ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 904
订阅者
+10524 小时
+3357 天
+33630 天
帖子存档
በእነማይ ወረዳ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት ጉዳይ ወቅቱን ያማካለ ስብሰባ ተካሂዶል። 64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም 64ኛ ክ/ጦር ትምህርት በተመለከተ በእነማይ ወረዳ የሚገኙ መምህራን፣ ዕርሰ መምህራንና ሱፕር ቫይዘሮች ጋር ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ዲማ ንዑስ ከተማ ጥልቅ ውይይት አካሂዶል። የብልፅግና አገዛዝ በዚህ ሶስት ዓመት ትምህርትን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ በማድረግ ሲጠቀምበት ቆይቷል። አገዛዙ በጊዚያዊነት በተቆጣጠረባቸው ቦታዎች ሳይቀር ማህበረሰቡን በመሰብሰብ ጽንፈኛው ልጆቻችሁ ትምህርት እንዳይማሩ ከልክሏል እኛ ግን ትምህርት እናስጀምራለን የሚሉ የሐሰት አጀንዳዎችን በመንዛት ማህበረሰቡን ከፋኖ ለመነጠል ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። መድረኩን የመሩት የ64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጠላት በትምህርት ጉዳይ ሲያሰራጨው የነበረው የሐሰት መረጃ መሆኑን ግንዛቤ በመስጠት አፋብን በሚያስተዳድረው የትኛውም ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር የፈቀደ መሆኑን ለመድረኩ ተሳታፊ መምህራን ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በእነማይ ወረዳ ፋኖ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የትምህርት ተቋማት ከየትኛው የፀጥታ አካላት ነፃ እንደሚያደረግና ህዝባችን ልጆቻቸውን ወደ ት/ት ተቋማት እንዲልኩና ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አስተላልፏል። በውይይት መድረኩ ከተገኙት መምህራን ጋር በተካሄደው ቅድመ አቅጣጫ መተግበር ያለባቸው ጉዳዩች ውስጥ ትምህርት ቤቶች ከማነኛም ወታደራዊ አካል ነፃ ማድረግ፣ በት/ቤቶች የትምህርት ቁሳቁስን እንዲሟሉ ማድረግ፣ የተሰባበሩ ወንበሮችን መጠገንና በአገዛዙ የወደሙ ት/ቤቶች ጥገናና እድሳት በማድረግ በ2019 ዓ.ም በሁሉም የ64ኛ ክ/ጦር ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር አቅጣጫ ሰጥቷል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!                   ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

የአፋብን ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ በተገኘበት  በመና መቀጠዋ ወረዳ አጊሳ ከተማ እና አካባቢዋ ማህበረሰብ ጋር ውይይት አካሄደ! ​ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም አፋብን የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ እና የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ከፍተኛ አመራሮች በመና መቀጠዋ ወረዳ አጊሳ ከተማ እና አካባቢዋ ማህበረሰብ ጋር  ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ፍሬያማ ውይይት አድርጓል። በዚሁ ህዝባዊ መድረክ ላይ የአፋብን ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ ፣የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ፣ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አጣናው፣ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ተሾመ አበባው፣ የፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሀብታሙ ሙላው፣የሰው ሀይል አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አዳነ ፀጋ እና ሌሎች የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ​በመድረኩም አደረጃጀትንና አንድነትን ማጠናከር፣ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት መገምገም፣ የቀጣይ የፖለቲካና የወታደራዊ ዘመቻዎችን ግብ ማስቀመጥ፣ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ስላለው የደጀንነት አሰላለፍና አጠቃላይ የትግሉ ሂደት በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የአጊሳ ከተማ እና የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የጎንደር ፋኖ ወደ አንድነት መምጣቱ ታላቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸው ማህበራዊ ፍትህን ማስፈን፣ህዝባዊ አደረጃጀቶችን ማስተካከል እና የአባት አርበኞችን አወቃቀር ወቅቱን የዋጀ እንዲሆን ማስቻል  ተገቢ ነው ብለዋል። ስለሆነም ግልጽ የሆነ የዕዝ ሰንሰለትና የአሰራር ስርዓት በመፍጠር የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ሊወሰድ ይገባል ያሉት የውይይቱ ተሳታፊዎች ፣ የመረጃ  የሞራል እና የመሰረታዊ ቁሳቁስ ድጋፍ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት ያስችላል ዘንድ የኦዲትና የቁጥጥር ስራዎች መኖር አለባቸው ሲሉም አንስተዋል ። በሌላ በኩል ህዝባዊ ደጀንነትን በተግባር ለማረጋገጥ መነሻ መሆኑን በመረዳት የመሰረተ ልማት እና ሌሎች ህዝባዊ ተቋማት ከአደጋና ከጉዳት እንዲጠበቁ ማድረግ ተገቢ ነው ሰመሉም  አጽንኦት ሰጥተዋል። በመጨረሻም ​የአፋብ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ረ/ፕ ጌታ አስራደ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ላይ ማብራሪያዎችን የሰጡ ሲሆን ህዝባችን ለትግሉ መሳካት ዋና መሰረት እና የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልጸፀው  ላለፍት ሦሥት ዓመታት በታዩ የመልካም አስተዳደር፣ የአደረጃጀት እና የፍትህ ጥያቄዎች ተገቢዎች መሆናቸውን በመውሰድ የታዩ ድክመቶችን በፍጥነት በማስተካከል ከህዝቡ ጋር በቅርበት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠው ፣ በየግንባሩ የሚደረገው መራር ትግል የህዝብን ህልውና፣ ነጻነትና ክብር ለማስጠበቅ ያለመ መሆኑን በመጠቆም፣ ህዝቡ የገባውን ቃል በማደስ ያደረገውን የመስመርና የደጀንነት ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ አዳዲስ የኃይል ምልመላዎች እና የደህንነት ስጋቶች መኖራቸው ተገለጸ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ በንጹሃን ዜጎች ላይ ያለውን የደህንነት ስጋት የሚጨምሩ አዳዲስ የኃይል ምልመላዎች እና የጥቃት ዝግጅቶች እየተካሄዱ መሆናቸውን የሚጠቁሙ ስጋቶች መውጣታቸው ተገለጸ። ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በወረዳው በሚገኙ በየቀበሌዎቹ ከ60 እስከ 80 የሚደርሱ ወጣቶች በብልጽግና ባለስልጣናት እየተመለመሉ እንደሆነ ታውቋል። እነዚህ የተመለመሉ ኃይሎች ከአካባቢው የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት፣ በወረዳው በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች እና በንብረቶቻቸው ላይ ጥቃት ለማድረስ ዝግጅት እያደረጉ እንደሆነ ተጠቅሷል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ዘመቻው ለመምራት ወደ አካባቢው ለሚገቡ የገዳ ኮማንዶ ኃይሎች አቀባበል እና ግብዣ ለማደራጀት በሚል፣ ከእያንዳንዱ ነዋሪ በነፍስ ወከፍ 500 ብር እንዲሰበሰብ ትእዛዝ ተላልፏል። እንደ ምንጮቹ ዘገባ፣ ይህ የዘረፋና የጥቃት ዝግጅት በዋናነት ያነጣጠረባቸው ቀበሌዎች፦ * ሀሮ አዲስ አለም፣ * ኖሌ ገብርኤል፣ * ስደን፣ * ቦቃ፣ * ነጭሎ፣ * ወዴሳ ዲማ እና ሌሎች አቅራቢያ የሚገኙ ዐማራው በብዛት የሚኖርባቸው ቦታዎች እንደሆኑ ታውቋል።

‎የ2019 የት/ት ዘመንን አስመልክቶ ከመምህራን ጋር ጥልቅ ውይይት ተካሄደ! ‎ ‎ለ3 አመታት ተቋርጦ የነበረውን ት/ት ለማስቀጠል እና የተማረ ትውልድ መገምባት አስፈላጊ በመሆኑና የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ያወረደውን መመሪያ ተከትሎ የቅድመ ዝግጅት ስራዎዝና ከመምህራን ጋር ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል። ‎ውይይቱ የተካሄደው ከውጊያ ጎን ለጎን በርካታ ስራዎችን እየሰራ በሚገኘው 34ኛ ክ/ጦር ከሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች ውስጥ በሆኑት ደጀን ወረዳ እንድሁም አዋበል ወረዳ ሲሆን በመጭው የት/ት ዘመን ዙሪያ በርካታ ሀሳቦች ተነስተዋል። ‎በውይይቱ ላይ የተገኙት መምህራን እንድሁም ርዕሰ መምህራን ፋኖ ትምህር ለማስጀመር የሚያደርገውን ርብርብ አድንቀው እና አመስግነው ነገር ግን በርካታ ት/ቤቶች እንድሁም ለትምህርት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች በአገዛዙ ተጭነው ተወስደዋል ፣ ተቃጥለዋል ያሉ ሲሆን ስለዚህ ፋኖ የሚችለውን ሁሉ ድጋፍ እንዳደርግልን ሲሉም ጠይቀዋል። ‎በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የ34ኛ ክ/ጦር አመራሮች እንድሁም የወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች ፋኖ በተቆጣጠራቸው ቦታዎች ያሉ ት/ቤቶች ሙሉ ጥገና እና ጥበቃ ተደርጎላቸው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው አሁንም ድጋፋቸው እንደማይለይ ተናግረዋል ። ነገር ግን በርካታ ት/ቤቶች እና ቁሳቀስ በአገዛዙ መዘረፋቸውንና መውደማቸውን የተናገሩ ሲሆን የተወሰዱ ጥሬ እቃዎች እንድመለሱ ጫና ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል ። ‎ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

የኋላ ከሌለ የፊቱ አይኖርም! ​በአፋብን በጎንደር ሰማይ ሰር ግንባር የሚንቀሳቀሰው የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ አመራሮችና አርበኞች የታሪክን መሠረትና የመስዋዕትነትን ዋጋ በግንባር ቀደምትነት በማሰብ፣
+3
የኋላ ከሌለ የፊቱ አይኖርም! ​በአፋብን በጎንደር ሰማይ ሰር ግንባር የሚንቀሳቀሰው የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ አመራሮችና አርበኞች የታሪክን መሠረትና የመስዋዕትነትን ዋጋ በግንባር ቀደምትነት በማሰብ፣ የማይረሳ የክብርና የደህንነት ጉብኝት አድርገዋል። ​በዚህ ልብ የሚነካ መርሃ-ግብር ላይ ​አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር አርበኛ ሰለሞን አጠና ​እና ሌሎች የትግል ጓዶቻቸው በአንድነት በመሆን ​የጀግናው ወንዱ አስቻለው ደሴ ወላጅ አባት እና እናት ዘንድ በአካል በመገኘት ሞቅ ያለ ሰላምታና የእንክብካቤ ጥየቃ አድርገዋል። ​አርበኞቹ የወላጆችን ጤናና ደህንነት በጥበቃና በእንክብካቤ ከመጠየቅ ባለፈ፣ ለሀገርና ለትግሉ ስላበረከቱት ጀግና የከበረ የወንድማማችነት በማሰብ ወንድማችን ለእኛ ትልቅ ጉልበትና ብርታት ነው፤ የእናንተ አብራክ ደግሞ የሁላችንም ኩራት ነው! ​በዚህ ውብ አጋጣሚ አርበኞቹ የጀግናውን ቤተሰቦች በመጎብኘት፣ ደህንነታቸውን በማረጋገጥና አብሮነታቸውን በማሳየት የማይናወጥ የትግል አጋርነታቸውን እና ጥልቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። #Dave #Amhara

ቀን፡ 27/12/2018 ዓ/ም ቁጥር፡ አፋብን/አስ/ዕ/ማ/ጉ/መ/001/18 ​በየደረጃው ላሉ የፋኖ አመራሮች ለወላጆች ለመምህራንና ለርዕሰ መምህራን ለሚመለከተው ሁሉ ባለበት ​ጉዳዩ፡- ትምህርት ማስጀመርን ይመለከታል ------------------------------------------------------ ​ትምህርት ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሳሪያ መሆኑ ግልፅ ነው። ምንም እንኳን ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ጉዳይ አኳያ በስጋት ሁኔታ ውስጥ ሆነንም ቢሆን ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራ በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር ሲል አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ያሳውቃል። አስታውሰኝ ላቀ አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ ​ድል ለአማራ ህዝብ! ድል ለአማራ ፋኖ! ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!

ሰበር ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ በዞብል እና በተኩለሽ ግንባር በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፀሙ። ነሐሴ 26 /2018ዓ/ም የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ ከቆቦ ከተማ በምስራቅ እና በምዕራብ በሚገኙ በዞብል እንድሁም በተኩለሽ በተባሉ አካባቢዎች በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ያልተጠበቀ የደፈጣ ጥቃት ወሰዱ። አገዛዙ ከቆቦ ከተማ በምዕራብ ግንባር እና በምስራቅ ግንባር ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ጥቃት ሊከፍት እንዳሰበ የ102ኛ ኮር ፀረ-መረጃዎች ባገኙት መረጃ መሰረት የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ በሌሊት ተስበው ቀድመው ቦታዎችን በመያዝ ጠላት ባልጠበቀው እና ባለአቀድው መንገድ ዋጋ አስከፍለውታል። በመሆኑም አገዛዙ የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ ጀግኖችን ክንድ መቋቋም ባለመቻሉ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኋላ እንድያፈገፍግ ተገዷል። በአውደ ውጊያው የተገኘ አጠቃላይ ውጤት 7 ክላሽን ኮፍ መሳሪያ ፣ ስድሰት F1 ቦንብ ፣ አምስት የወገብ ትጥቅ ፣ሁለት ሞርኮ ፣ አስራ ሶስት የተደመሰሰ እንድሁም ስምንት የቆሰለ መሆኑን የ12ኛ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሳል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ጋፋት ክፍለ ጦር የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም  በጠላት ላይ  ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ! ​በደቡባዊ ጎንደር ዞን ከደብረ ታቦር  በቅርብ ርቀት ወደ ጋሳይ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ በተጣለ ደፈጣ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ጋፋት ክፍለ ጦር ደጀን ብርጌድ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት አድርሰዋል። ​ልዩ ስሟ “ዋዶ” በተባለ  ቦታ ላይ በተካሄደው ከባድ አውደ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሚሊሻ አባላት የሆኑ 5 ሰራዊቶቹ ወዲያውኑ ሲደመሰሱ 7 የሚሆኑት ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት አስተናግደው  ደብረ ታቦር ሆስፒታል ገብተዋል። በአውደ ውጊያው ከተደመሰሱ የአገዛዙ ኃይሎች  3 የነፍስ ወከፍ  ክላሽኮቭ የጦር መሳሪያዎች ገቢ ሆነዋል። ምንጭ፦በ​አፋብን 3ኛ በላይ ዘለቀ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር አቡበክር ሰይድ መሐመድ ያስተላለፈው መልዕክት! ጃዋር መሀመድ እውነተኛ ቀለሙን አሳየ መፅሐፍን በሽፋኑ አትመዝን! አብሮ የማያኗኑር ፅንፈኛ ብሔርተኝነት አቀንቃኙ ጀውሐር መሐመድ ጭምብሉ ወልቆ እውነተኛ ቀለሙን ተገልጾ አየነው። እውነት ለመናገር እንደ አንድ ሙስሊም ከነጥፋቱም ቢሆን የወንድምነት ስሜት ይሰማሀል። ይሻሻል ዘንድ በጎም ትመኝለታለህ። ሰው በፍጥረቱ ለሥህተት ቅርብ ነው። ከተሳሳቾች ምርጦቹ ደግሞ ይህን ሀቅ የተረዱት፣ ለመታረምም ዝግጁ የሆኑትና ዳግም ከዚያው ሥህተታቸው ላይ ወድቆ ላለመገኘት የሚጠነቀቁት ናቸው። የአማራ ጥላቻ ያሰከረው ጀውሐር ወንድማችን ግን ዛሬም አዳልጦት ወድቆ ጠብቶት ያደገው ፅንፈኛ ብሔርተኝነት ያለበሰውን ማቅ ለሱ በተሰላ መንገድ፣ ለአራዶቹ የነፃነት ዘቦች ግን ግልፅ በሆነ መንገድ ለማንሳት ሲሞክር  ጭንብሉ ተገልጾ መበልፀጉን አሳበቀበት። በርግጥ የጀውሐርን የፖለቲካ ሀሁ ለሚገነዘብ የሱ ፀረ ብልፅግናነት ለይስሙላ እንጅ የ7ኛ ጨውን ቦታ ባቋራጭ ቢሰጡት ከማንም በላይ በልፅጎ እንደሚገኝ ድሮም እሙን ነው። እስልምና በኢትዮጵያ ..... የሚለውን መፅሐፍ በሽፋኑ ላለመመዘንና የማላውቀውን ለመገንዘብ ሲባል አነበብኩት። እንደዚህ በሙህራዊ ትንተና አለም አቀፍ የታሪክ ምንጮችን በማጣቀስ የሙስሊሙን የሀገር ባለቤትነት ማሳወቅና መብቱን መጠየቅ ማለማመድ የሚበረታታ መልካም ሥራ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ሙስሊሙ በሀገራችን የነበረውን የፖለቲካ ተሳትፎ ያሳድጋል ብየ አምናለሁ። ነገር ግን የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጉዳይን በትከሻቸው ተሸክመው በህዝበ ሙስሊሙ ሥም ዘር አጥፊ ሥርአትን ማውገዛቸው ቢቀር በስልት መደገፍም ይሁን መተባበር ላይ ለሚገኙ ወንድሞቼ ልነግራቸው የምፈልገው ሀቅ ፋኖ አያደርገውም እንጂ በሌሎች አካባቢዎች ባየነው ተሞክሮ ቢሆን ለህዝበ ሙስሊሙ ቄራን እያዘጋጁለት እንደሆነ እንድያውቁት ነው። ሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተጎዳ እንደ አማራ ደግሞ በግ ተብሎ እየታረደ ባለበት ሁኔታ መቼ ነው የነፍስ መዳኛ፣ የፍትህና የእውነት ዘብነታችሁን የምናየው? እዚህ ላይ ለኔ የመልስ ምት የሚሆኑ አንዳንድ ክስተቶችን እንደምታነሱ አልጠራጠርም። እኔም እላችኋለሁ ኑ ሁሉንም ኢፍትሃዊነቶች በጋራ እንታገላቸው። የእናንተ የበለፀገ ቤት ያለን ኢፍትሃዊነት እየታገልን እኛ ቤት ኢፍትሐዊነትን አናነግስም። ልጅ በጨቅላነቱ ለምን ሸናህብኝ አይባልም። ድርጅት ሳይመሠረትና ሁሉም በመሠለው በሚንቀሳቀስበት ወቅ የታዘብናቸው ግድፈቶች ሊኖሩ ይችላሉ። አሁን በድርጅታዊ የተጠየቅ ሠንሠለት በሚሠራበት ወቅት ያ ይደገማል ብላችሁ እንዳታስቡ። ድርጅቴ ውስጥ የተማርኩት እውነተኛ ትግል ይህንን ነው። በውርስ ሥልጣን ላይ የጃጀው ብልፅግናችሁ ብልግና መቼ ነው የሚታያችሁ? ሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደማንኛውም ያገሬው ሰው ፀረ ህዝቡን ሥርአት እንዳይታገል የተሳሳተ ትርክት የምትሰጡትን ነገርስ መቼ ነው የምታቆሙት? በአለም ፊት በሰብአዊ መብት ጥሰትና በጦር ወንጀል የፍርድ አደባባይ ላይ መቅረብ ያለበትን ግለሰብ ከፈጣሪ የቅርብ ወዳጆች ተርታ ያሳለፉ የኛ የህዘበ ሙስሊሙ መሪ እጅግ በጣም አሳዝነውኛል። ከገጠመን የህልውና ሥጋትና ሀገራዊ ቀዉስ ለመውጣትና ሙስሊሙም መብቱን በልኩ ለማስከበር ዛሬ ከኛ ከወንድሞቹ ጎን ሆኖ ይህንን ፀረ ሰው ሥርአት መታገል አለበት። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር አቡበክር ሰይድ መሐመድ!

የ14ኛክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አዲስ የፌስቡክ ገፅ ነው ይወዳጁት https://www.facebook.com/profile.php?id=61589412698840

የአርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የደራው አንበሳ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የህግ መምሪያ የብረት ክንድ !! ​የሸዋ ተራራዎች በባሩድ ጭስ ሲሸፈኑ፣ የደራና የሰላሌ ምድር በአረመኔያዊ አብይ አህመድ ወራሪው የጠላት ከበባ ሲደቀንባት የህዝቡን እንባና ቁጭት ወደ ወኔ ቀይሮ በወራሪው ፊት እንደ አለት የቆመው አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የመጀመሪያው ነው። አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የወታደራዊ ስልት አዋቂ የማንነት አስመላሽ የትግል አቅኚ እና በአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ህግ መምሪያ የፅናትና የድል አርማ ሆኖ የሚሰራው የዘመናችን አሳምነው ጀግና ነው። አረበኛ ​የማንነት ትግልና የህዝብ አለኝታነት፡ ደራ በጠላት በወራሪ ኃይሎች መሬቷ ሲቀማ፣ ህዝቧ ሲፈናቀልና መንደሯ በእሳት ሲጋይ፣ አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የማንነት አስመላሽ ኮሚቴን በመምራት የህዝቡን ድምፅና ቁስል ይዞ የተነሳ። የተፈናቀሉትን ወገኖች በማስተባበር የትግል አጋር በማድረግ ቀያቸውን ለማስመለስ የቀደመውን መንገድ ጠረገ። የጠላት ከባድ መሳሪያና የሰው ማዕበል ሲወርድ፣ አርበኛ ሽመልስ ከፊት መስመር ተሰልፎ ሰራዊቱን መራ። "ማረፊያችን ግንባር፣ ፋኖነት ክንዳችን ነው!" በሚል የቆራጥነት መርሃ-ግብር የጠላትን ሰራዊት በደፈጣና በፊት-ለፊት ውጊያ ከጀግኖቹ የደራ ጀግኖች ጋር ሆኖ በከፍተኛ አመራርነቱና ወታደራዊ ታክቲኩ የጠላትን የማጠቃቃት እቅድ አፈር ድሜ አስበልቷል። አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ በአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የብረት ዲሲፕሊንና መሪነት የትግሉን ስነ-ስርዓት፣ ወታደራዊ ዲሲፕሊንና የህግ የበላይነት በመቅረፅ ረገድ አስተዋፅኦ ታላቅ የሆነ ሲሆን። ሰራዊቱ ህዝባዊ ዓላማውን ሳይስቅ፣ የወገኑን ደህንነት በመጠበቅ እና የጠላትን ስንቅና ትጥቅ በመበተን ረገድ አብነታዊ ወታደራዊ ስልት እንዲከተል እያደረገ ይገኛል። አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ ​የነበልባሉ ታሪካዊ ጥሪ፡ በሆነው አንደበቱ በጅቡቲ፣ በሳውዲ አረቢያ፣ በዱባይና በዓለም ዙሪያ የተሰደዱ የደራ ልጆችንና የፋኖ አባላትን ጥሪ በማስተላለፍ፤ "ከመሞት መሰንበት፣ ከመቀመጥ መነሳት ይሻላል!" በሚል ቃል ትውልዱን አነቃቃ። ይህ ጥሪ በሺዎች የሚቆጠሩ የደራ ልጆች ወደ ግንባር እንዲያጠናክሩ ምክንያት ሆነ። ​"አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የደራ ልጅ ብቻ አይደለም ከሸዋ እስከ ወሎ፣ ከጎንደር እስከ ጎጃም የተዘረጋው የአማራ ህዝብ ብሔራዊ አንድነት፣ የጽናትና የድል አርማ የደራ ህዝብ መከታ፣ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የህግ ክፍል መምሪያ መሪና የሸዋ ተራራዎች የማይበገሩበት የጀግንነት ታሪክ ባለቤት ነው ! ይቀጥላል......!! #Dave #Amhara