uk
Feedback
WANIA TRADING S.C

WANIA TRADING S.C

Відкрити в Telegram

WANIA TRADING S.C is here to empower the Muslim community and create economically influential share company. ዋንያ ትሬዲንግ አ.ማ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማብቃት እና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ የአክሲዮን ኩባንያ ለመፍጠር ነው:: ለበለጠ መረጃ 👇 0935608888 ይደውሉልን

Показати більше
1 160
Підписники
-124 години
-47 днів
-2430 день
Архів дописів
​✨ የምስራች ለሙሉው ኡማ! የ"ዋኒያ ሄልዝ" ይፋዊ ምዝገባ ተከፈተ! ✨ ​አካላዊ ጥንካሬን (Al-Quwwa) ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የጤና እና የአመጋገብ ሱና ጋር ያቀናጀው ልዩ የጤና ጉዟችን አሁን በ
​✨ የምስራች ለሙሉው ኡማ! የ"ዋኒያ ሄልዝ" ይፋዊ ምዝገባ ተከፈተ! ✨ ​አካላዊ ጥንካሬን (Al-Quwwa) ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የጤና እና የአመጋገብ ሱና ጋር ያቀናጀው ልዩ የጤና ጉዟችን አሁን በይፋ ምዝገባ ጀምሯል! ​መንፈሳዊ እና አካላዊ ህይወቶትን በሱና መስመር ለመቃኘት፣ ጥንካሬንና በረካን የተላበሰ አዲስ የህይወት ዘይቤ ለመጀመር ዝግጁ ነዎት? ​🌿 በፕሮግራማችን የሚያገኙት፡ ​🏋️‍♂️ አካላዊ ጥንካሬ (Al-Quwwa): ከሱና ጋር የተጣጣሙ ዘመናዊ የስፖርት እና የአካላዊ ብቃት እንቅስቃሴዎች ​🥗 የሱና አመጋገብ (Prophetic Diet): በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮ ላይ የተመሰረተ ጤናማ የአመጋገብ ስርዓት ​🤍 በረካ ያለው የህይወት ዘይቤ: አካልን፣ አእምሮን እና መንፈስን የሚያነቃቃ ቀጣይነት ያለው ልምድ ​⚠️ ቦታዎች የተወሰኑ ስለሆኑ አሁኑኑ በኦንላይን ወይም በስልክ ይመዝገቡ! ​👉 ለመመዝገብ እና ሙሉ መረጃ ለማግኘት፡ ​📞 ስልክ ቁጥሮች: 0935608888 / 0942133513 ​💬 ቴሌግራም: @Meki999 ​"ጠንካራ አማኝ ከደካማ አማኝ ይበልጥ አላህ ዘንድ ተወዳጅ ነው!" ​#WaniaHealth #PropheticFitness #SunnahLifestyle #RegistrationOpen #የኡማውጤና #አካላዊጥንካሬ #ሱና

​የዛሬው መልዕክት ​"ጥንካሬ የሚገኘው በጡንቻዎች ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ አላህ (ሱ.ወ) በሰጠን ጸጋ ተጠቅመን ራሳችንን ለመለወጥ በምናደርገው ቁርጠኝነት ጭምር ነው። ዛሬ ለጤናህ የምታደርገው ጥንቃቄ
​የዛሬው መልዕክት"ጥንካሬ የሚገኘው በጡንቻዎች ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ አላህ (ሱ.ወ) በሰጠን ጸጋ ተጠቅመን ራሳችንን ለመለወጥ በምናደርገው ቁርጠኝነት ጭምር ነው። ዛሬ ለጤናህ የምታደርገው ጥንቃቄ ለነገው ጥንካሬህ መሠረት ነው።"
የዋኒያ ሄልዝ ኤንድ ፊትነስ መሪ ቃል፦ "ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን በመከተል፣ ነገን በተሻለ ብቃት እና ስኬት ለመቀበል ዛሬውኑ እንዘጋጅ

ዋኒያ ሄልዝ (Wania Health & Fitness) አካላዊ ጥንካሬን (Al-Quwwa) ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) የጤና እና የአመጋገብ ሱና ጋር ያቀናጀ፣ ለኡማው የሚመጥን አዲስ "በረካ ያለው የጤና ጉዞ"
ዋኒያ ሄልዝ (Wania Health & Fitness) አካላዊ ጥንካሬን (Al-Quwwa) ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) የጤና እና የአመጋገብ ሱና ጋር ያቀናጀ፣ ለኡማው የሚመጥን አዲስ "በረካ ያለው የጤና ጉዞ" ይዞላችሁ እየመጣ ነው። ​#WaniaHealth #PropheticFitness #SunnahLifestyle #ComingSoon #የኡማውጤና

photo content

የበደል ጨለማ ክፍል 2 ('የአለም ዋንጫ ጨዋታ' ሲጫወትብን) አለም የምትዘወረው የኢኮኖሚ ሀይሏን እና የስልጣን ዙፋኗን በተቆጣጠረው ሰዎች እጅ ነው። በመዝናኛ ስም የስጦታ እቃ ተለብጠው የሚቀርቡ ሁሉም ማማለያዎች እኛ እንደምናስበው አዝናንተውን ብቻ የሚያልፉ የአንድ ሰሞን የደስታ ድግስ አይደሉም። እነዚህ 'ፌሽታዎች' እልፍ ቢሊዮን ዶላር የተበጀተባቸው ፤ ብዙ የረጅም እርቀት እና የአጭር ርቀት ግብ ያላቸው ፥ የማህበረሰብን ቅርፅ ፣ መልክ እና ማንነት መወሰን የሚችሉ የሰው ልጆችን ወደ ሚፈለገው የመንጋነት (collective un/consciousness) ወይም በግለሰብነት ቁሞ የማሰብን ሀይል የመንጠቅ ውጥኖች ናቸው። የህይወትን ጊዜያዊ ከረሜላ እያስላሱ በሚጣፍጥ የቅፅበታት የጣእም ደሰታ ሱስ አስረው መንፈሳዊነትን እና ታላቅ አላማ ያለው ሰው የመሆንን ግብ የማክሸፍ አላማ ያነገቡ የጥፋት እቅዶችም ጭምር። አለም በዱርዬ ኸሊፋዎች/መሪዎች እጅ ወድቃለች። በመዝናኛ ስም አደንዝዘው ገንዘብን እውቀት እና ጊዜን ከሰው ልጆች ላይ የሚነጥቁ የመጨረሻውን አለም እውነት የካዱ ግባቸው እቺ አለም እና እቺ አለም ብቻ የሆነች፤  ደስታቸው ሴት ፣ አልኮልና ቁማር የሆኑ ህሙማን ሰዎች የሚያዙባት መፈንጫ ሆናለች። - በፊልም የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ስም ስንት የሰውን ተፈጥሯዊ ግብረገብነት የሚንድ መርዛማ ሀሳብ ሳናውቅ ገዝተን ህይወታችን አድርገነዋል? - በሆሊውድ ፊልሞች ሴሰኝነትን እና ቁማርን ፣ በ Netflix ዝሙትን እና ክህደትን አለማምደውናል ፣ በሙዚቃ ግጥሞቻቸው ጥፋትን አስነብንበውናል? የአልባሳት ኢንዱስትሪው በፋሽን ስም የሙስሊም ሴቶችን ጅልባብ እና አብያ ካስጣለ ቆየ። ዛሬ ሴቶች ለሙስሊምነታቸው ምልክት ያህል ፀጉራቸው ላይ ጨርቅ ጣል ያደርጋሉ ሱሪ የመልበስ ወረርሽኝ በሴቶቻችን መሀከል ተስፋፍቷል ፥ ይህን ተከትሎ የመጣው ፈሳድ/ብልሽት ቀላል የማይባል ነው። 'የአለም ዋንጫም' የዚህ በመዝናኛ ስም የሚሸጡ የማደንዘዣ ንግዶች አንዱ እና ከኳስ ጨዋታ የመዝናኛ ገበያዎች ዋነኛውን ድርሻ የሚይዝ በአለም ሀገራት ወዳጅነት ጨዋታ ስም የሚሰራ ማደናገሪያ  ነው። በቃ ትውልድ ላይ ከባድ የበደል ጨለማ ደመና አንዣብቧል። በመለኮት ብርሀን እና በእውነት ቃል እዝነት ይህን ድቅድቅ ፅልመት የሚፋለሙ የኢስላም ቀንዲል ፋኖሶች ፣ የዋህይ እሳት መቀጣጠያ ትውልዶች አስኪፈጠሩ አለም በድንዛዜ እና በስካር ውስጥ ትዋዥቃለች። እንንቃ! ክፍል 3 ይቀጥላል። ኢንሻአላህ ✍️ usmán muŝ

የበደል ጨለማ ክፍል 2 ('የአለም ዋንጫ ጨዋታ' ሲጫወትብን) አለም የምትዘወረው የኢኮኖሚ ሀይሏን እና የስልጣን ዙፋኗን በተቆጣጠረው ሰዎች እጅ ነው። በመዝናኛ ስም የስጦታ እቃ ተለብጠው የሚቀርቡ ሁሉም ማማለያዎች እኛ እንደምናስበው አዝናንተውን ብቻ የሚያልፉ የአንድ ሰሞን የደስታ ድግስ አይደሉም። እነዚህ 'ፌሽታዎች' እልፍ ቢሊዮን ዶላር የተበጀተባቸው ፤ ብዙ የረጅም እርቀት እና የአጭር ርቀት ግብ ያላቸው ፥ የማህበረሰብን ቅርፅ ፣ መልክ እና ማንነት መወሰን የሚችሉ የሰው ልጆችን ወደ ሚፈለገው የመንጋነት (collective un/consciousness) ወይም በግለሰብነት ቁሞ የማሰብን ሀይል የመንጠቅ ውጥኖች ናቸው። የህይወትን ጊዜያዊ ከረሜላ እያስላሱ በሚጣፍጥ የቅፅበታት የጣእም ደሰታ ሱስ አስረው መንፈሳዊነትን እና ታላቅ አላማ ያለው ሰው የመሆንን ግብ የማክሸፍ አላማ ያነገቡ የጥፋት እቅዶችም ጭምር። አለም በዱርዬ ኸሊፋዎች/መሪዎች እጅ ወድቃለች። በመዝናኛ ስም አደንዝዘው ገንዘብን እውቀት እና ጊዜን ከሰው ልጆች ላይ የሚነጥቁ የመጨረሻውን አለም እውነት የካዱ ግባቸው እቺ አለም እና እቺ አለም ብቻ የሆነች፤  ደስታቸው ሴት ፣ አልኮልና ቁማር የሆኑ ህሙማን ሰዎች የሚያዙባት መፈንጫ ሆናለች። - በፊልም የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ስም ስንት የሰውን ተፈጥሯዊ ግብረገብነት የሚንድ መርዛማ ሀሳብ ሳናውቅ ገዝተን ህይወታችን አድርገነዋል? - በሆሊውድ ፊልሞች ሴሰኝነትን እና ቁማርን ፣ በ Netflix ዝሙትን እና ክህደትን አለማምደውናል ፣ በሙዚቃ ግጥሞቻቸው ጥፋትን አስነብንበውናል? የአልባሳት ኢንዱስትሪው በፋሽን ስም የሙስሊም ሴቶችን ጅልባብ እና አብያ ካስጣለ ቆየ። ዛሬ ሴቶች ለሙስሊምነታቸው ምልክት ያህል ፀጉራቸው ላይ ጨርቅ ጣል ያደርጋሉ ሱሪ የመልበስ ወረርሽኝ በሴቶቻችን መሀከል ተስፋፍቷል ፥ ይህን ተከትሎ የመጣው ፈሳድ/ብልሽት ቀላል የማይባል ነው። 'የአለም ዋንጫም' የዚህ በመዝናኛ ስም የሚሸጡ የማደንዘዣ ንግዶች አንዱ እና ከኳስ ጨዋታ የመዝናኛ ገበያዎች ዋነኛውን ድርሻ የሚይዝ በአለም ሀገራት ወዳጅነት ጨዋታ ስም የሚሰራ ማደናገሪያ  ነው። በቃ ትውልድ ላይ ከባድ የበደል ጨለማ ደመና አንዣብቧል። በመለኮት ብርሀን እና በእውነት ቃል እዝነት ይህን ድቅድቅ ፅልመት የሚፋለሙ የኢስላም ቀንዲል ፋኖሶች ፣ የዋህይ እሳት መቀጣጠያ ትውልዶች አስኪፈጠሩ አለም በድንዛዜ እና በስካር ውስጥ ትዋዥቃለች። እንንቃ! ክፍል 3 ይቀጥላል። ኢንሻአላህ ✍️ usmán muŝ

🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባቶች (በዚህ አርእስት ስር የምናየው የመጨረሻ የስነልቦና ፅሁፍ ይሆናል) 6. Hindsight Bias/ 'እንደሚመሆን ታውቆኝ/አውቅ ነበር' መዛባት (ብዬ ወደ አማርኛ መልሼዋለሁ ለጊዜው) (This bias leads people to believe that they would have predicted an outcome after it has already happened.) ይህ ቢያዝ/መዛባት አንድ ነገር ከተከሰተ በኋላ ያ ነገር እንደሚፈፀም ማወቅ ችለን ወይም እንችል እንደነበር ሲሠማን ማለት ነው። ለምሳሌ:- የሆነ ውድድር ስናሸንፍ ቀድመን እንደምናሸንፍ የምናውቅ መስሎ ይሠማናል። ጠይቀን የሆነ ነገር ሲሰጠን ወይም ስንከለከል መጀመሪያውኑ ያንን ድርጊት ቀድመን እናውቀው እንደነበር ሲሰማን ማለት ነው። ('ታውቆኝ ነበር' 😁 የሚሉ ሰዎች ካጋጠሟችሁ የዚህ ቢያዝ ተጠቂ ሊሆኑ ይችላሉ። [ላኩላቸው ይህን ፅሁፍ] ) 🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. stud.) #ስለ_ስነልቦና To join👇 https://t.me/+Axzalt8LOXNiZTY0

የበደል ጨለማ ክፍል 1 አለም ድቅድቅ የበደል ጨለማ ውስጥ ሰጥማለች። መልእተኛው (ሰ.ዐ.ወ) የለኮሱት የህይወት እና የእዝነት ብርሀን ተዳፍኖ መዛግብቶች እና መፃህፍት ውስጥ ተደብቆ ተቀምጧል። ቃሉን የሚያነበንበው እንጂ የሚኖረው ጠፍቷል። ምድር ህልቆ መሣፍርት በሌለው የርዚቅ/የሀብት ማማ ላይ እየተንፈላሰሰች ግን ቢሊየን ሰዎቿ አሁንም በእርዛት ፣ በርሀብ እና በመጠለያ አልባነት ተኮራምተው የስቃይን ፅዋ ይጋታሉ። በታመመው ስርአቷ ሳቢያ የአለም 90 ፐርሰንቱ ሀብት  አንድ ፐርሰንት (1%) የሚሆኑ ሰዎች እጅ ላይ ወድቆ ሌላው ሲጠበስ የሚያሸት ፣ ሲበሉ የሚጎመጅ ፣ ሲያምርባቸው የሚማልል ብቻ ሆኖ በባይተዋርነት እና በባዳነት ምድር ላይ ይኖራል። - ውሀ ተጠምተው የሚሞቱ ሰዎችም የሚሊዮን ዶላር ውስኪ ሲያዳፉ የሚያድሩ ሰዎችም የሚኖሩባት አለም። - በርሀብ የሚሞቱባትም በቁንጣን/በጥጋብ ታመው በየሆስፒታሉ ውሮ ወሸባ የሚባልላቸው ሰዎች የሚኖሩባት አለም። ጫማ ያጡም መኪና በማማረጥ ጭንቀት (stress) ውስጥ ገብተው ባለሙያ ለማማከር የስነልቦና ባለሙያዎችን ደጃፍ ያጨናነቁ ሰዎች የሚኖሩባት አለም። በቃ አለም የኢፍትሀዊነት መናገሻ የበደል ማስፈፀሚቃ ቀጠና ከሆነች ቆይታለች። አሁን "የኢስላም ህግ ነው የአለም የፍትህ ብርሀን" ማለትም የተለመደ የሽንገላ ቃል መስሏል። ቃሉን ሰምቶ የሚያስተጋባ እንጂ ህይወት አድርጎ መስዋዕትነት ከፍሎ ለመኖር የቆረጠ ሰው የለም። ሙስሊሞች ጥልቅ የግብዝነት እንቅልፍ ውስጥ ወድቀናል። በበደል ቆፈን የቀዘቀዘው ልባችን በመለኮታዊው ቃል ፍም እሳት ህያው እስኪሆን ድረስ አካላችን በድን ፥ ኑሯችንም ህይወት አልባ ነው።  የፈጣሪን ቃል ቁርአን እስትንፋሳችን ፥ የመልእክተኛውን የህይወት መርህ ልብሳችን እስካልሆነ ድረስ በዚች ምድር ላይ ውርደትን ጠጥተን ዝቅታን ተግተን ከሰብዓዊነት ያነሰ ህይወትን ለራሳችን እና ለመሰል የሰው ልጆች የምናወርስ የበደል አሸጋጋሪ የአምባገነኖች ገባሪ ሆነን እንቀጥላለን። እንንቃ! ክፍል 2 ይቀጥላል። ኢንሻአላህ ✍️ usmán muŝ

🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባቶች 5. Sunk Cost Fallacy/ ለተከፈለ ዋጋ ሌላ ዋጋ የመክፈል መዛባት (ብዬ ወደ አማርኛ መልሼዋለው ለጊዜው ) (This bias leads individuals to continue an endeavor once they have invested time, money, or resources into it, even if it is clear that the endeavor is no longer beneficial.) ይሄ ቢያዝ አንድ ሰው ለሆነ ነገር ጊዜ ሀብት እና ንብረቱን ፈሰስ ካደረገ በኋላ ያ ነገር እንደማይጠቅመው ቢያውቅም ያሳለፈውን ጊዜ እና ወጪ በማሰብ ብቻ እዛ ነገር ላይ መቆየት ማለት ነው ለምሳሌ:- ምግብ አዘን ባንወደውም ወይ ጠቃሚነቱ ብዙም ያልጎላ ቢሆንም ስለከፈልንበት ብቻ መመገብ። አንድ ስልጠና/ትምህርት ጀምረን እንደማይጠቅመን ብናውቅም ላሳለፍነው ጊዜ እና ላጠፋነወ ገንዘብ ብለን ትምሀርቱን ለመቀጠል መወሰን። የጀመርነው ዶክመንተሪ ባይመቸንም ስለከፈልንበት ብቻ ለመጨረስ መቀመጥ። ኢንሻአላህ ይቀጥላል... 🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. stud.) #ስለ_ስነልቦና To join👇 https://t.me/+Axzalt8LOXNiZTY0

የተረሳው ቋንቋ (እዝነት) .1 መድረክ ትናንት በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል። (አልሃምዱሊላህ) በዚህ ዝግጅትም ሁሉም አቅራቢዎች የተዘጋጁበትን ዘርፍ በላቀ ብቃት ያቀረቡ ሲሆን ከታ
+5
የተረሳው ቋንቋ (እዝነት) .1 መድረክ ትናንት በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል። (አልሃምዱሊላህ) በዚህ ዝግጅትም ሁሉም አቅራቢዎች የተዘጋጁበትን ዘርፍ በላቀ ብቃት ያቀረቡ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ጥሩ ቆይታ ነበራቸው። ይህ ጥበባዊ እና ሁሉን አካታች የመዝናኛ እና የመማማሪያ ዝግጅት ቁጥር ሁለት የተረሳው ቋንቋ (ፍትህ).2 በሚል ርእስ በአላህ ፍቃድ ሞቅ ብሎ በቅርቡ የሚቀጥል ሲሆን የመግቢያ ዋጋውም 250 ብር ሆኗል። አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ ፣ መግቢያ ቲኬቱን ማግኘት እንዲሁም ለኡማው የሚጠቅም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ስልኮች ያናግሩን 0921390122 0912027023 (የቀጣዩን ዝግጅት ሰአት እና ቦታ በቅርብ እናሳውቃለን) የእለቱ ፕሮግራም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች በቅርቡ ለህዝብ ይለቀቃል። ኢንሻአላህ!!

photo content

የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት 🎭✨ የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው
የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1  የመድረክ ዝግጅት 🎭✨ የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው🌟🕌 ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም በነፃ ተጋብዛችኋል!!🎉🙌 📆 ቀን ዛሬ ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል 🕔  ከ አሱር በኋላ ከ10:00 ጀምሮ (በሰአታችን የምንጀምር ስለሆነ በጊዜ እንድትገኙልን በትህትና እንጠይቃለን) 🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ አድራሻ:- 📍 ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ አላማችንን መደገፍ 🥰፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን ☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman ኢንሻአላህ! Telegram channel link https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram 🔗

የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት 🎭✨ የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው
የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1  የመድረክ ዝግጅት 🎭✨ የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው🌟🕌 ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም በነፃ ተጋብዛችኋል!!🎉🙌 📆 ቀን ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል 🕔 ከ አሱር በኋላ ከ10:00 ጀምሮ (በሰአታችን የምንጀምር ስለሆነ በጊዜ እንድትገኙልን በትህትና እንጠይቃለን) 🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ አድራሻ:- 📍 ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ አላማችንን መደገፍ 🥰፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን ☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman ኢንሻአላህ! Telegram channel link https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram 🔗

ድግሱ በዛ እና ጉዳይ ይዞን ሄደ! ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ በቢልኮር ፖድካስት ያደረጉት ቆይታ #bilcorpodcas... https://youtube.com/watch?v=EiM0KOXze8M&si=B-ww-Ct3FHozoa3c

'የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት ሊቀርብ ነው። የዚህ ጥበባዊ መድረክ
'የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1  የመድረክ ዝግጅት የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት ሊቀርብ ነው። የዚህ ጥበባዊ መድረክ አላማ የተደበቀ ተሰጥኦ ያላቸውን ግለሰቦች በማውጣት እና ለህዝብ ችሎታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ ለኡማው ጠቃሚ የሆኑ ግለሰቦችን ማፍራት መቻል እና ኡማው በየዘርፉ ያለበትን ክፍተት የሚሸፍንበትን የሰዎች ተዋፅኦ የሚያገኝበትን መንገድ ማመቻቸት ነው። ይህ መድረክ ፀሀፊዎች፣ የስራ ፈጣሪዎች ፣ ከያኒያን ፣ዳኢዎች፣  የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ፣ እና የንግግር ክህሎት ያላቸው (orators) ፣ መሪዎች ፣ አሳቢያን ...በሌሎችም ዘርፎች የአንድን ማህረሰብ ቀና መንገድ ሊጠርጉ የሚችሉ ሰዎች በአላህ ፍቃድ የሚፈሩበት መልካም ማሳ ይሆናል። ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!! 📆 ቀን ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል 🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ አድራሻ:- ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ አላማችንን መደገፍ ፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን ☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman Telegram channel link https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram

ክፍል 2 የመጨረሻው ታሪክ ነብዩ ሙሳ ﷺ ወደ ወጣትነት ሲቃረቡ በእስራኤላዊ እና በ ግብፃውያን ድብድብ መሀከል ሰው በእጃቸው ይሞትባቸዋል። ነቢዩ ሙሳ ﷺ የነብዩ ሹአይብን (አለይሒ ሰላም) ሳፉራን ወደ አገቡበት ወደ ማድያን ይሔዳሉ። ማድያን ትንሽ ከቆዩ በሗላ ወደ ግብፅ ጉዞ ይጀምራሉ። በዛ በሀይለኛ ክረምት ነብዩ ሙሳ እና ሚስታቸው ወደ ገብፅ በሚያደርጉት ጉዞ መንገድ ይጠፋባቸዋል። ከዛም ከርቀት እሳት ያያሉ። ነብዩ ሙሳ ﷺ ሚስታቸውን ባለችበት እንድትቆይ ይነግሯት እና ወደ እሳቱ ይሔዳሉ። የተወሰነ እሳት ሊያመጡ እንደሚችሉም ያስባሉ። ነብዩ ሙሳ ﷺ ወደ 🔥 እሳቱ ሲጠጉ ነበልባሉ ከ አረንጓዴ ዛፍ ውስጥ ነው የሚወጣው ግን በአካባቢው ማንም የለም። ነብዩ ሙሳ ﷺ ይህን በግርምት እያዪ እያለ "ሙሳ እኔ ጌታህ ነኝ" የሚል ድምፅ በድንገት ይሠማሉ። የሰሙትም ድምፅ የያዟትን በትር ወደ መሬት እንዲወረወሩ ይጠይቃቸዋል። በትሩም በአንድ ጊዜ ወደ እባብነት ይቀየራል። ከዛም ይፈራሉ። ሙሳም ﷺ ያለ ፍርሀት እባቡን እንዲያነሱት ይጠየቃሉ ልክ ሲያነሱት ወደ በትርነት ይመለሳል። ከዛም እጃቸውን ብብታቸው ስር እንዲከቱ ይነገራቸዋል። እጃቸውን ከዛ ሲያወጡ። እጃቸው እንደ ፀሀይ ያበራል ከዛም መለኮታዊ ድምፁ እንደዚህ ይላቸዋል "ሙሳ ሆይ! እነዚህ ሁለት የአምላክህ ታላላቅ ምልክቶች ናቸው ወደ ፈርኦን እና ህዝቦቹ ተመልሰህ ወደ አምላክህ ጥራቸው!" ሙሳ ﷺ ይህን ምልክት ከአላህ ካገኙ በሗላ ወደ ፈርኦን በመሔድ የአላህ መልእክተኛ እንደሆኑና ለዚህም ማስረጃ እንዳላቸው ለፈርዖን ይነግሩታል ። ሙሳም ﷺ በትሩን መሬት ላይ ሲወረውሩት ወደ እባብነት ይለወጣል። በተአምራቱ የተደናገጠው ፈርኦንም ለምክር ወደ ሚኒስትሮቹ ይሄዳል። እነሱም ነብዩ ሙሳ ﷺ ተራ አስማተኛ እንደሆነ እና የእነሱም አስማተኞች የዚህ አይነት ቀላል ማታለያ እንደማያቅታቸው ይነግሩታል። ፈርኦንም ሁሉንም ታላላቅ የሚባሉ አስማተኞችን ሙሳ ያሳዩት አይነት አስማት እንዲሰሩ ወደ ቤተመንግሥቱ ጠራቸው። መደረግ ያለበት አይነት አስማት ሲነገራቸው ብዙም አልተጨነቁም። ቁራጭ ገመድ ወደ መሬት ሲወረውሩ እንደ እባብ መጥመልመል ጀመረ። ግን ሙሳ በትራቸውን ሲወረውሩ እባብ ሆነና ሁሉንም ሁሉንም ቁርጥራጭ ገመዶች በላቸው። አስማተኞቹም ወዲያው ይህ አስማት ሳይሆን ተአምር መሆኑን ተረዱ። ከዛም ሱጁድ (ስግደት) በማድረግ እንዲህ አሉ  "በሙሳ ሀይማኖት አምነናል" አላህም ለሙሳ ﷺ ፈርኦንን እንዲያስጠነቅቀው በዚህ እምነታቸው ከቀጠሉ ግን እሱን እና ህዝቦቹን እንደሚቀጣ ነገራቸው። ፈርኦን ግን ማስጠንቀቂያውን ለመስማት በጣም የኮራ ነበር። እናም እሱን እና ህዝቦቹን ለመቅጣት ሀገሪቱ በድርቅ ተመታች። የአንበጣ መንጋ ሰብሉን በልቶ አወደመው። የአባይ ወንዝ ጎርፍ ሆኖ ብዙ ቀውስ አስከተለ።ህዝቦቹ በበሽታና በወረርሽኝ ተጠቁ። ይህ ሁሉ ሲከሰት ህዝቦቹ ወደ ሙሳ እየሔዱ ችግሩ ከ እነሱ እንዲወገድ እንዲፀልይላቸው እና የእሱንም ሀይማኖት እንደሚከተሉ ቃል ይገቡለት ጀመር። ግን ከበሽታቸው ሲድኑ እና  ሁኔታዎች መሻሻል ሲጀምሩ ወደ ጣኦት አምልኳቸው ይመለሳሉ። ሙሳ ﷺ በኒ እስራኤላውያንን ሰበሰቡና ወደ ፍልስጤም ይዘዋቸው ሄዱ። ፈርኦን ይህን ሲሰማ ከግዙፍ ሰራዊት ጋር ተከተላቸው። ከ ሙሳ ﷺ ጋር እያመለጡ የነበሩት በኒ እስራኤላውያን ቀይ ባህር ሲደርሱ ፈርኦን ወደ እነሱ እንደቀረበ ያዪታል። እንደሚገድላቸውም እርግጠኛ ይሆናሉ። ሙሳም ﷺ በበትሩ ውሀውን ሲነኩት ወንዙ ለሁለት ይከፈላል። ደረቅ የመሻገሪያ ቦታም ያበጅላቸዋል። ህዝቦቹም በሰላም ይሻገራሉ። ፈርኦንም የገባበትን መንገድ ሲያይ ባህሩ የወታደሮቹ ጭንቅላት ላይ ደርሷል። ግን የባህሩ መሀል ላይ እያለ በሰራዊቱ እና በእሱ ላይ ባህሩ ይዘጋል። በዚህም ሁኔታ ፈርኦን እና ወታደሮቹ ውሀው ውስጥ ይሰጥማሉ። ✍️ኡስማን ሙስጠፋ ከእንግሊዝኛ የተመለሰ

(ዛሬ እየፆምን ያለነው አሹራ ነብዩ ሙሳﷺ በኒ እስራኤላውያንን ከ ፊርአውነ ባርነት በ አላህ እገዛ ነፃ ያወጡበት ቀን ነው) ክፍል 1 ታሪክ ሙሳ ﷺ በአንባገነኑ ፈርኦን ዘመን ነው የተወለዱት።  ፈርኦን እራሱን እንደ አምላክ ይቆጥር ነበር። ሰዎችን በዘር እና በብሔር ከፋፍሎ እርስ በእርስ የሚጋደሉ አንጃዎች አድርጓቸዋል። አይሁዳውያኑ- የእስራኤል ልጆች ፥ በታችኛው የማህበረሰብ መደብ ላይ ነበር ደረጃቸው እናም ባሪያ እና አገልጋይነት ላይ ነበር የሚሰሩት። ሙሳ ﷺ ከመወለዳቸው ጥቂት ጊዜያት በፊት ከ በኒ እስራኤል የሚወለድ ወንድ ልጅ ዙፉኑን እንደሚያፈርሰው ለ ፈርኦን ትንቢት ተነግሮት ነበር። ይህን ሲሰማ ጨካኙ ንጉስ ከ በኒ እስራኤል የሚወለዱ ወንድ ልጆች በሙሉ እንዲገደሉ ወታደሮቹን አዘዘ። የፈርኦን ወታደሮች ትእዛዙን ለማስፈፀም የእስራኤላውያንን ቤቶች መፈተሹን ተያያዙት።የሙሳ ﷺ እናትም መላ ወጠነች የወታደሮቹን መምጣት ስትሰማ ህፃኑን ሙሳ ﷺ ከነ ቅርጫቱ የቤቷ ጀርባ የሚገኘው የ አባይ ወንዝ ላይ አስቀመጠቻቸው። ቁርአን ላይ ይህ እንዲህ ተጠቅሷል :-  وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ أُمِّ مُوسَىٰ أَنْ أَرْضِعِيهِ ۖ فَإِذَا خِفْتِ عَلَيْهِ فَأَلْقِيهِ فِي الْيَمِّ وَلَا تَخَافِي وَلَا تَحْزَنِي ۖ إِنَّا رَادُّوهُ إِلَيْكِ وَجَاعِلُوهُ مِنَ الْمُرْسَلِينَ ወደ ሙሳም እናት «አጥቢው፣ በርሱም ላይ በፈራሽ ጊዜ በባሕሩ ውስጥ ጣይው አትፈሪም፣ አትዘኝም፣ እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልክተኞቹም አድራጊዎቹ ነንና» ማለትን አመለከትን፡፡ [28:7] ሙሳ ﷺ ያሉበት ቅርጫት እየተንሳፈፈ ወደ ፈርዖን ይደርሳል። የሱ ሰዎች ከወንዙ አውጥተው ወደ ፈርኦን ይወስዱታል። ከ በኒ እስራኤል ወንድ ልጆች አንዱ ይሆናል ብሎ በመጠርጠር በፍጥነት ሊገለው ይወስናል። ግን መልካሟ አስያ ሚስቱ ታስቆመዋለች። ልጅ አልነበራቸውም እና የማደጎ ልጅ አድርጋ እንዲያሳድጉት ትጠይቀዋለች ፍርኦንም የሚስቱ አስያን ጥያቄ ይቀበላል።የሚያለቅሰውን ህፃን ጡት እንዲያጠቡት ሴቶች ፍለጋ ምልመላ ይጀምራሉ። ህፃኑ ሊያጠቡት የመጡትን የሁሉንም ሴቶች ጡት እምቢ ይላል ከእናቱ ጡት በስተቀር። ሁሉን ቻዩ አላህ ፍፁም የልጇ ጠላት በሆነው የፈርኦን ቤተመንግሥት ውስጥ እናት እና ልጅን ያገናኛል። ነቢዩ ሙሳ ﷺ በፈርኦን ቤት አደጉ። (ከጥቂት ደቂቃ በሗላ 2 እና የመጨረሻ ክፍል ይለጠፋል ኢንሻአላህ) ✍ኡስማን ሙስጠፋ

🔖ፍሱ ከዒባዳ መሰላቸቷን ያስተዋለ፤ኢስቲግፋር ያብዛ። ማንኛውም ሰው ዒባዳን መፈፀም የሚሳነው በሰራው ወንጀል ምክንያት ነው። أَسْتَغْفِرُ اللَّهَ الْعَظِيمَ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ ، وَأَتُوبُ إِلَيْهِ. =

🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባቶች 4ተኛውን ዛሬ ኢንሻአላህ እናያለን (ለቀናት የቆመው በበአል ምክንያት ነበር ) 4. Self-Serving Bias/ራስን የመጠገን መዛባት (ብዬ ወደ አማርኛ ለጊዜው ተርጉሜዋለሁ) (This bias involves attributing positive outcomes to one’s own actions while attributing negative outcomes to external factors.) ይሄ 'ቢያዝ' ጥሩ ውጤቶችን የራሴ ችሎታ ነው ብሎ ማመን እና አሉታዊም ውጤቶችን ደግሞ በውጫዊ ነገሮች ላይ ማላከክ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው የሂሳብ ጥሩ የፈተና ነጥቡን የአይምሮ ችሎታዬ ውጤት ነው ብሎ ያምን እና የወደቀበትን ትምህርት ደግሞ የአስተማሪው ችግር ወይም የፈተናው መክበድ እንደሆነ ማመን/ማሰብ በዚህ ቢያዝ (ኢጎአችን) 'እኔነታችን' (self defense mechanism) ለራሱ ያለው ግምት እንዳይጎዳ በመከላከል ይጠበቃል። በሌላ ጎኑ ደግሞ የተዛባ ሰው ወቃሽነት እና ሀላፊነትን ያለመውሰድ ማንነት ሊዳብር ይችላል። ኢንሻአላህ ይቀጥላል... 🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. stud.) #ስለ_ስነልቦና To join👇 https://t.me/+Axzalt8LOXNiZTY0

✋የዘንድሮው የዐሹራ ፆም (የሙሐረም 10ኛው) ቀን ሐሙስ ሰኔ 18 ላይ ይውላል። ይህንን ታላቅ ቀን መፆም ያለፈውን የ365 ቀናት (የአንድ ዓመት) ወንጀል ያስምራል። ​በላጩና ተመራጩ አፆፃም...ነብዩ (ﷺ) አይሁዶችን ለመለየት ዘጠነኛውንም ቀን አብሮ ለመፆም አስበው ስለነበር፣ በላጩ መንገድ ረቡዕ (ሰኔ 17) እና ሐሙስን (ሰኔ 18) አከታትሎ መፆም ነው። ሌሎችንም በማስታዎስ የአጅሩ ተጠቃሚ ያድርጓቸው! ©️