Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Kanalga Telegram’da o‘tish
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Ko'proq ko'rsatish1 610
Obunachilar
+224 soatlar
+87 kunlar
+1430 kunlar
Postlar arxiv
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም ፊትን ለወንድ መግለጥ
~
አንዳንዴ ፊታቸውን ከባዳ ወንዶች የሚሸፍኑ እህቶቻችን እንዲገልጡ የሚገፋ ጫና ይገጥማቸዋል። ለምሳሌ ጥጋበኛ እጅ ላይ ወድቀው ካልገለጡ ለከባድ ጥቃት ሊጋለጡ ይችላሉ። በመሰል ሁኔታዎች ላይ መግለጥ ይችላሉ? ወይስ ችግሩ የፈለገ ቢከፋ እምቢ ማለት አለባቸው?
አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም የማይፈቀድ ነገር ይፈቀዳል። الضرورات تبيح المحظورات የሚለው የፊቅህ መርህ ጠንካራ መነሻ ያለውና የታወቀ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፦
{ لَا یُكَلِّفُ ٱللَّهُ نَفۡسًا إِلَّا وُسۡعَهَاۚ }
አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም።" [አልበቀረህ: 286]
በአስገዳጅ ሁኔታ ህይወትን ለማትረፍ በክት መብላት ይቻላል። ተጨባጭ የሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመ የክህደት ንግግር በመናገርም ራስን ማትረፍ ይቻላል።
{ مَن كَ.فَرَ بِٱللَّهِ مِنۢ بَعۡدِ إِیمَـٰنِهِۦۤ إِلَّا مَنۡ أُكۡرِهَ وَقَلۡبُهُۥ مُطۡمَىِٕنُّۢ بِٱلۡإِیمَـٰنِ }
"ከእምነቱ በኋላ በአላህ የካደ ሰው (ብርቱ ቅጣት አልለው)፡፡ ልቡ በእምነት የረጋ ሁኖ (በክህደት ቃል በመናገር) የተገደደ ሰው ብቻ ሲቀር።" [አነሕል: 106]
ሌሎችም ጉዳዮች እንዲሁ ይታያሉ። የሙስሊሟ ለባዳ ወንዶች ፊቷን መግለጥም በዚሁ አግባብ የሚታይ ይሆናል። ይህንን መርህ በመንተራስ አስገዳጅ ጉዳይ ሲገጥም ጊዜ ሴት ልጅ ፊቷን መግለጥ እንደምትችል ዓሊሞች ይገልፃሉ። በዚህ ላይ በምሳሌነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉትን ማንሳት ይቻላል:-
1ኛ፦ በማጨት ጊዜ :- ይሄ ሐዲሦች የመጡበት እንዲሁም ኢጅማዕ ያለበት በመሆኑ ለብዙ ሰውም የሚሰወር ስላልመሰለኝ ለማሳጠር ያክል በዚሁ ልለፈው።
2ኛ፦ ለህክምና፦ ጉዳቱ ያለበት ክፍል ፊትም ሆነ ሌላ ክፍል መግለጥ ይቻላል። ከተቻለ ባል ወይም ሌላ መሕረም (ቅርብ ቤተሰብ) አብሮ መኖር አለበት። ባይሆን ሴት ሃኪም ካለ ወደ ወንድ፣ ሙስሊም ካለ ወደ ሌላ መሄድ አይገባም ይላሉ ዓሊሞች። ለህክምና በሚያስፈልገው መጠን ሃኪሙ አካሏን መመልከት ይችላል ይላሉ ኢብኑ ቁዳማ። [አልሙግኒ፡ 7/459]
በነገራችን ላይ ጦር ሜዳ ላይ ሴቶች ሶሐቢያት ወንዶችን ያክሙ ነበር። ኡሙ ዐጢያህ - ረዲየሏሁ ዐንሃ - እንዲህ ትላለች፦
غَزَوْتُ مَعَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ سَبْعَ غَزَوَاتٍ أَخْلُفُهُمْ فِي رِحَالِهِمْ، فَأَصْنَعُ لَهُمُ الطَّعَامَ، وَأُدَاوِي الْجَرْحَى وَأَقُومُ عَلَى الْمَرْضَى
"ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር ሰባት ዘመቻዎችን ዘምቻለሁ። እቃዎቻቸውን እጠብቅ፣ ምግባቸውን አዘጋጅ፣ ቁስለኞችን አክም እንዲሁም ህመምተኞችን እንከባከብ ነበር።" [ሙስሊም፡ 1812] የቡኻሪን باب هل يداوي الرجل المرأة، والمرأة الرجل እንዲሁም ዘርዘር ያለ ነገር የፈለገ ፈትሑል ባሪን መመልከትም ይቻላል።
3ኛ፦ ችሎት ላይ፦ በፍርድ ችሎት ላይ ፍርድ ለመስጠት ዳኛው አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ፊቷን ይመለከታል። ካልሆነ ሐቅን ማስከበር አስቸጋሪ ሊሆንበት ይችላል። ምስክር ሆና ስትቀርብ ወይም በሷ ላይ ምስክርነት ለመስጠትም እንዲሁ መገለጥ ግዴታ ሊሆን ይቻላል። ኢብኑ ቁዳማ እንዲህ ይላሉ፦
وللشاهد النظر إلى وجه المشهود عليها لتكون الشهادة واقعة على عينها، قال أحمد: لا يشهد على امرأة إلا أن يكون قد عرفها بعينها
"መስካሪ ሰው ምስክርነቱ ቦታው ላይ ያረፈ ይሆን ዘንድ የሚመሰከርባትን ሴት ሊመለከት ይችላል። (ኢማሙ) አሕመድ 'በትክክል ለይቶ እስካላወቃት ድረስ አንዲት ሴት ላይ አይመሰክርም' ብለዋል።" [አልሙግኒ፡ 7/459]
ይሄ የሳቸው ሃሳብ ብቻ አይደለም። ሌሎችም "ኒቃብ በለበሰች ሴት ላይ ፊቷን ሳትገለጥ መመስከር አይቻልም" ይላሉ። [አሸርሑል ከቢር፣ ደርዲር፡ 4194]
4ኛ፦ በግብይት ላይም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ሻጭ ወንድ ገዢዋን ሴት ሊመለከት እንደሚችል ዑለማኦች ይገልፃሉ። [አልሙግኒ፡ 7/459] ያለበለዚያ በግብይቱ ላይ ለተፈጠረ ክፍተት ማስተካከያ ለማድረግ ሊቸገር ይችላል። ለምሳሌ እቃ ሽጦላት ፊቷን ካላየ ኋላ ላይ እቃው ችግር ኖሮበት መመለስ ቢያስፈልግ በትክክል እሷ መሆኗን መለየት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል።
5ኛ፦ አስገዳጅ ህግ ባለበት ሁኔታ፦ በአንዳንድ ሃገራት ህግ ወይም ኤርፖርት አካባቢ ወይም ሌላ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመም ፊቷን መግለጥ ትችላለች። ለምሳሌ በመጥፎ ሰዎች እጅ ላይ ወድቃ ራሷን አደጋ ላይ ከምትጥል ፊቷን በመግለጥ ራሷን ማትረፍ ትችላለች። "አስገዳጅ ሁኔታዎች የተከለከለን ነገር ያስፈቅዳሉ።" ስለዚህ ማንነቷን ለመለየት የሚጠይቅ አስገዳጅ ሁኔታ ቢገጥም ወይም ሌላ ተጨባጭ ምክንያት ከኖረ ፊቷን መግለጥ ትችላለች ማለት ነው።
ይሄ እንግዲህ ከዑለማኦች አቋም ውስጥ ለደረሰች ሴት ልጅ ፊትን መሸፈን ግዴታ ነው የሚለውን ስንወስድ ነው። የሆነ ሆኖ ጫን ያለ ሁኔታ ካልገጠማት በስተቀር ለትንሽ ለትልቁ እጅ ልትሰጥ አይገባም። ፍተሻና መሰል ቦታዎች ላይ ሴቶችን መጠቀም የሚቻልበት ሁኔታ ካለ ወይም ደግሞ ጉዳዩ አንገብጋቢ ካልሆነ ባዳ ለሆኑ ወንዶች ፊትን መግለጥ አይገባም። አስገዳጅ ችግር ሲገጥም ደግሞ ጉዳዩን በችግሩ መጠን ብቻ ማስተናገድ ይገባል። "አስገዳጅ ሁኔታዎች በልካቸው ነው የሚስተናገዱት።" እንጂ ችግሩን ማመሀኛ አድርጎ አጉል መዘናጋት ውስጥ መግባት አይገባም። ወላሁ አዕለም! በነጥቡ ላይ ሃሳብ ያለው ሰው ማካፈል ይችላል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 01/2017)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
Baxsa le farmo...
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council gubat raqtah tan fatwâ malah buxa afdeerâ daqaarak cayli gubbil yekke bakaqak ugutak maybalaalaqa yeceen. Ta maybalaalaqal aham yalli waktiik waktil isi astoota akah yayballeem isi naqoosa edde meysiisá iggidaay, kaaduk qhiyaama xayiimih astooti kinnuuk yamaate jumqaatah qhiyaamah astooti elle baxxaqisan khutba imaamoota taceeh, ummatta kee sadga yaymaggeeniih, yunzullume marah cakki gacsaanam kee kalah tan meqaane yaymaggeenim kee yalla fanah yadaareenim faxxintam kassiisen.
Afar Kassis Media
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ፈታዋ ጥያቄ: የሙዚቃ መሳሪያ ያለበትን ነሺዳ ማዳመጥ ይቻላል ወይ?
ኡስታዝ አሕመድ አደም
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
“ሸይኻችን፣ ጠቢቡ አስተማሪ፣ የአኢማዎች ኢማም፣ የፍጥረቱ ሙፍቲ፣ የእውቀቱ ባህር፣ #የሓፊዞች_አውራ፣ የዐረብኛ ቋንቋው መሀንዲስ፣ የዘመኑ ብርቅየ፣ የወቅቱ ቁንጮ፣ ሸይኹል ኢስላም፣ የፍጡራኑ አርአያ፣ የዘመኑ ሊቅ፣ የቁርኣን ተርጓሚ፣ የዛሂዶች መሪ፣ የዓቢዶች አውራ፣ የሙብተዲዖች ቆራጭ፣ የመጨረሻው ሙጅተሂድ፣ ..” እያሉ አወድሰዋቸዋል። [ሙኽተሶሩ ጠበቃቲ ዑለማኢል ሐዲሥ፣ አልጃሚዕ248]
9. ሸምሱዲን አዘሀቢይ (748 ሂ.)፦
“ተቅዩዲን፣ ሸይኻችን፣ ሸይኹል ኢስላም፣ በእውቀትም በጀግንነትም በንቃትም፣ … በቸርነትም፣ ህዝብ በመምከርም፣ በመልካም በማዘዝና ከመጥፎ በመከልከልም የዘመኑ ብርቅየ ነው። ሐዲሥ ተማረ። ከዚያም በራሱ በስፋት ተመራመረ። በዘርፉ ኪታቦችን ፃፈ። በሐዲሥ ዘጋቢዎችና ሰንሰለቶች ላይ አጠና። #ሌሎች_ካልደረሱበት_ደረሰ። በቁርኣን ተፍሲርም መጠቀ። ከደቂቅ ትንታኔዎች ውስጥ ጭምር ጠለቀ። … በሐዲሥና በሽምደዳም እንዲሁ መጠቀ። እሱ #የሚሐፍዘውን_ያክል_የሚሐፍዝ_ቢገኝ_ጥቂት_ነው። ... ገድሎቹ በኔ አምሳያ ሊጠቆም ከሚችለው በላይ ታላቅ ናቸው። በሩክንና በመቃም መሀል ሆኜ ብምል በአይኖቼ #አምሳያውን_እንዳላየሁ፣ #እሱም_አምሳያውን_እንዳላየ_እምላለሁ።” [ዘይል፡ 4/496 - 497]
“ #በእውቀት_ከሱ_ጋር_አቻ_የሚሆን_ቀርቶ_የሚቀርበውን_እንኳን_አልተካም።” [ሙዕጀሙ ሹዩኽ አልከቢር፡ 1/57]
“ስለ ተፍሲር ቢወራ እሱ ነው የሰንደቁ ተሸካሚ። የፊቅህ ምሁራን ቢቆጠሩ እሱ ነው ሁለገቡ ሙጅተሂድ። #የሐዲሥ_ሓፊዞች_ቢታደሙ_እሱ_ሲናገር_ድዳ_ይሆናሉ። እሱ ሲተነትን ደርቀው ይቀራሉ። ... እሱ የኔ ብእር ከሚገልፀው የላቀ ነው።” [አልዑቁድ፡ 40]
10. ዑመር ብኑ ዐሊይ አልበዛር (749 ሂ.)፦
“በየትኛውም ዘርፍ ላይ የተፃፈን ኪታብ እጁ ላይ ያልደረሰ ከተገኘ ጥቂት ነው። የሆነን ነገር በፅሁፍ ካነበበ ወይ ደግሞ በቃል ከሰማው ቃል በቃል ወይም ቢያንስ መልእክቱን ይይዘዋል። ልክ እውቀት ከስጋው፣ ከደሙ፣ ከመላ አካሉ ጋር የተዋሃደው ይመስላል። እሱ ነብያችን ﷺ ‘አላህ ለዚህ ህዝብ በየክፍለ ዘመኑ ሃይማኖታቸውን የሚያድስላቸው ይልክላቸዋል’ ካሏቸው ውስጥ ነው።” “ጤነኛውን ሐዲሥ ከበሽተኛው በመለየት በኩል #ጫፉ_የማይደረስበት_ተራራ_ማለት_ነው።” [አልአዕላም፡ 18 - 19]
11. ኢብኑል ወርዲ (749 ሂ.)፦
“ወደር የለሽ እንቁ ነው። የዘመኑ ዑለማዎች ፈለኮች ሲሆኑ መሀል ላይ ያለው ዛቢያው ግን እሱ ነው። ሌሎች አካላት ናቸው። እሱ ግን ልብ ነው። ፀሐይ ከጨረቃ፣ ባህር ከጠብታ የሚበልጡትን ያክል ይበልጣቸዋል።” [አሸሃደቱ ዘኪያ ፊ ሠናኢል አኢማ ዐለ’ብኒ ተይሚያ፡ 30]
12. ኢብኑ ፈድሊላህ አልዑመሪይ (749 ሂ.)፦
“ታላቁ ሊቅ፣ #አልሓፊዝ፣ አልሑጃህ፣ አልሙጅተሂድ፣ አልሙፈሲር፣ ሸይኹል ኢስላም፣ የዘመኑ ብርቅየ፣ የዛሂዶች አውራ፣ … ነው። በየትኛውም አቅጣጫ ብትመጣ ባህር ነው። በየትኛውም በኩል ብትመለከት ሙሉ ጨረቃ ነው። አባቶቹ ብዙ ርቀት ቢጓዙም በዚያ ላይ አልረካም። እራሱን ከድካም አሳርፎ ከቆሙበት አልቆመም። ወሰን የማይገታው የዒልም ፍለጋ። መቋጫ የሌለው የማይቆም ትጋት። ጡት ከጣለ ጀምሮ የዒልም ጡት የጠባ። አፍላነት ሊያዘናጋው ቢመጣ አጮለው። ቀንና ሌት ሲተካኩ ቆረጣቸው። እውቀትና ተግባርን ጓደኞቹ አድርጎ ያዘ። … በልቅናው ተአምር ሆነ። ያውም የ(አላህ) ጥበቃ ተአምር።
ኮረብታዎች ቢያጋጥሙት አስገለላቸው። ባህሮች ቢጋፈጡት ዳርቻ አደረጋቸው። ከዚያ ብቻውን ህዝብ ሆነ። ቀብር እስከሚገባም ብቸኛ ሆነ። ከእኩዮቹ ታላላቁን ሁሉ አከሰመው። ከሃገሬው ባላባቱን ሁሉ ፀጥ አደረገው። ከነሱ ውስጥ ልክ ከአረመኔዎች እንደሚሸሸው ከሱ የማይሸሽ አልነበረም። አቻ የለሽ የሚባለው ከሱ ዘንድ ሲደርስ ይሟሽሻል። …
የመጣበት ዘመን፦ ዑለማእ የበዛበት፣ የሰማይ ከዋክብት የሞሉበት፣ በጎኑ ታላላቅ ባሕሮች የሚላጉበት፣ በአድማሶቹ ላይ እድሜ ጠገብ ንስሮች የሚበሩበት፣ በጉባኤው ፅልመት ላይ ጨረቃዎች የፈነጠቁበት፣ ጦሮች የተወደሩበት፣ የእባብ ሰራዊት የሚያፏጭበት፣ ያሰፈሰፉ አናብስት የሚያገሱበት ዘመን ነው። ግና የሱ ንጋት እነዚያን ከዋክብት አጠፋቸው። ባሕሩ ጭጋጎቹን ዋጣቸው። ቁርቁራው ያንጋጠጡትን ሁሉ ቀለበሳቸው። አይበገሬነቱ እነዚያን አውሬዎች ረታቸው።
ከዚያም ብርጌዶች ተዘጋጁለት። ሰልፋቸውን አተራመሰው። አፍንጫቸውን ሰባበረው። የተንጣለለ ወራጅ ጎርፉ ጅረቶቹን ዋጣቸው። የፀና ተራራው ግዙፍ ቋጥኞቻቸውን ነቃቀላቸው። ንፋሱ እስትንፋሳቸውን አጠፋቸው። መብራቱ ፍንጣሪዎቹን አከሰማቸው። …
ሞተ። የለም! ይልቅ ህያው ሆነ። ልኩም ታወቀ። ምክንያቱም አምሳያው አልታየምና። የቀብሩ እለት ሰፊ ህዝብ የተገኘበት ነበር። ሃገሩ ከነዳርቻው ተጨናነቀ። የመጀመሪያዎቹም የመጨረሻዎቹም መከራዎች ታወሱበት። ከበርካታ መቶ አመታት ጀምሮ ከሱ አስከሬን የላቀ ትከሻ ላይ ያረፈ፣ የበዛ እርምጃ የተከተለውም የለም። ከራስ በላይ ከፍ ብሎ፣ ነፍሶች ተከትለውት ተሸኘ። …
በፅሁፉ በተከሰሰና ከወህኒ በተወረወረ ቁጥር ከተቀናቃኞቹ ጋር ለክርክር እንዲገናኝ፣ ተመልካች ባለበት ለጥናት እንዲቀርብ ስላልተደረገ ጥሙ አልረካም። ይልቁንም ዳኛ ከቀረበ ቀጥታ እስር ነው የሚበይንበት። ወይም ከፈትዋ ነው የሚከለክለው። ወይም ይህን የመሰሉ ፈተናዎችን ነው የሚለቁበት። ይህ ሁሉ ሲሆን ምስክር አይቀረብም። ክስ አይመረመርም። ማስረጃ አይታይም። ጉዳዩ ለማስተዋል ግልፅ አይደረግም። በዚህም ሁኔታ የማይገፋ ቁስለት፣ የማይጠፋ ንዳድ ይሰማው ነበር። … ይህ ሁሉ ግን እኩዮቹ ወደኋላ ሲሉ ክብሩን አጉልቶታል። እይታዎች ሲጨልሙ እንደ ፋኖስ ብርሃናማ አድርጎታል።” [መሳሊኩል አብሷር፡ 5/687 - 692]
13. ሲዩጢይ (911 ሂ.)፦
ሸይኽ፣ አልኢማም፣ ታላቁ ምሁር፣ #አልሓፊዝ፣ ሀያሲው፣ የፊቅህ ሊቅ፣ አልሙጅተሂድ፣ የመጠቀ የቁርኣን ሙፈሲር፣ ሸይኹል ኢስላም፣ የዛሂዶች አውራ፣ የዘመኑ ብርቅየ፣ … ከእውቀት ባህሮች ውስጥ ነበር።” [ጦበቃቱል ሑፋዝ፡ ቁ. 1142]
14. ሸውካኒይ (1250 ሂ.)፦
“ #ከኢብኑ_ሐዝም_በኋላ_የሱን_አምሳያ_አላውቅም። በሁለቱ ሰዎች ዘመን መካከል እነሱን የሚመስልም፣ #የሚቀርብም እንዲኖር ዘመን የፈቀደ አይመስለኝም።” [አልበድሩ ጧሊዕ፡ 64]
ተመልከቱ! በዘመናቸው ባለፉት አምስት መቶ አመታት አምሳያው አልታየም ይባልላቸዋል። በ13ኛ ክፍለ ዘመንም እንዲሁ ሸውካኒይ፡ አምሳያው አልታየም እያሉ ነው። የተይሚያ ልጅ ፍትሃዊነትን የተላበሱ እና ቡድንተኝነት ያልተጫናቸው ዑለማኦች ዘንድ ይህን ያህል ደረጃቸው የራቀ ነው። አላህ በፊርደውሱ ያሞናድላቸው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጁማደል ኣኺራ 02/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አልሓፊዝ ኢብኑ ተይሚያ፣ ድንቅ የዘመን ክስተት፣ ልዩ የአላህ ተአምር
~
በሐዲሥ እውቀት ዘርፍ ላይ በጣም ከፍተኛ የሆነ የሐዲሥ ሒፍዝ/ሽምደዳ ያላቸው ሊቃውንት ሓፊዞች ይባላሉ። ኢብኑ ተይሚያ ከነዚህ ሓፊዞች ውስጥ አንዱ ነበሩ። ዑለማእ ዘንድ ማለቴ ነው። ዑለማእ ከመሰከሩ በኋላ ክፉ ቡድንተኝነት ያወራቸው መሃ ^ይማን ምንም ቢሉ የራሳቸውን ር ካሽ ማንነት ከማጋለጥ ውጭ እውነታውን አይቀይሩም። ጃሂል የራሱን ልክ አያውቅም፤ ታዲያ እንዴት የሌሎችን ልክ ሊያውቅ ይችላል?!
የኢብኑ ተይሚያ የሒፍዝ ችሎታ ተአምር የሚባል ነው። ጀማሉዲን አሱረመሪይ (776 ሂ.) እንዲህ ይላሉ፦ “ከዘመናችን ሰዎች በሒፍዝ ላይ ከተከሰቱ አስደናቂ ነገሮች ውስጥ አንዱ የኢብኑ ተይሚያ ጉዳይ ነው። የሆነን ኪታብ አንድ ጊዜ ካነበበው በአእምሮው ላይ ይታተም ነበር። ሌላ ጊዜ ኪታቦችን ሲያዘጋጅ ቃል በቃል እና መልእክቱን ያሰፍረው ነበር።” [አዱረሩል ካሚና፣ ኢብኑ ሐጀር፡ 1/178 - 179]
ለዚህ ማረጋገጫ የሚሆን አንድ አስገራሚ ነገር ላንሳ። ግብፅ ውስጥ በታሰሩ ጊዜ ወህኒ ቤት ውስጥ ሆነው በርካታ ኪታቦችን ፅፈዋል። በጣም ከሚደንቁ ነገሮቻቸው ታዲያ ማጣቀሻ ኪታቦች እንዳይደርሷቸው ቢደረጉም ባዘጋጇቸው ኪታቦች ውስጥ ሐዲሦችን፣ ትውፊቶችን፣ የሐዲሥ ዘጋቢዎችንና አስተላላፊዎችን፣ ዑለማዎችንና ኪታቦቻቸውን ከነ ስማቸውና መገኛ ምንጫቸው በሒፍዛቸው ሲያጣቅሱ አንድም አለመሳሳታቸው ነው። ሱብሓነላህ! አያ ሚን ኣያቲላህ! “ኢብኑ ተይሚያ የማያውቀው ሐዲሥ ሐዲሥ አይደለም” እስከሚባል የተደረሰው ለዋዛ አይደለም።
ይሄ ተአምራዊ ችሎታ ገና በጠዋት ነው የታየው። ገና በልጅነት ነበር ስማቸው የናኘው። ልጅ ሳሉ ከሐለብ ከተማ ሸይኾች ውስጥ አንዱ ወደ ደማስቆ በመምጣት “አሕመድ ኢብኑ ተይሚያ ስለሚባል ፈጣን ሒፍዝ ያለው ልጅ ሰምቼ ነበር። እሱን ለማየት ነው የመጣሁት” ሲል ይጠይቃል። አንድ ልብስ ሰፊ፡ “ልጁ ወደሚማርበት የሚሄደው በዚህ መንገድ ነው። እስካሁን ስላልመጣ ትንሽ ከኛ ጋር ቆይ” አለው። ተቀመጠ። ከአፍታ በኋላ ህፃናት አለፉ። ልብስ ሰፊው፡ “ያውና ያ ትልቅ ሉሕ የያዘው ልጅ ነው አሕመድ ኢብኑ ተይሚያ ማለት” በማለት አመላከተው። ሸይኹ ተጣራ። ህፃኑ ሲደርስ ሉሑን ተቀብሎ አየው። ከዚያም “ልጄ! አንዴ ይህን አጥፋውማ። የሆነ ነገር እንድትፅፍ ልንገርህ” አለ። ህፃኑ እንደተባለው አደረገ። ሸይኹ የተወሰኑ አስራ አንድ ወይም አስራ ሶስት ሐዲሦችን አፃፈውና “አንብበው” አለው። አንዴ ብቻ አስተዋለው። ከዚያም ሉሑን ለሸይኹ በማሳለፍ “ስማኝ” አለ። ከዚያም ባማረ ሁኔታ አሰማው። ሸይኹ ዳግም አስጠፍቶ የተወሰኑ የሐዲሥ ሰነዶችን አፃፈው። ህፃኑ ተመሳሳይ ስራ ሰራ። መጨረሻ ላይ ሸይኹ “ይሄ ልጅ ከቆየ ትልቅ ደረጃ ላይ ይደርሳል። ይሄ አምሳያው ታይቶ አይታወቅም” አለ። [አልዑቁድ፡ 20]
በአንድ ወቅት ቤተሰቡ ቅዳሜ ቀን ዘና ለማለት አብሯቸው እንዲወጣ ኢብኑ ተይሚያን ይጠይቃሉ። እሱ ግን እንደ ልጅ ሊፈነጥዝ ቀርቶ ደንታም አልሰጠው። እንዲያውም ተደበቀ። ኋላ ለእረፍት ወጥተው ሲዝናኑ ቆይተው ከሰዓት በኋላ ሲመለሱ ብቻውን በመቅረቱ ወቀሱት። በዚህን ጊዜ “እናንተ ምንም የጨመራችሁት ነገር የለም። እኔ ግን እናንተ ስትወጡ ይህን ጥራዝ ሐፍዣለሁ” አለ። ኪታቡ “ጀነቱ ናዚር ወጁነቱል ሙናዚር” የተሰኘ መጠኑ የቀለለ፣ ዝናው የገነነ ኪታብ ነው።” [አዕያኑል ዐስር ወአዕዋኑል ዐስር፡ 1/236]
ኢብኑ ተይሚያ ኪታብ ማዘጋጀት የጀመሩት ገና በአስራ ሰባት አመታቸው ነው። አስራ ዘጠኝ አመት እያሉ ፈትዋ መስጠት ጀምረዋል። ብስለታቸውን ተመልክተው ፈትዋ መስጠት እንዲጀምሩ የፈቀዱላቸው ሸይኽ ሸረፈዲን አልመቅዲሲይ “እኔ ነኝ ለኢብኑ ተይሚያ ለፈትዋ የፈቀድኩለት” እያሉ ይኮሩባቸው ነበር። [አልቢዳያ ወኒሃያ፡ 13/341]
ኢብኑ ተይሚያ በሐዲሥ ጥናት መስክ ሓፊዝ ደረጃ የደረሱ እና እንዳጠቃላይ ለብዙ ክፍለ ዘመናት አምሳያቸው ያልታየ ድንቅ ዓሊም እንደሆኑ የዑለማኦችን ምስክርነት ላስፍር። ባ'ዲስ መስመር፦
1. ኢብኑ ዘምለካኒይ (727 ሂ)፦
“ከአምስት መቶ አመታት ጀምሮ እንደ ኢብኑ ተይሚያ ያለ #ሐፊዝ አልታየም።” [ዘይል፡ 4/503]
ልብ በሉ! በዚህ መልኩ ያወደሷቸው ገና የሰላሳ አመት ወጣት በነበሩበት ጊዜ ነው። ከዚህ በኋላ በኖሩት 37 ተጨማሪ አመታት ያካበቱትን እውቀትና ብስለት ጨምራችሁ አስቡት እንግዲህ።
2. ኢብኑል ሐሪሪ አልሐነፊይ (728 ሂ.)፦
“ባለፉት ሶስት መቶ አመታት ሰዎች የሱን አምሳያ አላዩም” ብለዋል። ይሄ ቃዲ በዚህ ንግግራቸው ሳቢያ በኢብኑ ተይሚያ ጠላቶች ከሃላፊነታቸው ተባረዋል። [አዱረሩል ካሚና፡ 536]
3. ኢብኑ ሰይዲናስ አልየዕመሪይ (734 ሂ.)፦
“አልኢማም፣ ሸይኹል ኢስላም፣ … ሱነኖችንና ትውፊቶችን #ሙሉ_በሙሉ_ሊሓፍዝ የተቃረበ ነው። ስለተፍሲር ቢናገር የባንዲራው ተሸካሚ ነው። በፊቅህ ጉዳይ ፈትዋ ቢሰጥ ያለመውን የሚያሳካ ነው። ስለ ሐዲሥ ቢያወሳ የእውቀቱም የዘገባውም ባለቤት ነው። ስለ አንጃዎች ቢደሰኩር ከሱ የሰፋም የጠለቀም የሚያቀርብ የለም። #በሁሉም_የእውቀት_ዘርፍ_ላይ #ከአምሳያዎቹ_ነጥሮ_የወጣ ነው። #እሱን_ያየ_ሰው_ሁሉ_አይኑ_የሱን_አምሳያ_አላየም። እሱ እራሱ እሱን የመሰለ አላየም። ስለ ተፍሲር ሲናገር እልቆ መሳፍርት ህዝብ እየታደመ ጣፋጭ ባህር ከሆነው እውቀቱ ይጎነጭ ነበር። … ከሃገሬው ሰዎች የምቀኝነት ልክፍት ያጠቃቸው አሴሩበት።” [አልዑቁድ፡ 26 - 27]
4. ሸይኽ ሙሐመድ ብኑል ቁወይዕ (738 ሂ.):-
“ኢብኑ ተይሚያ ሲሞት ምድር ላይ #አምሳያውን_አልተወም” ይላሉ። [ነሥሩል ጁማን ፊ ተራጂሚል አዕያን፣ በአልጃሚዕ በኩል፡ 403]
5. ሸምሱዲን አልጀዘሪይ (739 ሂ.)፦
“ሸይኹል ኢስላም፣ የፍጥረቱ ሙፍቲ፣ የጊዜው #ሓፊዝ፣ የዘመኑ ሙሐዲሥ፣ በተለያዩ የእውቀት ዘርፎች ላይ የበላይ እጅ ያለው፣ ደግ፣ ዛሂድ፣ ጥንቁቅ፣ ከዱንያ ብርቅርቅ የራቀ፣ አላህን ፈሪ፣ በሐቅ የፀና፣ በመልካም አዛዥ፣ ከመጥፎ ከልካይ፣ በአላህ ላይ የወቃሽን ወቀሳ የማይፈራ፣ የታወቁ ፈትዋዎችና ዝነኛ ኪታቦች ባለቤት ነው። #በዘመኑ_ከሱ_የበለጠ_ሓፊዝ_አልነበረም። በተፍሲርና በዑለማዎች ንግግሮች፣ በሐዲሥና በሶሐቦች ልዩነቶች ላይም፣ በፊቅህና በፉቀሃእ ውዝግብም ላይ እንዲሁ።” [ታሪኹ ሐዋዲሢ ዘማን፣ በአልጃሚዕ በኩል የተወሰደ፡200 - 201]
6. አልሓፊዝ አቡል ሐጃጅ አልሚዝዚይ (742 ሂ.)፦
“ #አምሳያ_አላየሁለትም። እሱ_እራሱ_አምሳያውን_አላየም። የአላህን ኪታብና የመልእክተኛውን ሱና ከሱ በላይ የሚያውቅና የሚከተል አላየሁም።” “ባለፉት አራት መቶ አመታት አምሳያው አልታየም።” [አልዑቁድ፡ 23] [ዘይል፡ 4/503]
7. ዐብዱልባቂ ብኑ ዐብዲል መጂድ አልየማኒይ (743 ሂ.)፦
“ #አልሓፊዝ ተቅዩዲን ኢብኑ ተይሚያ … በየትኛውም ርእስ ላይ ቢናገር አትጠራጠር! ባህር ነው።… ዱንያንና ብልጭልጯን አርግፎ በመተውም ጫፍ የደረሰ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ከሱ ዘንድ ያለው ጥግ የደረሰ ነው። እውቀቱን የተመለከተ፣ ምሁርነቱን ያረጋገጠ በእውቀቱም፣ በክብሩም የዘመኑ ልዩ ክስተት እንደሆነ ይደመድማል። [ሉቀጦቱል ዐጅላን ፊ ሙኽተሶሪ ወፈያቲል አዕያን፣ አልጃሚዕ፡ 246 - 247]
8. ኢብኑ ዐብዲልሃዲ (744 ሂ.)፦
Repost from Kassis Faage
#Acbaash❌️ Qhuraan kee Sunna cabba heenih Kas/Qaqhli le mara kinnino axcuk Falsafa❗️katayen wak Kas ella haa mari elle yasuule yaaboobaa kee diini lih solla iyyen:
📍Tamaa gubal hayu waam ken yaaboobak baaliy kasal akkewaynuh tani:
1. Sunna kataya mari Acbaashak isin Yalli mayana intan keenik iyyan wak kee nanu innem hinnak nee maarrina iyyan.
Hay meqehik Yalli ankel yaniih anni kabu yaniih inna wak ulikkel yani maxcinaay uli kabu yani maxcinay yanih inxeca iyyan,
Cubbusa bas yaniih uli katul mayanaay uli rikel mayan tah qaafiyatah yan kas oggolam kinnii woo Qhuraan kee Cadiisil tan Alaafaatal loowimta daliilittey dumaak cineeni hinnay linoh iyyan kasal wagiitan wak kas oggolam hinna. Ken kasay lakmise tamah oggolah laakin.
▪️Kaadu ken essernah Yalli Gino/Qaalamak baxsah yanii Qaalamat xakabuh yanii? inna wak Qaalamak baxsah mayan Qaalamat xakabuh mayan iyyan. Hay mayana intaanaa inna wak mayana manna iyyaanaah wadirih Qaalamak irol mayan Qaalamak addal mayan iyyan.
Oson iyyaanam Yalli daga yani manna iyyan, guba yani manna iyyan migdal yani manna iyyan, gural yani manna iyyan, Qaalamak irol yani manna iyyan, Qaalamak addal yani manna iyyan, hay ankel yaniih anni kabu yaniih inna wak ulikkel mayan uli kabu mayan iyyan.
Tamah inkih iyyaanaah Yallih yanih inna iyyan uxiih. Anewaytam weeloosay axcinnoonu kas faxe caddo kak maada num taa oson Yalla elle weeloosen innaak daga weeloosam xiiqak maana.
Tamah Jahmiyya iyyan maray Yalli mayana axcuk sugek nagaren qaqhiidata.
2. Salat abaanah Salat ken lih abta Muslimiiniy Yalli daga yani intak korosu iyyan, mangih kaaduk ken luk salaataanam ma duudumta axcuk Salat Muslimiinik baxsah salaatan woh jaamiqatitte culte barteenit nagay tableeh taaxige caagidi sinam ken cintaamak nanu Muslimiinih miqinoh iyyaanam aaxigeh laakin kinnon mara ken abto keenil sumaaqittakkal taqabi mali, Laakin takkel baaham faxem macaay inteenik Salat aban wak Sujuudul "سبحان ربي الأعلى " "Subcaana Rabbiyal Al Aqlaa" inxeca iyye Yallih Farmoyti ﷺ Kulli Sujuudul toh nanu innaah oson iyyaanah. Hay too maxcok maqna macaay inneh wagitnek "Yi Rabbiy daga yani saytunih" iyyaanama. Hay Acbaash Yalli daga mayana iyyaanaah Yalli daga yani inta Muslimiinik Korosu iyyan wak oson Salat elle abaanamal Koroosinni cokmi sinnil maay aban, toh keenit amaatelem yaaxigeenimih sabbatah maqna kak makkoosaanah, Qarabiy edde tanit tamaa edde yaabe maqnaksa geeri maqnah lem malih anuk.
3. Muuminiinil Akheeral Yalla ableloonum ma nummassan keenik inna wak kee tah nanu inkinnah ma cininnino iyyan Hay Yalli anni kabul able loonuuh dagal ableloonuu manni kabul ableeloonuuh inna wak uli kabul mayablan Yalli uli kabul yani innam bicewewaytaamih sabbatah iyyan Hay tah ciniyya hinnaa kee cakkumoow num foocah edde afkuneweem yablem maay bicta kasah ma bicta laakin ken kasay lakmiseh yanih xaqul tamah akkewayni hinna, Yalla ableloonuuh uli katul kaa mayablan iyyan.
Tamah kee kalah mangoh tan Yallih diiniliiy oobewayteh qaafiyatah yan kasaay oggole sinni fadaacah tan qaqhiidah amol yan mara. Tama gideh badit yaniinih anuk sinam badsoonuh nanu elle nanim cakkik nee kataya axcuk seecan mawacarriyaanaay.
Yalli nee make waay
#Join ⤵️⤵️ Telegram channel
https://t.me/Kassisfaage
https://t.me/Kassisfaage
Repost from MuhammedSirage M.Noor
ስልኮቻችን !
ከስልኮቻችን ጋር ያለንን ግንኙነት ሳናስተካክል የቀልብን መፅዳት መጠበቅ የዋህነት ነው - የብዙዎች ቀልብ እየደፈረሰ ፣ እየታመመ አንዳንዴም እየሞተ ያለው በዚሁ መሳሪያ ነውና !!!
… ከስልክ ጋር ያለን ውሎ እና አዳር ከተስተካከለ ብዙ የቀልብ ነገር ይስተካከላል - በአሏህ ፈቃድ !!!
በስልኮቻችን ላይ አሏህን እንፍራ !
https://t.me/msirage4
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
Cajjih niya le marak ahak afal mekla kinnih gide amixxige wayta way yaakume bica abtaanamih seeco qafár rakaakayak islaaminnâ caagiidah malah buxa siinih abta. Addatino
👇
https://www.facebook.com/share/1CPKHdojbL/
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
የ150 ሚሊዮን ብር የኸይር ሥራ ጥሪ‼
========================
✍️ ውድ የዚህ ቻነል ቤተሰቦች፣ ከአመታት በፊት ካስታወሳችሁ በ10 ሚሊዮን ብር ወጪ ንፁሕ የውሃ ፕሮጀክት ገንብተው ለህዝብ ያስረከቡና ቃላቸውን የሞሉት ሑዘይፋዎች፤ ዛሬ ደግሞ ሌላ ታሪክ ለመሥራት ተነስተዋል!
ፕሮጀክቱ ምንድን ነው?
በቀራኒዮ የሺ ደበሌ አካባቢ «ሑዘይፋ ኢብኑል የማን» የተሰኘና በዲዛይኑ የሸገር ሲቲ ፈርጥ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቅ ግዙፍ መስጂድ እና መድረሳ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል። አለፍ ሲልም ቁፋሮ ጨርሰው የግንባታ መሠረቱን እያጧጧፉት ነው።
ትናንት የውሃውን ፕሮጀክት በጋራ እንደሠራነው ሁሉ፣ ዛሬም ይህንን የ150,000,000 (መቶ ሃምሳ ሚሊዮን) ብር ፕሮጀክት ሁላችንም ከተባበርን፤ በአላህ ፈቃድ እውን ማድረግ አያቅተንም።
🏗 እንዴት እንሳተፍ?
ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ማቴሪያል (ሲሚንቶ፣ አሸዋ፣ ብረት፣ ጠጠር) መግዛት የሚችል በማቴሪያል፣ ይህ ያልተመቻችሁ ደግሞ ይህንን መልዕክት SHARE በማድረግ የዚህ ታላቅ "ሶደቀተል ጃሪያ" ተካፋይ እንሁን። እንዳውም በብር መልክ ከምትሰጡት የበለጠ፤ ከቻላችሁ በጥሬ እቃ መልክ የአቅማችሁን ያክል ሲሚንቶ ወይም አሸዋ ወይም
ብረት… ገዝታችሁ በአካል ብታስረክቧቸው ነው።
✅ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች:
• ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:
1000680622543
• አቢሲንያ ባንክ: 115183818
• አዋሽ ባንክ: 01437999853200
• ሒጅራ ባንክ: 1000034780001
• ዘምዘም ባንክ: 0054754710301
• ዳሸን ባንክ: 2959082956711
☑የአካውንት ስም፡ ሑዘይፋ ኢብኑል የማን መስጂድ
📍 አድራሻ: ቀራኒዮ የሺ ደበሌ፣ ወረዳ 08 ከፍ ብሎ
ምርጥ ሰደቃ ማለት ካለን ከትንሹ ላይ የምንሰጠው ነው!
ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ሁኑ!
ለኸይር ማነሳሻ ይሆን ዘንድ የምትሰድቁበትን ደረሰኝ በውስጥ @Murad_Tadesse ላይ ላኩልኝ።
ባረከ-ል'ሏሁ ፊኩም!
||
t.me/MuradTadesseRepost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
+1
#Garci_Kaloot_Farmo...
Baadal taybullik /Telfizoonuk (TVik) wagittaanam kinni tv isinnik cubbusa‼
Yallih migaq kee yallih farmoytih (q.s.w) migaq edde cusaanam ceelisak seecoy qhabri kee rabe marih qibaadah takkeh tani elle tatrusaanah yanin TVitte wagittaanamak isinni cubbusa‼
Ceelalloh:
Sunna tv ❌
Harima tv ❌
Tama chanalittel (Tv) qafár afat yabta tumay qhabri qibaadâ fanah sinam secta elle tanim kinnuuk buxaaxil le marak duuga (Delet) aba.
Afar Kassis Media
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
منظومة القواعد الفقهية
. الحـمــدُ للـــهِ العـــليِّ الأَرْفَــقِ ... وجَــامِــعِ الأَشْـيــاءِ وَالمُـفَــرِّقِ
ذِي النِّـعَـمِ الواسِعَـةِ الْغَـزِيـــرَه ... والحِـكَــمِ البـاهِــرَةِ الكَـثـيـــرَه
ثُــمَّ الصَّــلاةُ مـعْ سَــلامٍ دَائــمِ ... عَـلى الـرَّسـولِ القُرَشِـيِّ الخاتـَمِ
وَآلِــهِ وصَـحــبِـــــهِ الأَبـْـــرارِ ... الحـائِــزِي مَـراتِـبَ الفَــخَـــارِ
اِعْلَـمْ هُـدِيـتَ أَنَّ أفـضـلَ الْمِنَـنْ ... عِلمٌ يُزيـلُ الشَّـكَّ عَنْـكَ وَالـدَّرَنْ
وَيَكْشِـفُ الحـقَّ لِـذِي القُــلُـوبِ ... وَيُوصِـلُ العَبْـدَ إِلـى المطْلُـــوبِ
فَاحْـرِصْ عـلى فَهْمِـكَ للقَواعِـدِ ... جَـامِـعَـةِ المَسَــائِــلِ الشَّــــوارِدِ
لِتَـرْتَقِي في العِلْـمِ خَيْـرَ مُرتَـقَــى ... وتَقْتَفِـي سُبْـلَ الَّـذِي قَــدْ وُفِّقَــا
وَهَــذِهِ قَـواعِـــدٌ نَـظَـمْـتُـهـــا ... مِنْ كُتْبِ أَهْلِ الْعِلْمِ قَـدْ حَصَّلْتُهـا
جَـزاهُـمُ المَــوْلَى عَـظِيـمَ الأَجْــرِ ... وَالْعَـفْــوَ مَــعْ غُفْـرانِــهِ وَالْبِــرِّ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
