WANIA TRADING S.C
Відкрити в Telegram
WANIA TRADING S.C is here to empower the Muslim community and create economically influential share company. ዋንያ ትሬዲንግ አ.ማ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማብቃት እና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ የአክሲዮን ኩባንያ ለመፍጠር ነው:: ለበለጠ መረጃ 👇 0935608888 ይደውሉልን
Показати більше1 173
Підписники
Немає даних24 години
-67 днів
-2130 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '260
в 0 каналах
червень '26
+12
в 1 каналах
Get PRO
травень '26
+11
в 1 каналах
Get PRO
квітень '26
+10
в 1 каналах
Get PRO
березень '26
+20
в 1 каналах
Get PRO
лютий '26
+36
в 1 каналах
Get PRO
січень '26
+31
в 1 каналах
Get PRO
грудень '25
+11
в 1 каналах
Get PRO
листопад '25
+7
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+4
в 1 каналах
Get PRO
вересень '25
+14
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+11
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+19
в 1 каналах
Get PRO
червень '25
+9
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+14
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+21
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+16
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+25
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+29
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+27
в 1 каналах
Get PRO
листопад '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '24
+123
в 1 каналах
Get PRO
вересень '24
+76
в 1 каналах
Get PRO
серпень '24
+75
в 1 каналах
Get PRO
липень '24
+73
в 1 каналах
Get PRO
червень '24
+72
в 1 каналах
Get PRO
травень '24
+285
в 3 каналах
Get PRO
квітень '24
+55
в 1 каналах
Get PRO
березень '24
+52
в 1 каналах
Get PRO
лютий '24
+161
в 6 каналах
Get PRO
січень '24
+132
в 1 каналах
Get PRO
грудень '23
+590
в 3 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 05 липня | 0 | |||
| 04 липня | 0 | |||
| 03 липня | 0 | |||
| 02 липня | 0 | |||
| 01 липня | 0 |
Дописи каналу
+5
የተረሳው ቋንቋ (እዝነት) .1 መድረክ ትናንት በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል። (አልሃምዱሊላህ)
በዚህ ዝግጅትም ሁሉም አቅራቢዎች የተዘጋጁበትን ዘርፍ በላቀ ብቃት ያቀረቡ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ጥሩ ቆይታ ነበራቸው።
ይህ ጥበባዊ እና ሁሉን አካታች የመዝናኛ እና የመማማሪያ ዝግጅት ቁጥር ሁለት የተረሳው ቋንቋ (ፍትህ).2 በሚል ርእስ በአላህ ፍቃድ ሞቅ ብሎ በቅርቡ የሚቀጥል ሲሆን የመግቢያ ዋጋውም 250 ብር ሆኗል።
አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ ፣ መግቢያ ቲኬቱን ማግኘት እንዲሁም ለኡማው የሚጠቅም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ስልኮች ያናግሩን 0921390122
0912027023
(የቀጣዩን ዝግጅት ሰአት እና ቦታ በቅርብ እናሳውቃለን)
የእለቱ ፕሮግራም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች በቅርቡ ለህዝብ ይለቀቃል። ኢንሻአላህ!!
| 2 | Немає тексту... | 15 |
| 3 | የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት 🎭✨
የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው🌟🕌
ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም
በነፃ ተጋብዛችኋል!!🎉🙌
📆 ቀን ዛሬ ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል
🕔 ከ አሱር በኋላ ከ10:00 ጀምሮ (በሰአታችን የምንጀምር ስለሆነ በጊዜ እንድትገኙልን በትህትና እንጠይቃለን)
🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ
አድራሻ:- 📍 ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ
አላማችንን መደገፍ 🥰፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን
☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman
ኢንሻአላህ!
Telegram channel link
https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram 🔗 | 324 |
| 4 | የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት 🎭✨
የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት የሚቀርብበት ሰአት እየደረሰ ነው🌟🕌
ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም
በነፃ ተጋብዛችኋል!!🎉🙌
📆 ቀን ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል
🕔 ከ አሱር በኋላ ከ10:00 ጀምሮ (በሰአታችን የምንጀምር ስለሆነ በጊዜ እንድትገኙልን በትህትና እንጠይቃለን)
🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ
አድራሻ:- 📍 ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ
አላማችንን መደገፍ 🥰፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን
☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman
ኢንሻአላህ!
Telegram channel link
https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram 🔗 | 1 |
| 5 | ድግሱ በዛ እና ጉዳይ ይዞን ሄደ! ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ በቢልኮር ፖድካስት ያደረጉት ቆይታ #bilcorpodcas...
https://youtube.com/watch?v=EiM0KOXze8M&si=B-ww-Ct3FHozoa3c | 381 |
| 6 | 'የተረሳው ቋንቋ' (እዝነት) .1 የመድረክ ዝግጅት
የኢስላም ውበት እና እውነት በኪነት የሚገለጥበት ባለ ተስጥኦቹ ወጣቶችም አቅማቸው የሚያሳዩበት ታላቅ ዝግጅት ሊቀርብ ነው።
የዚህ ጥበባዊ መድረክ አላማ የተደበቀ ተሰጥኦ ያላቸውን ግለሰቦች በማውጣት እና ለህዝብ ችሎታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ ለኡማው ጠቃሚ የሆኑ ግለሰቦችን ማፍራት መቻል እና ኡማው በየዘርፉ ያለበትን ክፍተት የሚሸፍንበትን የሰዎች ተዋፅኦ የሚያገኝበትን መንገድ ማመቻቸት ነው።
ይህ መድረክ ፀሀፊዎች፣ የስራ ፈጣሪዎች ፣ ከያኒያን ፣ዳኢዎች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ፣ እና የንግግር ክህሎት ያላቸው (orators) ፣ መሪዎች ፣ አሳቢያን ...በሌሎችም ዘርፎች የአንድን ማህረሰብ ቀና መንገድ ሊጠርጉ የሚችሉ ሰዎች በአላህ ፍቃድ የሚፈሩበት መልካም ማሳ ይሆናል።
ወደ እዚህ መድረክ ሁላችሁም
ተጋብዛችኋል!!
📆 ቀን ሰኔ 23 ማክሰኞ 2018 ዓ.ል
🏟️ ቦታ ቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ
አድራሻ:- ሳርቤት አደባባይ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ-አባድር መስጊድ አጠገብ-ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ህንጻ 2ተኛ ፎቅ አዳራሽ
አላማችንን መደገፍ ፥ አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ እንዲሁም ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ሰዎች በሚከተሉት ቁጥሮች አናግሩን
☎️ 0921390122 / 0912027023 tg username @usmanoman
Telegram channel link
https://t.me/USMAN_MUSTOFA_telgram | 523 |
| 7 | ክፍል 2 የመጨረሻው ታሪክ
ነብዩ ሙሳ ﷺ ወደ ወጣትነት ሲቃረቡ በእስራኤላዊ እና በ ግብፃውያን ድብድብ መሀከል ሰው በእጃቸው ይሞትባቸዋል።
ነቢዩ ሙሳ ﷺ የነብዩ ሹአይብን (አለይሒ ሰላም) ሳፉራን ወደ አገቡበት ወደ ማድያን ይሔዳሉ። ማድያን ትንሽ ከቆዩ በሗላ ወደ ግብፅ ጉዞ ይጀምራሉ።
በዛ በሀይለኛ ክረምት ነብዩ ሙሳ እና ሚስታቸው ወደ ገብፅ በሚያደርጉት ጉዞ መንገድ ይጠፋባቸዋል።
ከዛም ከርቀት እሳት ያያሉ። ነብዩ ሙሳ ﷺ ሚስታቸውን ባለችበት እንድትቆይ ይነግሯት እና ወደ እሳቱ ይሔዳሉ። የተወሰነ እሳት ሊያመጡ እንደሚችሉም ያስባሉ። ነብዩ ሙሳ ﷺ ወደ 🔥 እሳቱ ሲጠጉ ነበልባሉ ከ አረንጓዴ ዛፍ ውስጥ ነው የሚወጣው ግን በአካባቢው ማንም የለም። ነብዩ ሙሳ ﷺ ይህን በግርምት እያዪ እያለ "ሙሳ እኔ ጌታህ ነኝ" የሚል ድምፅ በድንገት ይሠማሉ።
የሰሙትም ድምፅ የያዟትን በትር ወደ መሬት እንዲወረወሩ ይጠይቃቸዋል። በትሩም በአንድ ጊዜ ወደ እባብነት ይቀየራል። ከዛም ይፈራሉ። ሙሳም ﷺ ያለ ፍርሀት እባቡን እንዲያነሱት ይጠየቃሉ ልክ ሲያነሱት ወደ በትርነት ይመለሳል።
ከዛም እጃቸውን ብብታቸው ስር እንዲከቱ ይነገራቸዋል። እጃቸውን ከዛ ሲያወጡ። እጃቸው እንደ ፀሀይ ያበራል ከዛም መለኮታዊ ድምፁ እንደዚህ ይላቸዋል "ሙሳ ሆይ! እነዚህ ሁለት የአምላክህ ታላላቅ ምልክቶች ናቸው ወደ ፈርኦን እና ህዝቦቹ ተመልሰህ ወደ አምላክህ ጥራቸው!"
ሙሳ ﷺ ይህን ምልክት ከአላህ ካገኙ በሗላ ወደ ፈርኦን በመሔድ የአላህ መልእክተኛ እንደሆኑና ለዚህም ማስረጃ እንዳላቸው ለፈርዖን ይነግሩታል ።
ሙሳም ﷺ በትሩን መሬት ላይ ሲወረውሩት ወደ እባብነት ይለወጣል።
በተአምራቱ የተደናገጠው ፈርኦንም ለምክር ወደ ሚኒስትሮቹ ይሄዳል።
እነሱም ነብዩ ሙሳ ﷺ ተራ አስማተኛ እንደሆነ እና የእነሱም አስማተኞች የዚህ አይነት ቀላል ማታለያ እንደማያቅታቸው ይነግሩታል።
ፈርኦንም ሁሉንም ታላላቅ የሚባሉ አስማተኞችን ሙሳ ያሳዩት አይነት አስማት እንዲሰሩ ወደ ቤተመንግሥቱ ጠራቸው።
መደረግ ያለበት አይነት አስማት ሲነገራቸው ብዙም አልተጨነቁም። ቁራጭ ገመድ ወደ መሬት ሲወረውሩ እንደ እባብ መጥመልመል ጀመረ። ግን ሙሳ በትራቸውን ሲወረውሩ እባብ ሆነና ሁሉንም ሁሉንም ቁርጥራጭ ገመዶች በላቸው።
አስማተኞቹም ወዲያው ይህ አስማት ሳይሆን ተአምር መሆኑን ተረዱ።
ከዛም ሱጁድ (ስግደት) በማድረግ እንዲህ አሉ "በሙሳ ሀይማኖት አምነናል"
አላህም ለሙሳ ﷺ ፈርኦንን እንዲያስጠነቅቀው በዚህ እምነታቸው ከቀጠሉ ግን እሱን እና ህዝቦቹን እንደሚቀጣ ነገራቸው።
ፈርኦን ግን ማስጠንቀቂያውን ለመስማት በጣም የኮራ ነበር። እናም እሱን እና ህዝቦቹን ለመቅጣት ሀገሪቱ በድርቅ ተመታች።
የአንበጣ መንጋ ሰብሉን በልቶ አወደመው። የአባይ ወንዝ ጎርፍ ሆኖ ብዙ ቀውስ አስከተለ።ህዝቦቹ በበሽታና በወረርሽኝ ተጠቁ። ይህ ሁሉ ሲከሰት ህዝቦቹ ወደ ሙሳ እየሔዱ ችግሩ ከ እነሱ እንዲወገድ እንዲፀልይላቸው እና የእሱንም ሀይማኖት እንደሚከተሉ ቃል ይገቡለት ጀመር።
ግን ከበሽታቸው ሲድኑ እና ሁኔታዎች መሻሻል ሲጀምሩ ወደ ጣኦት አምልኳቸው ይመለሳሉ።
ሙሳ ﷺ በኒ እስራኤላውያንን ሰበሰቡና ወደ ፍልስጤም ይዘዋቸው ሄዱ።
ፈርኦን ይህን ሲሰማ ከግዙፍ ሰራዊት ጋር ተከተላቸው። ከ ሙሳ ﷺ ጋር እያመለጡ የነበሩት በኒ እስራኤላውያን ቀይ ባህር ሲደርሱ ፈርኦን ወደ እነሱ እንደቀረበ ያዪታል።
እንደሚገድላቸውም እርግጠኛ ይሆናሉ።
ሙሳም ﷺ በበትሩ ውሀውን ሲነኩት ወንዙ ለሁለት ይከፈላል። ደረቅ የመሻገሪያ ቦታም ያበጅላቸዋል። ህዝቦቹም በሰላም ይሻገራሉ።
ፈርኦንም የገባበትን መንገድ ሲያይ ባህሩ የወታደሮቹ ጭንቅላት ላይ ደርሷል። ግን የባህሩ መሀል ላይ እያለ በሰራዊቱ እና በእሱ ላይ ባህሩ ይዘጋል። በዚህም ሁኔታ ፈርኦን እና ወታደሮቹ ውሀው ውስጥ ይሰጥማሉ።
✍️ኡስማን ሙስጠፋ
ከእንግሊዝኛ የተመለሰ | 590 |
| 8 | (ዛሬ እየፆምን ያለነው አሹራ ነብዩ ሙሳﷺ በኒ እስራኤላውያንን ከ ፊርአውነ ባርነት በ አላህ እገዛ ነፃ ያወጡበት ቀን ነው)
ክፍል 1 ታሪክ
ሙሳ ﷺ በአንባገነኑ ፈርኦን ዘመን ነው የተወለዱት። ፈርኦን እራሱን እንደ አምላክ ይቆጥር ነበር። ሰዎችን በዘር እና በብሔር ከፋፍሎ እርስ በእርስ የሚጋደሉ አንጃዎች አድርጓቸዋል። አይሁዳውያኑ- የእስራኤል ልጆች ፥ በታችኛው የማህበረሰብ መደብ ላይ ነበር ደረጃቸው እናም ባሪያ እና አገልጋይነት ላይ ነበር የሚሰሩት።
ሙሳ ﷺ ከመወለዳቸው ጥቂት ጊዜያት በፊት ከ በኒ እስራኤል የሚወለድ ወንድ ልጅ ዙፉኑን እንደሚያፈርሰው ለ ፈርኦን ትንቢት ተነግሮት ነበር።
ይህን ሲሰማ ጨካኙ ንጉስ ከ በኒ እስራኤል የሚወለዱ ወንድ ልጆች በሙሉ እንዲገደሉ ወታደሮቹን አዘዘ።
የፈርኦን ወታደሮች ትእዛዙን ለማስፈፀም የእስራኤላውያንን ቤቶች መፈተሹን ተያያዙት።የሙሳ ﷺ እናትም መላ ወጠነች
የወታደሮቹን መምጣት ስትሰማ ህፃኑን ሙሳ ﷺ ከነ ቅርጫቱ የቤቷ ጀርባ የሚገኘው የ አባይ ወንዝ ላይ አስቀመጠቻቸው።
ቁርአን ላይ ይህ እንዲህ ተጠቅሷል :-
وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ أُمِّ مُوسَىٰ أَنْ أَرْضِعِيهِ ۖ فَإِذَا خِفْتِ عَلَيْهِ فَأَلْقِيهِ فِي الْيَمِّ وَلَا تَخَافِي وَلَا تَحْزَنِي ۖ إِنَّا رَادُّوهُ إِلَيْكِ وَجَاعِلُوهُ مِنَ الْمُرْسَلِينَ
ወደ ሙሳም እናት «አጥቢው፣ በርሱም ላይ በፈራሽ ጊዜ በባሕሩ ውስጥ ጣይው አትፈሪም፣ አትዘኝም፣ እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልክተኞቹም አድራጊዎቹ ነንና» ማለትን አመለከትን፡፡ [28:7]
ሙሳ ﷺ ያሉበት ቅርጫት እየተንሳፈፈ ወደ ፈርዖን ይደርሳል። የሱ ሰዎች ከወንዙ አውጥተው ወደ ፈርኦን ይወስዱታል።
ከ በኒ እስራኤል ወንድ ልጆች አንዱ ይሆናል ብሎ በመጠርጠር በፍጥነት ሊገለው ይወስናል።
ግን መልካሟ አስያ ሚስቱ ታስቆመዋለች።
ልጅ አልነበራቸውም እና የማደጎ ልጅ አድርጋ እንዲያሳድጉት ትጠይቀዋለች ፍርኦንም የሚስቱ አስያን ጥያቄ ይቀበላል።የሚያለቅሰውን ህፃን ጡት እንዲያጠቡት ሴቶች ፍለጋ ምልመላ ይጀምራሉ።
ህፃኑ ሊያጠቡት የመጡትን የሁሉንም ሴቶች ጡት እምቢ ይላል ከእናቱ ጡት በስተቀር።
ሁሉን ቻዩ አላህ ፍፁም የልጇ ጠላት በሆነው የፈርኦን ቤተመንግሥት ውስጥ እናት እና ልጅን ያገናኛል።
ነቢዩ ሙሳ ﷺ በፈርኦን ቤት አደጉ።
(ከጥቂት ደቂቃ በሗላ 2 እና የመጨረሻ ክፍል ይለጠፋል ኢንሻአላህ)
✍ኡስማን ሙስጠፋ | 470 |
| 9 | 🔖ነፍሱ ከዒባዳ መሰላቸቷን ያስተዋለ፤ኢስቲግፋር ያብዛ። ማንኛውም ሰው ዒባዳን መፈፀም የሚሳነው በሰራው ወንጀል ምክንያት ነው።
أَسْتَغْفِرُ اللَّهَ الْعَظِيمَ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ ، وَأَتُوبُ إِلَيْهِ.
= | 382 |
| 10 | 🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባቶች 4ተኛውን ዛሬ ኢንሻአላህ እናያለን (ለቀናት የቆመው በበአል ምክንያት ነበር )
4. Self-Serving Bias/ራስን የመጠገን መዛባት (ብዬ ወደ አማርኛ ለጊዜው ተርጉሜዋለሁ)
(This bias involves attributing positive outcomes to one’s own actions while attributing negative outcomes to external factors.)
ይሄ 'ቢያዝ' ጥሩ ውጤቶችን የራሴ ችሎታ ነው ብሎ ማመን እና አሉታዊም ውጤቶችን ደግሞ በውጫዊ ነገሮች ላይ ማላከክ ነው።
ለምሳሌ አንድ ሰው የሂሳብ ጥሩ የፈተና ነጥቡን የአይምሮ ችሎታዬ ውጤት ነው ብሎ ያምን እና የወደቀበትን ትምህርት ደግሞ የአስተማሪው ችግር ወይም የፈተናው መክበድ እንደሆነ ማመን/ማሰብ
በዚህ ቢያዝ (ኢጎአችን) 'እኔነታችን' (self defense mechanism) ለራሱ ያለው ግምት እንዳይጎዳ በመከላከል ይጠበቃል። በሌላ ጎኑ ደግሞ የተዛባ ሰው ወቃሽነት እና ሀላፊነትን ያለመውሰድ ማንነት ሊዳብር ይችላል።
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. stud.)
#ስለ_ስነልቦና
To join👇
https://t.me/+Axzalt8LOXNiZTY0 | 429 |
| 11 | ✋የዘንድሮው የዐሹራ ፆም (የሙሐረም 10ኛው) ቀን ሐሙስ ሰኔ 18 ላይ ይውላል። ይህንን ታላቅ ቀን መፆም ያለፈውን የ365 ቀናት (የአንድ ዓመት) ወንጀል ያስምራል።
በላጩና ተመራጩ አፆፃም...ነብዩ (ﷺ) አይሁዶችን ለመለየት ዘጠነኛውንም ቀን አብሮ ለመፆም አስበው ስለነበር፣ በላጩ መንገድ ረቡዕ (ሰኔ 17) እና ሐሙስን (ሰኔ 18) አከታትሎ መፆም ነው።
ሌሎችንም በማስታዎስ የአጅሩ ተጠቃሚ ያድርጓቸው!
©️ | 277 |
| 12 | https://youtu.be/RBiyNlRpFGc?si=lliqClrTMHiLRTNI | 528 |
| 13 | 🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባት።
3. Availability Heuristic/መረጃዊ ድንጋሬ (ብዬ ወደ አማርኛ መልሼዋለው/ ለጊዜው🤔)
(People tend to judge the likelihood of an event based on how easily examples come to mind,)
ይህኛው 'ቢያዝ' አሁን ላይ ወደ አይምሯችን በሚመጣው ወይም በብዛት በሰማነው መረጃ ላይ ብቻ ተመሠርተን ስለ አንድ ማንኛውም ጉዳይ የተዛባ እምነት የምንይዝበትን የአስተሳሰብ መዛባት የሚገልፅ ነው።
ለምሳሌ:- በተደጋጋሚ ስለ የአይሮፕላን መከሰከስ ዜና በመከታተል አይሮፕላን ከሌሎች መጓጓዣ መንገዶች በጣም ለአደጋ የተጋለጠ ነው ብሎ ማመን (ባይሆንም እንኳ)።
የጦርነት ዜናዎችን በብዛት ሲዘገብ ከገጠመን ወይም ተደጋጋሚ ስለ ጦርነት የሚያወሩ ሰዎች እና ከባቢ አየር ውስጥ ከሆንን አለም በሙሉ የጦርነት አውድማ እንደሆች ማሰብ።
በግርድፉ ሲገለፅ ለተጋለጥንበት ወሬ ወይም በሰማነው ቁንፅል መረጃ ላይ ተመርኩዘን የሁኔታውን እውነታ በዛ ውስጥ የመቃኘት የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ መድረስ ወይም መደናገር ነው ማለት ይቻላል።
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
🖊️ usman mus( from A.A.U behavioral study dep. stud.)
#ስለ_ስነልቦና
To join👇
https://t.me/usmanic_psychology | 472 |
| 14 | ⭐️ ጌታዬ ሆይ! ከአንተ ዘንድ ለእኔ የምታወርደውን ማንኛውንም በጎ ነገር በጣም የምፈልግ ድሀ ነኝ።
ሁሉንም ጭንቀትህን፣ ሀዘንህንና ህመምህን ይዘህ ለአላህ ብትሰግድ ከዚህ ታላቅ ቁርኣናዊ ዱዓ ውጭ ምንም ባትደጋግም እንኳ፣ ይህ ዱዓ በውስጡ ያንተን ፍላጎትና ድህነት የሚገልጽ ታላቅ ትርጉም ይዟል። አላህም ጉዳይህን ያስተካክልልሃል፣ ያበለጽግሃል፣ ታላላቅ የሆኑ የበጎ ገፀበረከት መክፈቻዎችንም ታያለህ።
﴿ربِّ إنّي لمَا أنزلتَ إليَّ من خَيرٍ فَقِيرٌ﴾
"ጌታዬ ሆይ! ከአንተ ዘንድ ለእኔ የምታወርደውን ማንኛውንም በጎ ነገር በጣም የምፈልግ ድሀ ነኝ።"
የነብዩ ሙሳ ልብ በፍርሃትና በሀዘን ተጭኖ ሳለ በዚህ ዱዓ ተጓዘ። እውነተኛ ደግ ባሮች ወደ አላህ የሚጓዙበትን የፍላጎትና የመተማመን ጣፋጭነትን ይዞ ወደ አላህ በልቡና በነፍሱ ተመለሰ ።
👉 አላህም ዱንያን ሰጠው፣ ደህንነትን አጎናጸፈው፣ በአእምሮው እንኳ ውል ብሎ የማያውቀውን መልካም በሮችንም ከፈተለት።
እኔም ምንም ያህል በመልካም ሁኔታ ውስጥ ብሆን "ጌታዬ ሆይ! ከአንተ ዘንድ ለእኔ የምታወርደውን ማንኛውንም በጎ ነገር እጅግ የምፈልግ ድሀ ነኝ❗️
©️ | 380 |
| 15 | በማህበራዊ ሚዲያዎች | 454 |
| 16 | 🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባት።
2,Bandwagon Effect
(People are more likely to adopt certain behaviors or beliefs if they see others doing so)
ይህ የባንድዋገን ተፅዕኖ የሚባለው 'ኮግኒቲቭ ቢያዝ' አንድን በጊዜው ገናና የሆነነ ተግባር ወይም ቁስ በማድረግ ወይ በመግዛት መገኘት ወይም በብዙሀኑ ተግባር ተፅዕኖ ጥላ ስር የመውደቅ ዝንባሌ ነው።
ለምሳሌ ፋሽን ተብሎ የመጣ ልብስ ብዙዎች ሲያደርጉት በማየት ማድረግ። የአነጋገር ዘይቤ ወይም የማህበራዊ ሚዲያ 'ቻሌንጅ' መሠል ዘርፈ ብዙ በጊዜው አየሩን የተቆጣጠሩ ተግባራትን የማድረግ ባህሪያዊ ሁኔታ 'ባንድዋገን ኢፌክት' ይባላል።
እናንተስ የዚህ ተፅእኖ ሰለባ የሆናችሁበት ጊዜ አለ? መለስ ብላቹ አስታውሱ እስኪ።
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. student.)
#ስለ_ስነልቦና
To join👇
https://t.me/usmanic_psychology | 1 038 |
| 17 | 🏝Cognitive biases/የአይምሮ ውቅር የድምዳሜ መዛባት (ብዬ ተርጉሜዋለው) በዚህ ስር ያሉ የተወሰኑ ተመሣሣይ ፅንሰ ሀሳቦችን ለመጪው ቀናት እናያለን ተከታተሉኝ/ኢንሻአላህ!
1.Confirmation Bias/የጭፍን ሙጥኝ
(confirms one’s preexisting beliefs while disregarding contradictory evidence.)
- ይህ ፅንሰ ሀሳብ በአጭሩ ሲብራራ:- ከዚህ በፊት የነበረንን አመለካከት የሚለውጥ አዲስ እና ተጨባጭ መረጃ ቢኖርም ያንን ይዘነው የቆየነውን አስተሳሰብ እና መረጃ ላለማጥፋት እና ይበልጥ ለማዳበር የሚጠቅሙንን መሰል ሀሳቦችን ማሰብ እና መሰል እምነታችንን የሚያጠናክርልንን መረጃ ከአይምሮ ጓዳ እየመዘዙ ያለንን የቀደመ እምነት ማዳበር ነው።
ለምሳሌ-:የምንደግፈው የፖለቲካ ቡድን አሁን ጥሩ እየሰራ እንደሆነ የሚያወራ መረጃ ብቻ ማሳደድ እና ማዳመጥ ወይም ማሰብ።የምንደግፈው የኳስ ቡድንን ችሎታ አለመውረድ የሚያሳይ መረጃ እና የሀሳብ ማረጋገጫ ለራስ መስጠት።የምንወደው ሰው በድሎን ቢሆን እንኳ ያለፈ መልካም ተግባሩን እያስታወስን እመነታችንን ላለመለወጥ መታገል። የምናምነው ሰው ቢከዳንም አሁንም ትክክል እንደሆነ ለማሰብ ወይም ለማመን መጣር።
🖊️ usman mus( from AAU behavioral study dep. student.)
#ስለ_ስነልቦና
To join👇
https://t.me/usmanic_psychology | 560 |
| 18 | "ከሰአቲቱ መቅረብ ምልክት አንዱ የድንገተኛ ሞት መብዛት ነው" ነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ)
የድንገተኛ ሞቶች መበራከት ከምንጊዜውም በላይ የአለም አስደንጋጭ ሁነት የሆነበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
የህክምና መስፋፋቶች እና የስልጣኔዎች መበራከት የዚህን አስደንጋጭ ክስተት ቁጥር ሊቀንሱት አልቻሉም።
የሰዎች የአኗኗር ዘይቤ፣ የአመጋገብ ስርአት ጤናማ አለመሆን የወለደው ውፍረት (obesity)፣ የልብ ህመም፣ ደም ግፊት፣ የሰው ልጆች የስራ ዘይቤ መቀየር ጥንት ከነበረው ጉልበት የሚሹ ብዙ አድካሚ የእርሻ ስራዎች የአኗኗር ዘይቤ ወደ ከተሜነት እና ብዙ ወደ መቀመጥ መለወጥ የሰውነት እንቅስቃሴ የሚፈልጉ የስራ ዘርፎች መመናመን ወዘተ...በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ ለጠቀስናቸው የድንገተኛ ሞት የሚዳርጉ ህመሞች መንስኤ ሆኗል።
የመኪናና የተፈጥሮ አደጋ ፣ ራስን በቀላሉ ለማጥፋት የሚረዱ መሳሪያዎች መብዛት ፣ የሽጉጥ መሣሪያዎች በቀላሉ ሰዎች እጅ መግባት ፣የወንጀል መስፋፋትም ተያያዥ ለዚህ ትንቢት ተፈፃሚነት በሰበብነት የሚነሱ ነገሮች ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱት የድንገተኛ ሞት መንስኤዎች በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሀዲስ በቀጥታ ባይጠቀሱም እሳቸው የምፅአት ቀን መቅረብን እና የድንገተኛ ሞት መብዛትን ቁርኝች ሲገልፁ ከዘመኑ ጋር አብረው ተያይዘው የሚነሱ የድንገተኛ ሞት ሰበቦች በውስጥ አዋቂነት ምክንያት ሆነው መቅረባቸው የማይቀር ነው።
በዚህ ውስጥ ለማሳየት የተሞከረውም ከድንገተኛው ሞት መንስኤዎች ጀርባ ያሉ ጉዳዮች ከምፅአት ቀን መድረስ ጋር ተያይዘው የተከሰቱ የአለም ስልጣኔ እና የሰው ልጆች ህይወት የአኗኗር ዘይቤ ለውጦች ናቸው።
ይህም ትንቢትም አሁን እውን ሆኖ የአለምን የህክምና እና የኑሮ ሁኔታ እየተገዳደረ ያለ ነገር ነው።
ሰዎች ብዙ ያልማሉ ግን ሞት አድፍጧል። ድንገተኛው ሞት በሞት መልአክ በኩል ነፍሳቸውን ከስጋቸው ነጥሎ ይወስደዋል። ህያው ሆነው ያደሩ ሰዎች በድን ሆነው ያነጋሉ። ልተኛ ብለው በሰላም ወደ አልጋቸው የሄዱ ሰዎች ጠዋት ላይነቁ እስከወዲያኛው አሸልበው ይገኛሉ።የተለያየ ሰው ዳግም ስለመገናኘቱ ጥርጣሬው ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን የበረታ ነው። ሁሉም የስልጣኔ መሣሪያዎች የሰው ልጆችን ሞት የሚደግሱበት ስውር ክንዶች አሏቸው።
አሁን ምድርን ተሰናብተው ላይመለሱ በድንገት ወደ ቀጣዩ አለም መሸጋገር የሰው ልጆች አስፈሪ እጣ ሆኗል። ዜናዎችም ከዚህ የድንገተኛ ህልፈት ዘገባ ቅኝት አልራቁም።
ምንጭ:-
📖 'ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ' መፅሐፍ
ምዕራፍ 4 | በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የተነገሩ ትንቢቶች እና ይህ ዘመን
ገፅ 103-105
✍️ በኡስማን ሙስጠፋ | 892 |
| 19 | 👍የተረሱ 💛 ሱናዎች👈🏼
⛱➰⛱➰⛱➰⛱
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናወች 1️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
🌽ምግብን አናንቆ ከመተው መቆጠብ
💓ረሱል
ﷺ
አንዳችንም የምግብ ችግር ተናግረው አያቁም። ምግቡ ቀርቦ ከተመቻቸው ይበሉታል,ካልፈለጉት ደግሞ ሳያናንቁት ይተውታል።
ከሃዲሱ ምንማረው
🎈1👉🏼ምግብ ፊትለፊታችን በቀረበ ጊዜ አለማጥላላት‼️
🎈2👉🏼ለምግብ አቅራቢው ስሜት መጠበቅ እንዳለብን‼️
🎈3👉🏼የተሰጠንን ምግብ በቻልነው ያክል ለአክብሮት መብላት‼️
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናወች 2️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
👉🏼ሱና ሰላቶችን መጠበቅ👈🏼 በቀን እና በሌሊት ባለው ሰዓት አስራ ሁለት ሱና 🕌ሰላቶችን(ከፈርድ ወጪ)
የሰገደ አላህ ጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል።
አራት ከዝሁር በፊት እና ሁለት ረከዓ ከዝሁር በኋላ=6 ረከዓ
ከመግሪብ በኋላ ሁለት ረከዓ=2 ረከዓ
ከኢሻ በኋላ ሁለት ረከዓ=2 ረከዓ
ከሱብሂ በፊት ሁለት ረከዓ=2 ረከዓ
አጠቃላይ አስራ ሁለት ረከዓ
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናወች 3️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
👉🏼መንገድ ልንጓዝ ስንል 🕌መስጂድ
👉🏼ሁለት ረከዓ መስገድ
💓ረሱል ﷺ መንገድ ሲወጡ በቀን እንጂ አይወጡም በዱሃ ወቅት ወይም ከንጋት ጀምሮ እስከ ዙሁር ወቅት ባለው ሰዓት ነበር ልክ ሲወጡ ከመስጂድ ነበር ሚጀምሩት ከዛም በውስጡ ሁለት ረከዓ ይሰግዳሉ ከዛም ትንሽ ተቀምጠው ይወጣሉ።(ሰሂህ ሙስሊም)
ከሃዲሱ ምንማረው
🔂 🔂 🔂
🎈1👉🏼መንገድ ስንወጣ ኸይር ነገር ይገጥመናል።
🎈2👉🏼ምናልባት ለጊዜው መጥፎ ቢያገኘን እንኳን መጨረሻው ኸይር ቢሆን እንጂ።
🎈3👉🏼ለአላህ እጅ መስጠት ነው።
🎈4👉🏼በአላህ ላይ መመካትን ያፀናል።
የተረሱ ሱናወች 4️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
👉🏼ከአዛን በኋላ ሚደረግ ዱዓ👈🏼
ጃቢር ረዲየላሁ አንሁ እንደዘገቡት 💓ረሱል
ﷺ
አሉ፦
🕌ጥሪ(አዛን) ከሰማ በኋላ ይህንን ዱዓ ያለ
ﺍﻟﻠﻬﻢ ﺭﺏ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﺪﻋﻮﺓ ﺍﻟﺘﺎﻣﺔ، ﻭﺍﻟﺼﻼﺓ ﺍﻟﻘﺎﺋﻤﺔ ﺁﺕ ﻣﺤﻤﺪﺍً ﺍﻟﻮﺳﻴﻠﺔ
ﻭﺍﻟﻔﻀﻴﻠﺔ، ﻭﺍﺑﻌﺜﻪ ﻣﻘﺎﻣﺎً ﻣﺤﻤﻮﺩﺍً ﺍﻟﺬﻱ ﻭﻋﺪﺗﻪ
🔥የቂያማ ዕለት ምልጃዬ (ሸፈዓዬ)ታገኘዋለች። ከሃዲሱ ምንማረው፦
🎈1👉🏼🕌አዛን ካለቀ በኋላ ይህንን ዱዓ ያለ 💓የነብያችን ﷺምልጃ በአላህ ፍቃድ ያገኛል። እናም ሁላችንም ዘንድ አዛን ሲደረግ የአዛኑ መልስ ወሬ ሆኗል። እንጠንቀቅ
ተረሱ ሱናዎች 5️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
🔥መፋቂያን መጠቀም አቡ ሁረይራ እንደዘገቡት 💓ረሱል
ﷺ
((ህዝቦቼ አከብዳለሁ ብዬ ባልሰጋ ኖሮ በእያንዳንዱ ሰላት ወቅት መፋቅያን
ባዛቸው ነበረ)) ከሃዲሱ ምንማረው
🎈1👉🏼ለመፋቂያ ትልቅ ትዕዛዝ መኖሩን።
🎈2👉🏼ንፅህና በየሰላት ወቅቱ መጠበቅ
🎈3👉🏼ሰጋጅን እና መላዒካዎችን አዛ አለማድረግ
የተረሱ ሱናዎች 6️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
ዶሮ እና አህያ ሲጮሁ ሚደረግ ዱዓ🙏🏼
💓ረሱላችን
ﷺ
እንዲህ ብለዋል፦ ዶሮ ስትጮህ ከሰማችሁ ከአላህ ችሮታን ጠይቁ እሷ እኮ መላዒካን አይታ ነው የጮሀችው,አህያ ሲጮህ ደግሞ ከሰማችሁ ከሸይጣን በአላህ ተጠበቁ እሱ እኮ 👹 ሸይጣንን አይቶ ነው የጮሀው።
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናዎች 7️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
👉🏼ደረጃ ሲወጣ እና ሲወረድ ሚደረግ አዝካር
💓ረሱል
ﷺ
፦ወደላይ ስንወጣ ተክቢር እናደርጋለን(አላሁ አክበር) ስንወርድ ደግሞ ተስቢህ (ሱብሃነላህ) እንል ነበር። እኛ ዘንድ ጭራሽ የለም ማለት ይቻላል። በጣም ጠፍቷል። ከአሁን በኋላ ለመስራት ዝግጁ እንሁን።
⤵️
የተረሱ ሱናዎች 8️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
☞ወደ ሰው ቤት ስንገባ ማስፈቀድ
አቡ ሙሳ አልኣሽሪይ እንደዘገቡት የአላህ 💓መልእክተኛ
ﷺ
እንዲህ ብለዋል፦ማስፈቀድ ሶስት ጊዜ ነው ከተፈቀደልህ ካልሆነ ግን ተመለስ።
ከሃዲሱ ምንማረው በሩን ስታንኳኳ ሶስቴ መሆን አለበት በሶስቱ ምንም መልስ ካላገኘህ ተመለስ። ከተፈቀደልህግባ ከተባልክ ደግሞ መግባትን ያመለክታል። ግን አብዛኞቻችን ጋር ከሶስት በላይ ማንኳኳት ልምድ ሆኖ መቷል። ስለዚህ መቆጠብ ይኖርብናል።
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናዎች 9️⃣
✔️✔️✔️✔️✔️
💓ረሱል
ﷺ
🌽ምግብን ሲመገቡ በ👉🏼3👈🏼 ጣታቸው ነበር፣ልክ በልተው ሲጨርሱ ከመታጠባቸው በፊት ጣታቸውን ይልሱት ነበር። ይህ ግን እኛ ዘንድ የጠፋ ነገር ነው ለማለት አያዳግትም። ልክ በልተን እንደጨረስን ሮጦ ሳሙናና ውሃ ወይም ሶፍት መጠቀም ይህ ደግሞ አግባብ አደለም። ይታሰብበት!!!
⤵️ ⤵️ ⤵️
የተረሱ ሱናዎች 🔟
✔️✔️✔️✔️✔️
እንቅልፍ ከመተኛታችን በፊት ውዱዕ ማድረግ ሱና ነው። ግን አብዛኞቻችን ዘንድ በጣም ተዘንግቷል።
ከሃዲስ፦ወደ መጋደሚያክ በመጣቅ ጊዜ ለሰላት እንደምታደርገው 🙏🏼ውዱዕ አይነት ውዱዕ አድረገህ በቀኝ ጎንህ ተኛ(ተጋደም) | 826 |
| 20 | ዕድሜያችሁን ቁርኣንን በመሐፈዝ (በመሸምደድ) እና በተደቡር (በማስተንተን) በአግባቡ ተጠቀሙበት፤ ለቀጣዩ ዓለም (ለአኺራ) የሚሆን ስንቅ ሳትይዙ ዕድሜያችሁ በከንቱ እንዲባክን አትፍቀዱ!
በቂያማ ቀን ሰዎች ቁርኣንን እያነበቡ በጀነት ደረጃዎች ላይ ከፍ ሲሉ እኛ ግን እዚያው ባለንበት ቦታ እንዳንቀር.....
በትንሹ ደረጃ አትደሰቱ፤ ሰዎች ቀድመዋችሁ ሲሄዱና ማዕረጋቸው ከፍ ሲል እያያችሁ እናንተ በአንድ ቦታ ላይ መቅረትን አትውደዱ! 💪🏻
ተፎካከሩ! የበላይ ለመሆን የሚደረግ ውድድር ቢኖር እርሱም የአኺራ ውድድር ነው!
አስተውሉ! ቁርኣን የሕይወት ዘመን ፕሮጀክት ነው፤ ከእርሱ ውጪ ዕድሜያችንን ልንሰጠው የሚገባ ምንም ነገር የለም። ዕድሜያችንን በሙሉ ለቁርኣን ብናጠፋ እንኳ ከዚህች ምድር ያመለጠን ምንም ነገር የለም!
#ቁርኣን_የሕይወት_ዘመን_ፕሮጀክት | 750 |
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
