uk
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Відкрити в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Показати більше
2 923
Підписники
+3224 години
+3727 днів
+36630 днів
Архів дописів
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር በጣላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ያደረ አውደ ውጊያ አደረገ❗    ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር አሃድ የሆኑት:- ➛ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር ጉና ክፍለ ጦር (መቅደላ ብርጌድ፣አንዳቤት ብርጌድ፣ጉና ክፍለ ጦር ቃኝና  መሐንዲስ ፣የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ቃኝና መሐንዲስ ) በተሳተፉበት የማህደረ ማርያም አውደ ውጊያ ( መተረይ፣ ናዳ፣ ዳዋ፣ ማሕደረ ማርያም፣ እማ ወተት ጊዎርጊስ እና ዳዋ መድኃኒዓለም ላይ ከንጋት ) ከንጋት 11:30 የተጀመረው አውደ ውጊያ እስከ ቀኑ 08:00 ሰዓት የቀጠለ ሲሆን  ውጊያ የተደረገባቸው ቦታዎችም በጠላት ላይ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ የደረሰ ሲሆን ቁጥሩ ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ሄዷል።                  ➛ጉና ክፍለ ጦር/ገብረ መስቀል ብርጌድ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር  ከደብረ ታቦር ወርቄን-ገና መጫወቻ፣ ከጋሳኝ በደንጊል አስኩማ- ገና መምቻን አድርጎ ወደ ማሕደረ ማርያም  ለማቅናት ቢሞክርም የጉና ክፍለ ጦር አካል የሆነው ገብረ መስቀል ብርጌድ ከጠዋቱ 01:00 ሰዓት ላይ የመጣውን መከላከያ ባለበት እንዲቆም በማድረግ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ከጀርባ በወርቄን በኩል ከበባ በማድረግና በመቁረጥ የገባው ኃይል ቁስቋም፣ ሺሞፈና፣ ሰንሳ ውኋ፣ ጣልሚዱ ሚካኤል፣ ስርስራውና ገና መጫወቻ  እንዲመታ በማድረግ ወደ ጋሳኝ እንዲወጣ ተገዷል ።ቁጥሩ ያልታወቀ የጠላት ኃይልም ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።  ➛ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር ከአባ ኪሮስ እስከ  መነጉዘ የክፍለ  ጦርዘሩ ቃኝና መሐንዲስ፣ 3ኛ ሻለቃ እና የክፍለ ጦር ስታፍ ሸኸቲ ተራራ ፣ አባኪሮስ ፣ ቀሰር ተራራ ፣ እንድርያስ ተራራ ፣ ባንዲገዝ ፣ጮሪት እና  መነጉዘር ላይ ድል ተቀዳጅቷል። በሌላኛው አውደ ውጊያ ግንባር ዓለም በር ከተማ የነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር አካል የሆነችው 2ኛ ሻለቃ ዓለም በር ከተማ ከረፋዱ ጀምሮ እስከ ቀኑ 08:00 የቆዬ ውጊያ አድርጋለች።                       ➛ ጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር አፈርዋናት ብርጌድ  ከአምበሳሜና አርብ ገበያ ተነስቶ ወደ ግንዳ ጠመምና ማሕደረ ማርያም ለመድረስ ዙ-23 እና መሰል የቡድን መሳሪያዎችን ይዞ ሲከንፍ ገላውዴዎስ ላይ አፈርዋናት ብርጌድ በደፈጣ ተመቷል። አምበሶ ብርጌድና ጣና ብርጌድ የጠላት ኃይል ከዋንዛዬና ከጉራምባ መካከል ከምትገኘው ''ተኬ በር'' ከተባለች ቦታ ላይ ሁለቱ ብርጌዶች በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ ጠላትን ማምበርከክ ችለዋል።                ​​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

በራያ ቆቦ ግንባር  11 የመከላከያ ሰራዊት አባላት አንድ እስናይፐር ፣ አንድ መትረየስ እና ክላሾችን በመያዝ ወደ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ። ዛሬ ነሀሴ 15/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ 11 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከላይ በተጠቀሰው መሰረት 2 የቡድን መሳሪያ እና 6 ክላሽን ኮፍ መሳሪያ በመያዝ 12ኛ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ። የመጡት የመከላከያ ሰራዊት አባላት 1200 የክላሽ ጥይት ተተኳሽ እና 200 የመትረየስ ጥይት ተተኳሽ በመያዝ 12ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። የተቀላቀሉት የሰሜን ዕዝ 801ኛ ኮር 45ኛ እና 46ኛ ክፍለጦር እንድሁም ከደቡብ ዕዝ 202ኛ ኮር 21ኛ ክፍለጦር የጠላት የሰራዊት አባላት ህዝባችንን አንወጋም በብለው ወደ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 102ኛ ኮር በመምጣታቸው በ102ኛ ኮር እና በ12ኛ ክፍለጦር አመራሮች የጀግና አቀባበል ተደርጓል ሲል የ102ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም

ትግል መርህ ሲኖረው እንዲህ ነው የአፋብን ምክትል ሊቀመንበር ለወታደራዊ ጉዳይ አርበኛ ሃብቴ ወልዴ እና የበላይ ዘለቀ (3) ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ ከትግል አጋሮቻቸው ጋር በግዳጅ ቀጠና!!

በአማራ ፋኖ ስም መኪናዎችን በማስቆም ሲዘርፉ በነበሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ ተወሰደ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)  ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ከፍተኛ ክትትል በማድረግ ከላሊበላ ወደ ሰቆጣ በሚጓዙ ከቀላል እስከ ከባድ መኪናዎችን በማስቆም ከመረዝ በር እስከ ፀዳ ወንዝ እየተዟዟሩ በፋኖ ስም ይዘርፉ የነበሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ ተወሰደ። . ነሃሴ 14/2018 ዓ/ም 303ኛ ኮር አካል የሆኑት ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር እና ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር በሚቀሳቀሱበት ቀጠና በተለምዶ ሞሰቢት ከሚባል ቦታ አንድ የካስኒ ሹፊር በማገት ወደ ጫካ ከወሰዱ በኋላ አንድ ሚሊዮን ብር አምጣ እኛ የአማራ ፋኖ ነን በማለትና ከብልፅግና ተልዕኮ በመቀበል ፋኖን ከህዝብ ለመነጠል ሲያደርጉ የነበረ ማለትም መኪና መዝረፍ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ተቋም መዝረፍ የመሳሰሉትን ወጀሎች ከፋኖ በመሰወር ሲተገበሩ የነበሩ ናቸው። በተደረገው ክትትል ታጥቀው መኪና አግተው አንድ ሚሊዮን ብር ሲጠይቁ ከነበሩት ተመስጌን ባዩህ እጂ ከፍንጂ በመያዝ እርምጃ የተወሰደበት ሲሆን ተባባሪዎቹ አለቤ ጉበና እና አለሙ ብርሐኑ የተባሉ ግለሰቦች ሲቆስሉ ጌታሁን አዲሴ የተባለው ግለሰብ ከተማ በመቀመጥ የተዘረፈ ገንዘብ በተለያዩ አካውንቶች እየተላከለት እንደሆነ ታውቋል። በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች በእንደዚህ አይነትና መሰል ድርጊቶች የሚሳተፍና የፋኖን ስም ለማጠልሸት የተዘረጉ ስውር እጆችን እንደማንታገስና ማንኛውም ግለሰብ ከእንደዚህ አይነት ድርጊት ተባባሪ እንዳይሆን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሚኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ነሃሴ15/12/2018ዓ.ም

ድል ለአማራ ፋኖ! የአፋብን ቴዎድሮስ (2) ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሰርጂካል ኦፕሬሽን ቡድን በሞጣ ከተማ ልዩ ኦፕሬሽን ፈጸመ በዛሬው ዕለት ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በጥዋቱ የዕዙ
ድል ለአማራ ፋኖ! የአፋብን ቴዎድሮስ (2) ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሰርጂካል ኦፕሬሽን ቡድን በሞጣ ከተማ ልዩ ኦፕሬሽን ፈጸመ በዛሬው ዕለት ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በጥዋቱ የዕዙ የሰርጂካል ኦፕሬሽን ቡድን አባላት በሞጣ ከተማ አየር ማረፊያ ሥላሴ አካባቢ ዋርድያ በተቀመጡ በሚሊሻ አባላት ላይ በወሰዱት የተቀናጀ የሰርጂካል እርምጃ በጠላት ኃይል ላይ ጉዳት በማድረስ ተልዕኳቸውን በድል አጠናቀዋል። በዚሁ መብረቃዊ እርምጃ 3 የሚሊሻ አባላት የተደመሰሱ ሲሆን፡ በላይነህ ሙናቻ — ሚሊሻ ገብሬ ስንሻው — ሚሊሻ አንድ በስም ያልታወቀ — የቆሰለ ሚሊሻ መሆናቸው ተረጋግጧል። የተማረከ የጦር ቁሳቁስ፡ 1 ክላሽኮቭ (AK-47) 1 ኤስ.ኬ.ኤስ (SKS) ጠመንጃ የኦፕሬሽን ቡድኑ አባላት የተጣለባቸውን  ተልዕኮ በብቃት ከተወጡ በኋላ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው ወደ አሀዳቸው በሰላም ተቀላቅለዋል። አንዲስ ትውልድ ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ ! ነሐሴ 15/2018 ዓም አሻራ ሚዲያ/ኃይሌ ሙሉ

⚫️#ገዳዩ_የኦሮሙማው_ቡድን‼️ በአንገር ጉትን ወረዳ፤ በኦሮሚያ ክልል የገዳ ኮማንዶዎች በሚደገፉ ኦሮሞ ወጣቶች (ቄሮዎች) የተፈጸመ ጥቃት ሦስት አረጋዊያን አማራዎች በመጥረቢያ ተገድለዋል፣ ቤተክርስቲያንም ተቃጥላለች፤ በሺዎች የሚቆጠሩም ተፈናቅለዋል ። በአንገር ጉትን በሚገኙት መንደር 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6 እና 22 ውስጥ የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ አማራዎች ተፈናቅለዋል ። መንደር 3 እና የፈንድቃ ቀበሌ ሙሉ በሙሉ ተዘርፈውና ወድመው የተቃጠሉ ሲሆን፣ የለሚ ተክለኃይማኖት ቤተክርስቲያንም በእሳት ተቃጥላለች ። ከፈንድቃ መሸሽ ያልቻሉ ከ70 እስከ 85 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሦስት የአማራ አረጋዊያን በጥቃቱ ወቅት በመጥረቢያ ተገድለዋል። ይህ ጥቃት የተፈጸመው በኦሮሚያ ክልል የገዳ ኮማንዶ ኃይሎች በሚደገፉ ቄሮዎች አማካኝነት ነው። ከሰሞኑን በህጋዊ መንገድ የተደራጁ የክልሉ ወታደራዊ ኃይል ፣ በፌደራል ስም የተቋቋመው ኃይል እንዲሁም በኢ-መደበኛ አደረጃጄት በክልሉ የተደራጀው ገዳይ ቡድንን አዝምቶ በተለያዩ የወለጋ ቀጠናዎች በፋኖ እየተቀጠቀጡ ቢሆንም ንፁሀን ግን እየጨፈጨፈ ይገኛሉ። መጨፍጨፋቸው ሳያንስ የአማራ ፋኖ ጭፍጨፋ ፈፅሞብናል ፣ አማራ ከክልላችን ይጥፋ በማለት ሞታችንን ለማድበስበስ እየሰሩ ይገኛሉ! 15/12/2018 ዓ.ም

የእውነትና የፍትህ ዋጋ፡ በአጣዬና በሸዋ ህዝብ መከራ ላይ ያልተደራደሩት የኮማንደር ሞገስ ባዩ እንግልት!! ​አንድ ህዝብ መከራና እንግልት ሲገጥመው፣ ከጎኑ ቆሞ በታማኝነት ማገልገል የሁልጊዜም የሞራልና የሙያ ግዴታቸው ያደረጉ ጥቂት የህዝብ አለኝታዎች አሉ። ከእነዚህ መካከል ህዝባቸው ሲበደልና ሲቃጠል ዝም ብለው ማየት ያልቻሉት የአጣዬው ጀግና መሪ ኮማንደር ሞገስ ባዩ አንዱ ናቸው። ​ሸዋሮቢትና አጣዬ ከ14 በላይ በእሳት ሲያሩ፣ የህዝብ ሰደድና የእናት እንባ እያቃጠለ በነበረበት ያንን ጥቁር ወቅት፣ የፌደራል ፖሊስ ምርመራ ሀላፊ ሆኖ መዝገብ ሲገልጥ የነበረው፣ ትውልዱ የወሎና የኦሮሞ ድብልቅ የሆነው አሁን ወደ ፌደራል ፖሊስ የተመለሰው ፀረ-ሸዋው ኮሚሽነር ዘላለም፣ በወቅቱ የተፈጸመውን ቃጠሎና ውድመት በበላይነት ሲመራና የወንጀሉን እውነተኛ አፈጻጸም ለማስቀየር ሲሞክር እና የአጣዬ ከተማ ዋና ተጠያቂውም ነበር፣ ሆኖም ኮማንደር ሞገስ ግን በታላቅ ጽናት ተቃውመውታል! "የፈረሰውና የተቀጠለው ህዝቤ ነው፤ የደም መዝገብ በውሸት ሊደፈቅ አይገባም!" በማለት የህዝባቸውን እንባና በደል ለመሸፈን ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። ​ነገር ግን እውነትን በመናገራቸውና ለወገናቸው ፍትህ በመቆማቸው የተከፈለው ዋጋ እጅግ ከባድና ልብ የሚሰብር ነበር። ከዚያች ሰዓት ጀምሮ በኮማንደር ሞገስ ላይ የበቀልና የጫና እጁን የዘረጋው ይህ አካል፣ እውነትንና ፍትህን በማሳደድ የበደልና እንግልት እርምጃውን እስከ ሸዋሮቢትና ደብረ ብርሃን ድረስ ተከተላቸው። ​በመጨረሻም ይህ ፀረ-ሸዋ አካል የአጣዬውን ጀግና መሪ ኮማንደር ሞገስን ከአማራ ፖሊስ መረጃ ሀላፊነታቸው "የፋኖ ዘመድ/ቤተሰብ ነው" የሚል ሰበብ በማቅረብ በግፍ ከስራቸው አባረራቸው፤ አገዳቸውም። ​ዛሬ ላይ ይህ ለህዝብና ለእውነት ያደረ የህዝብ ልጅ፣ ለሀገር ያበረከተው ታማኝ አገልግሎት ተረስቶ፣ የመንግስት ስራውን ትቶ በደብረ ብርሃን ከተማ በግል ስራው ላይ ቢሰማራም፣ አሁንም ድረስ በእሱና በቤተሰቡ ላይ የሚደረገው መንገላታትና የስነ-ልቦና ጫና አልቆመም። ለህዝባቸው መቆማቸውና በሸዋ ህዝብ ላይ ከተሸረበው የውድመትና የመዝገብ ማደፈን ሴራ ጋር አለመተባበራቸው፣ ዛሬ ላጋጠማቸው እንግልትና በደል ዋና ምክንያት ሆኗል። ሁሌም አዲስ መርጃ እንዲደርሳችሁ የቴሌግራም ፒጃችን ይወዳጁን!! https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

ታዳጊዋ አንሻ ሰይድ  ያኔ😭😭😭

ሰላም ቤተሰብ አዲሱ ፒጃችን ይወዳጁን፦ https://www.facebook.com/share/1PujpCN5d4/

ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ እና ለ5ቱም ዕዎችጉዳዩ፡- የዕች ስም ማስተካከልን ይመለከታል!! ​ከላይ በጉዳዩ ለመግለጽ እንደተቻለው የአፋንን ወታደራዊ የአደረጃጀት መምሪያ ደንብ ከድርጅቱን የሥራ-ድርቀት ለማስተካከል ከሃገሮች አውራጅ ጀምሮ የዕች፤የኮር እና የክፍል መር ከሰራዊታዊ መምሪያዎች የመሠረታዊ አደረጃጀት መመሪያ ደንብ ፅሁፍ ላይ እንዲውል አሳቢነት እንትንአለን። የአፋንን ወታደራዊ አደረጃጀት ከድርጅቱ ዓላማ፤ ከዕብ፤ ከሰራዊታዊ መምሪያ እና የተሰማራበት መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት አሁኑ ላይ የተደረገውን የሰራዊት ደረጃን በሚመጥን ሁኔታ ጥንካሬ እና ዓለም አቀፋዊ የወታደራዊ አደረጃጀት መመሪያዎች መመሪያዎች መሠረትነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የድርጅቱን አደረጃጀት ግልፅ እና ጥራት ያለው ዕዝና ስንክስት ለማስፈጠር አብሏል፡- ስለሆነም የሰራዊቾችዎ የዕች፤የኮር እና የክፍል መር ሰራዊትን እንዲሁም አጠቃላይ የድርጅቱን የአደረጃጀት መመሪያ ደንብ ተግባራዊ እንዲሆን እየሰላሰን የአፋንን የዕች ስም ከዕለት 12/12/2018 ዓ/ም ጀምሮ ከዚህበታች በመመሪያው እንደሚመጣ ጥብቅ መመሪያ ሰጥተን መሆኑን እናሳውቃለን፡- ​ቀድሞአሙ አመለ-ር ወሎ ቤ/አልዓል ፅ/መ \rightarrow ሚሊሻ 1ኛ ዕች ​ቀድሞአሙ አመለ-ር ጎጃም ጠቅላይ ሣ/ት ተምሮዕስ ፅ/መ \rightarrow ተምሮዕስ 2ኛ ዕች ​ቀድሞአሙ አመለ-ር ጎንደር ጠቅላይ ሣ/ት በለ ሃላቶ ፅ/መ \rightarrow በለ ሃላቶ 3ኛ ዕች ​ቀድሞአሙ አመለ-ር ዎልቃይት ፅ/መ \rightarrow ዎልቃይት 4ኛ ዕች ​ቀድሞአሙ አመለ-ር የሸዋ ጠቅላይ ሣ/ት አሳምነው ፅ/መ \rightarrow አሳምነው 5ኛ ዕች በመባል የተሰየመው. ሲሆን የዕች ስምም ሆነ የሚለጁ አመለ-ር ማስተካከል እንዲፈጸሙ በጥብቅ በጥብቅ መመሪያ አናሳስባለን።

ዲሽቃ ምድብተኛው እና ዋናብሬን ተኳሹ እንዲሁም የቀበሌ አስ/ሪው ፋኖን ተቀላቅለዋል ብልሆቹ እራሳቸውን እያተረፉ ነው """""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""" ........ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም በዛሬው እለት በፋኖ ከፍተኛ ብትር ያረፈበት መከላከያ የ117ኛ ክፍለ ጦር አመራር እና አባላት እየከድ ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉ ነው፦ 1.ጌታቸው ቢረጋ...117ኛ ክፍለ ጦር ዲሽቃ ምድብተኛ 2.አብድረህማን መሀመድ ...117ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሬጅመንት ዋና ብሬን ተኳሽ 3.ያሬድ ሰሀሞን...ከ25ኛ ክ/ጦር መከላከያ 4.አብድ ተገኑ......ከ25ኛክ/ጦር መከላከያ 5.እግዜሩ መሌ...ፓራ ኮማንዶ ወደ74ኛክ/ጦር 6.ስማቸው ይበልጣል....ሚሊሻ ከፈለገ 7.ይንገስ አየነው ...ሚሊሻ የቀበሌ ሊቀመንበር ሆኖ ሲያገለግል የቆየው ወደ 74ኛክ/ጦር ከእነ መሉ ትጥቃቸው 201ኛ ኮር 54ኛእና 74ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን በአመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት