ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 924
Підписники
+10524 години
+3357 днів
+33630 днів
Архів дописів
በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ወረዳ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት ጉዳይ ወቅቱን ያማካለ ስብሰባ ተካሔደ።
~~~~~~~~
ነሐሴ 28 /2018 ዓ.ም
ድርጅታችን አፋብን በአወረደው መመሪያ መሠረት በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የሚገኙ መምህራን፣ ዕርሰ መምህራንና ሱፕር ቫይዘሮች ጋር ነሀሴ 28/12/2018 ዓ.ም በጎንቻ ወረዳ ባርጃኖ ከተማ ጥልቅ ውይይት አካሂዶል።
የብልፅግና አገዛዝ በዚህ ሶስት ዓመት ትምህርትን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ በማድረግ ሲጠቀምበት ቆይቷል። አገዛዙ በጊዚያዊነት በተቆጣጠረባቸው ቦታዎች ሳይቀር ማህበረሰቡን በመሰብሰብ ጽንፈኛው ልጆቻችሁ ትምህርት እንዳይማሩ ከልክሏል እኛ ግን ትምህርት እናስጀምራለን የሚሉ የሐሰት አጀንዳዎችን በመንዛት ማህበረሰቡን ከፋኖ ለመነጠል ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
መድረኩን የመሩት የ74ኛ ክ/ጦር እና የጎንቻ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጠላት በትምህርት ጉዳይ ሲያሰራጨው የነበረው የሐሰት መረጃ መሆኑን ግንዛቤ በመስጠት አፋብን በሚያስተዳድረው የትኛውም ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር የፈቀደ መሆኑን ለመድረኩ ተሳታፊ መምህራን ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ፋኖ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የትምህርት ተቋማት ከየትኛው የፀጥታ አካላት ነፃ እንደሚያደረግና ህዝባችን ልጆቻቸውን ወደ ት/ት ተቋማት እንዲልኩና ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አስተላልፏል።
በውይይት መድረኩ ከተገኙት መምህራን ጋር በተካሄደው ቅድመ አቅጣጫ መተግበር ያለባቸው ጉዳዩች ውስጥ ትምህርት ቤቶች ከማነኛም ወታደራዊ አካል ነፃ ማድረግ፣ በት/ቤቶች የትምህርት ቁሳቁስን እንዲሟሉ ማድረግ፣ የተሰባበሩ ወንበሮችን መጠገንና በአገዛዙ የወደሙ ት/ቤቶች ጥገናና እድሳት በማድረግ በ2019 ዓ.ም በሁሉም የጎንቻ ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር አቅጣጫ ሰጥቷል።
አፋብን ቴዎድሮ ፪ኛ ዕዝ 201ኛኮር 74ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት
መረጃ ምንጭ ፦ የጎ/ ሲ /እነሴ ወ/ጊ/መ/ አስተዳደር ሚዲያ አና ኮምኒኬሽን
"ክፋት ለማንም በጎነት ለሁሉም"
ሰበር አሁን ከመሸ‼️
እጅግ በርካታ ህፃናት በአስገዳጅ ወታደራዊ አፈሳ ታፍሶ ከአዲስ አበበ ወደ አማራ ክልል ደጀኝ ከተማ የደረሱ ህፃናት ኢትዮጵያዊን🤔
በመርሐቤቴ አውራጃ በአገዛዙ ሆድ አደር ሚሊሻዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወሰደ!!
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ ታች ቤት ጊደብ ወረጎ ቀበሌ፣ በአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር የአገዛዙ ሆድ አደር ሚሊሻዎች ላይ አመርቂ እርምጃ መወሰዱን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት አስታወቀ።
ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ላይ የአገዛዙ ጥምር ጦር ከአለም ከተማ በመነሳት፣ «የሰላም አስከባሪ» ሲል የሚጠራቸውን ሚሊሻዎች ሰብል ለማረም በሚል ወደ ታች ቤት ጊደብ ወረጎ ቀበሌ አሰማርቶ ነበር።
አገዛዙን የሚያገለግለው ይህ ኃይል የጭቁኑን ህዝብ በአስገዳጅነት ሰብል ሊያሳርም በሚንቀሳቀስበት ወቅት የተካሄደ ልዩ ፈጣን እርምጃ ነው። በጊደብ ወረጎ ቀበሌ ሸንኮራ ጎጥ በተሰማራው የዚሁ ሚሊሻ ኃይል በየናደው ክፍለ ጦር ቀኝ አዝማች ለማ ጠጁ 3ኛ ሻለቃ ቃኝዎች በበቂ ወታደራዊ ስልት ፈጣን ደፈጣ በማካሄድ የማያዳግም ምት አድርሰውበታል።
በነበረው አውደ ውጊያ በፋኖ ፈጣንና የተቀናጀ የማጥቃት ስልት ግራ የተጋባው የአገዛዙ ሚሊሻ ኃይል ግራ ተጋብቶ መበታተኑ ሲገለፅ፤ ከ6 በላይ የሚሊሻ አባላት ከባድና ቀላል ቁስለኛ ሆነዋል።
አቶ አይደንፉ ብልጭ የተባሉ አንድ ቀንደኛ የአገዛዙ ተላላኪ ሚሊሻ ላይ የማያዳግም እርምጃ ሲወሰድበት፦1 ክላሽንኮቭ (AK-47) ጠመንጃ በምርኮ መያዙ ተረጋግጧል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአደረጃጀት ዜና!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 14ኛ ኮር 142ኛክ/ጦር ለተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የቆየውን ጥልቅ ግምገማ በስኬት በማጠናቀቅ፣ ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልኮን ለማስፈፀም ብቁ የሆኑ አመራሮች የተመደቡ ሲሆን በግምገማውም የኮሩና የክ/ጦር አመራሮች በንቃት ተሳትፈዋል።
ይህ አደረጃጀት በየደረጃው ያሉ አርበኞችን አፈፃፀምና ብቃት መሠረት በማድረግ የተከናወነ ሲሆን፣ የክ/ጦሩን የወደፊት ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልዕኮዎች በተሻለ ቁመና ለማስፈጸም ያለመ ነው።
በዚህም የግምገማ ፕሮግራም የምኒልክ 1ኛዕዝ ሰብሳቢ ፊታውራሪ ድርሳን ብርሀኔ እና የ14ኛ ኮር አመራሮች በመገኘት ጥልቅ ግምገማ በማድረግ የስራ ልምድና የስራ አፈፃፀም ጥንካሬን እንድሁም የአመራር ጥበብና ብቃትን ከግምት ውስጥ በማስገባት የክ/ጦሩን አመራር አደረጃጀት ሰርተዋል።
ወደ ክ/ጦሩ የተመደቡ አመራሮችም ትግሉን የማስቀጠል ታሪካዊ አደራ ከትግሉ ሰምዓት ስላለብን የህዝባችን መከራ ለማሳጠር ቆርጠን ለመታገልና ለማታገል ቃለ-መሀላ በመፈፀም አጠናቀዋል።
📌
አዲስ የተመደቡ የ142 ክ/ጦር አመራሮች ዝርዝር
1, አርበኛ እንድሪስ ጉደሌ.... ወታደራዊ አዛዥ
2, አርበኛ ቃሪው ጌቶ..ም/ታደራዊ አዛዥ
3, አርበኛ ጌታቸው ሰጠ.....አስተዳደር
4,አርበኛ ገዛህኝ ካሳ....ሎጀስቲክ
5 አርበኛ ደምሌ መኮነን..ፓለቲካዘርፍ ሀላፊ
6, አርበኛ ይማም አህመድ .....ፀሀፊ
7,አርበኛ በረከት ተገኘ ...ኦድትና ቁጥጥር
8,አርበኛ ሰይድ እንድሪስ....ኢንስፔክሽን
9, አርበኛ እሸቱ ወርቁ....ዘመቻ
10, አርበኛ ሁሴን ሷሊህ....ም/ዘመቻ
11, አርበኛ ሻለቃ ክንዱ....ስልጠና ዘርፍ
12, አርበኛ ተስፋዬ አበራ....መገናኛ
13, አርበኛ __መረጃ
14, አርበኛ __ም/መረጃ
15, አርበኛ ይማም ሀይሌ.....ም/አስተዳደር
16, አርበኛ ............ቃኝ መሪ
17, አርበኛ ሙጃይል ሽመልስ ....የሰው ሀይል
18, አርበኛ አብዱ ሀሰን ....ፋይናስ
19,ህግ አገልግሎት
1ኛ አርበኛ ሰይድ የሱፍ
2ኛ አርበኛ ተመስገን አሰፋ
3ኛ አርበኛ ከድር ይማም
20, አርበኛ ግዛው ሰለሞን.....ግዥ
21, አርበኛ ጀማል ሙሳ ......ም/ሎጀስቲክ
22, አርበኛ አወል ተገኝ .......ኦርድናስ
23, አርበኛ በለጠ ተፈራ ......ስቶር
24, አርበኛ ፍቅሩ ጌታሁን.....ስንቅና እደላ
25, ዶ/ር ከድር ሁሴን ....ህክምና
26, ዶ/ር መልካሙ ተገኘ......ም/ህክምና
27, አርበኛ ሙሀመድ አያሌው......ነዘቅ
28,አርበኛ ጀማል ሙሀመድ.....ትራንስፖርት
29, አርበኛ አብዱ ዳውድ.......ኢንዶክትሪኔሽን/ስርፀት/
30, አርበኛ ዮወናስ አሉላ....የክፍለ ጦሩ ቃል አቀባይ በማድረግ አደረጃጀቱ በተሳካ ሁኔታ ተከናዉኗል!!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ነሀሴ :- 28/2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ በይፋ እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል!!
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም።
ትምህርት ለአንድ ሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሠረት መሆኑ በውል የሚታወቅ ሲሆን፤ ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ችግር እና የጸጥታ ስጋት አንጻርም ጭምር የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች ጥሪ አስተላልፈዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ባስቀመጠው አጠቃላይ አቅጣጫ መሠረት፦
፩. አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስታወሰኝ ላቀ በኩል) እንደገለጸው፤ ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም፣ ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በስጋት ውስጥ ሆነንም ቢሆን የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በወቅቱ እንዲጀመር አቅጣጫ ተቀምጧል። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፋኖ አመራሮች፣ ወላጆች፣ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን እና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
፪. አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ለሁሉም ኮሮች ባስተላለፈው ጥሪ፣ ድርጅታችን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት መደበኛ ትምህርት እንዲጀመር አሳስቧል። ለዚህም ስኬት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ አሳስቦ፣ ሁሉም ኮሮች ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አቅርበዋል።
፫. አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው አማካኝነት) በሰጠው መግለጫ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በዕዙ ሥር የሚገኙ ሁሉም ኮሮች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው ትምህርት እንዲያስጀምሩ አሳስቧል። ሙሉው ሕዝብ፣ መምህራን፣ የተማሪ ወላጆች እና ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ተላልፏል።
፬. አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በሰጠው ማሳሰቢያ፣ የ2019 ዓ/ም የትምህርት መርሐ ግብር እውን እንዲሆን በቁጥጥራቸው ሥር በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ሥራ እንዲገቡና የምዝገባ ሥራዎች እንዲጀመሩ አሳስቧል፤ ለዚህም አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
በአጠቃላይ የአፋብን ዕዞች ባስተላለፏቸው መልእክቶች፤ ትውልድን ለማዳን፣ አስተሳሰብን ለመገንባት እና ትናንትን በአዲስ ተስፋ ለመተካት ትምህርት ቤቶች መደበኛ አገልግሎታቸውን እንዲጀምሩና መላው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን እገዛና ትብብር እንዲያደርግ አጽንኦት ተሰጥቷል።
— የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ
የአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት የ1ዓመት ህፃንና የ70ዓመት ሽማግሌወች ላይ በዙ=23 ጉዳት አደረሰ።
==================
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም
አብይ አህመድ የአማራን ህዝብ አጠፋለው ብሎ ወደ ክልሉ ከገባ ጊዜ ጀምሮ ንፁሃንን በሁሉም የአማራ ቀጠናዎች ሰለቫ አድርጓል።
በሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ቆንትር ቀበሌ በዛሬው እለት ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ከቤታቸው የተቀመጡ ንፁሀንን በዙ=23 ሰለቫ አድርጓቸዋል።
መኖር ያልተፈቀደለት ህዝብ መኖሪያ ቤቱ ድረስ እየተሰቃዬ ይገኛል።
ይኸውም
1.ብዙአለም አሰማ
2.ዳሳሽ ብየዋለሁ
3.ምትኬ ብዙአየሁ
4.አቧሀይ ጨቤ እና ለጊዜው በስም ያልደረሱኝ 2ወደ ጤና ጣቢያ የሄዱትን ጨምሮ ጭፍጨፋ ፈፅሟል።
አማራን የማጥፋት ዘመቻ በየቀኑ እየፈፀመ የሚገኘው አገዛዝ በአካባቢው ቁጣን ቀስቅሷል።
ህፃን በተኛበት የሚቀርበትን፤ አረጋዊ በመጡሪያው የሚረሸንበትን የጥፋት ዘመቻ አቅዶ የሚንቀሳቀሰው ብልፅግና መራሹ የአብይ አህመድ አማራ ጠል ስርዓት በፋኖነት መቃብሩ ይፈፀማል።
ህዝባችን ከወትሮው በተለዬ ራሱን ያዘጋጅ።
አ.ፋ.ብ.ን ቴወድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት።
በእነማይ ወረዳ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት ጉዳይ ወቅቱን ያማካለ ስብሰባ ተካሂዶል።
64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም
64ኛ ክ/ጦር ትምህርት በተመለከተ በእነማይ ወረዳ የሚገኙ መምህራን፣ ዕርሰ መምህራንና ሱፕር ቫይዘሮች ጋር ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ዲማ ንዑስ ከተማ ጥልቅ ውይይት አካሂዶል።
የብልፅግና አገዛዝ በዚህ ሶስት ዓመት ትምህርትን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ በማድረግ ሲጠቀምበት ቆይቷል። አገዛዙ በጊዚያዊነት በተቆጣጠረባቸው ቦታዎች ሳይቀር ማህበረሰቡን በመሰብሰብ ጽንፈኛው ልጆቻችሁ ትምህርት እንዳይማሩ ከልክሏል እኛ ግን ትምህርት እናስጀምራለን የሚሉ የሐሰት አጀንዳዎችን በመንዛት ማህበረሰቡን ከፋኖ ለመነጠል ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
መድረኩን የመሩት የ64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጠላት በትምህርት ጉዳይ ሲያሰራጨው የነበረው የሐሰት መረጃ መሆኑን ግንዛቤ በመስጠት አፋብን በሚያስተዳድረው የትኛውም ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር የፈቀደ መሆኑን ለመድረኩ ተሳታፊ መምህራን ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በእነማይ ወረዳ ፋኖ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የትምህርት ተቋማት ከየትኛው የፀጥታ አካላት ነፃ እንደሚያደረግና ህዝባችን ልጆቻቸውን ወደ ት/ት ተቋማት እንዲልኩና ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አስተላልፏል።
በውይይት መድረኩ ከተገኙት መምህራን ጋር በተካሄደው ቅድመ አቅጣጫ መተግበር ያለባቸው ጉዳዩች ውስጥ ትምህርት ቤቶች ከማነኛም ወታደራዊ አካል ነፃ ማድረግ፣ በት/ቤቶች የትምህርት ቁሳቁስን እንዲሟሉ ማድረግ፣ የተሰባበሩ ወንበሮችን መጠገንና በአገዛዙ የወደሙ ት/ቤቶች ጥገናና እድሳት በማድረግ በ2019 ዓ.ም በሁሉም የ64ኛ ክ/ጦር ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር አቅጣጫ ሰጥቷል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!
ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የአፋብን ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ በተገኘበት በመና መቀጠዋ ወረዳ አጊሳ ከተማ እና አካባቢዋ ማህበረሰብ ጋር ውይይት አካሄደ!
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም
አፋብን የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ እና የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ከፍተኛ አመራሮች በመና መቀጠዋ ወረዳ አጊሳ ከተማ እና አካባቢዋ ማህበረሰብ ጋር ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ፍሬያማ ውይይት አድርጓል።
በዚሁ ህዝባዊ መድረክ ላይ የአፋብን ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ ፣የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ፣ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አጣናው፣ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ተሾመ አበባው፣ የፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሀብታሙ ሙላው፣የሰው ሀይል አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አዳነ ፀጋ እና ሌሎች የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩም አደረጃጀትንና አንድነትን ማጠናከር፣ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት መገምገም፣ የቀጣይ የፖለቲካና የወታደራዊ ዘመቻዎችን ግብ ማስቀመጥ፣ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ስላለው የደጀንነት አሰላለፍና አጠቃላይ የትግሉ ሂደት በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የአጊሳ ከተማ እና የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የጎንደር ፋኖ ወደ አንድነት መምጣቱ ታላቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸው ማህበራዊ ፍትህን ማስፈን፣ህዝባዊ አደረጃጀቶችን ማስተካከል እና የአባት አርበኞችን አወቃቀር ወቅቱን የዋጀ እንዲሆን ማስቻል ተገቢ ነው ብለዋል።
ስለሆነም ግልጽ የሆነ የዕዝ ሰንሰለትና የአሰራር ስርዓት በመፍጠር የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ሊወሰድ ይገባል ያሉት የውይይቱ ተሳታፊዎች ፣ የመረጃ የሞራል እና የመሰረታዊ ቁሳቁስ ድጋፍ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት ያስችላል ዘንድ የኦዲትና የቁጥጥር ስራዎች መኖር አለባቸው ሲሉም አንስተዋል ።
በሌላ በኩል ህዝባዊ ደጀንነትን በተግባር ለማረጋገጥ መነሻ መሆኑን በመረዳት የመሰረተ ልማት እና ሌሎች ህዝባዊ ተቋማት ከአደጋና ከጉዳት እንዲጠበቁ ማድረግ ተገቢ ነው ሰመሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የአፋብ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ላይ ማብራሪያዎችን የሰጡ ሲሆን ህዝባችን ለትግሉ መሳካት ዋና መሰረት እና የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልጸፀው ላለፍት ሦሥት ዓመታት በታዩ የመልካም አስተዳደር፣ የአደረጃጀት እና የፍትህ ጥያቄዎች ተገቢዎች መሆናቸውን በመውሰድ የታዩ ድክመቶችን በፍጥነት በማስተካከል ከህዝቡ ጋር በቅርበት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠው ፣ በየግንባሩ የሚደረገው መራር ትግል የህዝብን ህልውና፣ ነጻነትና ክብር ለማስጠበቅ ያለመ መሆኑን በመጠቆም፣ ህዝቡ የገባውን ቃል በማደስ ያደረገውን የመስመርና የደጀንነት ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ አዳዲስ የኃይል ምልመላዎች እና የደህንነት ስጋቶች መኖራቸው ተገለጸ
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ በንጹሃን ዜጎች ላይ ያለውን የደህንነት ስጋት የሚጨምሩ አዳዲስ የኃይል ምልመላዎች እና የጥቃት ዝግጅቶች እየተካሄዱ መሆናቸውን የሚጠቁሙ ስጋቶች መውጣታቸው ተገለጸ።
ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በወረዳው በሚገኙ በየቀበሌዎቹ ከ60 እስከ 80 የሚደርሱ ወጣቶች በብልጽግና ባለስልጣናት እየተመለመሉ እንደሆነ ታውቋል።
እነዚህ የተመለመሉ ኃይሎች ከአካባቢው የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት፣ በወረዳው በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች እና በንብረቶቻቸው ላይ ጥቃት ለማድረስ ዝግጅት እያደረጉ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ዘመቻው ለመምራት ወደ አካባቢው ለሚገቡ የገዳ ኮማንዶ ኃይሎች አቀባበል እና ግብዣ ለማደራጀት በሚል፣ ከእያንዳንዱ ነዋሪ በነፍስ ወከፍ 500 ብር እንዲሰበሰብ ትእዛዝ ተላልፏል።
እንደ ምንጮቹ ዘገባ፣ ይህ የዘረፋና የጥቃት ዝግጅት በዋናነት ያነጣጠረባቸው ቀበሌዎች፦
* ሀሮ አዲስ አለም፣
* ኖሌ ገብርኤል፣
* ስደን፣
* ቦቃ፣
* ነጭሎ፣
* ወዴሳ ዲማ እና ሌሎች አቅራቢያ የሚገኙ ዐማራው በብዛት የሚኖርባቸው ቦታዎች እንደሆኑ ታውቋል።
የ2019 የት/ት ዘመንን አስመልክቶ ከመምህራን ጋር ጥልቅ ውይይት ተካሄደ!
ለ3 አመታት ተቋርጦ የነበረውን ት/ት ለማስቀጠል እና የተማረ ትውልድ መገምባት አስፈላጊ በመሆኑና የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ያወረደውን መመሪያ ተከትሎ የቅድመ ዝግጅት ስራዎዝና ከመምህራን ጋር ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል።
ውይይቱ የተካሄደው ከውጊያ ጎን ለጎን በርካታ ስራዎችን እየሰራ በሚገኘው 34ኛ ክ/ጦር ከሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች ውስጥ በሆኑት ደጀን ወረዳ እንድሁም አዋበል ወረዳ ሲሆን በመጭው የት/ት ዘመን ዙሪያ በርካታ ሀሳቦች ተነስተዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት መምህራን እንድሁም ርዕሰ መምህራን ፋኖ ትምህር ለማስጀመር የሚያደርገውን ርብርብ አድንቀው እና አመስግነው ነገር ግን በርካታ ት/ቤቶች እንድሁም ለትምህርት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች በአገዛዙ ተጭነው ተወስደዋል ፣ ተቃጥለዋል ያሉ ሲሆን ስለዚህ ፋኖ የሚችለውን ሁሉ ድጋፍ እንዳደርግልን ሲሉም ጠይቀዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የ34ኛ ክ/ጦር አመራሮች እንድሁም የወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች ፋኖ በተቆጣጠራቸው ቦታዎች ያሉ ት/ቤቶች ሙሉ ጥገና እና ጥበቃ ተደርጎላቸው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው አሁንም ድጋፋቸው እንደማይለይ ተናግረዋል ።
ነገር ግን በርካታ ት/ቤቶች እና ቁሳቀስ በአገዛዙ መዘረፋቸውንና መውደማቸውን የተናገሩ ሲሆን የተወሰዱ ጥሬ እቃዎች እንድመለሱ ጫና ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል ።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
+3
የኋላ ከሌለ የፊቱ አይኖርም! በአፋብን በጎንደር ሰማይ ሰር ግንባር የሚንቀሳቀሰው የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ አመራሮችና አርበኞች የታሪክን መሠረትና የመስዋዕትነትን ዋጋ በግንባር ቀደምትነት በማሰብ፣ የማይረሳ የክብርና የደህንነት ጉብኝት አድርገዋል።
በዚህ ልብ የሚነካ መርሃ-ግብር ላይ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር አርበኛ ሰለሞን አጠና እና ሌሎች የትግል ጓዶቻቸው በአንድነት በመሆን የጀግናው ወንዱ አስቻለው ደሴ ወላጅ አባት እና እናት ዘንድ በአካል በመገኘት ሞቅ ያለ ሰላምታና የእንክብካቤ ጥየቃ አድርገዋል።
አርበኞቹ የወላጆችን ጤናና ደህንነት በጥበቃና በእንክብካቤ ከመጠየቅ ባለፈ፣ ለሀገርና ለትግሉ ስላበረከቱት ጀግና የከበረ የወንድማማችነት በማሰብ ወንድማችን ለእኛ ትልቅ ጉልበትና ብርታት ነው፤ የእናንተ አብራክ ደግሞ የሁላችንም ኩራት ነው!
በዚህ ውብ አጋጣሚ አርበኞቹ የጀግናውን ቤተሰቦች በመጎብኘት፣ ደህንነታቸውን በማረጋገጥና አብሮነታቸውን በማሳየት የማይናወጥ የትግል አጋርነታቸውን እና ጥልቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። #Dave #Amhara
ቀን፡ 27/12/2018 ዓ/ም ቁጥር፡ አፋብን/አስ/ዕ/ማ/ጉ/መ/001/18
በየደረጃው ላሉ የፋኖ አመራሮች
ለወላጆች
ለመምህራንና ለርዕሰ መምህራን
ለሚመለከተው ሁሉ ባለበት
ጉዳዩ፡- ትምህርት ማስጀመርን ይመለከታል
------------------------------------------------------
ትምህርት ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሳሪያ መሆኑ ግልፅ ነው። ምንም እንኳን ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ጉዳይ አኳያ በስጋት ሁኔታ ውስጥ ሆነንም ቢሆን ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራ በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር ሲል አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ያሳውቃል።
አስታውሰኝ ላቀ
አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለአማራ ፋኖ!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
