uz
Feedback
ር ግ ብ የ 🕊

ር ግ ብ የ 🕊

Kanalga Telegram’da o‘tish

“ርግቤ🕊️ መደምደሚያዬም አንዲት ናት፤ ለእናትዋ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት። ቈነጃጅትም አይተው አሞገሱአት፥ ንግሥታትና ቍባቶችም አመሰገኑአት።”⛪🤍 — መኃልየ. 6፥9

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
356
Obunachilar
-224 soatlar
+37 kunlar
+4530 kunlar
Postlar arxiv
መዝሙር 47 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ። ⁶ ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ።

Repost from N/a
ከትንሳኤ በኋላ 40ኛው ቀን ዓረገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፣ ወነበረ በየማነ አቡሁ፤ ወፈነወ ለነ ጰራቅሊጦሳሃ መንፈሰ ጽድቅ። በምስጋና ወደ ሰማያት አረገ፣ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ፤ የእውነት መንፈስ የሚሆን ጰራቅሊጦስንም ሰደደልን። ከማኅሌት ምስጋና የተወሰደ

😇ቅዱስ ቄርሎስ (Cyril):
✅ ሰው በኃጢአቱ ምክንያት እንደ እንስሳ ሆኖ ነበር። ጌታ በእንስሳት መኖ (ግርግም) ውስጥ መተኛቱ፣ እንደ እንስሳ የነበረው የሰው ልጅ ከእንስሳዊ ባሕርይ ወጥቶ ሰማያዊውን እንጀራ (የክርስቶስን ሥጋ) እንዲመገብና ወደ ቀደመው ክብሩ እንዲመለስ ነው።✍️

☦️በድንግል ትሕትና ዓለም ተደነቀ እውነተኛ መጠጥ ከሆዷ ፈለቀ ሰው የሚድንበት ሮማንና ገውዝ ሮማንና ገውዝ ከሆዷ ፈለቀ እንደ ምንጭ እንደ ወንዝ💗

ያከብርዋ ለሰንበት መላዕክት በሰማያት ጻድቃን በውስተ ገነት /2/ ወኩሉ ፍጥረት አሳት ወአናብርት እለ ውስተ ደይን ያእረፉ ባቲ እስመ ባቲ አእረፈ እምኩሉ ግብሩ 💗

ኃጢአት ላለማድረግ በግልጽም በስውርም ስትጋደል ያየህም ያላየህም ሰው አይቶ ሰምቶ ሲፈርድብህ፣ ”አልቀረብህም” ሲልህ… ግልጽና ስውር ትግልህን አይቶ ለመተው መሞከርህን ተመልክቶ ስለትግልህ ዋጋ ኃጢአ
ኃጢአት ላለማድረግ በግልጽም በስውርም ስትጋደል ያየህም ያላየህም ሰው አይቶ ሰምቶ ሲፈርድብህ፣ ”አልቀረብህም” ሲልህ… ግልጽና ስውር ትግልህን አይቶ ለመተው መሞከርህን ተመልክቶ ስለትግልህ ዋጋ ኃጢአቱን የሚያስተውህ እግዚአብሔር ነው!
ዲ/ን ዘለዓለም ታዬ

ምን ማግኘት ይፈልጋሉ ??

_"ጌታ ሆይ፣ ዛሬ መስቀልህን አስባለሁ። የእኔንም መስቀል የመሸከም ኃይል ስጠኝ። አሜን። #መልካም_እለተ አርብ"_

ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል። አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው። እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።
 😇የያቆብ መልክት 4 ፥14-17

😇" ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።"🧡
😇(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:9)

ንስሐ🙌 🛜ንሰሐ ሰው ሕይወቱን ወደተሻለ ደረጃ ለመለወጥ የሚያስችለው መንፈሳዊ ጥንካሬ ወይም ኃይል ነው:: ✅ንስሐ በልቡናችን ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ፍቅረ እግዚአብሔር እንዲወለድ ያደርጋል:: 🔻ምክንያቱም በንስሐ ሕይወት የምንኖረው ከሆነ እግዚአብሔር ስለ እኛ ብሎ የተሸከመልንን ሸክምና ይቅር ያለንን እጅግ የከፋ ኃጢአት እንድናስብ ስለሚያደርግና ለእግዚአብሔርም ያለን ፍቅር እያደገ ስለሚሄድ ነው::

በትንሽ ነገር መማር ትወድ የለ አንተ በቃ ዝም ብለህ ማረኝ እንዳትመረምረኝ አደራ ምክንያቱም ምንም ለምህረት የሚያበቃ ምግባር የለኝም አንድ ደና ምግባር ምላት በሳምንትም በወርም አንዴ ደጅህን መርገጤን ነው ግን እኮ እሱንም ምመጣው ዓለም ፊቷን ስታዞርብኝ እና ሰው ሁሉ ጀርባውን ሲሰተኝ መሄጃ ሲጠፋኝ ነው እንጂ መቼ አንተን ፈለኩኝና መጣው በቃ አባቴ በጥቂት ነገር አይደል አንተ መማር ምትወደው እኔንም በጥቂት ነገር ማረኝ ቢያንስ ቢያንስ ክርስቲያን ስለመባሌ ብለህ ማረኝ ባንተ ስም ነውና ምጠራው ስለ ተጠራውበት ስምህ ብለክ ማረኝ 🛐 አደራ ግን እንዳትመረምረኝ ✍✍ Esuye ከሀጢያተኞች ዋና

Telegram ላይ በቀላሉ ምን ማግኘት ይፈልጋሉ ? በቀላሉ ከስር ያሉትን በተኖች በመንካት መቀላቀል ይችላሉ 👍
Telegram ላይ በቀላሉ ምን ማግኘት ይፈልጋሉ ? በቀላሉ ከስር ያሉትን በተኖች በመንካት መቀላቀል ይችላሉ 👍

💛ጦም እጅግ ግሩም የሆነ ነገር ነው፡፡ኃጢአታችንን እንደማይጠቅም አረም ከውስጣችን ይነቅለዋል፡፡ እውነተኛው የጽድቅ ተክልም በውስጣችን ልክ እንደ አበባ እንዲያብብ ይረዳዋል፡፡✅ 😇ቅዱስ ባስልዮስ💗

በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ✝ ➳●◎◌➳●◎◌➳●◎◌➳●◎◌➳ “የምናስተውል ካለን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል”፤ 😇በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ ብልቶቻችሁን የፅድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ ◌ (ሮሜ 6፥12-14) ✝ ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው ካልተቻለ ዝሙትን ለመከላከል በአንድ ይፅና ከዚህ ውጭ ጉዞ ወደ እሳት ነው ◌ (1ኛ ቆሮ 7፥1) 😇ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱ ያፈርሰዋል ቤተ መቅደሱም እናንተው ናችሁ ◌ (1ኛ ቆሮ 3፥17) 😇 ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእረፍትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ◌ (1 ኛ ጢሞ 2፥9) 😇የወንድ ልብስ የለበሰች ሴት በአምላክ ዘንድ የተጠላች ናት ◌ (ዘዳ 22፥5; ዘፀ 39፥28) 😇ፀጉሯን ሳትሸፍን የምትፀልይ ሴት እራሷን ያዋረደች ናት ◌ 📖(1ኛ ቆሮ 11፥5) 📖የወይን ጠጅ ከሚጠጣ ጋር አትቀመጥ ◌ (ምሳ 23፥20) 📖ዘፈን የሰነፎች ዜማ ነው ◌ (መክ 7፥5) 📖 በዛም አጋንንት ይዘፍናሉ ◌ (ኢሳ 13፥21) አቤቱ ጌታሆይ ልቦና ስጠን🕯✝

አንድ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ቆመና፦ "ጌታ ሆይ ተመልከት እጆቼ ንፁህ ናቸው ደም አላፈሰሱም የሰው ገንዘንብ አልቀሙም" አለው። እግዚአብሔርም ሲመልስለት፦ "ልጄ ሆይ አዎ እጆችህ ንፁህ ናቸው ግን ባዶ ናቸው" አለው ይባላል። ንፁህ እጅ ግን ባዶ እጅ፣ ያልገደለ ግን ያላዳነ እጅ፣ ያልሰረቀ ግን ያልመፀወተ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የለውም። እውነተኛው መልካምነት ክፉ አለማድረግ ብቻ ሳይሆን መልካም ማድረግም ነው። 🧡

ꨄከማህፀኗ ወደዚህ አለም ለማምጣትም ✔ ሆዷን እንደጨርቅ ተቀዳልሻለች ✔ አምጣለች ✔ህይወቷን አደጋ ላይ ጥላለች 📌ለዚች እናት ከ አመት አንዴ እንኳን ለእናቶች አደረሰሽ ብለሽ ስጦታ መስጠት በቂ አ
ꨄከማህፀኗ ወደዚህ አለም ለማምጣትም ✔ ሆዷን እንደጨርቅ ተቀዳልሻለች ✔ አምጣለች ✔ህይወቷን አደጋ ላይ ጥላለች 📌ለዚች እናት ከ አመት አንዴ እንኳን ለእናቶች አደረሰሽ ብለሽ ስጦታ መስጠት በቂ አይደለም። ለእናት በእያንዳንዱ ቀን ስጦታ ይገባታ። ይህ ሶጦታ ግን ገንዘብ ወይም ቁስ አይደለም። መልካም የእናቶች ቀን 🤱💗🧡