ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 923
Підписники
+3224 години
+3727 днів
+36630 днів
Архів дописів
ዲሽቃ ምድብተኛው እና ዋናብሬን ተኳሹ እንዲሁም የቀበሌ አስ/ሪው ፋኖን ተቀላቅለዋል ብልሆቹ እራሳቸውን እያተረፉ ነው
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
........ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት በፋኖ ከፍተኛ ብትር ያረፈበት መከላከያ የ117ኛ ክፍለ ጦር አመራር እና አባላት እየከድ ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉ ነው፦
1.ጌታቸው ቢረጋ...117ኛ ክፍለ ጦር ዲሽቃ ምድብተኛ
2.አብድረህማን መሀመድ ...117ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሬጅመንት ዋና ብሬን ተኳሽ
3.ያሬድ ሰሀሞን...ከ25ኛ ክ/ጦር መከላከያ
4.አብድ ተገኑ......ከ25ኛክ/ጦር መከላከያ
5.እግዜሩ መሌ...ፓራ ኮማንዶ ወደ74ኛክ/ጦር
6.ስማቸው ይበልጣል....ሚሊሻ ከፈለገ
7.ይንገስ አየነው ...ሚሊሻ የቀበሌ ሊቀመንበር ሆኖ ሲያገለግል የቆየው ወደ 74ኛክ/ጦር ከእነ መሉ ትጥቃቸው 201ኛ ኮር 54ኛእና 74ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን በአመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የእውነትና የፍትህ ዋጋ፡ በአጣዬና በሸዋ ህዝብ መከራ ላይ ያልተደራደሩት የኮማንደር ሞገስ ባዩ እንግልት!!
አንድ ህዝብ መከራና እንግልት ሲገጥመው፣ ከጎኑ ቆሞ በታማኝነት ማገልገል የሁልጊዜም የሞራልና የሙያ ግዴታቸው ያደረጉ ጥቂት የህዝብ አለኝታዎች አሉ። ከእነዚህ መካከል ህዝባቸው ሲበደልና ሲቃጠል ዝም ብለው ማየት ያልቻሉት የአጣዬው ጀግና መሪ ኮማንደር ሞገስ ባዩ አንዱ ናቸው።
ሸዋሮቢትና አጣዬ ከ14 በላይ በእሳት ሲያሩ፣ የህዝብ ሰደድና የእናት እንባ እያቃጠለ በነበረበት ያንን ጥቁር ወቅት፣ የፌደራል ፖሊስ ምርመራ ሀላፊ ሆኖ መዝገብ ሲገልጥ የነበረው፣ ትውልዱ የወሎና የኦሮሞ ድብልቅ የሆነው አሁን ወደ ፌደራል ፖሊስ የተመለሰው ፀረ-ሸዋው ኮሚሽነር ዘላለም፣ በወቅቱ የተፈጸመውን ቃጠሎና ውድመት በበላይነት ሲመራና የወንጀሉን እውነተኛ አፈጻጸም ለማስቀየር ሲሞክር እና የአጣዬ ከተማ ዋና ተጠያቂውም ነበር፣ ሆኖም ኮማንደር ሞገስ ግን በታላቅ ጽናት ተቃውመውታል! "የፈረሰውና የተቀጠለው ህዝቤ ነው፤ የደም መዝገብ በውሸት ሊደፈቅ አይገባም!" በማለት የህዝባቸውን እንባና በደል ለመሸፈን ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ።
ነገር ግን እውነትን በመናገራቸውና ለወገናቸው ፍትህ በመቆማቸው የተከፈለው ዋጋ እጅግ ከባድና ልብ የሚሰብር ነበር። ከዚያች ሰዓት ጀምሮ በኮማንደር ሞገስ ላይ የበቀልና የጫና እጁን የዘረጋው ይህ አካል፣ እውነትንና ፍትህን በማሳደድ የበደልና እንግልት እርምጃውን እስከ ሸዋሮቢትና ደብረ ብርሃን ድረስ ተከተላቸው።
በመጨረሻም ይህ ፀረ-ሸዋ አካል የአጣዬውን ጀግና መሪ ኮማንደር ሞገስን ከአማራ ፖሊስ መረጃ ሀላፊነታቸው "የፋኖ ዘመድ/ቤተሰብ ነው" የሚል ሰበብ በማቅረብ በግፍ ከስራቸው አባረራቸው፤ አገዳቸውም። ዛሬ ላይ ይህ ለህዝብና ለእውነት ያደረ የህዝብ ልጅ፣ ለሀገር ያበረከተው ታማኝ አገልግሎት ተረስቶ፣ የመንግስት ስራውን ትቶ በደብረ ብርሃን ከተማ በግል ስራው ላይ ቢሰማራም፣ አሁንም ድረስ በእሱና በቤተሰቡ ላይ የሚደረገው መንገላታትና የስነ-ልቦና ጫና አልቆመም።
ለህዝባቸው መቆማቸውና በሸዋ ህዝብ ላይ ከተሸረበው የውድመትና የመዝገብ ማደፈን ሴራ ጋር አለመተባበራቸው፣ ዛሬ ላጋጠማቸው እንግልትና በደል ዋና ምክንያት ሆኗል።
ሰላም ቤተሰብ የብልፅግናው ስርዓት ትናንት የፊስቡክ አካውንታችን ላይ እገዳ ስለጣለ አዲሱ ፒጃችን ይወዳጁን!!
https://www.facebook.com/share/r/19HiCVEn4a/
የጀግኖች መስዋዕትነት ለአንድነታችን መጠናከርና ለህዝባችን ነጻነት መረጋገጥ ጉልበት ሆኖ ይቀጥላል!
ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም
በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ
የአማራ ህዝብ የሚያካሂደው የህልውና ትግል ማህበረሰባዊ፣ ታሪካዊና ፖለቲካዊ መብቶቹን፣ ማንነቱን እንዲሁም የደህንነት ዋስትናውን ለማስከበር የሚደረግ ሁለገብ እንቅስቃሴ ነው።
ይህ ትግል በተለያዩ ጊዜያት በህዝቡ ላይ የተፈጸሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን፣ መፈናቀሎችን እና ስልታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ገለልተኝነትን ለመመከት ያለመ ሲሆን፣ በዋናነት የእኩልነት፣ የፍትህ፣ የታሪካዊ ርስት መከበር እና በገዛ ሀገሩ በሰላምና በክብር የመኖር መብቱን ማረጋገጥን ማዕከል ያደረገ ነው።
በዚህ ፍትሐዊ ትግል ውስጥ አርበኛ ታርቆ ከበደ እና አብረውት የተሰለፉት የቁርጥ ቀን አርበኞች የተቀናጀ የህልውና ውጊያ እና ስትራቴጂያዊ አመራር በመስጠት የላቀ የውጊያ ብቃት፣ የደፈጣ ስልት እና የጽናት አርአያነታቸውን ያስመሰከሩ የወታደራዊ መስዋዕትነት ተምሳሌቶች ናቸው።
አርበኛ ታርቆ ከበደ የግል ህይወቱን፣ ስራውን እና ቤተሰቡን ወደ ጎን በመተው ሙሉ በሙሉ ለህዝቡ ህልውና ሲል በግንባር ቀደምትነት ተሰልፎ ተዋግቷል፣ አዋግቷል።
የሜዳ ላይ ግዳጅን ከመወጣት ባሻገር አሃዶችን በማደራጀት፣ የስነ-ስርዓትና የፍትህ የበላይነትን በማረጋገጥ፣ የሰራዊቱን የስነ-ልቦና የበላይነት በመገንባት እና ፈታኝ የመሬት አቀማመጦችን ለታክቲካዊ ብልጫ በመጠቀም የጠላትን እንቅስቃሴ የመግታትና የማክሸፍ የላቀ የአዛዥነት ሚናውን ባለፉት ሦሥት አመታት ያለመታከት መርቷል። በወታደራዊ ውሎው፣ በአመራርነቱና በህዝባዊ ደጋፍ እና ግንባታ ረገድ ያሳየው ቁርጠኝነትና የከፈለው ውድ ዋጋ በታሪክ ማህደር የማይረሳ የጀግንነትና የታማኝነት ማረጋገጫ ሆኖ ይኖራል።
በተጨማሪም በጎንደር አንድነት የአመራርነት ስብጥር ውስጥ የዕዙ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ እና የኪንፋዝ በገላ ታዲዬስ ታንቱ ዋና ወታደራዊ አዛዥ በመሆን የተጣለበትን ኃላፊነት እና ግዳጅ በቅንነት ፣በልበ ሙሉነትና በአስተዋይነት በመወጣት ላይ ነበር።
ይሁን እንጂ የአማራን ብሎም የጎንደርን አንድነት የማይፈልጉ እና ለፀረ-አንድነቶችና ለጠላት ተላላኪ የሆኑ የትግል አረሞች ከጠላት ጋር መረጃ በመለዋወጥ፣ ልዩ ግዳጆችን በመቀበል እና የመግቢያና መውጫ በሮችን በመዝጋት የባንዳነት ጥጋቸውን በማሳየት ይህንን ቅዱስ ህዝባዊ ትግል ለማደናቀፍ ተንቀሳቅሰዋል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከጠላት ጋር በሚደረግ አውደ ውጊያ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳያጋጥመው በጠላት ላይ ድልን ይቀዳጅ የነበረው ይህ ጀግና አርበኛ፣ ዛሬ ግን በነዚህ ተላላኪዎችና ፀረ-አንድነት ግለሰቦች ሴራ ምክንያት ብርቱ ዋጋ ከፍሏል።
ስለሆነም እኒህ ፀረ አንድነት ግለሰቦች ጠላት በሚሰጣቸው የክህደት መግደያ ኮድ እና መመሪያ መሰረት ከበባና ጥቃት እንዲፈጸምበት በማስተባበርና በመዝመት ጭምር ህዝባችን፣ ሰራዊታችን እና ደጋፊዎቻችን አንገት እንዲደፋ ሙከራ በማድረግ ላይ ግንባር ቀደም ሆነው ሰርተዋል።
በአርበኛ ታርቆ ከበደና ጓዶቹ ላይ የተፈጸመው የባንዳነት ድርጊት በአንድነታችን ላይ የተቃጣ ትልቅ ፈተና ቢሆንም፣ በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ግን የጀግኖቹን ደም በከንቱ የሚያስቀር አይደለም። ዕዙ የጎንደርን ህዝብ አንድነት ለመሸርሸር፣ የትግሉን መስመር ለማሳት እና በወንድሞቻቸው ላይ እጃቸውን ባነሱ ማንኛቸውም ፀረ-አንድነት ግለሰቦች ላይ ያለ ምንም ማወላወል አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ ሲሆን፣ የአርበኛ ታርቆ ከበደ እና የባልደረቦቹ መስዋዕትነት ለአንድነታችን መጠናከርና ለህዝባችን ነጻነት መረጋገጥ ጉልበት ሆኖ ይቀጥላል።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ!
"በኢትዮጲያ የፖለቲካ ሥርዓት ለውጥ ሳይደረግ በሀገሪቱም ሆነ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም ሊመጣ አይችልም" አርበኛ አስረስ ማረ
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የፖሊት ቢሮ አባል አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ በዓለም አቀፉ ‹The Africa Report› ጋዜጣ ላይ ባስነበቡት ሰፊና ጥልቅ መጣጥፍ፣ የፋኖ የህብረ-ብሔር ተጋድሎ በአዲስ አበባ ያለውን የዐቢይ አሕመድ አገዛዝ እንዴት እግር መንገዱን እንዳሳጣውና በአዲስ አበባ የፖለቲካ ሥርዓት ለውጥ ሳይደረግ በሀገሪቱም ሆነ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም ሊመጣ እንደማይችል በዝርዝር አስረድተዋል።
አርበኛ አስረስ ማረ በመጣጥፋቸው እንደገለጹት፣ እሳቸውን ጨምሮ ፋኖ መሳሪያ ለማንሳት የተገደደው በአዲስ አበባ ባለው የፌደራል መንግሥት በአማራ ሕዝብ ላይ የተደቀነውን የህልውና ሥጋት ለመመከት ነው። ሕዝቡ የታጠቀ ትግል ውስጥ ከመግባቱ በፊት በዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እንዲቆም የሰላም ጥሪዎችን ቢያቀርብም አገዛዙ ሙሉ በሙሉ ወደ ጎን ብሎታል። ሰላማዊ መንገዶች በዘጋጉበትና መንግሥት ዜጎችን የመጠበቅ ግዴታውን ባጣበት ወቅት፣ መመከት ብቸኛ የህልውና መንገድ የሚሆን ሲሆን፣ ድርጊቱም በሞራልም ሆነ በሕግ ደረጃ ሙሉ በሙሉ አሳማኝና ሕጋዊ ነው። ትግሉም ከግል ጥቅም ወይም ከፖለቲካ ስልጣን ፍላጎት የመነጨ ሳይሆን ከአስገዳጅ የህልውና ሁኔታ የተወለደ እንደሆነ አብራርተዋል።
የቅርብ ጊዜው የፋኖ እንቅስቃሴ የፕሪቶሪያው ስምምነት ውጤት እንደሆነ አድርገው የሚያቀርቡ ተረኮች የተሳሳቱና የሕዝቡ ቅሬታ ከስምምነቱ በፊት የነበሩ ናቸው ያሉት አርበኛ አስረስ፤ አገዛዙ በአማራ ሕዝብ ላይ የጦርነት አዋጅ ካወጀ በኋላ፣ ፋኖ ባለው ነገር፣ ከጠላት በሚማርከው መሣሪያና በሕዝባዊ ደጋፊነት የህልውና ተጋድሎውን ጀምሮ ዛሬ ላይ ሊበገር የማይችል ግዙፍ ኃይል መሆን መቻሉን ገልጸዋል።
በመጣጥፉ እንደተመላከተው፣ ፋኖ ለሚያደርገው የህልውና ትግል አሳማኝና ሕጋዊ ምክንያት ያለው ሲሆን፣ የአገዛዙ ኃይሎች ግን በገዛ ሕዝባቸው ላይ ጦርነት የከፈቱ በመሆናቸው ግልጽ የስትራቴጂ ዓላማ የላቸውም። የገዛ ሕዝቡን ህልውና ለማስጠበቅ በሚዋጋው ፋኖ እና ጨካኙን አገዛዝ ሥልጣን ላይ ለማቆየት በሚዋጋው የአገዛዙ ኃይል መካከል ያለው የሞራልና የፅናት ልዩነት ሰፊ በመሆኑ፣ የአገዛዙ ሰራዊት የማሸነፍ ፍላጎትና አቅሙ እየተሸረሸረ፣ መሣሪያቸውን እየጣሉ እጅ የመስጠት ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል ብሏል።
ፋኖ በተበታተነ መልኩ ይደረግ የነበረውን ምከታ አሁን ላይ ወደ ተደራጀና የተቀናጀ ከፍተኛ የውጊያ ኃይል ቀይሮታል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) መመሠረቱም የስትራቴጂክ ዕቅድና የወታደራዊ እርምጃዎችን ቅንጅት ያሳደገ ሲሆን፣ አገዛዙ የተጠቀማቸው ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎች፣ ድሮኖች፣ የውጊያ አውሮፕላኖች፣ ቢኤም (BM) ሮኬቶችና የሜካናይዝድ ክፍሎች ወታደራዊ አሸናፊነትን ሊያጎናጽፉት አልቻሉም፤ የቴክኖሎጂ የበላይነት ብቻውን በህልውና ትግል ላይ ስኬትን ሊያረጋግጥ እንደማይችል ማረጋገጫ ሆኗል።
ባለፉት ሦስት የጦርነት ዓመታት፣ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) ባለሙያዎችና አቅሞች በቀጥታ በተሳተፉበት መልኩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሺዎች የሚቆጠሩ የድሮንና የአየር ጥቃቶችን የፈጸመ ሲሆን፣ ጥቃቶቹ በሙሉ ማለት ይቻላል የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰቪሎችንና እንደ ትምህርት ቤቶችና ጤና ተቋማት ያሉ ሕዝባዊ መሠረተ ልማቶችን ኢላማ ያደረጉ ሽብርተኝነትና ጥላቻ የታከለባቸው ነበሩ ሲል አርበኛ አስረስ ማረ በሰፊው አብራርተዋል።
አገዛዙ ጾታዊ ጥቃትን፣ ረሃብንና በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እንደ የጦር መሣሪያ በመጠቀም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግን በስርዓት የሚጥስ ሲሆን፣ በተቃራኒው ፋኖ የጄኔቫ ኮንቬንሽን መመሪያዎችንና የዓለም አቀፍ ሕግጋትን እንደሚያከብር አርበኛ አስረስ አስታውቀዋል።
አገዛዙ ሥልጣኑን ለማስቀጠል ሲል ውዥንብርን፣ ጦርነትን፣ የብዙኃን እስርንና ከፋፋይ ንግግሮችን እንደ መሣሪያ ይጠቀማል። ሀገሪቱ ወደ ሰላም በቀረበች ቁጥር ጦርነትና አለመረጋጋትን ዳግም የሚጭረው አገዛዙ፣ የሞራልና የሰብዓዊነት መሠረታዊ መርሆዎችን ችላ በማለት፣ የሕዝብ ውክልና የሌላቸውን ሕዝባዊ ተቀባይነት የሌላቸው ምርጫዎችና የውሸት ብሔራዊ የምክክር መድረኮችን በማዘጋጀት ሕጋዊ መስሎ ለመታየት ይሞክራል።
በፋኖ በኩል በደረሰበት ከፍተኛ ወታደራዊና ግዛታዊ ስብራት፣ ከትግራይ ክልል ጋር ባለው የሻከረ ግንኙነት፣ በኦሮሚያና በሌሎች አካባቢዎች ባሉ ግጭቶች፣ እንዲሁም በዲፕሎማሲያዊና በሕጋዊነት ቀውስ ምክንያት የአገዛዙ ሥልጣን ላይ የመቆየት እድል አብቅቶለታል ሲል አርበኛ አስረስ ማረ በእርግጠኝነት አስቀምጠዋል።
የዐቢይ አሕመድ አገዛዝ አጥፊና ሀገራዊ ሽብርተኝነት እንቅስቃሴው ከኢትዮጵያ ወሰን አልፎ፣ በሱዳን እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ጦርነት የፈጣን ደህንነት ኃይልን (RSF) በመደገፍና ከአጎራባች ሀገራት ጋር አላስፈላጊ ፍጥጫ በመፍጠር ለቀይ ባሕርና በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ትልቅ የደህንነት ሥጋት ደቅኗል።
የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) ለአገዛዙ የድሮን፣ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ድጋፍ በመስጠት በዜጎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ያደረገችው ጣልቃ ገብነት፣ በሕዝብ ታክስ የተገነባውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሽብር መሣሪያ ያደረገው ሲሆን፣ ይህ አቋሟ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ያላትን የረጅም ጊዜ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑ ተመልክቷል።
በመጨረሻም፣ አርበኛ አስረስ ማረ እንደገለጹት አገዛዙ ሥልጣን ላይ የመቆየት እድሉ ሙሉ በሙሉ ያበቃለት በመሆኑ፣ ከአገዛዙ ውድቀት በኋላ የሚመሠረተው የሽግግር ሂደት ሁሉንም ወገኖች ያካተተ፣ ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ፣ የዜጎችን መብት የሚያስከብርና ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረት የሚጥል መሆን አለበት። ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ሊመጣ የሚችለው በዚህ መንገድ ብቻ እንደሆነ አበክረው አስንበበዋል።
ኢትዮ 251 ሚዲያ
በጣም ብዙ ተከታይ ያለው ነባሩ የፌስቡክ ገፄ ስለተዘጋ ይህንን ገፅ share እንድታደርጉ ትብብራችሁን እጠይቃለሁ!! የጀግናው ወንድማችን ነው ይወዳጁት!!
https://www.facebook.com/mesert.temesgen.50
#አፋብን ቢዛሞ አንሻሰይድ ዕዝ ሰበር የድል ዜና!!!
👉24 ፓትሮልን ጨምሮ ተሽከርካሪ
👉75 ጥቁር ክላሺ እደታሰረ አዲስ
👉 ካስክሬን የተለቀመ 196 ክላሽ እኮቭ
👉ሁለት(2) ብሬን
👉ሁለት(2) ስናይፐር
👉ሶስት(3) ኩንታል ብር
👉አንድ(1) የሻለቃ አመራርን ጨምሮ በመቶዎች
የሚቆጠሩ የተደመሰሰ
👉አንድ(1)የሺ አለቃ ምክትል ጨምሮ በድምሩ 10 የተማረኩ
👉ስድስት(6) መገናኛ
👉3ሺ500 የድሽቃ ተተኳሽ
👉9ሺ800 የብሬን ተተኳሽ
👉14ሺና ከዚያ በላይ ለመቁ ጠር የሚያዳግት የክላሽ
ተተኳሽ
👉በርካታ F1ቦብ፣ትጥቆች ካዝና እድሁም የተለያዩ ወታደራዊ ሻንጣዎች እና ቁሳቁሶች የተማረኩ ናቸው።
የአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!!
+1
ንስሮች ስራቸውን ቀጥለዋል መሀል ከተማ ሞጣ በመግባት #_3ሚላሻወችን በማስወገድ ክላሽ ይዘው መጥተዋል።
►►►►►►►►►►►►►►►►►►
....... ነሐሴ13/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ልዩ ቦታው ሞጣ ሆስፒታል አካባቢ ምከረው ምከረው እንቢ ካለ መከራ ይምከረው ነው እና በተደጋጋሚ በከተማው ህዝብ ላይ ከስርአቱ አሽከሮች ጋር በመመሳጠር የከተማውን ሰላማዊ ሰርቶ አዳሪ ህዝብ ምክኒያት በመፍጠር ዝርፊያ እና አንግልት ሲፈፅሙ እና ሲያስተባብሩ የነበሩ ሆድ አደር የሚሊሻ አባላት እስከወዲያኛው ተሸኝተዋል።
1.ጌታ ዑስማን.........ሚሊሻ
2.ይማም.......ሚሊሻ
3.ትዋ.... ...ሚሊሻ ለከርሳቸው ብለው አማራን ከድተው ለብልፅግና ሲያጎበድዱ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት በንስሮች ተሸኝተዋል አሁንም ከዚህ ድርጊታቹህ የማትቆጠቡ ከሆነ በቀጣይም የተጠናከረ እርምጃችን ይቀጥላል በማለት ይኸን ድንቅ ኦፕሬሽን የሰሩት #_ፈንታሁን_ጥጋቡ ተሾመ አጃነው እና ከፋለ በለጠ ሲሆኑ እንደ አማራ እንድንጠፋ ስለሆነ የተፈረደብን ወደ ትክክለኛ ማንነታቸህ ተመለሱ ኑ የሚል ጥሪያችን እናቀርባለን።
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ስናን ወረዳ፤ ደብረዘይት ከተማ መሽጎ የነበረው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊትና ካድሬ ሙሉ በሙሉ ተደመሰሰ!
ነሐሴ 13/ 2018 ዓ.ም
ዛሬም፣ ከሰሞኑን ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ወደ ስናን ወረዳ እየመራ ይዞት ከገባው 6ኛ ዕዝ፣ 10ኛ ክ/ጦር ቀሪ ሰራዊት፣ በርካታ ሚሊሻና የአገዛዙ ቅጥረኛ ካድሬዎች፤ በስናን ወረዳ፣ ደብረዘይት ቀበሌ ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል።
አፋብን፤ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 206ኛ ኮር፣ 14ኛ ና 24ኛ ክ/ጦሮች ንጉስ ተክለኃይማኖት ሻለቃ፤ ስናን አባጅሜ ሻለቃና የ14ኛ ክ/ጦር ቃኝና መሃንዲስ በጥምረት ባካሄዱት ፈጣን ኦፕሬሽን፣ የአገዛዙ ሰራዊት፣ ሚሊሻና ካድሬው ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተደምስሷል።
ከተደመስሱት ካድሬዎች መካከል ያረጋል አበራ/የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ኃላፊ፣ እንየው ታደገ /የስናን ወረዳ የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም በስም ያልተለዩ ሌሎች የአገዛዙ አገልጋዮችና ወታደራዊ አዛዦች፣ ዛሬ ማለዳ በፋኖ ጥምር ጦር በደረሰባቸው ፈጣንና ጠንካራ ምት ተደምስሰዋል።
ይህ የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት የአካባቢውን ማኀበረሰብ በቡድንና በከባድ መሳሪያ እየደበደበ ንፁሃንን ሲገድል፣ ሲዘርፍና ሲያሰቃይ ቆይቷል። በተጨማሪም በእድሜ የገፉ አካላትን ጨምሮ ሰላማዊ ኗዋሪውን በኃይል እያፈሰ ለአገዛዙ የእርስ በእርስ ጦርነት ሲማግድ የነበረ ነው።
ዛሬ ጠኋት በፋኖ ጥምር ጦር በደብረዘይት ቀበሌ በተወሰደው ፈጣን እርምጃ ከ 20 ያላነሱ በእጅ ሲማረኩ፣ የተቀረው ከምሽግ ሳይወጣ ባለበት ተደምስሶ ትጥቁን በሙሉ አስረክቧል።
ብሬኖች፣ በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የክላሽና የቡድን መሳሪያ ተተኳሾችና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች በምርኮ ገቢ ተደርገዋል።
መረጃው የቴዎድሮስ ዕዝ፤ 206ኛ ኮር፤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
በከበባ ለማፈን የመጣው የጠላት ኃይል በቆረጣ ጥቃት ድባቅ ተመታ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋግሹም ብርጌድ በዋግኸምራ ዞን ደሐና ወረዳ አዚላ ቀበሌና ዙሪያው በከበባ ለማፈን የመጣውን የጠላት ኃይል ባልተጠበቀ የቆረጣ ጥቃት ድባቅ መታው።
ነሐሴ 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የሁለት ቀን ውጊያ፣ የብርጌዱ አባላት የአካባቢውን መልከዓ ምድር በመጠቀም በወሰዱት የቆረጣ እርምጃ፦
12 የጠላት ኃይል ሲደመሰስ፣
ከ 17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል።
በፋኖወች ምት ክፉኛ የተበሳጨዉ የጠላት ኃይል በአካባቢው በሚገኙ ንጹሃን አርሶ አደሮችና ህፃናት ላይ ጥቃት ማድረሱና የህዝብ ንብረት ሲዘርፍ ዉሏል ሲል የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ነሃሴ 13/2018 ዓ.ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ማዕከል 3 ከተወርዋሪ ጦር አባላት ጋር የውይይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ!
ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም
የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ማዕከል 3 ከተወርዋሪ ጦር አባላት ጋር የውይይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል። በዚህ መድረክ ላይ በማዕከል 3 የተመደቡት የዕዙ ግብረ ኃይል አስተባባሪ እና የዕዙ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ተሾመ አበባው፣ የዕዙ ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በላይ ዘለቀ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ከተወርዋሪ ሠራዊቱ ጋር ተወያይተዋል።
በመድረኩ በዕዙ ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አርበኛ መቶ አለቃ ገዳም ካሳ እና በዕዙ ፕሮጀክት ቀረጻ እና አስተዳደር ኃላፊ አርበኛ ባንቴ ጌትነት አቅራቢነት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ተሰጥቷል። ውይይቱም ባሳለፍናቸው የትግል ሂደቶች ባጋጠሙ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች፣ የጎንደር አንድነት ከተበሰረ በኋላ እየተከናወኑ ባሉ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ተግባራት፣ አንድነትን ስለማጽናት፣ በአንዳንድ አካባቢዎች አባላትንና ሠራዊቱን ለማደናገር የሚደረጉ ፀረ-አንድነት እንቅስቃሴዎችን ስለመመከት፣ ተቋማዊ አሰራርን በአግባቡ የመከተል አስፈላጊነት እንዲሁም በህዝባዊ አስተዳደር መመሪያዎች ላይ ያተኮረ ነበር።
በመጨረሻም ሕዝባዊ አስተዳደር ፍትህን፣ ተቋማዊ አሰራርን እና የሕዝብ አመኔታን በማጠናከር አንድነታችንን የሚያጸኑ ሥራዎችን መስራት፣ ሠራዊቱ በህግና በሥርዓት እንዲመራ ማድረግ፣ ጥብቅ ዲሲፕሊንን እና የውጊያ ዝግጁነትን ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ ለየትኛውም ወታደራዊ ግዳጅ ራስን ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
