uz
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Kanalga Telegram’da o‘tish

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
447
Obunachilar
+124 soatlar
+197 kunlar
+6730 kunlar
Postlar arxiv
መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ሕያው እንድሆን፣ ቃልህንም እንድጠብቅ፣ ለአገልጋይህ መልካም አድርግ። ¹⁸ ከሕግህ ድንቅ ነገርን እንዳይ፣ ዐይኖቼን ክፈት። ¹⁹ እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝ፤ ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር። ²⁰ ዘወትር ደንብህን በመናፈቅ፣ ነፍሴ እጅግ ዛለች። ²¹ ከትእዛዛትህ የሳቱትን፣ እብሪተኞችንና ርጉሞችን ትገሥጻለህ። ²² ምስክርነትህን ጠብቄአለሁና፣ ስድብንና ንቀትን ከእኔ አርቅ። ²³ ገዦች ተቀምጠው ቢዶልቱብኝ እንኳ፣ አገልጋይህ ሥርዐትህን ያሰላስላል። ²⁴ ምስክርነትህ ለእኔ ደስታዬ ነው፤ መካሪዬም ነው።

jerry (7).mp34.72 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ ጒልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል? በቃልህ መሠረት በመኖር ነው። ¹⁰ በሙሉ ልቤ ፈለግሁህ፤ ከትእዛዛትህ ፈቀቅ እንዳልል አድርገኝ። ¹¹ አንተን እንዳልበድል፣ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ። ¹² እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ቡሩክ ነህ፤ ሥርዐትህን አስተምረኝ። ¹³ ከአንደበትህ የሚወጣውን ደንብ ሁሉ፣ በከንፈሬ እናገራለሁ። ¹⁴ ሰው በሀብቱ ብዛት ደስ እንደሚለው፣ ምስክርነትህን በመከተል ደስ ይለኛል። ¹⁵ ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ። ¹⁶ በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አልዘነጋም።

“ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣ በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤” — መዝሙር 119፥2 (አዲሱ መ.ት) ✨ SELAH ✨ A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience
“ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣ በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤”   — መዝሙር 119፥2 (አዲሱ መ.ት) ✨ SELAH ✨ A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience Through God’s Word Join us and invite others to grow together in God’s Word. 📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10 📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10

4_6003470346789849039.mp36.01 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ መንገዳቸው ነቀፋ የሌለበት፣ በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው። ² ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣ በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤ ³ ዐመፅን አያደርጉም፤ ነገር ግን በመንገዱ ይሄዳሉ። ⁴ ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ፣ አንተ ሥርዐትን አዘሃል። ⁵ ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣ ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ! ⁶ ወደ ትእዛዛትህ ስመለከት፣ በዚያን ጊዜ አላፍርም። ⁷ የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣ በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ። ⁸ ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤ ፈጽመህ አትተወኝ።

ውድ ቤተሰቦቻችን ጌታ ፈቅዶ ብንኖር ነገ ማለዳ ለምንጀምረው የመዝሙረ ዳዊት (119) ጥናት መግቢያ እንዲሆነን በማሰብ ከታች ያለውን አጭር ዳሰሳ አቅርበናል። 📖 የመዝሙረ ዳዊት ዳሰሳ ☑️ ጸሐፊው፦ ዳዊትና ሌሎች ናቸው። የ 100 መዝሙሮች ጸሐፊ በየመዝሙሩ መጀመሪያ ላይ ተመልክቷል። • ዳዊት-73 • አሳፍ-12 • ቆሬያውያን-11 • ሰሎሞን-2 • ሙሴ-1 • ኢታን-1 መዝሙሮች ሲጽፉ የተቀሩት 50 መዝሙሮች በማን እንደተጻፉ አልተገለጸም። ሆኖም ለምሳሌ በሐዋ 4:25 እና ዕብ 4:7 መሠረት መዝ 2 እና 95 በዳዊት እንደተጻፉ ስለተገለጸ ቀሪዎቹም በዳዊት የተጻፉ ሊሆኑ ይችላሉ። ☑️ የተጻፈበት ጊዜ፦ ከ1400-500 ዓ.ዓ። መዝሙሮቹ በተለያዩ ጸሐፊዎች የተጻፉ ስለሆኑ ጊዜው ይለያያል። ከሁሉም የሚቀድመው በሙሴ የተጻፈው መዝ 90 ከ1400 ዓ.ዓ. እንደሚሆን ሲገመት የዳዊት መዝሙሮች ደግሞ ከ1020-975 ዓ.ዓ ባለው ጊዜ እንደሆነ ይታሰባል። እንዲሁም ከምርኮ ስለመመለስ የሚናገሩት መዝ 126 እና 137 ከ500 ዓ.ዓ. በፊት እንደተጻፈ ይገመታል። ☑️ የመጽሐፉ ስያሜ: መጽሐፉ በእስራኤል ዘንድ መልካም ባለቅኔ በሆነው በእሴይ ልጅ ዳዊት (2ሳሙ 23:1) የተሰየመ ነው። በዕብራይስጥ #ተሂሊም ወይም ውዳሴ ይባላል። የመዝሙረ ዳዊት አጻጻፍ #ፓራራሊዝም የተሰኘ የአጻጻፍ ስልት ይጠቀማል። ፓራራሊዝም ማለት አቻ ዘይቤ ወይም እኩያ አባባል እንደ ማለት ነው። ☑️ ዋና ሰዎች፡ ዳዊት፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ። ☑️ ዋና ሀሳብ፦ ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን ማመስገንና ማወደስ ነው። መዝሙረ ዳዊት ብዙ ጸሎቶችን በመዝሙር ስለሚገልጽ የመዝሙር-ጸሎት ሊባልም ይችላል። የእግዚአብሔር ስም በሁሉም መዝሙሮችና በአጠቃላይ 1200 ጊዜ ተጠቅሶአል። ይህም በሀዘንም ጊዜ ቢሆን (መዝ 74) ወይም በሃሌ ሉያ (150) የዝማሬ ትኩረቱ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታል። እግዚአብሔር ካልተመሰገነ መንፈሳዊ መዝሙር የለምና። ☑️ መዝሙረ ዳዊት ከመጽሐፍ ቅዱስ ሰፊው መጽሐፍ ሲሆን ረጅሙ ምዕራፍ ምዕ 119 ነው። ሰው ላለበት የተለያየ ሁኔታ ሁሉ ለውስጥ ልቡ የሚናገር መጽሐፍ ስለሆነ ሰዎች በብዛት የሚያነቡት መጽሐፍ ነው። መዝሙረ ዳዊት በአዲስ ኪዳን 81 ጊዜ ተጠቅሷል። ☑️ የመጽሐፉ አከፋፈል፦ ብዙዎች 150 መዝሙሮች የያዘውን መጽሐፍ በ5 የመጽሐፍ ክፍሎች ይከፍሉታል። እያንዳንዱ የመጽሐፍ ክፍል የሚጨርሰው በምስጋናና ውዳሴ ነው። መጽሐፉን ከፔንታቱክ መጻሕፍት ጋርም በማዛመድ የሚከፍሉት አሉ። 1️⃣ መጽሐፍ 1: ስለ ሰውና ተፈጥሮ (1-41) ዘፍጥረት 2️⃣ መጽሐፍ 2: ስለ እስራኤልና ነጻ ስለ መውጣት (42-72) ዘጸአት 3️⃣ መጽሐፍ 3: ስለ አምልኮና ቤተ መቅደስ (73-89) ዘሌዋውያን 4️⃣ መጽሐፍ 4: በምድር ላይ ጉዞ (90-106)- ዘኁልቁ 5️⃣ መጽሐፍ 5: የእግዚአብሔር ቃልና ውዳሴ (107-150) ዘዳግም ✍️ ዶ/ር መልሳቸው መስፍን (የቀደመው ክብር: የብሉይ ኪዳን ዳሰሳ) ከተሰኘው መጽሐፍ የተወሰደ። ከዚህ በተጨማሪ በግል ጊዜ ወስደን ሌሎች ተጨማሪ የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎችን በማንበብ ክፍሉን በጥልቀት ማጥናትና መረዳት እንችላለን። ጌታ ቢፈቅድ እና ብንኖር ቀደም ሲል ባጋራነው የንባብ ሰሌዳ መሰረት ነገ ማለዳ ጥናታችንን እንጀምራለን። ሁላችሁም ከእኛ ጋር ቃሉን እንድታጠኑ፣ እንድታሰላስሉ፣ እንድትጸልዩ፣ በሕይወታችሁ እንድትተገብሩት እንጋብዛለን። ከታች የተሰጡትን ሊንኮች በመጠቀም ሌሎች ሰዎችም ጥናቱን እንዲቀላቀሉ እንጋብዝ🙏 👇 https://t.me/hopministry10 https://www.facebook.com/hopministry10

4_5920344476001245776.mp356.27 MB

🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience Through God’s Word 📜 Reading-Schedule: #Psalm_119 📖 1️⃣ Monday: ኤሌፍ፣ ቤት፣ ጋሜል 🌞 ጠዋት፡ 1-8 ☀️ቀን፡ 9-16 🌙 ማታ፡17-24 2️⃣ Tuesday፡ ዳሌጥ፣ ሄ፣ ዋው 🌞 ጠዋት፡25-32 ☀️ ቀን፡ 33-40 🌙 ማታ፡ 41-48 3️⃣ Wednesday: ዛይ፣ ሔት፣ ጤት 🌞ጠዋት፡ 49-56 ☀️ ቀን፡ 57-64 🌙 ማታ፡ 65-72 4️⃣ Thursday: ዮድ፣ ካፍ፣ ላሜድ 🌞 ጠዋት፡ 73-80 ☀️ ቀን፡ 81-88 🌙 ማታ፡ 89-96 5️⃣ Friday: ሜም፣ ኖን፣ ሳምኬት 🌞 ጠዋት፡ 97-104 ☀️ ቀን፡ 105-112 🌙 ማታ፡113-120 6️⃣ Saturday: ዔ፣ ፌ፣ ጻዴ 🌞 ጠዋት፡ 121-128 ☀️ ቀን፡ 129-136 🌙 ማታ፡137-144 7️⃣ Sunday: ቆፍ፣ ሬስ፣ ሳን፣ ታው 🌞 ጠዋት፡ 145-152 ☀️ ቀን፡ 153-160 🌙 ማታ፡161-176 Join us and invite others to grow together in God’s Word. 📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10 📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10

4_5922243452841499066.mp311.24 MB

✨ #ሴላ ✨ #የመጽሐፍ_ቅዱስ_ጥናት_ሳምንት! መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ። ¹⁶ በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አል
✨ #ሴላ ✨ #የመጽሐፍ_ቅዱስ_ጥናት_ሳምንት! መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ። ¹⁶ በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አልዘነጋም። ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ከፊታችን ሰኞ- እሁድ (ከግንቦት 10-16) ይሄንን ቻናል በመጠቀም #ሴላ (Selah) በተሰኘ ርዕስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መዝሙረ ዳዊት በቅንፍ #119 እናጠናለን፣ እናሰላስላለን፣ እንጸልያለን፣ የተማርነውን በሕይወታችን እንተገብራለን። በዚህ ሂደት ውስጥ እግዚአብሔር ለቃሉ ያለንን ረሃብ ይመልሳል፣ ልባችንን ያድሳል፣ ከቃሉ ተአምራትን እናይ ዘንድ አይኖቻችንን ይከፍታል፣ በቃሉ ይናገረናል፣ ያስተምረናል፣ በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የቃሉ ረሃብ እንደገና በልባችን ይፈሳል። ኑ! አብረን የእግዚአብሔርን ቃል፦ ☑️ እናጥና፣ ☑️እናሰላስል፣ ☑️እንደ ቃሉ እንጸልይ፣ ☑️እንታደስ፣ ☑️ እንለወጠ፣ ☑️እንደ ቃሉ እንኑር!! 📖 የሳምንቱ የጥናት ክፍል፦ መዝሙረ ዳዊት (119) https://t.me/hopministry10 https://www.facebook.com/hopministry10

✨ SELAH ✨ A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience Through God’s Word “ I will meditate on your precepts and fix my
✨ SELAH ✨ A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience Through God’s Word “ I will meditate on your precepts and fix my eyes on your ways. I will delight in your statutes; I will not forget your word.” — Psalm 119:15–16 (ESV) HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. invites you to join us for a special Bible Reading & Meditation Week titled: 📖 SELAH 🗓 May 18 – May 24, 2026 Throughout the week, we will journey together through Psalm 119 — the chapter centered on loving, meditating on, obeying, and living by the Word of God. During this week we will: • Read the Word • Meditate on the Word • Pray over the Word • Be restored and transformed by the Word • Practice and obey the Word in daily life SELAH is a call to pause, reflect, hear God deeply, and walk in obedience. “Blessed rather are those who hear the word of God and keep it!” — Luke 11:28 Join us and invite others to grow together in God’s Word. 📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10 📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10

#ቃሉ_ላይ_መቆየት! በጎች ምግባቸው የሆነውን ሳር (ግጦሽ) እንዳገኙት ወዲያው ይግጡታል (ወደ ውስጣቸው ያስገቡታል)። የአመጋገብ ስርዓታቸው ግን እዛ ላይ አያበቃም። ይልቁንም ጠቃሚውን ንጥረነገር እ
#ቃሉ_ላይ_መቆየት! በጎች ምግባቸው የሆነውን ሳር (ግጦሽ) እንዳገኙት ወዲያው ይግጡታል (ወደ ውስጣቸው ያስገቡታል)። የአመጋገብ ስርዓታቸው ግን እዛ ላይ አያበቃም። ይልቁንም ጠቃሚውን ንጥረነገር እንዲያገኙበት #ይቆዩበታል፤ ማለትም #ያመነዥጉታል፣ መልሰው መላልሰው ያደቁታል። ይህም ለእድገታቸው፣ ለጤንነታቸው የሚያስፈልጋቸውን ግብአት እንዲያገኙ ይረዳቸዋል። የበሉት ምግብ ላይ በቆዩ ቁጥር ጠቃሚውን ነገር እያገኙ ይሄዳሉ። መጽሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ፣ በተለያየ ስፍራ ቃሉን እንድናሰላስል ይመክረናል፣ ያስተምረናል፣ ያዘናል። ቃሉን አንድ ጊዜ አንብበን፣ አጥንተን፣ ሰምተን፣ ተምረን ዘወር ከማለት በዘለለ ትኩረት ሰጥተን እንድናሰላስለው እንድንቆይበት፣ ትዝታችን እንዲሆን፣ በልባችን እንዲሞላ ያዘናል። እያሰላሰልነው፣ እያሰብነው (እያመነዥግነው) በቆየን መጠን ከቃሉ የሚፈሰው ሕይወት እያረሰረሰን፣ ለሁለንተናዊ ደህንነታችን የሚያስፈልገውን ንጥረነገር እያገኘን እንሄዳለን። ሕይወታችንም ቃሉ ላይ ባለን ቆይታ ልክ እየታደሰ፣ እየተሰራ፣ እየተለወጠ፣ ፍሬ እያፈራ ይሄዳል። ጌታ ሆይ ቃልህ ላይ የቆየ  ሰው ሕይወት ያገኛል፤ ቃልህ ትዝታው የሆነለት ሰው ከዓለም ተረታ ተረት ይጠበቃል፤ በአእምሮው መታደስም ይለወጣል። ቃልህን ያሰላሰለው ሰው ብዙ ያተርፍበታል፤ ይለመልማልና ቃልህን ያለማቋረጥ እንድናሰላስለው እርዳን!! መዝሙር 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በክፉዎች ምክር የማይሄድ፣ በኀጢአተኞች መንገድ የማይቆም፣ በፌዘኞችም ወንበር የማይቀመጥ፣ ሰው ብፁዕ ነው። ² ነገር ግን ደስ የሚሰኘው በእግዚአብሔር ሕግ ነው፤ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል። ³ እርሱም በወራጅ ውሃ ዳር እንደ ተተከለች፣ ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣ ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።

📖 “Let us know; let us press on to know the LORD; his going out is sure as the dawn; he will come to us as the showers, as t
📖 “Let us know; let us press on to know the LORD; his going out is sure as the dawn; he will come to us as the showers, as the spring rains that water the earth.”          Hosea 6:3 (ESV) 🌿 Let us press on to know the Lord. HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. https://t.me/hopministry10

#Corrie_ten_boom_the_Woman_Who_Hid_Hope Cornelia Arnolda Johanna ten boom እንደ ኤ.አ በሚያዝያ 15 1892 ለአምስተርዳም ቅርብ በሆነችው ሀርለም ኔዘርላንድ የተወለደች ሲሆን በአብዛኛው ሰው ዘንድ እውቅ የሆነው መጠሪያ ስሟ ኮሪ ይባላል፤ ይህ መጠሪያዋ ከወላጅ እናትዋ የወረሰችው ነው፡፡ ለቤተሰቧ የመጀመሪያ ልጅ ስትሆን ቤቲና ኖሊ የተባሉ ሁለት እህቶችና ዊሊየም የተባለ አንድ ወንድም አላት፡፡ በኖረችባቸው ዓመታት ከመደበኛ የኑሮ ዘይቤዋ ውጭ በታሪክ ውስጥ አስቀምጣ ያለፈችው ትልቅ አሻራ ያላት ሴት ነች፡፡ ወላጅ አባትዋ ካስፐር ጌጣጌጥና ሰዓት በመስራት ይተዳደር ነበር፡፡ ኔዘርላንዳዊቷ ኮሪ የእጅ ሰዓት በመጠገን፣ በኋላም ክርስቲያናዊ ጽሁፎችን በመጻፍና አነቃቂ ንግግሮችን በመናገር ትታወቃለች፡፡ ይህ ቤተሰብ የመኖሪያ ጎጆውን የቀለሰው ከአባትዋ የጌጣጌጥና የሰዓት መሸጫ ሱቅ በላይ ነው፡፡ “ቤጂ” የተባለው የዚህ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ከውጪ ለሚያየው ሰው እንደማንኛውም መኖርያ ቤት የተለመደ ቅርጽ እና ገጽታ ያለው ይመስላል፡፡ ነገር ግን በብሎኬት ከተሰራው ግድግዳና ከአነስተኛው የመጋዘኑ የጎን ክፍል ጀርባ ያልተለመደ ነገር ነበረው፡፡ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት እየተፋፋመ በሄደበት ወቅት የቴን ቡም ቤተሰብ መኖሪያ ቤት የድብቁ የትግልና የመከላከል እንቅስቃሴ አካል በመሆን የአይሁዳዊያን መጠለያና ከናዚዎች የመሸሸጊያ ስፍራ ሆነ፡፡ ይህ ቤተሰብ በህንጻው ሶስተኛ ወለል ላይ ባለው የኮሪ መኝታ ቤት ጀርባ በሚገኘው ድብቅ ክፍል ወይም (The Hiding Place)ተብሎ በሚጠራው ክፍል ወደ ሰባት የሚጠጉ የትግሉ አካል የሆኑ አይሁዳዊያንን ይሸሽግ ነበር፡፡ አንዳንዶቹን ረዘም ላለ ጊዜ ሲሆን ሌሎቹን ደግሞ የተሻለና ምቹ መኖሪያ አግኝተው እስከ ሚዘዋወሩ ድረስ ላሉት ለአንድ ወይንም ለሁለት ቀናት ነው፡፡ ከረዥም ጊዜ በፊት ወላጅ እናትዋን በሞት ያጣችው ኮሪ የመጀመሪያውን የህይወትዋን ክፍል ያሳለፈችው የቤት ውስጥ ስራ በመስራት ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ ግን እህቷ ቤቲ በህመም ምክንያት ለረጅም ጊዜ አልጋ ላይ በመቅረቷ የእህቷን ቦታ በመተካት የአባትዋ የሰዓት መሸጫ ሱቅ ውስጥ መስራት ጀመረች፡፡ ብዙም ሳትቆይ ከስራው ሁኔታ ጋር በመላመዷና የንግዱን ዓለም ስለወደደችው አዳዲስ ፈጠራዎችን በማምጣት ንግዳቸውን ማሳደግ ችላለች፡፡ እህቷ ቤቲ ከህመሟ ካገገመች በኋላም እንኳን ኮሪ የንግዱን ስራ በተገቢ ሁኔታ በማስቀጠል ላይ ስለነበረች እህቷ በእርሷ ምትክ የቤት ውስጥ ስራዎችን መስራትና ቤተሰቡን ማስተዳደር ጀመረች፡፡ ኮሪ በሰዓት ስራ ላይ ስልጠና ከወሰደች በኋላ እ.ኤ.አ በ1922 ዓ.ም በኔዘርላንድ ታሪክ ህጋዊ እውቅና እና ፈቃድ ያላት የመጀመሪያዋ ሴት ሰዓት ሰሪ ለመሆን በቅታለች፡፡ በቀጣዮቹ ዓስርት ዓመታት በአባትዋ ሱቅ ከምትስራቸው ስራዎች በተጨማሪ የወጣትና ታዳጊ ሴቶች ክለብ በማቋቋም መንፈሳዊ ነገሮችን እንዲሁም የተለያዩ የኪነጥበብና የእጅ ስራዎችን ታስተምራቸው ነበር፡፡ ኮሪ እና ቤተሰቦቿ በ Dutch Reformed church ውስጥ እግዚአብሔርን ያመልኩና ያገለግሉ የነበሩ Calvinist ክርስቲያኖች ናቸው፤ ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በመስራት፣ የተቸገሩ ሰዎችን በመርዳትና ማህበረሰባቸውን በማገልገል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ቤተሰቦች ከነበራቸው ዋና ዋና የእምነት መመሪያዎች መካከል፦ አይሁዳዊያን በእግዚአብሔር የተመረጡ ውድ ህዝቦች ናቸው፣ እና ሁሉም ሰው በእኩልነት ተፈጥሯል የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ እምነታቸው በቁርጠኝነት ለገቡበት ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት ለሚያደርሰው ሌሎችን የማዳን በጎ ምግባራቸው ጽኑ መሰረት ሆንዋል፡፡ ኮሪ ለአምላኩ ልዩ ፍቅርና መሰጠት ባለው ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደገችው፡፡ ይህ ቤተሰብ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ አይሁዳዊያውያንን ከናዚ ባለስልጣናት እስራት ታድጓል፡፡ ይህን ተከትሎ በመሰል ወንድሞቻቸው በመከዳት ለናዚ ወታደሮች ተላልፈው በመሰጠት ለእስር ተዳርገዋል፡፡ በእስር ቤቱ ስቃይ ወቅት ቤተሰቦችዋን በሞት ያጣችው ኮሪ ከመከራው አገግማ በመውጣት ዓለም አቀፍ አገልግሎት ጀምራለች፡፡ በመቀጠልም “The Hiding place” ተብሎ በሚጠራው ታዋቂ መጽሐፏ ግለ ታሪኳን በማስፈር ለአንባቢያን ተደራሽ ማድረግ ችላለች፡፡ እ.ኤ.አ በግንቦት 1940 ዓ.ም የጀርመኑ ብሊከዝሪግ ኔዘርላንድንና ሌሎች ዝቅተኛ ሀገሮችን ለመቆጣጠር ሩጫ በመጀመር በጥቂት ወራት ውስጥ “Nazification” በተሰኘው ሌሎች ናዚዝምን እንዲቀበሉና እንዲከተሉ በሚያደርግ እንቅስቃሴያቸው በርካታ ኔዘርላንዳውያንን መቆጣጠሩን ተያያዙት፡፡ በዚህን ወቅት ነበር ሰላም የሰፈነበት የቴን ቡም ቤተሰብ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የተናጋው፡፡ በጦርነቱ ወቅት ቤጂ የተሰኘው የቴን ቡም መኖሪያ ቤት ለአይሁዳዊያን ምሁራንና ተማሪዎች መሸሸጊያ ሆነ፡፡ ኮሪ ቴን ቡም በቤጂ የተጀመረው የዚህ እንቅስቃሴ ዋና መሪ በመሆንና በመላ ሀገሪቱ ውስጥም ሌሎች ተመሳሳይ ስፍራዎች መኖራቸውን በመከታተል ግንባር ቀደም ነበረች፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ አይሁዳዊያንን መታደግ ችለዋል፡፡ እ.ኤ.አ በየካቲት 1944 ዓ.ም አንድ ኔዘርላንዳዊ የናዚዎች ቃል አቀባይ ስለ አጠቃላይ የቴን ቡም ቤተሰብ እንቅስቃሴ በሰጠው ጥቆማ መሰረት የቴን ቡም መኖሪያ ቤት በወታደሮች ተከበበ፡፡ በቤቱ ላይ ጥብቅ ፍተሻና ክትትል እያደረጉ ከቆዩ በኋላ በቀኑ መገባደጃ ላይ የቴን ቡምን ቤተሰብ ጨምሮ በአጠቃላይ ሰላሳ አምስት ሰዎች በናዚ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ ምንም እንኳን የጀርመን ወታደሮች ቤቱን በደንብ ቢፈትሹም ከነበሩበት ምሽግ አስተማማኝነት የተነሳ ከግማሽ ደርዘን በላይ የሚሆኑ አይሁዳዊያንን ሊያገኝዋቸው አልቻሉም፡፡ #ይቀጥላል....

#Corrie_ten_boom_the_Woman_Who_Hid_Hope ☑️Hid Jews from the Nazis during WWII ☑️Survived a concentration camp ☑️Lost her fami
#Corrie_ten_boom_the_Woman_Who_Hid_Hope ☑️Hid Jews from the Nazis during WWII ☑️Survived a concentration camp ☑️Lost her family but never lost her faith ☑️Chose forgiveness instead of hatred ☑️Inspired millions with her courage The story of Corrie ten Boom continues on HOP Ministry Telegram Channel. Join Us:👇 https://t.me/hopministry10

“እርሱ ግን፣ “ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚታዘዙት ናቸው” አለ።” — ሉቃስ 11፥28 (አዲሱ መ.ት) #HOP_Ministry — Hear. Obey. Practice. በሉቃስ 11:28 መሰረ
“እርሱ ግን፣ “ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚታዘዙት ናቸው” አለ።”   — ሉቃስ 11፥28 (አዲሱ መ.ት) #HOP_Ministry — Hear. Obey. Practice. በሉቃስ 11:28 መሰረት፦ የእግዚአብሔርን ቃል መስማትን፣ መታዘዝን፣ መኖርን (መተግበርን) መርሁ ያደረገ፤ እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዝሙርነት ግቡ የሆነ ክርስቲያናዊ አገልግሎት ነው። አገልግሎቱ ከሚያካትታቸው ዋና ዋና ይዘቶች መካከል:- ☑️የእግዚአብሔር ቃል ጥናት፣ ☑️መጽሐፍ ቅዱሳዊ የጥሞና ጽሁፎች፣ ☑️በየዘመናቱ፣ በአገልጋዮቹ ሕይወት የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ሥራ የሚያሳዩ የተሃድሶ ታሪኮች ☑️የሕይወት ምስክርነቶች ☑️መንፈሳዊ ግለ-ታሪኮች ☑️መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው ክርስቲያናዊ የስነ-ጽሁፍ ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው። ከታች ያለውን የቴሌግራም ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን: 👇 https://t.me/hopministry10 በአንድነት በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እንደግ፤ ለእግዚአብሔር መንግሥት ፍሬ እናፍራ!

15_እርግጠኛ_ነኝ_Ergitegna_negn_amuel_Tesfamichael_Melihke_Album_Official.m4a6.50 MB

" #እናንተ_ግን፣ #አብሮአችሁ_ስለሚኖርና_በውስጣችሁ_ስለሚሆን_ታውቁታላችሁ።" በእኛ ውስጥ ሆኖ፣ በእኛ ውስጥ ኖሮ ራሱን ለሚገልጥልን፣ ትውውቃችን ከውጪ በተነገረንና በምንሰማው ነገር ላይ ብቻ እንዳይመሰረት #በአብሮነቱ፣ ከእኛ ጋር በመኖሩ ሕያውነቱን፣ እውነትነቱን ለሚያረጋግጥልን፣ ለሚያስረግጥልን፤ የርስታችን መያዣ፣ ዋስትናችን ለሆነው ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ይሁን!! እኛን እንደማንነታችን ቢሆን አይደለም ቤቱ፣ መኖሪያው ለማድረግ ይቅርና ለመጎራበት እንኳ የሚመርጠን አልነበረም፤ እርሱ ግን ማደሪያ መቅደሱ እንሆን ዘንድ ቀድሶ ሊያድርብን ወደደ። " #እናንተ_ግን፣ #አብሮአችሁ_ስለሚኖርና_በውስጣችሁ_ስለሚሆን_ታውቁታላችሁ።" የሚል ምስክርነት፣ ማረጋገጫም በኢየሱስ ክርስቶስ ተሰጠን። አሁን #አምላክ_ወዴት_አለ? እያልን ውጭ ውጪውን ስናይ አንባክንም፣ ዝለንም ተስፋ አንቆርጥም። ይልቁንም በውስጣችሁ ስለሚሆን ታውቁታላችሁ የሚለው መሠረት ላይ ቆመን፣ ካወቅነው በላይ ልናውቀው፣ ከተጠጋነው ይበልጥ ልንጠጋው እንበረታለን፤ እርሱም እንደ ወገግታ ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል። የቱንም ያልህ ብንወዳጅና ብንወዳቸው፤ ወዳጅ ያልናቸው የሰው ልጆች ልብ የሚጣልባቸውና የመለዋወጥ ዕድል የሌላቸው አይደሉም። ከዕለታት በአንዱ ቀን የቀን ጎዶሎ ይመጣና በልባችን ላይ ከሰጠናቸው ዙፋን ይወርዳሉ። ሕያው፣ ከእኛ ጋር ለዘላለም የሚኖር አምላክ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ግን እንጠረጥረው ዘንድ ሰው አይደለምና ታማኝ እንደሆነ ይኖራል፤ በአብሮነቱም በሕይወት ያኖረናል። ዮሐንስ 14 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ እኔ አብን እለምናለሁ፤ እርሱም ከእናንተ ጋር ለዘላለም የሚኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ ¹⁷ እርሱም የእውነት መንፈስ ነው፤ ዓለም ስለማያየውና ስለማያውቀው ሊቀበለው አይችልም። እናንተ ግን፣ አብሮአችሁ ስለሚኖርና በውስጣችሁ ስለሚሆን ታውቁታላችሁ።

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28. Join us: 👇 https://t.me/hopministry10 ☑️ Daily Devotionals ☑️ Bible Reflections ☑️ Revival Histories ☑️ Spiritual Biographies ☑️ Faith-Based Storytelling ☑️ Testimonies ☑️ Amharic Translated Christian Literature