ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 940
Підписники
-1524 години
+287 днів
+37030 днів
Архів дописів
+3
202ኛ ኮር 🙏
👉 የአማራ ፋኖ በአማራ ከልል ትምህርት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ትምህርት እንዲጀመር በታላቅ ቁርጠኝነት አውጆ የነበረ ሲሆን፤ ይህ ራዕይ ዛሬ ፍሬ አፍርቶ በቁጥጥር ስር ባሉ ቀጠናዎች ሁሉ አገር አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በድል እየተሰጠ ይገኛል።
የአገዛዙ ካድሬዎች ትናንት "ትምህርት ተስተጓጎለ" ብለው የለፈፉበትን ፕሮፓጋንዳ ዛሬ የአማራ ፋኖ የውሃ ሽታ አድርጎታል። ህዝቡን በባርነት ለመግዛት የሚጥሩት ስግብግብ ባለሥልጣናት፣ ፋኖ በፈጠረው የትምህርት ምህዳር ፊት መቆሚያ አጥተዋል። በጠመንጃ አስገድደው ሊያቆሙት ያልቻሉት ይህ ታላቅ የትምህርት እንቅስቃሴ፣ የአገዛዙን የውድቀት ጊዜ እጅግ እንዳፋጠነው ግልጽ ነው።
የ202ኛ ኮር በጌምድር ክፍለ ጦር በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች በአሁኑ ወቅት ሳንኪሳ፣ ፈንታይ፣ ናርቸቻ፣ ጨውድባ፣ ስምራ-ሮቢት፣ ገምበልዋ፣ ሰራቆ፣ ጉራንባ፣ ደምቢያ ሮቢት፣ ሰራባ፣ ዳብሎ ሚካኤል እና አቸራን ጨምሮ በበርካታ ቀጠናዎች የትምህርት ሂደቱን በጀግንነት እያካሄደ ይገኛል።
ይህ ክንውን፣ ፋኖ የትውልድን የወደፊት ዕድል ለመጠበቅ የጦር ሜዳ ውሎውን ከትምህርት ገበታ ጋር አስተሳስሮ እንደሚንቀሳቀስ የሚያሳይ ታሪካዊ ማረጋገጫ ነው። ፋኖ የጦር ሜዳ ጀግና ብቻ ሳይሆን የህዝብ አስተዳዳሪ እና የወደፊት የኢትዮጵያ ተስፋ ጠባቂ መሆኑን በአደባባይ ያረጋገጠበት ነው።
ክብር ለጀግኖቻችን🙏
ድል ለአማራ ፋኖ ✌️
ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ!
ሰኔ 11/2018 ዓ.ም
+1
አለምነው አየነው፣ ምስጋናው አየልኝ ከባሶሊበን ወረዳ ገበያው ታየ ከስናን ረቡዕ ገበያ ከተማ በመውጣት 206ኛ ኮር ተቀላቅለዋል።
ሰኔ 11/2018 ዓ.ም
=====================================
በኮርክ የመሸገችው የአድማ 2ኛ ሬጅመንት ሙሉ ለሙሉ ከተደመሰሰች በኋላ ተጨማሪ የአድማ ብተና ኃይል ሁነው ከተንቀሳቀሱት መካከል አለምነው አየነው፣ ምስጋናው አየልኝ ከባሶሊበን ወረዳ በመውጣት 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር አብራጅት ሻለቃን ተቀላቅለዋል።
በተከታታይ በስናን አባጅሜ ሻለቃ ከሚደረጉ ጠንካራ ውጊያዎች በህይወት መቆየት የቻለው ገበያው ታየ ከረቡዕ ገበያ ወጥቶ 14ኛ ክ/ጦር ንጉስ ተክለሃይማኖት ሻለቃን ተቀላቅሏል።
አዲስ ትውልድ ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ነጎድጓድ ክፍለ ጦር በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በባሶናወረና ወረዳ ድል ተቀዳጀ
ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ዓፄ ዘርያዕቆብ ኮር ሥር የሚንቀሳቀሰው ነጎድጓድ ክፍለ ጦር፣ ትላንት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ።
ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ ከመንዲዳ ከተማ ተነስቶ በተለያዬ አቅጣጫ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የአገዚዙን ኃይል፣ ክንደ-ነበልባሉ ክፍለ ጦር ከጀግኖች የተጉለት አባት አርበኞችና የፋኖ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት በደፈጣ ጥቃት አድቀውታል።
በዚህ ድንገተኛ ጥቃት ክፉኛ የተመታው የጠላት ኃይል፣ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ለመፈርጠጥ ተገዷል። ይሁን እንጂ ስብስቡ ወደ ኋላ በሚያፈገፍግበት ወቅት የሙጢ ጨርቆስ ትምህርት ቤትን ንብረት በመዝረፍ፣ የ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን የፈተና ወረቀት በመቅደድና ተማሪዎችን በማሸማቀቅ ጥቃት ፈጽሟል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሞዬ አማንጉልት ቀበሌን ለመቆጣጠር በሌላ አቅጣጫም የተንቀሳቀሰው ይኸው ኃይል፣ ረጅም ስአት በፈጀው ውጊያ በጀግኖቹ ክንድከባድ ምት አስተናግዶ ፤በውጊያው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የአገዛዙ ወታደሮች ሲገደሉ፣ ሁለት ከባድ ቁስለኞችን በመያዝ ወደ መነሻው መንዲዳ ከተማ ለመመለስ ተገድዷል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ሕልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
🚨 ትኩረት ለሸዋ ደራ ሕዝብ! 🚨
"በአፍንጫችን ስር እየፈሰሰ ያለ የንጹሃን ደም — እስከመቼ በዝምታ እንመለከታለን?"
የሸዋ ደራ ሕዝብ እዚሁ እጃችን ላይ፣ በአፍንጫችን ስር ሆኖ ከወለጋም ከአሩሲም የባሰ እጅግ ዘግናኝ እና ልብ የሚሰብር በደልና ሰቆቃ እየደረሰበት ይገኛል።
በየሳምንቱ እና በየወሩ ከመቶ ያላነሰ ንጹሕ ሰው በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እየታረደ፣ እየተገደለና እየታገተ ባለበት በዚህ አስከፊ ወቅት፣ የደራ ሕዝብ ዋስትና አጥቶ በገዛ ቀዬው እየረገፈ ነው። ይሄ የሰቆቃ ድምፅ የሁላችንም ድምፅ ሊሆን ይገባል!
👉ሕዝባችን አልቆ ሊጠፋ ነው! በየቀኑ የሚፈሰው የንጹሃን ደም፣ የሚቃጠለው ንብረት እና የሚፈናቀለው ወገናችን ቁጥር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
👉ዝምታው ይሰበር!
እስከመቼ ነው ይሄንን ሁሉ ግፍ እያየን እያለን እንደማያገባን ዝም ብለን የምንመለከተው?
➚ ወቅቱ የቃላት ሳይሆን የተግባር ነው!
➚መላው የአማራ ሕዝብ እና ሰብአዊነት የሚሰማው ወገን ሁሉ ለሸዋ ደራ ሕዝብ በጋራ ሊረባረብ፣ ድምፅ ሊሆንና ይሄንን ግፉአን ሕዝብ አንገቱን ቀና እንዲያደርግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት ይገባል።
የወገናችን ስቃይ ያማናል፤ የደራ ሕዝብ እልቂት በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል! ሚዲያዎች፣ አንቂዎች እና መላው ሕዝብ ትኩረታችሁን ወደ ሸዋ ደራ አድርጉ!
#ትኩረትለሸዋደራ #የደራሕዝብድምፅ #ፍትህለደራ #የንጹሃን_ደም_አይፍሰስ #HumanRights
ይህንን ፅሁፍ ኮፒ በማድረግ በየገጻችሁ ላይ በማጋራት (Share) የወገኖቻችን ድምፅ እንሁን!
ሽመልስ ንጉሴ የቀድሞው የደራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ
በአሁኑ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ
ሕግ መምሪያ ሓላፊ
ሶስት የወራሪው ሠራዊት አባላት የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ሻለቃን ተቀላቅለዋል‼️
~~~
በንጹሐን ላይ የግፍ ጭፍጨፋ እያደረሰ የሚገኘው የብልጽግና የጸጥታ አካላት በፍጥነት እየፈራረሰ ወደ ፋኖና ማሕበረሰቡ እየተቀላቀለ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት ማለትም ሰኔ 10/10/2018 ዓ.ም ሶስት የአገዛዙ መከላከያ አባላት የአገዛዙን አስከፊ ተግባር በመረዳትና ህዝብን ለመካሴ ከደብረ ኤልያስ ከተማ የቀስተ ደመና ብርጌድን መቀላቀላቸውን ፋኖ ዘመን ባሳዝነው የ206ኛ ኮር 14ኛ ክፍለ ጦር ህ/ግንኙነት መመሪያ ኃላፊ ለንስር አማራ በላከው መልዕክት ገልፀዋል።
10/10/2018 ዓ.ም
+3
🚨 አሳዛኝና አስቸኳይ የጥንቃቄ መልእክት ለሁላችንም!
"በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ፣ የአብይ አህመድ ስርዓት አማራን ለማጥፋትና ለማዳከም አሁንም ድረስ በተለያዩ አቅጣጫዎችና ስልቶች የክፋት ጥጥሩን ቀጥሏል። የአማራ ፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው፣ አሁን ደግሞ ንጹሃን ዜጎችን የወጥመዱ ሰለባ ለማድረግ ሌላ አደገኛ ስልት ዘርግቷል።
በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአማራ ሚዲያዎች የሚለቀቁ የሥራ ቅጥር ማስታወቂያዎችንና መሰል መረጃዎችን ሽፋን በማድረግ፣ ንጹሃን መረጃውን ሼር እንዲያደርጉና ስልካቸውን እንዲያስረክቡ እየተደረገ ይገኛል።
ይህ መረጃዎችን በመሰብሰብ ከፋኖ ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶችን ለመጥለፍና ለመከታተል እየተጠቀሙበት ያለ አሳዛኝ ሴራ ነው።
ስለዚህ፦ በአዲስ አበባም ሆነ በማንኛውም አካባቢ የምትኖሩ የአማራ ልጆች በሙሉ፣ ሕይወታችሁንና ደኅንነታችሁን ለመጠበቅ ስትሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉ በታላቅ ኃዘንና አክብሮት እንጠይቃለን።ወንድም እህቶቻችን በቁም ነገር ሳይጠቁና ሰለባ ሳይሆኑ ይህንን መልእክት በማጋራት (ሼር በማድረግ) ለመላው የአማራ ልጆች አድርሱ።
ጥንቃቄ ለሁላችንም!"
ይች ህፃን በዚህ ሰአት እንደ እኩዮቹዋ እየቦረቀች አደለም ከቤተሰቦቿ ተረት እየሰማችም አደለም ይች ህፃን ወንጀለኛ ተብላ በዳንግላ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስራ እንጅ ።
ወንጀሏን የተጠየቁት የከተማው እና የወረዳው አመራሮች የህፃን ማሪያማዊት ጥፋት ከፋኖ አባት ተወልደሻል ነው ። ነውር ጌጣቸው የሆኑት የብልፅግና አመራሮች ለእያንዳንዱ ጥፋታችሁ በክንዳችን ምላሽ እንሸጣለን ። የማሪያማዊት አምላክም ከእኛ ጋ ነው
ቀን10/10/2018
ለ፦ ለአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የበላይ አመራር
ከ፦ አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕግ ክፍል
ጉዳዩ፦ በደራ ወረዳ ላይ ስለተከፈተው ወረራ ዕዙ አስቸኳይ ስልታዊ መፍትሔና ስምሪት እንዲሰጥ የመጠየቅ ደብዳቤ።
የተከበራችሁ የዕዙ የበላይ አመራሮች፤
በአሁኑ ወቅት በሸዋ ደራ ወረዳ በሕዝባችን ላይ እየተፈጸመ ያለው መጠነ-ሰፊ ወረራ፣ የጅምላ ግድያ፣ ዕገታ እና የኢኮኖሚ ማውደም ተግባር እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
ይህ አስከፊ ሁኔታ የዕዛችንን አስቸኳይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነትና ልዩ ስልታዊ ትኩረት በጥብቅ ይሻል። ጠላት በከፍተኛ የዕዝ ደረጃና በከፍተኛ የሰው ኃይል በመንቀሳቀስ በንጹሐን ላይ ጥቃት እያደረሰ ሲሆን፣ በወረዳው ያሉ ዋና ዋና የትራንስፖርትና የንግድ መስመሮች በሙሉ በመዘጋታቸው ሕዝባችን ሙሉ በሙሉ የክበብ እስረኛ ሆኗል።
በአንጻሩ፣ በአካባቢው ያለው የመንግሥት የጸጥታ መዋቅር ይሄንን ወራሪ ኃይል ከመከላከል ይልቅ፣ ሕዝብን ለመጠበቅ በሚንቀሳቀሰው የፋኖ ክፍለ ጦር ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ መውጋቱ አደጋውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
ስለሆነም፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕግ ክፍል ኃላፊነቱን መሠረት በማድረግ፣ ይህንን የተደቀነውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ፣ ጠላትን ለመመከትና የሕዝባችንን ደኅንነት ለመታደግ ዕዙ አስቸኳይ ወታደራዊ ስልት፣ መፍትሔና የተግባር ስምሪት እንዲሰጥበት በጥብቅ ይጠይቃል።
የደራን ሕዝብ ከተደገሰለት ታላቅ አደጋ መታደግ የዕዛችን ቀዳሚ የታሪክና የሕግ ግዴታ በመሆኑ፣ ዕዙ ያለበትን ኃላፊነት ተረድቶ በአስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥበት እንጠይቃለን።
ከትግል ሰላምታ ጋር!
አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕግ ክፍል ኃላፊ
የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ከሰኔ 09 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ያከናወናቸው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች
ጎንደር — በጎጠግበላይ ዕዝ ስር የሚገኘው 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር፣ ከመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ጋር ባደረገው የተኩስ ልውውጥ ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡን የዕዙ የህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታወቀ።
እንደ ዘገባው ከሆነ፣ የፌዴራል መንግስት ሰራዊት ከሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ ከእብናት፣ አዲስ ዘመን፣ ደብረታቦር እና አለም በር በተለያዩ አቅጣጫዎች በመንቀሳቀስ የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮርን እና የፋሲል ክፍለ ጦርን ለማፈን ሙከራ አድርጎ ነበር። ሆኖም፣ በአርበኛ ጌቴ መሳፍንት (ዋግነር) የሚመራው የጀኔራል ፈንታ በላይ ክፍለ ጦር ተገቢውን የመከላከል እርምጃ በመውሰድ የጠላትን ጥቃት ማክሸፉ ተገልጿል።
በቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ በተጀመረው እና እስከ ምሽት በዘለቀው ይህ የተኩስ ልውውጥ፣ በጠላት ኃይሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል። በውጊያውም የሚከተሉት ወታደራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ዘገባው አመላክቷል፦
የሰው ኃይል እና አመራር፦ የሻለቃ መሪ፣ መገናኛ፣ ስናይፐር እና የሻለቃ መሪው አጃቢዎች መመታታቸው ተገልጿል።
የተማረኩ መሳሪያዎች፦ በርካታ የነብስ ወከፋ መሳሪያዎች፣ የዲሽቃ መትረየስ ከነተተኳሾቹ እና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች ተማርከዋል።
የጠላት ጉዳት፦ የጠላት ኃይል በሟች እና በቁስለኛ ተበታትኖ እንደወጣ የገለጸው መግለጫው፣ በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር የሟቾች ቀብር መፈጸሙን አስታውቋል።
የዕዙ የህዝብ ግንኙነት ክፍል አክሎም፣ የጠላት ኃይል አሁን ላይ የሞራል ውድቀት እንዳለበት በመግለጽ፣ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ማንኛውንም የጠላት እንቅስቃሴ የመቆጣጠር አቅም እንዳለው ገልጿል። አያይዞም ኮሩ አንድነትን እና ወንድማማችነትን በማጠናከር ትግሉን እንደሚቀጥል በመግለጽ ዘገባውን አጠናቋል።
ምንጭ፦ አፋብን ጎጠግበላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር የህዝብ ግንኙነት ክፍል
መገደል መጥፋት እንጂ መብዛት አይደለም፤ መረገጥም ስብራት እንጂ ጥንካሬ አይሆንም!
"እየተገደልን እንበዛለን አማራና ሚስማር ሲመታ ይበልጥ ይጠነክራል" የሚለውን እጅግ ኋላቀር አባባል ትክክል አለመሆኑን ለመናገር ፎቶውና ርዕሱ ከበቂ በላይ ማሳያ ነው። ይህ ፎቶ በአማራ ህዝብ ላይ የታወጀውን “መዋቅራዊ ውርደት” እና ራስ ጠል በሆኑ የአገዛዙ ፈረሶች ምክንያት የአማራን ህዝብ የህልውና ስጋት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የፖለቲካ ማኒፌስቶ ነው። የወጣቱ አንገት ላይ ያረፈው የፖሊስ ጫማ ፣ በስልጣን ላይ ያለው የብልፅግና ስርአት በአማራው ህዝብ ላይ ያለውን ንቀትና የጠላትነት ፍልስፍና የሚያሳይ የታሪክ አጋጣሚ ነው። ታሪክ እንደሚያስተምረን ፣ አንድ ህዝብ ማንነቱ ሊጠፋ የሚችለው ቀስ በቀስ በሚመጡ "የማዋረድ" እና "የማሳነስ" እርምጃዎች ነው። የታሪክ አጋጣሚዎች የሚያሳዩት ፣ አንድ ስርዓት የተወሰነን ማህበረሰብ "ጠላት" አድርጎ መፈረጅ ሲጀምር እና ያንን ህዝብ ማዋረድ ህጋዊ ሽፋን ሲያገኝ ፣ የመጨረሻው ግብ የህዝቡን ማንነት ማጥፋት መሆኑን ነው።
አንገትን መርገጥ የአካል ጉዳት ከማድረስ ባለፈ “መንፈስን የመስበር” ስልት ነው። የብልፅግናው ታጣቂ በአማራ ወጣት ላይ እንዲህ ያለ እርምጃ ሲወስድ በዘፈቀደ አደለም በተጠናና በታሰበ መልኩ ነው ፣ መልዕክቱም ግልጽ ነው “አንተ ዜጋ አይደለህም ፣ አንተ ተገዢና ተረጋጭ ነህ” የሚል ነው። ይህ ፎቶ አማራው በራሱ ሀገርና ተወልዶ ባደገበት ቀዬ ባይተዋር መደረጉን ፣ ሰብአዊ ክብሩ መገፈፉንና ህልውናው በከፍተኛ አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያል። የፋኖ ትግል መሰረታዊ መነሻውም ይኸው ነው የተገፈፈውን ክብር ማስመለስና ህልውናየን በክንዴ አስከብራለሁ በማለት እምቢ ብሎ ቀና ማለቱ ነው።
ፋኖ የጥቂት ታጣቂዎች ስብስብ ሳይሆን ፣ ምስሉ ላይ እንደሚታየው ያለውን ግፍ ለመመከት የተፈጠረ “በአማራ ህዝብ ላይ የመጣውን ብልፅግና የሚባል በሽታ መከላከያ ህዋስ” ነው።
አንድ ህዝብ በታሪክ አጋጣሚዎች የህልውና አደጋ ሲጋረጥበት ፣ በደሙ ውስጥ ያለው የነፃነት ስሜት ይገነፍላል። ለምሳሌ ያህል እንኳን የተወሰኑትን ብንመለከት በ1791 ዓ.ም የሃይቲ ጥቁር ባሪያዎች የፈረንሳይን ገዢዎች ለመጣል ሲነሱ ፣ ልክ እንደ ፋኖ ሁሉ “ከመገዛት ሞት ይሻላል” በሚል ፅኑ የህልውና ፍልስፍና ነበር አቢዮቱን የጀመሩት በዚህም ራሳቸውን ከባርነት ነፃ አውጥተው ታላቅ ድል ተቀዳጅተዋል። ዛሬ ፋኖ በሁሉም ቦታዎች የሚያደርገው ተጋድሎ ፣ ልክ በፎቶው ላይ ያለውን አይነት ውርደት ከህዝቡ ጫንቃ ላይ ለማውረድ የሚደረግ ቅዱስ ጦርነት ነው።
አማራ በአለም ታሪክ ህልውናቸውን ማስጠበቅ ባለመቻላቸው ከጠፉ ህዝቦች ታሪካዊ ትምህርትን ወስዷል ታሪክ ምህረት የለሽ ነች። በገዛ ምድራቸው ላይ የሚሰነዘርባቸውን ጥቃት መመከት ያልቻሉ ፣ በውስጥ ክፍፍል የደከሙ እና ለህልውናቸው መታገል የተሳናቸው ህዝቦች ከምድረ ገፅ ጠፍተዋል። ለምሳሌ ያህል በአለም ታሪክ ዘራቸው ከምድረ ገፅ የጠፋ ህዝቦችን እንወሰድ፦
የካርቴጅ ህዝብ፦ በጥንታዊቷ ሰሜን አፍሪካ የነበረው የካርቴጅ ስልጣኔ ፣ ከሮማውያን የሚሰነዘርበትን የህልውና አደጋ በቸልታ በማየታቸውና በፖለቲካዊ ሽኩቻ በመዳከሙ ፣ በመጨረሻ ሮማውያን ከተማዋን ደምስሰው ህዝቡን ጨርሰውታል። ዛሬ ካርቴጅ የታሪክ ማስታወሻ እንጂ ህያው ህዝብ የላትም።
የቢኦቱክ ህዝቦች፦ በካናዳ ኒውፋውንድላንድ ይኖሩ የነበሩ ህዝቦች ናቸው። ከአውሮፓውያን ሰፋሪዎች የሚሰነዘርባቸውን ጥቃት በአንድነት መመከት ባለመቻላቸውና ከመሬታቸው እየተገፉ በመሄዳቸው ፣ በ1829 ዓ.ም የመጨረሻዋ የዚህ ነገድ አባል ሻውናዲቲት ስትሞት ፣ ህዝቡና ቋንቋው ሙሉ በሙሉ ከምድረ ገፅ ጠፍቷል።
ሌሎችም ልክ እንደ ካርቴጅና ቢኦቱክ ህዝቦች ሁሉ በተከፈተባቸው ስልታዊ ጥቃትና በራሳቸው አለመደራጀት ምክንያት ፣ ሙሉ በሙሉ ዘራቸው የጠፋ ህዝቦች አሉ በታሪክ ውስጥም ታላላቅ ስልጣኔዎች የነበሯቸው ህዝቦች ህልውናቸውን የሚያስጠብቅ ሃይልና አንድነት በማጣታቸው ምክንያት ከምድረ ገፅ ጠፍተዋል። ለዚህም ነው በአንድ ወቅት አርበኛ ዘመነ ካሴ ህዝብ ይጠፋል! ያለተደራጀና እራሱን መከላከል ያልቻለ ህዝብ ይጠፋል ብሎ የተናገረው። ከታሪክ የምንማረው አንድ እውነት አለ እሱም “ጭቆና የሚቆመው ተጨቋኙ መታገል ሲጀምር ብቻ ነው” የሚል ድንቅ አበባል አለ። ታሪክ ሁልጊዜ ለአሸናፊዎችና ለታገሉ ህዝቦች ብቻ ቦታ አለው። መታገል ያቃታቸው ፣ በጊዜያዊ ጥቅም የተደለሉ ወይም በፍርሃት የተሸበቡ ህዝቦች እጣ ፈንታቸው መበተንና መጥፋት ነው።
አሁን ጥያቄው የአማራ ህዝብ በፋኖነት መንገድ ብልፅግና የተባለን ዘር አጥፊ ስርዓት መታገል ወይስ መጥፋት? የሚለውን አሁንም ቤቱ ቁጭ ብሎ የሞት እጣውን ለሚጠብቀው አማራ ልተወውና ከላይ በፎቶው ላይ የሚታየው የብልፅግና ፖሊስ እየፈፀመው ያለ ድርጊት በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን “ስልታዊና መዋቅራዊ የዘር ማጥፋት” ማሳያ ነው። አማራው ዛሬ በገዛ ሀገሩ መሬቱን ሲነጠቅ ፣ በዘሩ ምክንያት ሲፈናቀልና እንዲህ በፖሊስ ጫማ አንገቱ ሲረገጥ ዝም ካለ ፣ የታሪክ እጣ ፈንታው እንደ ካርቴጅ ወይም እንደ ቢኦቱክ ህዝቦች መጥፋት ይሆናል። ለዛም ነው ፋኖ የአቢዮቱን ችቦ ለኩሶ ስርዓቱን ድል እያደረገ እየገሰገሰ ያለው። ፋኖነት ለአማራ ህዝብ ስሜታዊ ምርጫ ሳይሆን ፣ እንዲህ ካለው መዋቅራዊ ውርደት ለመውጣት የተያዘ "የህልውና ማስከበሪያ" መንገድ ነው።
ይህ ፎቶ የሚያሳየው ህግና ፍትህ መጥፋታቸውን ነው። ህግ በሌለበት ሀገር ደግሞ መብትን ማስከበር የሚቻለው በሃይል ብቻ ነው። ፋኖ የዚህ ሃይል መገለጫ ነው። ይህ ጦርነት አማራው እንደ ህዝብ የመቀጠል ወይስ የመጥፋት ጉዳይ ነው። መሬት ላይ የወደቀው ወጣት የሁላችንም ህልውና ተምሳሌት ነው። ጫማው አንገቱ ላይ ያረፈው ወጣት ነገ ቀና ብሎ እንዲቆም ፣ የፋኖ ትግል ግቡን መምታት አለበት። ታሪክ እንደሚነግረን ፣ ለነፃነቱና ለክብሩ የማይታገል ህዝብ ፣ በታሪክ መቃብር ውስጥ መቀበሩ አይቀሬ ነው። ራሱን መከላከል ያልቻለ ህዝብ ታሪክ የለውም ፣ ታሪክ የሌለው ህዝብ ደግሞ የለም ይጠፋል። አማራው ግን ታሪካዊ ህዝብ በመሆኑ ፣ ይህንን የግፍ ቀንበር ሰብሮ የህልውናውን ዋስትና እንደሚያረጋግጥ የፋኖ ተጋድሎ ምስክር ነው። የፋኖ ትግልም የዚህ ህዝባዊ ምሬትና የህልውና ስጋት የመጨረሻ ውጤት በመሆኑ ፣ የአራት ኪሎ በትረ ስልጣንን በመቆጣጠር ፍትህና እኩልነትን ለማስፈን የሚቀጥል የነፃነት ጉዞ ነው።
ቋሚ ምስል፦ ይህ ፎቶ የተገኘው በአንድ ወቅት ፋኖ ባህር ዳር ላይ ባደረገው አውደ ውጊያ በባህር ዳር 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ በተማረከ የብልፅግና ፓሊስ አባል የእጅ ስልኩ ላይ የተገኘ ፎቶ ነው።
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኙ ሁለት ክፍለ ጦሮች ለውሕደት የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን አስታወቁ
ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መመስረቱን ተከትሎ፣ ቀደም ሲል በተለያዩ ጎራዎች ተሰልፈው የነበሩ የሁለት የተለያዩ ክፍለ ጦር አመራሮች እና አባላት በአካል ተገናኝተው ወቅታዊ የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ዕዙ በሰጠው መግለጫ መሠረት፣ የአማራ ፋኖ አንድነት ውጤት የሆነው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከተመሰረተ ወዲህ፣ በቀጠናው የሚገኙ የፋኖ ሰራዊት አባላትን በማናበብ በገዥው አካል የጦር ኃይሎች ላይ በርካታ አመርቂ ድሎችን በቅንጅት መቀናጀት ይታወቃል።
ከተከናወኑት ተጨባጭ የጋራ ዘመቻዎች በተጓዳኝ፣ ቀደም ሲል በሸዋ በነበሩ ሁለት ዕዞች ስር በተለያየ ጎራ ተሰልፈው የነበሩት፡ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር እና የአፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር አባላት፣ አመራሮች እንዲሁም በስራቸው የሚገኙ ሻለቆች በአካል ለምክክር ግንኙነት አድርገዋል።
በኤፍራታና ግድም ወረዳ በተካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የሁለቱ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ የናሁ ሰናይ ሻለቃ፣ የስበር ሻለቃ፣ የሲኖ ሻለቃ አመራሮች ና የደምላሽ ሻለቃ ኮማንድ አመራሮች እና የሰራዊት አባላት ተገናኝተው መክረዋል።
ተመሳሳይ ስም የነበራቸው እነዚህ ሁለት ነባር ክፍለ ጦሮች በአካል መገናኘታቸው ና መመካከራቸው በሰራዊቱና በአመራሮቹ እንዲሁም በሕዝቡ ዘንድ ደስታን ና ከፍተኛ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑ ተገለፀ። ይህ የጋራ ውይይት ለቀጣዩ የትግል ጉዞ እና በጠላት ላይ ለሚወሰዱ እርምጃዎች ይበልጥ ጥንካሬና አንድነትን የሰጠ መሆኑን አስታውቀዋል።
➾በተያያዘ ዜና፡ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ፣ መርሐቤቴ ወረዳ አገሪት ቁምአንባ ቀበሌ፣ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በግብርና ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩት አቶ እንጎቻ ክብርቱ የተባሉ አርሶ አደር በአገዛዙ ታጣቂዎች ተከበው መገደላቸው ተረጋግጧል።
ከአካባቢው በደረሱን ምንጮች እንደሚያመለክቱት፣ ሟቹ ቀደም ሲል በትግል ላይ እያለ መስዋዕትነት የከፈለው የአርበኛ ጎረምሳው ክብርቱ ወንድም በመሆናቸው ምክንያት ያነጣጠረ የበቀል እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው በሚገኙ የፋኖ አባላት ቤተሰቦች ላይ፣ ለከተማው ቅርብ በሆኑ የእርሻ ቦታዎቻቸው ላይ ወጥተው እንዳያርሱ እገዳ እንደተጣለባቸው ሰምተናል።
ይህን ተከትሎ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር የናደው ክፍለጦር አባላት በሰጡት ገለፃ፣ ድርጊቱን ለማስቆም ከባድ አፀፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ አስታውቀዋል።
ይሕንን ተከትሎ ቁርጠኝነታቸውን የገለጹት የክፍለጦሩ አባላት፣ የአገዛዙ የፍርሀት እርምጃዎች የህዝቡንና የሰራዊቱን የትግል ጉዞ እንደማያቆሙት ይልቁንም እዲጠነክር አድርገውታል ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
የብልፅግና ካምፕ በተከታታይ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል!!
=======================
.....ዛሬ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
ከደብረ ወርቅ ከተማ ከድተው ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ አድማ ብተና ፦
1.ዘለቀ.... ፀሀዬ
2.ሞላ.....ዋለ
3.በላቸው ...አባተ ሲሆኑ በዛሬው እለት የተቀላቀሉት አንድም አባል የመዋጋት ስነ ልቦና የሌለው መሆኑን የገለፁ ሲሆን በቀጣይ ሁሉም አባል ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል የመጡትን አባላት በክ/ጦሩ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
< በተደራጀ መንገድ ያለአንድ ጥይት ጩኸት የጠላትን ካምፕ እየፈራረሰ ነው ^
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የ64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ በሰሩት የደፈጣ ኦፕሬሽን 6 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሲወገዱ 2ቱ ቁስለኛ ሆነዋል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ ሰኔ 09/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ስድስት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እስከ ወዳኛው ሲወገዱ ሁለቱ ቁሰለኛ ሆነዋል ከእነዚህም ውስጥ #ተክለ አብ አባቡ አይተን የተባሉ የአገዛዙ ሰራዊት አባል ቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስቢታል የገባ ቢሆንም ወዲያውኑ መሞቱ ተረጋግጦል። ከዚህ ጋር በተየያዘ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በማህበረ ብርሃን ቅዱስ ገብሬኤል ቤተክርስትያን በጅምላ ተቀብረዋል።
በሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ከፍተኛ ኪሳራ ያስተናገደው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የንፁሃንን ሀብት ንብረት ዘረፎል አውድሟል። ከእነዚህም ውስጥ:-
1ኛ.መ/ር ሰው ዓለም የኔሰው ሙሉ የቤት ዕቃ
2ኛ.የሽዋስ መግስቱ የልብስ መስፊያ መኪና እና የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ሙሉ በሙሉ ሲዘረፍ
3ኛ.ሞጋ ስታየሁ እና
4ኛ.ሐብቴ አያሌዉ በዱላ ከጥቅም ውጭ የሆኑ
6ኛ.ዳቆን ባን ታምላክ ዉዱ በአፈሙዝ የተመታ
7ኛ.የቻለዉ ሞሴ የቀንድ ከብት በአገዛዙ ጥይት የተገደሉ ሲሆን አገዛዙ በፋኖ ከፍተኛ ብትር ሲገጥመው ንፁሃንን በመረሸን እና በመዝረፍ ለአማራ ህዝብ አረመኔ መሆኑን አረጋግጦል።
አዲስ ትውልድ! አዲስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
