uk
Feedback
MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👚‍🎓

MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👚‍🎓

ВіЎкрОтО в Telegram

A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU

ППказатО більше
557
ПіЎпОсМОкО
+124 гПЎОМО
+47 ЎМів
+2530 ЎеМь
Архів ЎПпОсів
March 8 Happy International Women's Day to all the incredible women who inspire change, lead with courage, and shape a bright
March 8 Happy International Women's Day to all the incredible women who inspire change, lead with courage, and shape a brighter future. 💜 @MTULSU

🌍 FALAS Ambassador Applications Now Open The Federation of African Law Students (FALAS) is pleased to announce that applications are open for the FALAS Ambassador position. If you are a 3rd-year law student or above, this is your opportunity to represent your institution, expand your network, and contribute to a vibrant community of African law students committed to legal excellence and continental unity. ✹ Who Should Apply? • Emerging student leaders • Passionate about academic engagement • Committed to collaboration across African law faculties 📌 Application Requirements: • Motivational Letter (350–450 words) • CV (Maximum 1 page) • One-Page Action Plan Step forward. Represent your institution. Create continental impact. 🌍⚖ 🗓 Deadline: March 8, 2026 📩 Submit to: @likehimself or @Dirshu65 #FALAS #AfricanLawStudents #LegalLeadership #AmbassadorCall@MTULSU

እንኳን ለ130ኛው ዚአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደሚሳቜሁ! Happy 130th Anniversary of the Victory of Adwa!
እንኳን ለ130ኛው ዚአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደሚሳቜሁ! Happy 130th Anniversary of the Victory of Adwa!

ዚአድዋ ድል በአለም አቀፍ ህግ እይታ *** በዳንኀል ፍቃዱ /ጠበቃና ዹህግ አማካሪ/ ዚአድዋ ድል በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ህግ (International Law) እና በዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ዹሚሰጠው ክስተት ነው።አድዋ ድል መሠሚት ዹሆነው ዹሕግ ክርክር ዹሚጀምሹው ኚጊርነቱ በፊት በነበሹው:: ዚውጫሌውል(Treaty of Wuchale) ላይበተፈጠሹ ዚትርጉም ልዩነት ነው። ይህ ክስተት በአለም አቀፍ ዹውል ሕግ (Law ofTreaties) ታሪክውስጥ እስካሁንም ድሚስ እንደ ትልቅ ማሳያ ይጠቀሳል። ዚአድዋ ድልኢትዮጵያ በአለም መድሚክ ላይ ያላትን ዚሉዓላዊነት ጥያቄ በደም እና በውል ያሚጋገጠቜበት ነው።በአለም አ ቀፍ ህግ እይታ ዚአድዋ ድል ዚሚኚተሉት ዋና ዋና ትርጉሞቜ አሉትፊ                                                                                                                                                                    1. ዚውጫሌ ውል አንቀጜ 17፡ ዚትርጉም ማታለልዚአድዋ ጩ ርነትመንስኀ ዹሆነው ዹዚህ አንቀጜ ዹአማርኛ እና ዚጣሊያንኛ ትርጉም አለመጣጣም ነበር።·      በአማርኛውቅጂ፡ኢትዮጵያ ኚሌሎቜ ዚአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ማድሚግ ኚፈለገቜ በጣሊያን በኩል ማድሚግ ትቜላለቜ(Optional) ይላል።·      በጣሊያንኛውቅጂ፡ኢትዮጵያ ኚሌሎቜ መንግስታት ጋር ዚምታደርገው ማንኛውም ግንኙነት በጣሊያን በኩል መሆን አለበት (Mandatory) ይላል።ጣሊ ያን በዚህዚትርጉም ልዩነት በመጠቀም ኢትዮጵያ ዚጣሊያን "ሞግዚትነት"(Protectorate) ስርእንደገባቜ ለዓለም ሀገራት አወጀቜ። አፄ ምኒልክ ግን ይህንን ሉዓላዊነትን ዹሚጋፋ ማታለል መሆኑን በመጥቀስ ውሉን ውድቅ አደሚጉት።                                                                                                         2. ዚዲፕሎማሲያዊ ክርክሩ ጥንካሬ                                                                                                      አፄ ምኒልክ እና እ቎ጌ ጣይቱ ዚጊርነት ዝግጅት ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ዚዲፕሎማሲ ስራ ሰርተዋል።·     ለአውሮፓነገስታት ደብዳቀ መጻፍ፡ አፄ ምኒልክ ለቪክቶሪያ (እንግሊዝ) እና ለሌሎቜ መሪዎቜ በጻፉት ደብዳቀ፣ ጣሊያን ውሉን በማጭበርበር ዚኢትዮጵያን ነጻነት ለመቀማት እዚሞኚሚቜ መሆኑን በሕግ አግባብ አስሚዱ።·      ውሉንበይፋ መሰሚዝ፡ ኢትዮጵያ በጣሊያን በኩል ሳይሆን በቀጥታ ለሌሎቜ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ደብዳቀዎቜን መላክ በመጀመር፣ በተግባር "ሞግዚትነቱን" ውድቅ አደሚገቜ ው። 3. ዚሉዓላዊነት እና ዚግዛት አንድነት ማሚጋገጫ(Sovereignty)                                                              በ19ኛው ክፍለ ዘመን ዚአውሮፓ ሀያላን በበርሊን ጉባኀ (1884-85) አፍሪካን ሲኚፋፈሉ፣ ጥቁር ህዝቊቜ ዚራሳ቞ው ዹህግ ስብዕና እንዳላ቞ው አይቆጥሩም ነበር። ዚአድዋ ድል ግን ፊ·       ኢትዮጵያ በሀይል ዹማይደፈር ዚመንግስትነት መዋቅር ያላት መሆኑን አስመሰኚሚ።·       "Terra Nullius" (ባለቀት ዹሌለው መሬት) ዹሚለውን ዹቅኝ ግዛት ህግ በኢትዮጵያ ላይ እንዳይሰራ አደሚገ።                                                                                                                                    4. ዚአዲስአበባ ውል(Treaty of Addis Ababa, 1896)                                                                        ድሉን ተኚትሎ ዹተፈሹመው ዚአዲስ አበባ ውል በአለም አቀፍ ህግ አይን እጅግ አስፈላጊ ሰነድ ነው። በዚህውል አማካኝነትፊ· ሊያን ዚውጫሌን ውል (Treaty of Wuchale) በይፋ ሰሚዘቜ።·       ኢትዮጵያ ፍጹም ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር መሆኗን ጣሊያን (እና ዹተቀሹው ዓለም) በህግ እንዲያውቁ ተገደዱ። ይህ ውል ኢትዮጵያ ኚአውሮፓ ሀገራት ጋር በደሹጃ እኩል (Equal footing) ሆና ዚዲፕሎማሲ ግንኙነት እንድትጀምር በር ኚፈተ።                                                                                                           5. ዹቅኝ ግዛት ህግጋትን መቃወም(Challenge to Colonial Jurisprudence)                                በወቅቱ ዹነበሹውዹአለም አቀፍ ህግ በአውሮፓውያን ዚበላይነት ላይ ዹተመሰሹተ ነበር። ዚአድዋ ድል ግንፊ·       ዚራስን እድል በራስ ዹመወሰን (Self-determination) መርህ ገና በህግ ሳይደነገግ በተግባር እንዲታይ አድርጓል።·       ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሎ ዹህግ እና ዚሞራል መሰሚት በመሆን፣ ሌሎቜ ዚአፍሪካ እና ዚእስያ ሀገራት ለነጻነታ቞ው እንዲታገሉ መንገድ አሳይቷል።                                                                                       6. ዚመንግስታቱማህበር (League of Nations) አባልነትአድዋ ያስኚበሚውነጻነት ኢትዮጵያበኋላ ላይ በ1923 ዓ.ም. ዚመንግስታቱ ማህበር አባል እንድትሆን አስቜሏታል። ይህ ደግሞ አንዲት ዚአፍሪካ ሀገር በአለም አቀፍ ዹህግ ተቋማት ውስ ጥ እኩል ድምጜ እንዲኖራት ያስቻለ ታሪካዊ ክስተት ነበር።                                                                                                                                          7. በአለም አቀፍ ደሹጃ ያስገኘው ዲፕሎማሲያዊ ድልኚአድዋ ድል  በኋላ፣ ኢትዮጵያዚአለም አቀ ፍ ማህበሚሰብ አባል መሆኗን ዚሚያሳዩ ክስተቶቜ ተኹተሉ፩                                                                  ·      ዚኀምባሲዎቜመኚፈት፡ፈሚንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ሩሲያ እና ጣሊያን ራሷ በአዲስ አበባኀምባሲዎቻ቞ውን ኚፈቱ።                                                                                                                      ·      ዚቀይመስቀል ማህበር አባልነት፡ ኢትዮጵያ ዚጄኔቫ ስምምነቶቜን (GenevaConventions ) በመፈሹምበአለም አቀፍ ዚሰብአዊ መብት ህግጋት ተሳታፊ ሆነቜ።                                                                               ·      ሉዓላዊእውቅና፡ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ብ ቾኛዋ (ኚላይቀሪያ ጋር) በአውሮፓውያን እኩል ዚታወቀቜ ሀገር ሆነቜ። ባጠቃላይፊ ዚአድዋ ድል በአለም አቀፍ ህግ አይን ሲታይ፣ "አፍሪካውያንዚራሳ቞ው ህግእና አስተዳደርያላ቞ው፣ በአለምአቀፍ መድሚክምእንደ መንግስትእውቅና ሊሰጣ቞ውዚሚገባ ህዝቊቜና቞ው" ዹሚለውን እውነት በሀይልም በዲፕሎማሲም ያስመሰኚሚ ድል ነው። Join us: @MTULSU

#update ለምርጫ ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቜ ወደ ቀታ቞ው አይሄዱም ለተወሰኑ ቀናት ብቻ መርጠው እንዲመለሱ ይደሹጋል ። ዚኀፌዎሪ ትምህርት ሚንስ቎ር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዚካቲት 18 2018
#update ለምርጫ ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቜ  ወደ ቀታ቞ው አይሄዱም  ለተወሰኑ ቀናት ብቻ መርጠው እንዲመለሱ  ይደሹጋል  ። ዚኀፌዎሪ  ትምህርት  ሚንስ቎ር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዚካቲት 18 2018 ዹህግ ተማሪዎቜ ህብሚት

🏛 ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝ እና ዚፖሊስ ግዎታ፡ ሕጉ ምን ይላል? ⚖ በመጀመሪያ ደሚጃ፣ ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝን አለማክበር በኢትዮጵያ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ 4⃣4⃣9⃣ መሠሚት በግልጜ "ዚፍትሕ ሥራን ማደናቀፍ" በሚል በወንጀል ያስጠይቃል። ፖሊስ ኹሕግ በላይ ሊሆን ዚሚቜልበት ምንም ዓይነት "ልዩ ሁኔታ" በሕገ-መንግሥቱም ሆነ በሌሎቜ ሕጎቜ አልተቀመጠም። 1⃣. ዚሰብዓዊ መብቶቜ ጥሰት (International Impact) አንድ ተጠርጣሪ በፍርድ ቀት ነፃ ኚተባለ ወይም በዋስ እንዲፈታ ኚታዘዘ በኋላ ፖሊስ ትዕዛዙን ባለመቀበል መልሶ ዚሚያስሚው ኹሆነ፩ ኢ-ሰብዓዊ አያያዝፊ ግለሰቡ ያለ ሕግ አግባብ ነፃነቱን ስለሚታገድ፣ ይህ ድርጊት በዓለም አቀፍ ዚሲቪልና ዚፖለቲካ መብቶቜ ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጜ 9⃣ ላይ ዹተቀመጠውን "ያለ ምክንያት አለመታሰር" መብትን በግልጜ ይጥሳል። 🚫👀 Arbitrary Detentionፊ ይህ አይነቱ እስር "ዘፈቀደ እስር" ተብሎ ዹሚፈሹጅ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ዚፈሚመቻ቞ውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶቜ ዚምትጥስበት ድርጊት ነው። 2⃣. በዓለም አቀፍ ተቋማት ላይ ዹሚኖሹው ተፅዕኖ ዓለም አቀፍ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋ቟ቜ (እንደ Amnesty International እና Human Rights Watch) እንዲሁም ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ ፍትሕ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲያጡ ያደርጋ቞ዋልፊ 📉 ዹደሹጃ ዝቅጠትፊ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ዹሕግ ዚበላይነት መለኪያ (Rule of Law Index) ላይ ያላት ደሹጃ ዝቅ እንዲል ያደርጋል። 💞 ዚኢኮኖሚ ተፅዕኖ፩ ዓለም አቀፍ ሚዳት ድርጅቶቜና ባለሀብቶቜ "ፍትሕ በሌለበትና ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝ በማይኚበርበት አገር መዋዕለ ንዋይ አናፈስም" በማለት ፊታ቞ውን እንዲያዞሩ ያደርጋል። 3⃣. መወሰድ ያለባ቞ው እርምጃዎቜ ይህንን "ዚእስር አዙሪት" ለመስበር ዚሚኚተሉት እርምጃዎቜ መወሰድ አለባ቞ውፊ ⚖ ተጠያቂነት (Accountability)ፊ ትዕዛዝ ያልፈጞሙ ዚፖሊስ አባላትና አመራሮቜ በግል በወንጀልና በዲስፕሊን እንዲጠዚቁ ማድሚግ። "ኹበላይ ታዝዀ ነው" ዹሚል ሰበብ ኹሕግ ተጠያቂነት አያድንም። ✹Habeas Corpus (አካልን ነፃ ዚማውጣታትአቀቱታ ማቅሚብ )ፊ ጠበቆቜና ቀተሰቊቜ ግለሰቡ ያለ ፍርድ ቀት ትዕዛዝ መታሰሩን በመግለጜ በአስ቞ኳይ ፍርድ ቀት እንዲቀርብና እንዲፈታ ክስ መመስሚት። 🛡 ዚፍትሕ ምክር ቀት ቁጥጥርፊ ዚፍትሕ ሚኒስ቎ርና ዚፌዎራል ፖሊስ ኮሚሜን ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝ መኚበሩን ዚሚኚታተል ገለልተኛ ዚክትትል ክፍል ማቋቋም ይኖርባ቞ዋል። ፖሊስ ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝን አለማክበሩ ዹሕግ ዚበላይነትhን ገደል ዚሚኚት ድርጊት ነው። ፍርድ ቀት ዚፍትሕ ሥርዓቱ ዚመጚሚሻ መቆሚያ በመሆኑ፣ ዚፍርድ ቀት ትዕዛዝ ካልተኚበሚ "ፍትሕ" ትርጉም አልባ ትሆናለቜ። Join Us:@MTULSU

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ ዹተጀመሹው ዚመውጫ ፈተና መሾጋሾጉን ገለጹ። ዚተለያዩ ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማቷ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎትን ዋቢ በማድሚግ ባሰራጩት መልዕክት ፀ ዚቅድመ ም
+1
ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ ዹተጀመሹው ዚመውጫ ፈተና መሾጋሾጉን ገለጹ። ዚተለያዩ ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማቷ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎትን ዋቢ በማድሚግ ባሰራጩት መልዕክት ፀ ዚቅድመ ምሹቃ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) ዛሬ መጀመሩ ገልጞዋል። " ነገር ግን ያልታሰበ ዹኃይል መቆራሚጥ ቜግር በዳታ ማዕኹል ላይ በማጋጠሙ ቜግሩን በመፍታት እንደገና ለማስጀመር ጥሚት ዹተደሹገ ቢሆንም ዚፕሮግራም መዛባትን አስኚትሏል " ብለዋል። በዚህም ምክንያት ዹፈተናው ሙሉ ፕሮግራም በአንድ ቀን መሾጋሾጉን ገልጞዋል። ሁሉም ፕሮግራሞቜ ዚዛሬን ጚምሮ ባሉበት ክፍለ ጊዜ ላይ ሆነው በተዋሚድ በአንድ ቀን ዹተሾጋሾጉ መሆኑን አማልክተዋል። ዛሬ ፈተና ጀምሹው ዚነበሩ ተፈታኞቜም እንደሙኚራ ፈተና (Mock Exam)  በመውሰድ ነገ በተመሳሳይ ሰዓት እንደገና ይፈተናሉ ተብሏል። @tikvahethiopia

ይህ ማስታወቂያ ለ(sponsor) በሚዛን ቮፒ ዩኒቚርሲቲ ዹህግ ትምህርት ክፍል ትምህርታ቞ውን ለሚኚታተሉት በሙሉ ነው ። 👇👇👇👇 @MTULSU
ይህ ማስታወቂያ ለ(sponsor) በሚዛን ቮፒ ዩኒቚርሲቲ ዹህግ ትምህርት ክፍል ትምህርታ቞ውን ለሚኚታተሉት በሙሉ ነው ። 👇👇👇👇 @MTULSU

ለመላው ዚእስልምና እምነት ተኚታዮቜ በሙሉ እንኳን ለሚመዳን ጟም በሰላም አደሚሳቜሁ። መልካም ጟም እንዲሆንላቜሁ እንመኛለን!!! 👇👇👇👇 @MTULSU

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ዹተወለደ ልጅ “አባትነት” ጉዳይ **** በዳንኀል ፍቃዱ / ጠበቃና ዹህግ አማካሪ/ አለም አቀፍ ዚሕፃናት እና ዚሎቶቜ መብት ድንጋጌዎቜ ይህንን ጉዳይ ዚሚመለኚቱት በሁለት ዋና ዋና መርሆቜ ላይ ተመስርተው ነው፩ ዹሕፃኑ በላጭ ጥቅም (Best Interest of the Child) እና በሎቶቜ ላይ ዹሚፈጾም ጥቃትን መኚላኚል። በኢፌድሪ ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ሕግ ዚወላጅነት ሥልጣን ዓላማ “ዹልጁን ጥቅም ማስጠበቅ“ እንደሆነ ይደነግጋሉ። ሃገራት ደግሞ እነዚህ ሁለት መርሆቜ ላይ በመመስሚት እና “ዚአባትነት መሚጋገጥ” (Paternity) እና “ዚወላጅነት ሥልጣን” (Parental Authority/Custody) ዚተለያዩ ዹሕግ ጜንሰ-ሐሳቊቜ መሆናቾውን በመለዚት ዚራሳ቞ውን አቋምና ውሳኔ ይሰጣሉ፣ በዝርዝር እንመልኚተው...

ያለ ስልጠና ሰርተፊኬት ጋብቻ አይፈቀድም! ዚኢፌድሪ ዚሎቶቜና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚጚመሚ ዚመጣውን ዚፍቺ ቁጥር ለመቀነስ አዲስና ጠንኹር ያለ መመሪያ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን
+1
ያለ ስልጠና ሰርተፊኬት ጋብቻ አይፈቀድም! ዚኢፌድሪ ዚሎቶቜና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚጚመሚ ዚመጣውን ዚፍቺ ቁጥር ለመቀነስ አዲስና ጠንኹር ያለ መመሪያ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ። ​📌 ዋና ዋና ነጥቊቜፊ 👉​መስፈርቱ፡ ማንኛውም ተጋቢ ወደ ትዳር ዓለም ኚመግባቱ በፊት ዚቅድመ ጋብቻ ስልጠና ወስዶ 'ዚሰርተፊኬት' ባለቀት መሆን ይኖርበታል። ​መቌ ይጀመራል? አሰራሩን በቀጣዩ አመት ስራ ላይ ለማዋል ዝግጅት መጠናቀቁን ዚሚኒስ቎ሩ ዚአሚጋውያንና ቀተሰብ ጉዳዮቜ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋዬ ሮበሌ ገልጞዋል። 👉​አጋር አካላት፡ ስራው ኚሀይማኖት ተቋማት፣ ኹሀገር ሜማግሌዎቜ እና ኚሚመለኚታ቞ው ዚፍትህ አካላት ጋር በቅንጅት ይኚናወናል። ​📉 ለምን አስፈለገ? በአዲስ አበባ ኹተማ ሲቪል ምዝገባና ዚነዋሪነት አገልግሎት ኀጀንሲ መሹጃ መሰሚት፣ በኹተማዋ ዚፍቺ መጠን ካለፉት ዓመታት አንጻር ዹ54 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ለትዳሮቜ መፍሚስ ዋነኛው ምክንያት "ዚግንዛቀ እጥሚት" መሆኑን ያመነው ሚኒስ቎ሩ፣ ይህንን ለመፍታት ስልጠናውን አስገዳጅ አድርጎታል። ​💡 ምን ተዘጋጅቷል? ​ለሰልጣኞቜ ዚሚያገለግሉ ዚማስተማሪያ ማኑዋሎቜ ተዘጋጅተዋል። ​በቀተሰብ ጉዳይ ላይ ዚሚሰሩ ተቋማት በቅንጅት ዚሚሰሩበት ዚጋራ ፎሹም ተመስርቷል። ​"ትዳር በስሜት ብቻ ሳይሆን በዕውቀትም ሊመራ ይገባል" ዹሚለው ይህ መመሪያ፣ በሀገሪቱ ዚማህበራዊ ትስስር ላይ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል። ዚጉድ ሀገር ገንፎ እያደር ይፋጃል😂😂 @legal_infoo

ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ኹመመሹቃቾው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ኚተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደሚግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስ቎ር ገለፀ፡፡ ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ
+1
ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ኹመመሹቃቾው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ኚተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደሚግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስ቎ር ገለፀ፡፡ ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ኹመመሹቃቾው በፊት ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያገለግሉ ዚሚያደርግ አሠራር ተግባራዊ ለማድሚግ መንግሥት ዕቅድ መያዙ ይታወቃል፡፡ በዕቅዱ ላይ ኹኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት ቢደሚግምፀ ኚክልሎቜ፣ ኚትምህርት ቀቶቜ እና ኚፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አለመካሔዱን በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹኹፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዎኀታ አቶ ኮራ ጡሜኔ ለሪፖርተር ተናግሚዋል፡፡ መንግሥት "ዕቅዱ ተግባራዊ ይሆናል ብሎ እስካሁን ውሳኔ አለማሳለፉን" ዚገለፁት ሚኒስትር ዎኀታውፀ በቀጣይ ሳምንታት ተማሪዎቜ፣ ወላጆቜ፣ መምህራን እና ዚሕዝብ ተወካዮቜን ጚምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ኚሚመለኚታ቞ው ሌሎቜ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ይደሹጋል ብለዋል፡፡ ኚዩኒቚርሲቲዎቜ ጋር በተደሹገው ውይይት ኚሎጂስቲክስ እና ኚአካዳሚክ ጉዳዮቜ ጋር እንዎት ይጣጣማል በሚለው ላይ ጥያቄ ኚማቅሚብ ውጪፀ "ሀሳቡ ተግባራዊ ቢሆን እንደሚደግፉት" መግለጻ቞ውን ጠቅሰዋል። ኚውይይቱ በኋላ ሀሳቡ ለፓርላማ እንደሚቀርብና ዚራሱ ዹሆነ ተቋም ተቋቁሞለት ሕግ ይወጣለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ አስሚድተዋል። ዕቅዱ ተቀባይነት ካገኘ በ2019 ዓ.ም እንደሚተገበር ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ሆኖም በውይይቱ ወቅት ተማሪዎቜን ጚምሮ ሌሎቜ ዚትምህርት ማኅበሚሰቡ ዕቅዱን ካልፈለገው ዚሚቀርበት ሁኔታ እንዳለም ጠቁመዋል፡፡ ዚእርስዎ አቋም ምንድነው?? @MTULSU

ለማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ፍሬሜማን ተማሪዎቜፊ ኚወዲሁ መልካም ፈተና እንዲሆንላቜሁ እዚተመኘን እንደሚታወቀው ዹህግ ትምህርት ቀት (Law School) ዹ2018 ዓ.ም ዚመጀመሪያ ዙር ትምህርት በስኬት እንደተጠናቀቀ አቅምና ፍላጎት ያላ቞ውን 40–50 ተማሪዎቜን ለመቀበል ተዘጋጅቷል። በድጋሚ መልካም ፈተና! To Social Science Freshman Students: We wish you all the very best in your upcoming examinations. Following the successful completion of the first phase of 2018 E.C academic year, the Law School is ready to admit 40–50 capable and motivated students who have the interest. Once again Best of luck in your exams! For further info 👇👇👇👇 Join us: @MTULSU

#ExitExam ዚመውጫ ፈተና (Exist Exam) ዚሚሰጥበት ጊዜ ኚዚካቲት 16 እስኚ ዚካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑ ተገለጞ። ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ባወጣው መርሃ-ግብር መሰ
#ExitExam ዚመውጫ ፈተና (Exist Exam) ዚሚሰጥበት ጊዜ ኚዚካቲት 16 እስኚ ዚካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑ ተገለጞ። ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ባወጣው መርሃ-ግብር መሰሚት፣ ዹ2018 ትምህርት ዘመን አጋማሜ ዹኹፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) ኚዚካቲት 16 - 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል። ይህንን ዹፈተና ፕሮግራም ተቋማት ለተማሪዎቻ቞ው እያሳወቁ ይገኛሉ።

#As MTU schedule 👆👆👆 2nd semester course registration for all regular students. Join us. @MTULSU
#As MTU schedule 👆👆👆 2nd semester course registration for all regular students. Join us. @MTULSU

"ሎሚ ውርወራ እና Tort Law" "ሎሚ ብወሚውር ደሚቷን መታሁት፣ አወይ ኩላሊቷን ልቧን ባገኘሁት።...." ጥንት ነበር ያ!... አባቶቻቜን ለወደዷት ኮሚዳ ሎሚ ወርውሚው፣ ፍቅራ቞ውን ገልጞው፣ በሎሚ ምት ልቧን አሾንፈው ትዳር ዚሚመሠርቱት — ድሮ ነበር። ዛሬ ግን ዘመን ተቀይሯል። ሎሚው በኚሚሜላ፣ ደብዳቀው በ቎ክስት፣ ዹሎሚው ሜታም በሜቶ ተተክቷል። ነገር ግን ዚጥምቀት በዓል ሲመጣ ያ ዚድሮው "ሎሚ ዹመወርወር" አምሮት በአንዳንዶቻቜን (በተለይ በፍቅር ህመም ለተያዝነው) ልብ ውስጥ ማቅበዝበዙ አይቀርም። ዛሬ ኚሰዓት... ላይብሚሪ እያጠናሁ ሳለሁ አንድ እንግዳ ሀሳብ መጣብኝ። በሚዛን እዚተኚበሚ ያለው ዹቃና ዘገሊላ ድባብ ኚሩቅ ይጠራኝ ዠመር። "ለምን አልወጣም?" አልኩ ለራሎ። ለምን ሄጄ፣ በልቀ ላይ "Exclusive Ownership" ያላትን ያቺን ልጅ ፈልጌ አላገኛትም? ሳስባት ዚምደነግጥላትን፣ ልቀን በውብ ምስሏ ዚሞላቜውን ልጅ አግኝቌ፣ አንድ ሎሚ ገዝቌ "ውዮ ሆይ፣ ዚወደድኩሜ እኮ ድሮ ነው!" ብዬ ሎሚ ብወሚውርባትስ? Romantic ነው አይደል? በባህል መነጜር ሲታይ "ዹፍቅር ሰው!" ያስብላል። ነገር ግን ቜግሩ እዚህ ጋር ነው። እንደምታውቁት እኔ ዹሕግ ተማሪ ነኝ። ዹሕግ ተማሪ ደግሞ እንኳን ሎሚ፣ አበባም ሲሰጥ "ይሄ ነገር በሕጉ አግባብ እንዎት ይታያል?" ብሎ ማሰቡ አይቀርም — አንዳንዎ ባያስብም። እናም Romantic ሀሳቀን á‹­á‹€ ኚላይብሚሪ ልወጣ ስል፣ ኚፊት ለፊቮ ዹተቀመጠው Civil Code (ዚፍትሐብሔር ሕግ) "ቆይ ወዎት?" ብሎ አፈጠጠብኝ። ወዲያውኑ አንቀጜ 2038 (Tort Law) አይኔ ላይ ድቅን አለብኝ! አንቀጜ 2038 እንዲህ ይላል፩ "አንድ ሰው ሆነ ብሎ ሌላው ሰው ሳይፈቅድ በሚያደርገው መንካት በዚህ በመንካቱ ጥፋተኛ ነው።" ይልና ይቀጥላል... "ሰውዬውን በቀጥታም ሆነ ወይም በሌላ ሕይወት ባለው ወይም በሌለው ነገር አማካይነት ቢነካውም ጥፋተኛ ነው።" እንግዲህ አስቡት! ለፍቅር ብዬ ዹምገዛው ሎሚ በሕጉ ፊት "ሕይወት ዹሌለው ነገር(object)" ነው። ያንን ሎሚ ወርውሬ ዚልጅቷን ደሚት ወይም ትኚሻ ባገኘው፥ በሕጉ አነጋገር "ያለ ፈቃድ መንካት" (Battery) ፈጜሜያለሁ ማለት ነው። ማሰቀን አላቆምኩም... ሎሚውን ወርውሬባት በፈገግታ ፈንታ "ይሄ ሰው ግን ምን ነካው?" ብላ ብትጮህስ? ወይም ሎሚው ስቶ ግንባሯን ቢላትስ? ወዲያውኑ ዹፍቅር ጥያቄዬ ወደ "ክስ" ተቀዹሹ ማለት ነው። "ክቡር ፍርድ ቀት ተኚሳሜ፣ ደንበኛዬን ያለ ፈቃዷ በሎሚ በመደብደብ አካላዊና ሥነ-ልቩናዊ ጉዳት አድርሶባታል" ብሎ ሲያነብልኝ ታዚኝ — ወፍራሙ ሰውዬ። ዹፍቅር መዝገብ ሳይሆን ኹውል ውጪ ዚሚመጣ ኃላፊነት (Tortious liability) መዝገብ ሲኚፈትብኝ ታዚኝ! ግና ተስፋ አልቆሚጥኩም። እንደማንኛውም ዹሕግ ሰው "መውጫ ቀዳዳ" (Defense) መፈለግ ጀመርኩ። ሕጉን ሳገላብጥ ሳገላብጥ ቆይቌ አንቀጜ 2039(ሠ) ላይ ደሚስኩ። አንቀጜ 2039(ሠ) እንዲህ ይነበባልፊ "ዚተኚሳሹ ሥራ አእምሮ ባለው ሰው ግምት ዚሚገባ ነው ዚሚያሰኝ ሌላ ማናቾውም ምክንያት በተገኘ ጊዜ ሁሉ" ተኚሳሹ ነጻ ነው። "አሃ!" አልኩ በልቀ። እዚህ ጋር ነው ጚዋታው! "ክቡር ፍርብ ቀት ድርጊቱ ዚፈጞምኩት በጥምቀት በዓል ነው። በጥምቀት ደግሞ ሎሚ መወርወር 'አእምሮ ባለው ሰው ግምት' (Reasonable person standard) ተቀባይነት ያለው ባህል ነው" ብዬ መኚራኚር እቜላለሁ። ሎሚ ዚመልካም መዓዛ እና ዹፍቅር መግለጫ እንጂ ድንጋይ ወይም ጠብመንጃ አይደለም። ስለዚህ ድርጊ቎ በሕጉ ፊት "Socially acceptable" ስለሆነ ጥፋት ሊሆን አይገባም። አይደል!? ነገር ግን... እንደገና አሰብኩት። በዘመናቜን "አእምሮ ያለው ሰው" (Reasonable person) ሎሚ መወርወርን እንደ ፍቅር ጥያቄ ይወስደዋል ወይስ እንደ ጥቃት? ልጅቷ "በሎሚ ዚምትመታኝ ምን አድርጌህ ነው?" ብላ ዹTort ክስ ብትመሠርትብኝ ዳኛው "ባህል ነው" ብሎ ይለቀኝ ይሆን? ወይስ "አንተ ዹተማርክ ሰው አይደለህ እንዎ? በዘመኑ አሠራር DM ማድሚግ ሲገባህ ለምን በሎሚ ትደበድባለህ?" ብሎ ይፈርድብኝ ይሆን? በመጚሚሻም በፍቅር እና በሕግ መሃል ተወጥሬ፥ አንቀጜ 2038ን ኚመተላለፍ፥ 2039(ሠ)ን ተማምኖ ኹመቆመር... "ይቅርብኝ!" አልኩ። ዚልቀን ንግሥት በሎሚ ኚመምታት፣ በሩቁ ማሰቡን መሚጥኩ። ኚላይብሚሪው አልወጣሁምፀ ቃና ዘገሊላም አልሄድኩም። ግን አንድ ተስፋ አለኝ... ምናልባት በሚቀጥለው ዓመት ዚፍትሐብሔር ሕጉ ተሻሜሎ "በጥምቀት በዓል ለፍቅር ተብሎ ዹሚወርወር ሎሚ በልዩ ሁኔታ ይፈቀዳል" ዹሚል አንቀጜ ኚተጚመሚበት... ያኔ ወጥቌ መወርወሬ አይቀርም! እስኚዚያው ግን እኔና ሕጉ በላይብሚሪ ተፋጠን እንውላለን። መልካም ምሜት ዛሬን በድጋሚ ፈግግግግ እድትሉ!!!! @MTULSU

ጥምቀት ሲመጣ ዹህግ ባለሙያ ወንዶቜ ኚቜሎት ይልቅ ጃንሜዳ ላይ "አዲስ ህግ" ሲያሚቁ ይታያሉ።! 👚‍⚖🍋 አንድ ዹህግ ባለሙያ ሎሚ ወርውሮ ደሚትሜ ላይ ካሚፈ፣ በህጉ አነጋገር "ይህቜ ልጅ ኚዛሬ ጀምሮ በሌላ ወንድ እንዳትታይ" ዹሚል ዚዕግድ ትዕዛዝ እንደመለጠፍ ይቆጠራል።🚫📜 ሎሚው ደሚትሜ ላይ ሲያርፍ፣ ባለሙያው "ይህ ልብ ዹኔ መሆኑን ዚሚያሚጋግጥ በቂ ማስሚጃ (Prima Facie Evidence) አግኝቻለሁ" ብሎ ለራሱ ይፈርማል።✍💖 ዹውል ግዎታፊ ሎሚውን አንስተሜ ካሞተትሜው፣ "ውሉን ያለምንም ተቃውሞ ተቀብያለሁ" (Acceptance of Offer) እንደማለት ነው። ኹዛ በኋላ "አልፈልግም" ማለት "ዹውል ጥሰት" (Breach of Contract) ያስኚትላል! 🀝⚠ዚጥምቀት ሎሚ ውርወራ "First and Final" ውሳኔ ነው። ይግባኝ (Appeal) ዚሚባል ነገር በባህሉ ፍርድ ቀት ተቀባይነት ዹለውም!⚖🙅‍♂ 💪ወንዶቜዚ ሎሚ ስትወሚውሩ "ዒላማቜሁ" ዹህግ ጥሰት ሳይሆን ዚልብ ስምምነት ይሁንላቜሁ!🎯❀ 💃 ለሎቶቜ ደግሞ ሎሚው ሲመጣ "ዚዕግድ ትዕዛዙን" በፈገግታ ተቀበሉ! እንኳን አደሚሳቹህ✚ ለፈገግታ ያህል!!! @MTULSU

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደሚሳቜሁ! መልካም በዓል! ሚዛን ቮፒ ዩኒቚርሲቲ ዹህግ ተማሪዎቜ ህብሚት @MTULSU
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደሚሳቜሁ! መልካም በዓል! ሚዛን ቮፒ ዩኒቚርሲቲ ዹህግ ተማሪዎቜ ህብሚት @MTULSU

Life is crazy and unpredictable. You never know when the last time you meet someone will be so treat every moment like it’s t
Life is crazy and unpredictable. You never know when the last time you meet someone will be so treat every moment like it’s the last. Rest in peace  🕊❀ Netsaneti 😭😭😭