fa
Feedback
MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

رفتن به کانال در Telegram

A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU

نمایش بیشتر
557
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
+2530 روز
آرشیو پست ها
March 8 Happy International Women's Day to all the incredible women who inspire change, lead with courage, and shape a bright
March 8 Happy International Women's Day to all the incredible women who inspire change, lead with courage, and shape a brighter future. 💜 @MTULSU

🌍 FALAS Ambassador Applications Now Open The Federation of African Law Students (FALAS) is pleased to announce that applications are open for the FALAS Ambassador position. If you are a 3rd-year law student or above, this is your opportunity to represent your institution, expand your network, and contribute to a vibrant community of African law students committed to legal excellence and continental unity. ✨ Who Should Apply? • Emerging student leaders • Passionate about academic engagement • Committed to collaboration across African law faculties 📌 Application Requirements: • Motivational Letter (350–450 words) • CV (Maximum 1 page) • One-Page Action Plan Step forward. Represent your institution. Create continental impact. 🌍⚖️ 🗓 Deadline: March 8, 2026 📩 Submit to: @likehimself or @Dirshu65 #FALAS #AfricanLawStudents #LegalLeadership #AmbassadorCall@MTULSU

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ! Happy 130th Anniversary of the Victory of Adwa!
እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ! Happy 130th Anniversary of the Victory of Adwa!

የአድዋ ድል በአለም አቀፍ ህግ እይታ *** በዳንኤል ፍቃዱ /ጠበቃና የህግ አማካሪ/ የአድዋ ድል በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ህግ (International Law) እና በዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ክስተት ነው።አድዋ ድል መሠረት የሆነው የሕግ ክርክር የሚጀምረው ከጦርነቱ በፊት በነበረው:: የውጫሌውል(Treaty of Wuchale) ላይበተፈጠረ የትርጉም ልዩነት ነው። ይህ ክስተት በአለም አቀፍ የውል ሕግ (Law ofTreaties) ታሪክውስጥ እስካሁንም ድረስ እንደ ትልቅ ማሳያ ይጠቀሳል። የአድዋ ድልኢትዮጵያ በአለም መድረክ ላይ ያላትን የሉዓላዊነት ጥያቄ በደም እና በውል ያረጋገጠችበት ነው።በአለም አ ቀፍ ህግ እይታ የአድዋ ድል የሚከተሉት ዋና ዋና ትርጉሞች አሉት፦                                                                                                                                                                    1. የውጫሌ ውል አንቀጽ 17፡ የትርጉም ማታለልየአድዋ ጦ ርነትመንስኤ የሆነው የዚህ አንቀጽ የአማርኛ እና የጣሊያንኛ ትርጉም አለመጣጣም ነበር።·      በአማርኛውቅጂ፡ኢትዮጵያ ከሌሎች የአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ማድረግ ከፈለገች በጣሊያን በኩል ማድረግ ትችላለች(Optional) ይላል።·      በጣሊያንኛውቅጂ፡ኢትዮጵያ ከሌሎች መንግስታት ጋር የምታደርገው ማንኛውም ግንኙነት በጣሊያን በኩል መሆን አለበት (Mandatory) ይላል።ጣሊ ያን በዚህየትርጉም ልዩነት በመጠቀም ኢትዮጵያ የጣሊያን "ሞግዚትነት"(Protectorate) ስርእንደገባች ለዓለም ሀገራት አወጀች። አፄ ምኒልክ ግን ይህንን ሉዓላዊነትን የሚጋፋ ማታለል መሆኑን በመጥቀስ ውሉን ውድቅ አደረጉት።                                                                                                         2. የዲፕሎማሲያዊ ክርክሩ ጥንካሬ                                                                                                      አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ የጦርነት ዝግጅት ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ የዲፕሎማሲ ስራ ሰርተዋል።·     ለአውሮፓነገስታት ደብዳቤ መጻፍ፡ አፄ ምኒልክ ለቪክቶሪያ (እንግሊዝ) እና ለሌሎች መሪዎች በጻፉት ደብዳቤ፣ ጣሊያን ውሉን በማጭበርበር የኢትዮጵያን ነጻነት ለመቀማት እየሞከረች መሆኑን በሕግ አግባብ አስረዱ።·      ውሉንበይፋ መሰረዝ፡ ኢትዮጵያ በጣሊያን በኩል ሳይሆን በቀጥታ ለሌሎች ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ደብዳቤዎችን መላክ በመጀመር፣ በተግባር "ሞግዚትነቱን" ውድቅ አደረገች ው። 3. የሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማረጋገጫ(Sovereignty)                                                              በ19ኛው ክፍለ ዘመን የአውሮፓ ሀያላን በበርሊን ጉባኤ (1884-85) አፍሪካን ሲከፋፈሉ፣ ጥቁር ህዝቦች የራሳቸው የህግ ስብዕና እንዳላቸው አይቆጥሩም ነበር። የአድዋ ድል ግን ፦·       ኢትዮጵያ በሀይል የማይደፈር የመንግስትነት መዋቅር ያላት መሆኑን አስመሰከረ።·       "Terra Nullius" (ባለቤት የሌለው መሬት) የሚለውን የቅኝ ግዛት ህግ በኢትዮጵያ ላይ እንዳይሰራ አደረገ።                                                                                                                                    4. የአዲስአበባ ውል(Treaty of Addis Ababa, 1896)                                                                        ድሉን ተከትሎ የተፈረመው የአዲስ አበባ ውል በአለም አቀፍ ህግ አይን እጅግ አስፈላጊ ሰነድ ነው። በዚህውል አማካኝነት፦· ሊያን የውጫሌን ውል (Treaty of Wuchale) በይፋ ሰረዘች።·       ኢትዮጵያ ፍጹም ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር መሆኗን ጣሊያን (እና የተቀረው ዓለም) በህግ እንዲያውቁ ተገደዱ። ይህ ውል ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሀገራት ጋር በደረጃ እኩል (Equal footing) ሆና የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንድትጀምር በር ከፈተ።                                                                                                           5. የቅኝ ግዛት ህግጋትን መቃወም(Challenge to Colonial Jurisprudence)                                በወቅቱ የነበረውየአለም አቀፍ ህግ በአውሮፓውያን የበላይነት ላይ የተመሰረተ ነበር። የአድዋ ድል ግን፦·       የራስን እድል በራስ የመወሰን (Self-determination) መርህ ገና በህግ ሳይደነገግ በተግባር እንዲታይ አድርጓል።·       ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ የህግ እና የሞራል መሰረት በመሆን፣ ሌሎች የአፍሪካ እና የእስያ ሀገራት ለነጻነታቸው እንዲታገሉ መንገድ አሳይቷል።                                                                                       6. የመንግስታቱማህበር (League of Nations) አባልነትአድዋ ያስከበረውነጻነት ኢትዮጵያበኋላ ላይ በ1923 ዓ.ም. የመንግስታቱ ማህበር አባል እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ደግሞ አንዲት የአፍሪካ ሀገር በአለም አቀፍ የህግ ተቋማት ውስ ጥ እኩል ድምጽ እንዲኖራት ያስቻለ ታሪካዊ ክስተት ነበር።                                                                                                                                          7. በአለም አቀፍ ደረጃ ያስገኘው ዲፕሎማሲያዊ ድልከአድዋ ድል  በኋላ፣ ኢትዮጵያየአለም አቀ ፍ ማህበረሰብ አባል መሆኗን የሚያሳዩ ክስተቶች ተከተሉ፦                                                                  ·      የኤምባሲዎችመከፈት፡ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ሩሲያ እና ጣሊያን ራሷ በአዲስ አበባኤምባሲዎቻቸውን ከፈቱ።                                                                                                                      ·      የቀይመስቀል ማህበር አባልነት፡ ኢትዮጵያ የጄኔቫ ስምምነቶችን (GenevaConventions ) በመፈረምበአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህግጋት ተሳታፊ ሆነች።                                                                               ·      ሉዓላዊእውቅና፡ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ብ ቸኛዋ (ከላይቤሪያ ጋር) በአውሮፓውያን እኩል የታወቀች ሀገር ሆነች። ባጠቃላይ፦ የአድዋ ድል በአለም አቀፍ ህግ አይን ሲታይ፣ "አፍሪካውያንየራሳቸው ህግእና አስተዳደርያላቸው፣ በአለምአቀፍ መድረክምእንደ መንግስትእውቅና ሊሰጣቸውየሚገባ ህዝቦችናቸው" የሚለውን እውነት በሀይልም በዲፕሎማሲም ያስመሰከረ ድል ነው። Join us: @MTULSU

#update ለምርጫ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ወደ ቤታቸው አይሄዱም ለተወሰኑ ቀናት ብቻ መርጠው እንዲመለሱ ይደረጋል ። የኤፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የካቲት 18 2018
#update ለምርጫ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች  ወደ ቤታቸው አይሄዱም  ለተወሰኑ ቀናት ብቻ መርጠው እንዲመለሱ  ይደረጋል  ። የኤፌዴሪ  ትምህርት  ሚንስቴር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የካቲት 18 2018 የህግ ተማሪዎች ህብረት

🏛️ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እና የፖሊስ ግዴታ፡ ሕጉ ምን ይላል? ⚖️ በመጀመሪያ ደረጃ፣ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 4️⃣4️⃣9️⃣ መሠረት በግልጽ "የፍትሕ ሥራን ማደናቀፍ" በሚል በወንጀል ያስጠይቃል። ፖሊስ ከሕግ በላይ ሊሆን የሚችልበት ምንም ዓይነት "ልዩ ሁኔታ" በሕገ-መንግሥቱም ሆነ በሌሎች ሕጎች አልተቀመጠም። 1️⃣. የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት (International Impact) አንድ ተጠርጣሪ በፍርድ ቤት ነፃ ከተባለ ወይም በዋስ እንዲፈታ ከታዘዘ በኋላ ፖሊስ ትዕዛዙን ባለመቀበል መልሶ የሚያስረው ከሆነ፦ ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ፦ ግለሰቡ ያለ ሕግ አግባብ ነፃነቱን ስለሚታገድ፣ ይህ ድርጊት በዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 9️⃣ ላይ የተቀመጠውን "ያለ ምክንያት አለመታሰር" መብትን በግልጽ ይጥሳል። 🚫👤 Arbitrary Detention፦ ይህ አይነቱ እስር "ዘፈቀደ እስር" ተብሎ የሚፈረጅ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የምትጥስበት ድርጊት ነው። 2️⃣. በዓለም አቀፍ ተቋማት ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች (እንደ Amnesty International እና Human Rights Watch) እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ ፍትሕ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲያጡ ያደርጋቸዋል፦ 📉 የደረጃ ዝቅጠት፦ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የሕግ የበላይነት መለኪያ (Rule of Law Index) ላይ ያላት ደረጃ ዝቅ እንዲል ያደርጋል። 💸 የኢኮኖሚ ተፅዕኖ፦ ዓለም አቀፍ ረዳት ድርጅቶችና ባለሀብቶች "ፍትሕ በሌለበትና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በማይከበርበት አገር መዋዕለ ንዋይ አናፈስም" በማለት ፊታቸውን እንዲያዞሩ ያደርጋል። 3️⃣. መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች ይህንን "የእስር አዙሪት" ለመስበር የሚከተሉት እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፦ ⚖️ ተጠያቂነት (Accountability)፦ ትዕዛዝ ያልፈጸሙ የፖሊስ አባላትና አመራሮች በግል በወንጀልና በዲስፕሊን እንዲጠየቁ ማድረግ። "ከበላይ ታዝዤ ነው" የሚል ሰበብ ከሕግ ተጠያቂነት አያድንም። ✨Habeas Corpus (አካልን ነፃ የማውጣታትአቤቱታ ማቅረብ )፦ ጠበቆችና ቤተሰቦች ግለሰቡ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታሰሩን በመግለጽ በአስቸኳይ ፍርድ ቤት እንዲቀርብና እንዲፈታ ክስ መመስረት። 🛡️ የፍትሕ ምክር ቤት ቁጥጥር፦ የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የፍርድ ቤት ትዕዛዝ መከበሩን የሚከታተል ገለልተኛ የክትትል ክፍል ማቋቋም ይኖርባቸዋል። ፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበሩ የሕግ የበላይነትhን ገደል የሚከት ድርጊት ነው። ፍርድ ቤት የፍትሕ ሥርዓቱ የመጨረሻ መቆሚያ በመሆኑ፣ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ካልተከበረ "ፍትሕ" ትርጉም አልባ ትሆናለች። Join Us:@MTULSU

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ የተጀመረው የመውጫ ፈተና መሸጋሸጉን ገለጹ። የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቷ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ባሰራጩት መልዕክት ፤ የቅድመ ም
+1
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ የተጀመረው የመውጫ ፈተና መሸጋሸጉን ገለጹ። የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቷ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ባሰራጩት መልዕክት ፤ የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) ዛሬ መጀመሩ ገልጸዋል። " ነገር ግን ያልታሰበ የኃይል መቆራረጥ ችግር በዳታ ማዕከል ላይ በማጋጠሙ ችግሩን በመፍታት እንደገና ለማስጀመር ጥረት የተደረገ ቢሆንም የፕሮግራም መዛባትን አስከትሏል " ብለዋል። በዚህም ምክንያት የፈተናው ሙሉ ፕሮግራም በአንድ ቀን መሸጋሸጉን ገልጸዋል። ሁሉም ፕሮግራሞች የዛሬን ጨምሮ ባሉበት ክፍለ ጊዜ ላይ ሆነው በተዋረድ በአንድ ቀን የተሸጋሸጉ መሆኑን አማልክተዋል። ዛሬ ፈተና ጀምረው የነበሩ ተፈታኞችም እንደሙከራ ፈተና (Mock Exam)  በመውሰድ ነገ በተመሳሳይ ሰዓት እንደገና ይፈተናሉ ተብሏል። @tikvahethiopia

ይህ ማስታወቂያ ለ(sponsor) በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል ትምህርታቸውን ለሚከታተሉት በሙሉ ነው ። 👇👇👇👇 @MTULSU
ይህ ማስታወቂያ ለ(sponsor) በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል ትምህርታቸውን ለሚከታተሉት በሙሉ ነው ። 👇👇👇👇 @MTULSU

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለረመዳን ጾም በሰላም አደረሳችሁ። መልካም ጾም እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!!! 👇👇👇👇 @MTULSU

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተወለደ ልጅ “አባትነት” ጉዳይ **** በዳንኤል ፍቃዱ / ጠበቃና የህግ አማካሪ/ አለም አቀፍ የሕፃናት እና የሴቶች መብት ድንጋጌዎች ይህንን ጉዳይ የሚመለከቱት በሁለት ዋና ዋና መርሆች ላይ ተመስርተው ነው፦ የሕፃኑ በላጭ ጥቅም (Best Interest of the Child) እና በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃትን መከላከል። በኢፌድሪ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ የወላጅነት ሥልጣን ዓላማ “የልጁን ጥቅም ማስጠበቅ“ እንደሆነ ይደነግጋሉ። ሃገራት ደግሞ እነዚህ ሁለት መርሆች ላይ በመመስረት እና “የአባትነት መረጋገጥ” (Paternity) እና “የወላጅነት ሥልጣን” (Parental Authority/Custody) የተለያዩ የሕግ ጽንሰ-ሐሳቦች መሆናቸውን በመለየት የራሳቸውን አቋምና ውሳኔ ይሰጣሉ፣ በዝርዝር እንመልከተው...

ያለ ስልጠና ሰርተፊኬት ጋብቻ አይፈቀድም! የኢፌድሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የፍቺ ቁጥር ለመቀነስ አዲስና ጠንከር ያለ መመሪያ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን
+1
ያለ ስልጠና ሰርተፊኬት ጋብቻ አይፈቀድም! የኢፌድሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የፍቺ ቁጥር ለመቀነስ አዲስና ጠንከር ያለ መመሪያ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ። ​📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦ 👉​መስፈርቱ፡ ማንኛውም ተጋቢ ወደ ትዳር ዓለም ከመግባቱ በፊት የቅድመ ጋብቻ ስልጠና ወስዶ 'የሰርተፊኬት' ባለቤት መሆን ይኖርበታል። ​መቼ ይጀመራል? አሰራሩን በቀጣዩ አመት ስራ ላይ ለማዋል ዝግጅት መጠናቀቁን የሚኒስቴሩ የአረጋውያንና ቤተሰብ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋዬ ሮበሌ ገልጸዋል። 👉​አጋር አካላት፡ ስራው ከሀይማኖት ተቋማት፣ ከሀገር ሽማግሌዎች እና ከሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ጋር በቅንጅት ይከናወናል። ​📉 ለምን አስፈለገ? በአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ መረጃ መሰረት፣ በከተማዋ የፍቺ መጠን ካለፉት ዓመታት አንጻር የ54 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ለትዳሮች መፍረስ ዋነኛው ምክንያት "የግንዛቤ እጥረት" መሆኑን ያመነው ሚኒስቴሩ፣ ይህንን ለመፍታት ስልጠናውን አስገዳጅ አድርጎታል። ​💡 ምን ተዘጋጅቷል? ​ለሰልጣኞች የሚያገለግሉ የማስተማሪያ ማኑዋሎች ተዘጋጅተዋል። ​በቤተሰብ ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ተቋማት በቅንጅት የሚሰሩበት የጋራ ፎረም ተመስርቷል። ​"ትዳር በስሜት ብቻ ሳይሆን በዕውቀትም ሊመራ ይገባል" የሚለው ይህ መመሪያ፣ በሀገሪቱ የማህበራዊ ትስስር ላይ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል። የጉድ ሀገር ገንፎ እያደር ይፋጃል😂😂 @legal_infoo

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
+1
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ መንግሥት ዕቅድ መያዙ ይታወቃል፡፡ በዕቅዱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት ቢደረግም፤ ከክልሎች፣ ከትምህርት ቤቶች እና ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አለመካሔዱን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ መንግሥት "ዕቅዱ ተግባራዊ ይሆናል ብሎ እስካሁን ውሳኔ አለማሳለፉን" የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በቀጣይ ሳምንታት ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና የሕዝብ ተወካዮችን ጨምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተደረገው ውይይት ከሎጂስቲክስ እና ከአካዳሚክ ጉዳዮች ጋር እንዴት ይጣጣማል በሚለው ላይ ጥያቄ ከማቅረብ ውጪ፤ "ሀሳቡ ተግባራዊ ቢሆን እንደሚደግፉት" መግለጻቸውን ጠቅሰዋል። ከውይይቱ በኋላ ሀሳቡ ለፓርላማ እንደሚቀርብና የራሱ የሆነ ተቋም ተቋቁሞለት ሕግ ይወጣለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ አስረድተዋል። ዕቅዱ ተቀባይነት ካገኘ በ2019 ዓ.ም እንደሚተገበር ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ሆኖም በውይይቱ ወቅት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ማኅበረሰቡ ዕቅዱን ካልፈለገው የሚቀርበት ሁኔታ እንዳለም ጠቁመዋል፡፡ የእርስዎ አቋም ምንድነው?? @MTULSU

ለማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ፍሬሽማን ተማሪዎች፦ ከወዲሁ መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ እየተመኘን እንደሚታወቀው የህግ ትምህርት ቤት (Law School) የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር ትምህርት በስኬት እንደተጠናቀቀ አቅምና ፍላጎት ያላቸውን 40–50 ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅቷል። በድጋሚ መልካም ፈተና! To Social Science Freshman Students: We wish you all the very best in your upcoming examinations. Following the successful completion of the first phase of 2018 E.C academic year, the Law School is ready to admit 40–50 capable and motivated students who have the interest. Once again Best of luck in your exams! For further info 👇👇👇👇 Join us: @MTULSU

#ExitExam የመውጫ ፈተና (Exist Exam) የሚሰጥበት ጊዜ ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑ ተገለጸ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መርሃ-ግብር መሰ
#ExitExam የመውጫ ፈተና (Exist Exam) የሚሰጥበት ጊዜ ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑ ተገለጸ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መርሃ-ግብር መሰረት፣ የ2018 ትምህርት ዘመን አጋማሽ የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) ከየካቲት 16 - 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል። ይህንን የፈተና ፕሮግራም ተቋማት ለተማሪዎቻቸው እያሳወቁ ይገኛሉ።

#As MTU schedule 👆👆👆 2nd semester course registration for all regular students. Join us. @MTULSU
#As MTU schedule 👆👆👆 2nd semester course registration for all regular students. Join us. @MTULSU

"ሎሚ ውርወራ እና Tort Law" "ሎሚ ብወረውር ደረቷን መታሁት፣ አወይ ኩላሊቷን ልቧን ባገኘሁት።...." ጥንት ነበር ያ!... አባቶቻችን ለወደዷት ኮረዳ ሎሚ ወርውረው፣ ፍቅራቸውን ገልጸው፣ በሎሚ ምት ልቧን አሸንፈው ትዳር የሚመሠርቱት — ድሮ ነበር። ዛሬ ግን ዘመን ተቀይሯል። ሎሚው በከረሜላ፣ ደብዳቤው በቴክስት፣ የሎሚው ሽታም በሽቶ ተተክቷል። ነገር ግን የጥምቀት በዓል ሲመጣ ያ የድሮው "ሎሚ የመወርወር" አምሮት በአንዳንዶቻችን (በተለይ በፍቅር ህመም ለተያዝነው) ልብ ውስጥ ማቅበዝበዙ አይቀርም። ዛሬ ከሰዓት... ላይብረሪ እያጠናሁ ሳለሁ አንድ እንግዳ ሀሳብ መጣብኝ። በሚዛን እየተከበረ ያለው የቃና ዘገሊላ ድባብ ከሩቅ ይጠራኝ ዠመር። "ለምን አልወጣም?" አልኩ ለራሴ። ለምን ሄጄ፣ በልቤ ላይ "Exclusive Ownership" ያላትን ያቺን ልጅ ፈልጌ አላገኛትም? ሳስባት የምደነግጥላትን፣ ልቤን በውብ ምስሏ የሞላችውን ልጅ አግኝቼ፣ አንድ ሎሚ ገዝቼ "ውዴ ሆይ፣ የወደድኩሽ እኮ ድሮ ነው!" ብዬ ሎሚ ብወረውርባትስ? Romantic ነው አይደል? በባህል መነጽር ሲታይ "የፍቅር ሰው!" ያስብላል። ነገር ግን ችግሩ እዚህ ጋር ነው። እንደምታውቁት እኔ የሕግ ተማሪ ነኝ። የሕግ ተማሪ ደግሞ እንኳን ሎሚ፣ አበባም ሲሰጥ "ይሄ ነገር በሕጉ አግባብ እንዴት ይታያል?" ብሎ ማሰቡ አይቀርም — አንዳንዴ ባያስብም። እናም Romantic ሀሳቤን ይዤ ከላይብረሪ ልወጣ ስል፣ ከፊት ለፊቴ የተቀመጠው Civil Code (የፍትሐብሔር ሕግ) "ቆይ ወዴት?" ብሎ አፈጠጠብኝ። ወዲያውኑ አንቀጽ 2038 (Tort Law) አይኔ ላይ ድቅን አለብኝ! አንቀጽ 2038 እንዲህ ይላል፦ "አንድ ሰው ሆነ ብሎ ሌላው ሰው ሳይፈቅድ በሚያደርገው መንካት በዚህ በመንካቱ ጥፋተኛ ነው።" ይልና ይቀጥላል... "ሰውዬውን በቀጥታም ሆነ ወይም በሌላ ሕይወት ባለው ወይም በሌለው ነገር አማካይነት ቢነካውም ጥፋተኛ ነው።" እንግዲህ አስቡት! ለፍቅር ብዬ የምገዛው ሎሚ በሕጉ ፊት "ሕይወት የሌለው ነገር(object)" ነው። ያንን ሎሚ ወርውሬ የልጅቷን ደረት ወይም ትከሻ ባገኘው፥ በሕጉ አነጋገር "ያለ ፈቃድ መንካት" (Battery) ፈጽሜያለሁ ማለት ነው። ማሰቤን አላቆምኩም... ሎሚውን ወርውሬባት በፈገግታ ፈንታ "ይሄ ሰው ግን ምን ነካው?" ብላ ብትጮህስ? ወይም ሎሚው ስቶ ግንባሯን ቢላትስ? ወዲያውኑ የፍቅር ጥያቄዬ ወደ "ክስ" ተቀየረ ማለት ነው። "ክቡር ፍርድ ቤት ተከሳሽ፣ ደንበኛዬን ያለ ፈቃዷ በሎሚ በመደብደብ አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ጉዳት አድርሶባታል" ብሎ ሲያነብልኝ ታየኝ — ወፍራሙ ሰውዬ። የፍቅር መዝገብ ሳይሆን ከውል ውጪ የሚመጣ ኃላፊነት (Tortious liability) መዝገብ ሲከፈትብኝ ታየኝ! ግና ተስፋ አልቆረጥኩም። እንደማንኛውም የሕግ ሰው "መውጫ ቀዳዳ" (Defense) መፈለግ ጀመርኩ። ሕጉን ሳገላብጥ ሳገላብጥ ቆይቼ አንቀጽ 2039(ሠ) ላይ ደረስኩ። አንቀጽ 2039(ሠ) እንዲህ ይነበባል፦ "የተከሳሹ ሥራ አእምሮ ባለው ሰው ግምት የሚገባ ነው የሚያሰኝ ሌላ ማናቸውም ምክንያት በተገኘ ጊዜ ሁሉ" ተከሳሹ ነጻ ነው። "አሃ!" አልኩ በልቤ። እዚህ ጋር ነው ጨዋታው! "ክቡር ፍርብ ቤት ድርጊቱ የፈጸምኩት በጥምቀት በዓል ነው። በጥምቀት ደግሞ ሎሚ መወርወር 'አእምሮ ባለው ሰው ግምት' (Reasonable person standard) ተቀባይነት ያለው ባህል ነው" ብዬ መከራከር እችላለሁ። ሎሚ የመልካም መዓዛ እና የፍቅር መግለጫ እንጂ ድንጋይ ወይም ጠብመንጃ አይደለም። ስለዚህ ድርጊቴ በሕጉ ፊት "Socially acceptable" ስለሆነ ጥፋት ሊሆን አይገባም። አይደል!? ነገር ግን... እንደገና አሰብኩት። በዘመናችን "አእምሮ ያለው ሰው" (Reasonable person) ሎሚ መወርወርን እንደ ፍቅር ጥያቄ ይወስደዋል ወይስ እንደ ጥቃት? ልጅቷ "በሎሚ የምትመታኝ ምን አድርጌህ ነው?" ብላ የTort ክስ ብትመሠርትብኝ ዳኛው "ባህል ነው" ብሎ ይለቀኝ ይሆን? ወይስ "አንተ የተማርክ ሰው አይደለህ እንዴ? በዘመኑ አሠራር DM ማድረግ ሲገባህ ለምን በሎሚ ትደበድባለህ?" ብሎ ይፈርድብኝ ይሆን? በመጨረሻም በፍቅር እና በሕግ መሃል ተወጥሬ፥ አንቀጽ 2038ን ከመተላለፍ፥ 2039(ሠ)ን ተማምኖ ከመቆመር... "ይቅርብኝ!" አልኩ። የልቤን ንግሥት በሎሚ ከመምታት፣ በሩቁ ማሰቡን መረጥኩ። ከላይብረሪው አልወጣሁም፤ ቃና ዘገሊላም አልሄድኩም። ግን አንድ ተስፋ አለኝ... ምናልባት በሚቀጥለው ዓመት የፍትሐብሔር ሕጉ ተሻሽሎ "በጥምቀት በዓል ለፍቅር ተብሎ የሚወርወር ሎሚ በልዩ ሁኔታ ይፈቀዳል" የሚል አንቀጽ ከተጨመረበት... ያኔ ወጥቼ መወርወሬ አይቀርም! እስከዚያው ግን እኔና ሕጉ በላይብረሪ ተፋጠን እንውላለን። መልካም ምሽት ዛሬን በድጋሚ ፈግግግግ እድትሉ!!!! @MTULSU

ጥምቀት ሲመጣ የህግ ባለሙያ ወንዶች ከችሎት ይልቅ ጃንሜዳ ላይ "አዲስ ህግ" ሲያረቁ ይታያሉ።! 👨‍⚖️🍋 አንድ የህግ ባለሙያ ሎሚ ወርውሮ ደረትሽ ላይ ካረፈ፣ በህጉ አነጋገር "ይህች ልጅ ከዛሬ ጀምሮ በሌላ ወንድ እንዳትታይ" የሚል የዕግድ ትዕዛዝ እንደመለጠፍ ይቆጠራል።🚫📜 ሎሚው ደረትሽ ላይ ሲያርፍ፣ ባለሙያው "ይህ ልብ የኔ መሆኑን የሚያረጋግጥ በቂ ማስረጃ (Prima Facie Evidence) አግኝቻለሁ" ብሎ ለራሱ ይፈርማል።✍️💖 የውል ግዴታ፦ ሎሚውን አንስተሽ ካሸተትሽው፣ "ውሉን ያለምንም ተቃውሞ ተቀብያለሁ" (Acceptance of Offer) እንደማለት ነው። ከዛ በኋላ "አልፈልግም" ማለት "የውል ጥሰት" (Breach of Contract) ያስከትላል! 🤝⚠️የጥምቀት ሎሚ ውርወራ "First and Final" ውሳኔ ነው። ይግባኝ (Appeal) የሚባል ነገር በባህሉ ፍርድ ቤት ተቀባይነት የለውም!⚖️🙅‍♂️ 💪ወንዶችየ ሎሚ ስትወረውሩ "ዒላማችሁ" የህግ ጥሰት ሳይሆን የልብ ስምምነት ይሁንላችሁ!🎯❤️ 💃 ለሴቶች ደግሞ ሎሚው ሲመጣ "የዕግድ ትዕዛዙን" በፈገግታ ተቀበሉ! እንኳን አደረሳቹህ✨ ለፈገግታ ያህል!!! @MTULSU

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች ህብረት @MTULSU
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች ህብረት @MTULSU

Life is crazy and unpredictable. You never know when the last time you meet someone will be so treat every moment like it’s t
Life is crazy and unpredictable. You never know when the last time you meet someone will be so treat every moment like it’s the last. Rest in peace  🕊❤️ Netsaneti 😭😭😭