uk
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Відкрити в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Показати більше
2 924
Підписники
+10524 години
+3357 днів
+33630 днів
Архів дописів
አጀብ ነው!! መነሻዋን ሶማሊያ ክልል አድርጋ ጎጃም መርጡለ ማርያም ፣ ፍኖተ ሰላም የተቀጠቀጠችውም የኮሎኔል አዱኛ 71ኛ ክ/ጦር ጎንደር ዳባት፣ ዳባርቅ ፣ አምባ ጊዮርጊስ ላይ ከደረሰባት ከፍተኛ ምት ሳታገግም ወደ ቤተ-አምሐራ ወሎ የተሸጋገረቸው ተቅበዝባዧ አሃድ ፍፃሜዋ ዋድላ ደላንታ ሁኗል። አጀብ ነው!! ጠላት ስትራቴጂካዊ መሸጋገሪያ ኮሊደሮችን ለመዝጋት ያሰማራት የመጀመሪያዋ ክ/ጦር ሙሉ ለሙሉ ተደምስሳለች። ዲሽቃ፣ ብሬን ፣ስናይፐር ፣ ክላሽ ያልታጠቀ የአማራ ወጣት እየታጠቀ ነው። የፌዴራል መረጃና ደህንነት ክፍሉ ጭንቀት እውን ሁኗል አወ እየመጣን ነው--------

#የብልፅግና_ሰራዊት_ዳሽቋል የአብይ አህመድን ስልጣን ለማስጠበቅ እየፎከረ ሆነ ታፍሶ ወደ አማራ ህዝብ ከቀላል መሳሪያ እስከ ከባድና አየር ኃይል መሳሪያዎችን ታጥቆ ፣ የቁም ምሽግ ገንብቶ ለመዋጋት ቢሞክርም በምስሉ እንደሚታዬው በምኒሊክ 1ኛ ዕዝ ዳሽቆ እንዲቀር ተደርጓል። አሁንም አረፈደም እጅ በመስጠት ህይዎታችሁን አትርፉ ሙሉውን ቴሌግራም ቻናሌ ላይ አለ ይወዳጁት!! ጳጉሜ 2018 ዓ.ም #Dave #Amhara

በሕዝባችን ላይ ታሪካዊ ስሕተት ለመሥራት ሕሊናችን አልፈቀደም ያሉ የአገዛዙ ሠራዊት ፋኖን ተቀላቀሉ!!       ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም     በርካታ የአገዛዙ መከላከያ የአየር ወለድ፣ የኮማንዶና የአድማ ብተና አባላት፡ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝን በገፍ እየተቀላቀሉ እደሆነ ተገለፀ። የብልፅግና አገዛዝ ሥልጣኑን ለማስረዘም በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን ደም አፋሳሽ ስርዓትን የተረዱ ሠራዊቶቹ፣ ለእውነትና ለወገናቸው በመወገን ስርዓቱን ለቀው ሕዝባዊ ትግሉን በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል። በመውደቂያ ማማው ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ ስርዓት፣ በግድም በውድም የስልጣኑ ጠባቂ ለማድረግ የጥላቻ ፖሊሲ አስተምሮ ያሠለፋቸው ሠራዊት፣ እኩይ ተግባርን በመጠየፍ "እኛ የሀገር ዘብና የሕዝብ ጠባቂዎች እንጂ የስርዓትሕ ጠባቂ አንሆንም" በማለት ፋኖን በክብር  መቀላቀል ችለዋል። በዚሕም መሠረት፦ 👉 ወደ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር 1.አበባው ሀብታሙ — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና 2.እሱባለው ገነት — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና 3.መብራቱ ጥላዬ — የ31ኛ ሻለቃ መሪ (የአለባቸው አጃቢ)  4.ምትኩ ታይቸው — የ31ኛ ሻለቃ አባል       ✔ ንብረቶች ● (3) ሶሥት ባለ ሁለት እግር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች ● (1) አንድ ሰደፍ ክላሽኮቭ መሣሪያ  ● (165) (መቶ ስድሳ አምስት) የክላሽኮቭ ጥይቶች 👉 ወደ 7ለ70 ክፍለ ጦር የተቀላቀለ 1. ምክትል ፲ አለቃ ማርቆስ በዳሳ -ከ102ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር        ✔ ንብረቶች ● (1) አንድ ክላሽኮቭ መሣሪያ  ● (90) ዘጠና የክላሽኮቭ ጥይቶች ● (1) አንድ የደረት ትጥቅ ● (1) አንድ ወታደራዊ ቦርሳ  👉 ወደ ከሠም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር የተቀላቀሉ 1. ፻ አለቃ አደራጀው አዱኛ- የ112ኛ አ/ወ/ክ/ር/ሻ/መሪ 2. **** የሻበል መሪው ጋርድ     ✔ ንብረቶች ● (2) ሁለት ጥርጥር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች  ● (1) አንድ የደረት ትጥቅ  ● (2) ሁለትF1 ቦምቦች  ● (3) ሶሥት ካዝናዎች  ● (120) መቶ ሃያ የክላሽኮቭ ጥይቶች  ● (1) አንድ ወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ  እነዚሕ ንብረቶች በመያዝ የሕዝብን ትግል ተቀላቅለዋል። በቀጣይም የአገዛዙ ወታደሮች ይህንን ታሪካዊና ህሊናዊ ውሳኔ በመከተል ወደ ሕዝባዊ ኃይሉ እንድትቀላቀሉ፣ ዕዛችን ጥሪውን አቅርቧል።   " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ይህንን የፊስቡክ ፒጅ ይወዳጁት ቤተሰብ ትኩስ አውደ ውጊያ ዜናዎችን ያገኙበታል። https://www.facebook.com/share/19YdKUwHRk/

+4
ተቀበል አይ አማራ እንዲያው ምን ልሁንልህ!!

በዳውንት ግንባር ተራሮች መሸከም ከሚችሉት በላይ በጠላት አስከሬን ተጥለቅልቀዋል‼️ ምንም እንኳን አማራን የማጥፋት ተልዕኮ ተሰጥቶት ወደ ግንባር የገባ ጠላት ቢሆንም ነገር ግን...#የደሀ_ልጅ በዚህ
+3
በዳውንት ግንባር ተራሮች መሸከም ከሚችሉት በላይ በጠላት አስከሬን ተጥለቅልቀዋል‼️ ምንም እንኳን አማራን የማጥፋት ተልዕኮ ተሰጥቶት ወደ ግንባር የገባ ጠላት ቢሆንም ነገር ግን...#የደሀ_ልጅ በዚህ ልክ አልቆ ማየት እጅግ ልብ ይሰብራል። አሁንም አልረፈደም፡ ቀሪው ባስቸኳይ እጁን ሰጥቶ ሕይወቱን ያትርፍ‼️ #ማስታወሻ ኦህዴድ መሩ የብልፅግና ቡድን ልጆቻቸውን አስገድዶ ወደ ውትድርና ወስዶ ላስገደለባቸው እናቶች ክብር ስንል ቀሪውን ምስል ለጊዜው ትተነዋል። ከላይ ያያችሁት ምስል በዳውንት ግንባር ብቻ ከተደመሰሰችው የጠላት ክፍለጦር ሠራዊት መካከል እጅግ በጣም ጥቂቱን ነው። አገዛዙ በግዳጅ ውትድርና አስገብቶ ትውልዱን ምን ያህል እንዳስጨረሰው ትረዳላችሁ። #ማሳሰቢያ ነገሮች እየከበዱ ነው ከአገዛዙ ጎን የተሰለፋችሁ እጅ በመስጠት ህይዎታችሁን አትርፉ‼️ ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም ሙሉውን ቴሌግራም ቻናላችን ይወዳጁን!! https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

ሰበር ዜና! ጀብደኛው ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በዋድላ-ደላንታ-ዳውንት ግንባር የአገዛዙን አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ደመሰሰ! በምርኮ የተገኘ፦ ✅ አራት (4) ዶሽቃ ✅ ዘጠኝ (9) ብሬን ✅ ሰባት (7) ስናይፐር ✅ ሁለት(2) አርፒጂ ✅ ከሶስት መቶ (300) በላይ ክላሽንኮቭ ✅እንዲሁም ከመቶ ሃምሳ (150) በላይ የሰው ሃይሉ ተማረከ! በዚህ ከፍተኛ የግንባር ዉጊያ ወታደራዊ አዛዡ ጨምሮ፤ አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ተደ*ደምስሷል! ይቀጥላል... የጀብዱ ባለቤቶች 16ኛ ኮር(የቀድሞው ደጋው መብረቅ) እና የዕዙ ልዩ ዘመቻ አሃዶች ናቸው። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ጷግሜ: 03/ 2018 ዓ/ም

ሰበር!....የምኒልክ ዕዝ አርበኞች የማረኩትን ዲሽቃ እና ብሬን እንዲሁም የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ቆጠራ ላይ ናቸው። ጠላት ዳሽቆ ቀርቷል። ምሽጎች በጠላት ደም ጨቅይተዋል። ምርኮኛው ወታደር ልክ እንደ
+1
ሰበር!....የምኒልክ ዕዝ አርበኞች የማረኩትን ዲሽቃ እና ብሬን እንዲሁም የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ቆጠራ ላይ ናቸው። ጠላት ዳሽቆ ቀርቷል። ምሽጎች በጠላት ደም ጨቅይተዋል። ምርኮኛው ወታደር ልክ እንደከብት እየተነዳ ነው። የወገንን ልብ የሚያሞቅና በድል ቁንጣን የሚያጨናንቅ በምትኩ ደግሞ ጠላትን ከነ ደጋፊ ኃይሉ የሚያሸብርና እንጦሮንጦስ የሚከት የድል ዜና ከወደ ወሎ ቤተ አማራ እየመጣ ነው። ይጠብቁን

የድል ዜና ዛሬ 03/13/2018ዓ.ም የአፋብን ምንሊክ 1ኛ ዕዝ 155ኛ ክፍለጦር በአርበኛ ጀማል(ብሬን) እየተመራች የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ ጥምር ጦር ተከማችቶ በነበረበት ከላላ ወረዳ ልጓማ እና ቲርቲራ አካባቢ ዶግ አመድ ተደርጓል። የአገዛዙ ጥምር ጦር ከፋኖ ነበልባሎች የደረሰበትን ጠንካራ ጡንቻ መቋቋም ባለመቻሉ ሙት እና ቁስለኛውን በማንጠብጠብ ወደ ከላላ ወረዳ መፈርጠጡ የታወቀ ሲሆን በውጊያው በርካታ የነፍስ ወከፍ እና የቡድን መሳሪያ እንዲሁም የተለያዩ አይነት በርካታ ተተኳሾች በምኒልክ ዕዝ አናብስቶች 15ኛ ኮር 155ኛ ክፍለጦር በምርኮ መግባቱ ታውቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ጷግሜ:-03/ 2018 ዓ/ም

30ኛ ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር በአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት ላይ የደፈጣ ጥቃት ፈፀመ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ303ኛ አሳምነው ኮር  አካል የሆነው 30ኛ ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር የአገዛዙ ሰራዊት ከላሊበላ ወደ ብልባላ ወታደራዊ ሬሽን ለማሳለፍ ሲል ሶርባ ከሚባል ቦታ ላይ ደፈጣ በመጣል የጠላትን ኃይል ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል። ጷግሜ 02/ 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 11:00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 2:00 ሰዓት በተደረገው ትንቅንቅ 26 የጠላት ኃይል ሲደመሰስ 19 ቁስለኞቹን ይዞ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ላሊበላ ሆስፒታል እያሳከመ እንደሚገኝ በደረሱን መረጃዎች ታውቋል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ      ጷግሜ:-03/ 2018 ዓ/ም

ሰበር የድል ዜና ! የአፋብን|ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር በረቀቀ ወታደራዊ ጥበብ በጠመደው ፀረ-ተሽከርካሪ ፈንጅ መተከል ፓዊ ወረዳ መንደር 24 ቀበሌ ልዩ ስሙ ሰኞ ገበያ ከተባለ ቦታ ላይ  የአረመ*ኔውን ብልፅግና አንድ ጋንታ ሙሉ ሠራዊት እና ሙሉ ሎጅስቲክስ የጫነ አንድ የኦራል ተሽከርካሪን ሙሉ በሙሉ አመድ አድርጓል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!

እነ ሞት አፈሪዎቹ የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!     ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አጣዬ አላላ ክላስተር ብርቂቶ ቀበሌ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።  ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል። በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል። ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦ ✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ ✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ ✔  (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች ✔ (2) የውሃ ኮዳዎች ✔ (8) ካዝናዎች ✔ (4) F1 ቦንቦች በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ