ር ግ ብ የ 🕊
Ir al canal en Telegram
“ርግቤ🕊️ መደምደሚያዬም አንዲት ናት፤ ለእናትዋ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት። ቈነጃጅትም አይተው አሞገሱአት፥ ንግሥታትና ቍባቶችም አመሰገኑአት።”⛪🤍 — መኃልየ. 6፥9
Mostrar másEl país no está especificadoLa categoría no está especificada
356
Suscriptores
-224 horas
+37 días
+4530 días
Archivo de publicaciones
356
መዝሙር 47
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።
⁶ ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ።
356
Repost from N/a
ከትንሳኤ በኋላ 40ኛው ቀን
ዓረገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፣ ወነበረ በየማነ አቡሁ፤ ወፈነወ ለነ ጰራቅሊጦሳሃ መንፈሰ ጽድቅ።
በምስጋና ወደ ሰማያት አረገ፣ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ፤ የእውነት መንፈስ የሚሆን ጰራቅሊጦስንም ሰደደልን።
ከማኅሌት ምስጋና የተወሰደ
356
😇ቅዱስ ቄርሎስ (Cyril):
✅ ሰው በኃጢአቱ ምክንያት እንደ እንስሳ ሆኖ ነበር። ጌታ በእንስሳት መኖ (ግርግም) ውስጥ መተኛቱ፣ እንደ እንስሳ የነበረው የሰው ልጅ ከእንስሳዊ ባሕርይ ወጥቶ ሰማያዊውን እንጀራ (የክርስቶስን ሥጋ) እንዲመገብና ወደ ቀደመው ክብሩ እንዲመለስ ነው።✍️
356
☦️በድንግል ትሕትና ዓለም ተደነቀ እውነተኛ መጠጥ ከሆዷ ፈለቀ ሰው የሚድንበት ሮማንና ገውዝ ሮማንና ገውዝ ከሆዷ ፈለቀ እንደ ምንጭ እንደ ወንዝ💗
356
ያከብርዋ ለሰንበት መላዕክት በሰማያት ጻድቃን በውስተ ገነት /2/
ወኩሉ ፍጥረት አሳት ወአናብርት
እለ ውስተ ደይን ያእረፉ ባቲ
እስመ ባቲ አእረፈ እምኩሉ ግብሩ 💗
356
ኃጢአት ላለማድረግ በግልጽም በስውርም ስትጋደል ያየህም ያላየህም ሰው አይቶ ሰምቶ ሲፈርድብህ፣ ”አልቀረብህም” ሲልህ…
ግልጽና ስውር ትግልህን አይቶ ለመተው መሞከርህን ተመልክቶ ስለትግልህ ዋጋ ኃጢአቱን የሚያስተውህ እግዚአብሔር ነው!
ዲ/ን ዘለዓለም ታዬ
356
ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል። አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው። እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው። 😇የያቆብ መልክት 4 ፥14-17
356
😇" ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።"🧡😇(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:9)
356
ንስሐ🙌
🛜ንሰሐ ሰው ሕይወቱን ወደተሻለ ደረጃ ለመለወጥ የሚያስችለው መንፈሳዊ ጥንካሬ ወይም ኃይል ነው::
✅ንስሐ በልቡናችን ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ፍቅረ እግዚአብሔር እንዲወለድ ያደርጋል::
🔻ምክንያቱም በንስሐ ሕይወት የምንኖረው ከሆነ እግዚአብሔር ስለ እኛ ብሎ የተሸከመልንን ሸክምና ይቅር ያለንን እጅግ የከፋ ኃጢአት እንድናስብ ስለሚያደርግና ለእግዚአብሔርም ያለን ፍቅር እያደገ ስለሚሄድ ነው::
356
በትንሽ ነገር መማር ትወድ የለ አንተ በቃ ዝም ብለህ ማረኝ እንዳትመረምረኝ አደራ ምክንያቱም ምንም ለምህረት የሚያበቃ ምግባር የለኝም አንድ ደና ምግባር ምላት በሳምንትም በወርም አንዴ ደጅህን መርገጤን ነው ግን እኮ እሱንም ምመጣው ዓለም ፊቷን ስታዞርብኝ እና ሰው ሁሉ ጀርባውን ሲሰተኝ መሄጃ ሲጠፋኝ ነው እንጂ መቼ አንተን ፈለኩኝና መጣው በቃ አባቴ በጥቂት ነገር አይደል አንተ መማር ምትወደው እኔንም በጥቂት ነገር ማረኝ ቢያንስ ቢያንስ ክርስቲያን ስለመባሌ ብለህ ማረኝ ባንተ ስም ነውና ምጠራው ስለ ተጠራውበት ስምህ ብለክ ማረኝ 🛐
አደራ ግን እንዳትመረምረኝ
✍✍ Esuye ከሀጢያተኞች ዋና
356
💛ጦም እጅግ ግሩም የሆነ ነገር ነው፡፡ኃጢአታችንን እንደማይጠቅም አረም ከውስጣችን ይነቅለዋል፡፡ እውነተኛው የጽድቅ ተክልም በውስጣችን ልክ እንደ አበባ እንዲያብብ ይረዳዋል፡፡✅
😇ቅዱስ ባስልዮስ💗
356
በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ✝
➳●◎◌➳●◎◌➳●◎◌➳●◎◌➳
“የምናስተውል ካለን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል”፤
😇በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ ብልቶቻችሁን የፅድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ
◌ (ሮሜ 6፥12-14)
✝ ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው ካልተቻለ ዝሙትን ለመከላከል በአንድ ይፅና ከዚህ ውጭ ጉዞ ወደ እሳት ነው
◌ (1ኛ ቆሮ 7፥1)
😇ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱ ያፈርሰዋል ቤተ መቅደሱም እናንተው ናችሁ
◌ (1ኛ ቆሮ 3፥17)
😇 ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእረፍትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸፍኑ
◌ (1 ኛ ጢሞ 2፥9)
😇የወንድ ልብስ የለበሰች ሴት በአምላክ ዘንድ የተጠላች ናት
◌ (ዘዳ 22፥5; ዘፀ 39፥28)
😇ፀጉሯን ሳትሸፍን የምትፀልይ ሴት እራሷን ያዋረደች ናት
◌ 📖(1ኛ ቆሮ 11፥5)
📖የወይን ጠጅ ከሚጠጣ ጋር አትቀመጥ
◌ (ምሳ 23፥20)
📖ዘፈን የሰነፎች ዜማ ነው
◌ (መክ 7፥5)
📖 በዛም አጋንንት ይዘፍናሉ
◌ (ኢሳ 13፥21)
አቤቱ ጌታሆይ ልቦና ስጠን🕯✝
356
አንድ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ቆመና፦
"ጌታ ሆይ ተመልከት እጆቼ ንፁህ ናቸው ደም አላፈሰሱም የሰው ገንዘንብ አልቀሙም" አለው። እግዚአብሔርም ሲመልስለት፦ "ልጄ ሆይ አዎ እጆችህ ንፁህ ናቸው ግን ባዶ ናቸው" አለው ይባላል። ንፁህ እጅ ግን ባዶ እጅ፣ ያልገደለ ግን ያላዳነ እጅ፣ ያልሰረቀ ግን ያልመፀወተ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የለውም። እውነተኛው መልካምነት ክፉ አለማድረግ ብቻ ሳይሆን መልካም ማድረግም ነው። 🧡
356
ꨄከማህፀኗ ወደዚህ አለም ለማምጣትም
✔ ሆዷን እንደጨርቅ ተቀዳልሻለች
✔ አምጣለች
✔ህይወቷን አደጋ ላይ ጥላለች
📌ለዚች እናት ከ አመት አንዴ እንኳን ለእናቶች አደረሰሽ ብለሽ ስጦታ መስጠት በቂ አይደለም።
ለእናት በእያንዳንዱ ቀን ስጦታ ይገባታ።
ይህ ሶጦታ ግን ገንዘብ ወይም ቁስ አይደለም።
መልካም የእናቶች ቀን 🤱💗🧡
