነብዩ ﷺ ልጅ ሩቀያ የሞተችውም የተቀበረችውም መዲና ውስጥ ነው፣ ነብዩ በህይወት እያሉ። በሚገርም ሁኔታ ሶሪያ ውስጥም ግብፅ ውስጥም በስሟ ዶሪሕ አለ።
ወደ ሀገራችን ስንመጣም በተመሳሳይ በርካታ የታወቁ ሰዎች መቃብር በላያቸው ላይ ዶሪሕ ተገንብቶባቸዋል። ከዚያም ዶሪሑ ዘንድ የሚፈፀሙ ብዙ ዘግናኝ ሺርኮች አሉ። ይሄ ሁሉ ኢስላም የሚያዘው ነው ወይ? በፍፁም! መረጃውስ? አቡል ሀያጅ አል አሰዲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
قَالَ لِي عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ : أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ ﷺ؟ ( ... وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ)
"0ሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ እንዲህ ብለውኛል፦ 'አላህ መልእክተኛ ﷺ በላኩብኝ አምሳያ አልክህምን? { ...ከፍ ያለ ቀብር አይተህ (ከሌሎች ቀብሮች ጋር እኩል) ሳታስተካክለው እንዳታልፍ!}' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 969]
ኢብኑ ዑመር - ረዲየላሁ ዐንሁማ - ከዐብዱረሕማን ቀብር ላይ ቤት ተሰርቶ ቢመለከቱ “አስወግደው አንተ ልጅ። የሚያጠልለው ስራው ነው” ብለዋል። [ተሕዚሩ ሳጂድ፡ 130]
ስለነዚህ ጉዳዮች የምንማማረው ወገናችን በሺርክ እንዳይፈተን በማሰብ ቀድሞ ለማስታወስ እንጂ አንዳንዶች እንደሚመስላችሁ ለእልህና ለብሽሽቅ አይደለም። ደግሞም ሁሉ ይቀበላል ብለን አንጠብቅም። ነገር ግን በኛ ላይ ያለው ሐቁን ማድረስ ብቻ ነው። እስትንፋሳችን እስካለ ድረስ ይህንን ማድረግ ይጠበቅብናል። አላህ ያለለት ለመረጃ እጅ ይሰጣል ኢንሻአላህ። በእልህ በመነሳሳት ብዙ ርቀት አልፈው ለሚሄዱት ወገኖቻችን በዚህ የአላህ ቃል ለማስታወስ እንሞክራለን፦
{ یَـٰۤأَیُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّمَا بَغۡیُكُمۡ عَلَىٰۤ أَنفُسِكُمۖ مَّتَـٰعَ ٱلۡحَیَوٰةِ ٱلدُّنۡیَاۖ ثُمَّ إِلَیۡنَا مَرۡجِعُكُمۡ فَنُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ }
"እናንተ ሰዎች ሆይ! ወሰን ማለፋችሁ (ጥፋቱ) በነፍሶቻችሁ ላይ ብቻ ነው። (እርሱም) የቅርቢቱ ሕይወት መጠቀሚያ ነው። ከዚያም መመለሻችሁ ወደኛ ነው። ትሠሩት የነበራችሁትንም ሁሉ እንነግራችኋለን።" [ዩኑስ፡ 23]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Qhur-aan tafsiir qafar afat bicsen Applicationi
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.jannahismygoal.quranafar
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
Qafár rakaakayak daga raqta islaam caagiidah malah buxa tatrussa sissik ...
https://youtube.com/watch?v=vEDVpWhFwRQ&si=hqMmYHdJFwVy2Fzx
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
“Suurat Kahfik Maca Barinna” Dr. Seqid Qali Haaruun
https://youtube.com/watch?v=u-zItpSn394&si=ryW3PKo-oUeqyI5p
Repost from የኡስታዝ ኢልያስ አሕመድ የትምህርት መድረክ (official)
ከ 4 አመታት በፊት…
https://youtu.be/KLMtm54Fks0?si=xkTkMqE4hPczgHnG
Repost from የኡስታዝ ኢልያስ አሕመድ የትምህርት መድረክ (official)
🎞 ከክርክር ራስን ማራቅ
በሸይኽ ኢልያስ አህመድ (ከ 30 ምክሮች)
https://youtu.be/jmEiUeI_ssM?si=vJ9K4obeU5EQh-RR
✍️Yalli cakki cakkiinot yableeh, katya mara nee abay!
🤚Baatil baatiliinot yableeh, kak yaxxeere mara nee abay!!
✍️Md Ali
