uk
Feedback
MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👚‍🎓

MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👚‍🎓

ВіЎкрОтО в Telegram

A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU

ППказатО більше
557
ПіЎпОсМОкО
+124 гПЎОМО
+47 ЎМів
+2530 ЎеМь
Архів ЎПпОсів
✋✋7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ✋✋      👉ሊጠናቀቅ 4 ቀን ብቻ ቀሚው👈 ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ለ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በመራጭነት ዚሚመዘገቡበት ሂደት ቀድሞ በተለጠፈው መሠሚት ሲሆን አሁን ዹቀሹው 4 ቀን ብቻ ስለሆነ ዋናው ግቢ ያላቜሁ ተማሪዎቜ ዛሬ ማክሰኞ 8:00 ሰዓት ጀምሮ National Id እና ዚዩኒቚርሲቲ መታወቂያ በመያዝ Ict room ተገኝታቜሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን። # ይሳተፉ! # ይመዝገቡ! # ይምሚጡ! ✍ዚተማሪዎቜ ሕብሚት ጜ/ቀት      ✋✋7th National Election✋✋               👉Only 4 days left 👈 The process for university students to register as voters for the 7th National Election is as previously announced, and now there are only 4 days left. We urge students on the main campus to register at the ICT room starting today,Tuesday, 8:00 local time with their National ID and University ID. # Participate! # Register! # Vote! ✍MTU students' union office

ዚመውጫ ፈተና ዚሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ኹሰኔ 24 እስኚ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድሚስ እንደሚሰጥ ዚትምህርት ምዘናና ፈተ
ዚመውጫ ፈተና ዚሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ኹሰኔ 24 እስኚ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድሚስ እንደሚሰጥ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አሳውቋል። በሌላ በኩልፊ - ዚሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ኚግንቊት 17 እስኚ ግንቊት 20 ቀን 2018 ዓ/ም - ዚቅድመ ምሹቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ኹሰኔ 2 እስኚ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም - ዚድህሚ ምሹቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ኹሃምሌ 29 እስኚ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም - ዚመሰሚታዊ ዚንባብና ዚስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መሹጃ መሰብሰብ ኚሚያዚያ 26 እስኚ ግንቊት 7 ቀን 2018 ዓ/ም

〰 I mportant Latin Legal Term and Abbreviations: ___ • LL.B - Legum Baccalaureus [Bachelor of Laws] • LL.M - Legum Magister [Master of Laws] • LL.D - Legum Doctor [Doctor of Laws] The two L's are often confused us to mean, but the actual abbreviation is based on the Latin words as shown above. In Latin abbreviations, the plural form of a word is indicated by doubling the letter, for example “ pp. is Latin abbreviation for – pages". hence ‘LL.’ is short for Laws. Legum is the plural form of the Latin word lex, which means "specific laws". _ • Ead. - eadem - The same • Id. - Idem - The same • ibid. - ibidem - In the same place • i.a. - inter alia - Among other things • i.e. - id est - That is, / in other words • viz. - videlicet - Namely / that is to say • vs or v. - versus - Against _ • a quo - Previous • ab extra - From outside • ab initio - From the beginning • actus reus - Guilty act • ad hoc - For this • ad idem - To the same thing • ad valorem - According to value • affidavit - A formal statement of fact • Audi alteram partem - Hear the other side • bona fide - In good faith • bona vacantia - Ownerless goods • caveat emptor - Let the buyer beware • consensus ad idem - Agreement as to the subject or object of the contract. • cui bono - As a benefit to whom? • de facto - Concerning fact • doli incapax - Incapable of guilt • ejusdem generis - Of the same class • ex facie - On the face • ex officio - From the office • ex post facto law - A law that makes a past act illegal that was not illegal when it was done. • in camera - In the chamber • in pari materia - In the same matter • locus standi - The right of a party to appear and be heard before a court. • male fide - Bad faith • mens rea - Guilty mind • nemo dat quod non habet - No one gives what he doesn't have. • obiter dictum - A thing said in passing • pro bono publico - For the public good • quid pro quo - This for That • ratio decidendi - Reason for the decision • res judicata - A matter that has been finally adjudicated, no further appeals or legal actions by the involved parties is now possible. • stare decisis - The obligation of a judge to stand by a prior precedent. • sui generis - Something that is unique amongst a group. • supra - Above actio in personam "action against a person" ad hominem "to the man" (Appealing to a person's interests or prejudices rather than to reason) ad litem "for the suit/action" amicus curiae "friend of the court" bona fide "in good faith" de jure "according to law / by right" Dura lex, sed lex. "The law is hard, but it is the law." ex curia "out of court" ex lege - "arising from the law; as a matter of law" habeas corpus -"You shall have the body. / (I command that) you have the body." (A judge's order to bring a person before the court to see whether he is justly imprisoned.) Hoc indictum volo. - "I wish this to be unsaid. (I withdraw the statement.)" Ignorantia legis neminem excusat. "Ignorance of the law excuses no one." in camera - "in chamber / in secret / closed session" in facie curiae - "in the face/presence of the court" in personem "against a/the person" ipso facto "by the fact itself / by that very fact" lex scripta "written law" mala fide "in/with bad faith / treacherously" mala in se "bad/evil in itself" ne bis in idem "A person may not be punished twice for the same thing." ne exeat "Let him not go out from the jurisdiction of the court" noli-me-tangere "do not touch me" (A warning against touching) nolle prosequi "I do not wish to pursue" (A prosecutor is dropping all or part of an indictment.) nolo contendere "I do not wish to contend." (A guilty plea, leaving open the option of denying alleged facts in later proceedings) non compos mentis "not having control of the mind" (Not legally responsible) nunc pro tunc "now for then" (Indicates action in the present that should have been taken before) per se "in/by itself" prima facie "on first appearance / at first sight" pro forma "as a matter of form / according to form" pro tempore "for the time / temporarily"

በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ ያሉ ተማሪዎቜ ለ7ኛው ምርጫ ዚመራጭነት ምዝገባ ኚሚያዝያ 17-24/2018 ዓ.ም እንደሚኚናወን ተሰምቷል፡፡ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ለዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚመመዝገቢያ ፖ
በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ ያሉ ተማሪዎቜ ለ7ኛው ምርጫ ዚመራጭነት ምዝገባ ኚሚያዝያ 17-24/2018 ዓ.ም እንደሚኚናወን ተሰምቷል፡፡ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ለዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚመመዝገቢያ ፖርታል (https://uni.mirchaye.nebe.org.et) አዘጋጅቷል፡፡ ምዝገባውን ለማኹናወን ምን ያስፈልጋል? ➫ በሚገኙበት ዩኒቚርሲቲ ኔትዎርክ ላይ መሆን፣ ➫ ስልክ፣ ኮምፒውተር ወይም ላፕቶፕ፣ ➫ ብሔራዊ መታወቂያ፣ ➫ ብሔራዊ መታወቂያ ሲያወጡ ዚወጣበት ዚስልክ ቁጥር፡፡

ዚፌደሬሜን ምክር ቀት ዚህገመንግስት ትርጉም ዚሚሰጥባ቞ዉ ጉዳዮቜ ምንድ ና቞ዉ፡፡ በኢፌድሪ ዚፌደሬሜን ምክር ቀት ስልጣን ዹሚደነገግዉ አዋጅ ቁጥር 1262 መሰሚት ለህገመንግስት ትርጉም ዚሚቀርቡት ዚሚኚተሉት ጉዳዮቜ ና቞ዉ፡፡ ✅ በሕገ መንግስቱ ውስጥ ለመንግስት አካላት ወይም ሌሎቜ ተቋማት በተሰጡት ስልጣን፣ ተግባራትና ኃላፊነቶቜ ይዘትና ዳራ ላይ ዹሕገ-መንግስት ትርጉም ጥያቄ ሲነሳ ✅ በፌደራል መንግስትም ሆነ በክልል ሕግ አውጪ አካላት ዚሚወጡ ሕጎቜ ኹሕገ መንግስቱ ጋር ይቃሹናል ዹሚል ጥያቄ ሲነሳና ጉዳዩ በሚመለኹተው ፍርድ ቀት ወይም በባለ ጉዳዩ ሲቀርብፀ ✅ በማናቾውም ዚመንግስት አካል ወይም ዚባለስልጣን ዚመጚሚሻ ውሳኔ በሕገ መንግስቱ ዚተደነገጉት መሰሚታዊ መብቶቜና ነጻነቶቜ ተጥሰዋል በሚል ጥያቄ ለማቅሚብ መብት ባለው ሰው አቀቱታ ሲቀርብ ✅  በፌደራል ዚመንግስት አካላት መካኚል ዚሚነሱ አለመግባባቶቜ ሲቀርብ ✅ በፌደራል መንግስቱ እና በክልል መንግስታት መካኚል ዚሚነሱ አለመግባባቶቜ ሲኖሩፀ ✅  በክልሎቜ መካኚል ዚሚነሱ አለመግባባቶቜ ሲኖሩፀ ✅ በፍርድ ቀት ሊወሰን በማይቜል በማናቾውም ሕገ መንግስታዊ ጉዳይ ላይ በፌደራል ወይም በክልል ሕግ አውጪ ምክር ቀት አንድ ሶስተኛ አባላት ወይም በፌደራልም ሆነ በክልል አስፈጻሚ አካላት ጥያቄ ሲቀርብፀ ✅  በፌደራል መንግስት ዚሚያወጣ቞ው ሕጎቜ በክልሎቜ ስለሚፈጞሙበት ሁኔታ አለመግባባት ሲፈጠርና ጥያቄውም በሚመለኹተው አካል ሲቀርብፀ ✅ ዹክልል መንግስት ህጎቜና ፖሊሲዎቜ በህገ መንግስቱ ውስጥ በተደነገጉት መርሆዎቜና ዓላማዎቜ ላይ ዚተመሰሚቱ አይደለም ዹሚል ክርክር ሲቀርብ፣ ✅ በፌደራል መንግስት፣ በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አንድ ሶስተኛ አባላት ወይም ዹክልል ምክር ቀት አንድ ሶስተኛ አባላት ሲቀርብፀ ✅ ዹክልል ሕገ መንግስት ተርጓሚ አካል ዹክልል ሕገ መንግስትን በመተርጎም ሂደት ቀደም ሲል በፌደሬሜን ምክር ቀት ወይም በሌላ ክልል ሕገ መንግስት ተርጓሚ አካል በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ ኹተሰጠ ዹሕገ መንግስት ተርጉም ዹተለዹ ውሳኔ ባሰበ ዹክልል ሕገ መንግስት ተርጓሚ አካል በሚቀርብ ጥያቄፀ በእነዚህ ኹላይ በተዘሚዘሩት ጉዳዮቜ ዚህገመንግስት ትርጉም ሊሰጥ ይቜላል፡፡

በተፋጠነ ሥነ ሥርዓት ታይተው ዹሚወሰኑ ጉዳዮቜ (Accelerated Procedure) (ዹፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ  300 - 314) (1). ዚንግድ ማህበር አስ቞ኳይ ስብሰባ     እንዲጠራ ይደሹግልኝ (2). ለአካለ መጠን ያልደሚሰ ልጅ        በስጊታ/በውርስ ስለሚተላፍ        ንብሚት አቀቱታ (3). በንግድ ድርጅት/በማህበር ኹተሰጠው        ስልጣን  ውጪ ሰርቷል/ፈፅሟል ዹሚል        አቀቱታ (4). ዚንግድ ማህበር ውሣኔን በመቃወም         ዚሚቀሚብ አቀቱታ (5). ዚጉዲፈቻ ስምምነት ይፅደቅልን አቀቱታ (6). ሞግዚትነ቎ ይሚጋገጥልኝ ዹሚል አቀቱታ (7). ክስ ይዛወርልኝ ዹሚል አቀቱታ              (8). ወላጅነት ይሚጋገጥልኝ ዹሚል አቀቱታ (9). ስም ይለወጥልኝ ዹሚል አቀቱታ (10). ልጅነቮ ይታወቅልኝ ዹሚል አቀቱታ (11). በስምምነት ዹሚቀር ፍቺ ይፅደቅልን           ዹሚል አቀቱታ (12). ወራሜነ቎ ይሚጋገጥልኝ ዹሚል አቀቱታ (13). አካልን ነፃ ዚማውጣት አቀቱታ          ( Habeas Corpus Suit) (14). መተላለፊያ መንገድ ይኚፈትልኝ          ዹሚል አቀቱታ (15). እሜግ ይኚፈትልኝ ዹሚል አቀቱታ (16).ዚመጥፋት ውሣኔ ይሰጠን ዹሚል አቀቱታ

CIVIL CODE SUCCESSION ARTICLES AMHARIC-ENGLISH.pdf5.40 KB

+2
CIVIL CODE PROPERTY LAW (1).pdf1.92 MB

Happy Ethiopian Easter (Fasika). Dear MTULSU Members, the Mizan Teppi university community, and all Ethiopians, On behalf of
Happy Ethiopian Easter (Fasika). Dear MTULSU Members, the Mizan Teppi university community, and all Ethiopians, On behalf of the Mizan Teppi university law students union we extend our warmest wishes for a happy and blessed Fasika. This special occasion reminds us of hope, renewal, and unity. It is a time to reflect, support one another, and move forward together with a shared commitment to respect, justice, and community. May this Fasika bring peace to your hearts, joy to your families, and strength in your journey. Happy Easter! With sincere regards, @MTULSU

አዋጅ ቁ.1410/2018 ወይም ዹወንጀል ሕግ ስነ-ሥርዓትና ዚማስሚጃ ሕግ በHPR መፅደቁ መልካም ነገር ነውፀ ለዓመታት ዚተለፋበት ሰነድ ነውፀ ብዙ አዳዲስና ጥሩ ጥሩ ነገሮቜን ዚያዘ ነውፀ በስራው ዚተሳተታፉት አካላት በሙሉ ምስጋና ይገባ቞ዋል! ይህ በእንዲህ እንዳለ ኹዚህ በፊት ባዚሁት ሹቂቅ ላይ ሕጉ ተግባራዊ መሆን ዹሚጀምሹው በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ኚወጣ ኹ180 ቀናት (6 ወር) በኋላ ነው ይላል። በመጚሚሻው ሰነድ ላይ ይህ ጊዜ እንዳለ አልፎ/ፀድቆ ኹሆነ (መፅደቅም አለበት ለsensitization ሰፊ ጊዜ ስለሚያስፈልግ) አዲሱ ሕግ ተግባራዊ ዹሚሆነው በሚቀጥለው ዓመት ነው። ዚማጠናቀቂያ ስራዎቜ ዚሚሰሩበት ጊዜ + ለሕትመት ዚሚያስፈልግ ጊዜ + 6 ወር ኚዚያ ወደ ተግባር መግባት! It is going to be a long time but it will be a tiny fraction of the time needed to get to this stage. So, till then, please, hold on to your 1961 CPC. Cheers!በደጀንግርማ

For more information, you can visit their linkdin address above.

Legal Ideas Forum International (LIFIN) Ethiopia Call for Applications The Legal Ideas Forum International (LIFIN) – Ethiopia
Legal Ideas Forum International (LIFIN) Ethiopia Call for Applications The Legal Ideas Forum International (LIFIN) – Ethiopia is now opening applications for its National executive and Regional,campus director Leadership Teams. We are currently accepting applications for the following positions: National Executive Committee 1.Deputy National Campus Director 2.Secretary 3.Financial Secretary 4.Director of Media & Publicity 5.Director of Programs, Policies & Projects 6.Director of Academics, Moot & Mock Trial 7.Director of Socials & Welfare 8.Public Relations Officer Regional Leadership 1.Regional Campus Directors (All regions) 2.Deputy Regional Directors Campus-Level Leadership 3.Campus Directors (All universities) 4.Campus Ambassadors Application Requirements Updated CV (maximum 2 pages) Leadership Experience Deadline April 12 Submit email- lifinethiopia@gmail.com Mention your specific position in the subject line FOR KNOWLEDGE AND JUSTICE

Take part in this opportunity and represent our institution.

ቻዉ🀷‍♂ ስለነበሚን ቆይታ እናመሰግናለን ስንለይህ በእምባ ነው ኹ64 አመት በኋላ ....😃😅 On behalf of all legal practitioners..
ቻዉ🀷‍♂ ስለነበሚን ቆይታ እናመሰግናለን ስንለይህ በእምባ ነው ኹ64 አመት በኋላ ....😃😅 On behalf of all legal practitioners..

Are you interested in attending an online training ? Ethiopian Human Rights Commission Organized online training on "Youth on Human Rights and Transitional Justice" Digital certificate available upon completion. Enjoy it! https://online.atingi.org/course/view.php?id=5069

ምክር ቀቱ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን መርምሮ አፀደቀ ---------------------- (ዜና ፓርላማ) መጋቢት 24፣ 2018 ዓ.ምፀ ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በ13ኛ መደበኛ ስብሰባውፀ ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን አፅድቋል፡፡ በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዹሕግና ፍትህ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ  ሪፖርት እና ዚውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ ሹቂቅ ሕጉ በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሥርዓት ዹወንጀል ፍርድ ሂደት ዚተጠርጣሪን እና ዚተኚሳሜን እንዲሁም በወንጀል ምክንያት ዚተጎዱ ሰዎቜን ሰብአዊ መብቶቜ ለማክበርና ለማስኚበር ዹሕግ ዚበላይነት በማስፈን ዚአሰራር ስርዓትን ለመዘርጋት ዚሚያስቜል መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጞዋል፡፡ ዹተቀላጠፈ ዚፍትህ ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል እና ልዩ ዹወንጀል ምርመራ ዘዮን እንዲሁም ለተጎጂዎቜ ካሣ ዚሚኚፈልበትን አግባብ ያካተተ ዓለም አቀፍ መርህን ዹተኹተለ ሹቂቅ ሕግ እንደሆነ ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ  አያይዘው አስሚድተዋል፡፡ ሹቂቅ ሕጉ ኚኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት እና ኢትዮጵያ ኚተቀበለቻ቞ው ዓለም አቀፍ ስምምነቶቜ፣ መርሆቜ እና እሎቶቜ እንዲሁም ኹወንጀል ህጉ ጋር ዚተጣጣመና ዘመናዊ በመሆኑ ጠቀሚ እንደሆነ  ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል፡፡   ሹቂቅ ህጉ በህገ መንግስቱ፣ በወንጀል ሕጉ፣ ዓለም አቀፍ ህጎቜ እና በሌሎቜ አግባብነት ባላ቞ው ህጎቜ ዚተሚጋገጡ ልዩ ትኩሚት ለሚያሻ቞ው ለሎቶቜ፣ ህፃናት እና አካል ጉዳተኞቜ ዚተሰጣ቞ውን መብቶቜ ለማሚጋገጥ ዚሚያስቜል እንደሆነም ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ገልጞዋል፡፡ ዹምክር ቀት አባላት በበኩላ቞ው ሹቂቅ አዋጁ ሹጅም ጊዜ ዹቆዹና ዹዘገዹ ቢሆንም በህዝቡ ዘንድ ዚቅሬታ ምንጭ ዚነበሩ ቜግሮቜን ለመፍታት ወቅቱን ዚሚመጥን አዋጅ በመሆኑ ዚህዝብን ዚፍትህ ሥርዓቱን ለማስፈን እንደሚያግዝ ገልጞዋል፡፡ ዚዜጎቜን ሰብአዊ እና ዲሞክራሲአዊ መብቶቜን ለማስኚበር እና ዚፍትህ ሥርዓቱን በማዘመን ወቅቱን ያዋጅ አግልግሎት ለመስጠት ሹቂቅ አዋጁ ሚናው ዹጎላ መሆኑን ዹምክር ቀት አባላት አመላክተዋል፡፡፡ በሌላ በኩል ዹምክር ቀት አባላት በበኩላ቞ውፀ ሹቂቅ አዋጁ በአተገባበር ሂደት ላይ ሊያጋጥሙ ዚሚቜሉ ቜግሮቜን ታሳቢ በማድሚግ ኚፍትህ አካላት ጋር መወያዚት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ ኚምርመራ ሂደት እና ኚዲጂታል አሰራሮቜ ጋር በተያያዘ ዜጎቜን ህገ መንግስታዊ መብትን በጠበቀ መልኩ መሆን እንዳለበት ዹምክር ቀት አባላቱ አስገንዝበውፀ በማሚሚያ ቀት ቆይተው ፍርድ ቀት ነፃ ዹሚላቾው ዜጎቜ ዚካሳ ክፍያ ሥርዓትን ለመዘርጋት በግልጜ በሹቂቅ አዋጁ ማስቀመጥ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ምክር ቀቱፀ ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅ ፀ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 አድሚጎ በሁለት ተቃውሞፀ በአብላጫ ድምጜ አጜድቋል፡፡ Via : HPR

ምክር ቀቱ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን መርምሮ አፀደቀ ---------------------- (ዜና ፓርላማ) መጋቢት 24፣ 2018 ዓ.ምፀ ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በ13ኛ መደበኛ ስብሰባውፀ ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን አፅድቋል፡፡ በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዹሕግና ፍትህ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ  ሪፖርት እና ዚውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ ሹቂቅ ሕጉ በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሥርዓት ዹወንጀል ፍርድ ሂደት ዚተጠርጣሪን እና ዚተኚሳሜን እንዲሁም በወንጀል ምክንያት ዚተጎዱ ሰዎቜን ሰብአዊ መብቶቜ ለማክበርና ለማስኚበር ዹሕግ ዚበላይነት በማስፈን ዚአሰራር ስርዓትን ለመዘርጋት ዚሚያስቜል መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጞዋል፡፡ ዹተቀላጠፈ ዚፍትህ ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል እና ልዩ ዹወንጀል ምርመራ ዘዮን እንዲሁም ለተጎጂዎቜ ካሣ ዚሚኚፈልበትን አግባብ ያካተተ ዓለም አቀፍ መርህን ዹተኹተለ ሹቂቅ ሕግ እንደሆነ ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ  አያይዘው አስሚድተዋል፡፡ ሹቂቅ ሕጉ ኚኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት እና ኢትዮጵያ ኚተቀበለቻ቞ው ዓለም አቀፍ ስምምነቶቜ፣ መርሆቜ እና እሎቶቜ እንዲሁም ኹወንጀል ህጉ ጋር ዚተጣጣመና ዘመናዊ በመሆኑ ጠቀሚ እንደሆነ  ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል፡፡   ሹቂቅ ህጉ በህገ መንግስቱ፣ በወንጀል ሕጉ፣ ዓለም አቀፍ ህጎቜ እና በሌሎቜ አግባብነት ባላ቞ው ህጎቜ ዚተሚጋገጡ ልዩ ትኩሚት ለሚያሻ቞ው ለሎቶቜ፣ ህፃናት እና አካል ጉዳተኞቜ ዚተሰጣ቞ውን መብቶቜ ለማሚጋገጥ ዚሚያስቜል እንደሆነም ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ገልጞዋል፡፡ ዹምክር ቀት አባላት በበኩላ቞ው ሹቂቅ አዋጁ ሹጅም ጊዜ ዹቆዹና ዹዘገዹ ቢሆንም በህዝቡ ዘንድ ዚቅሬታ ምንጭ ዚነበሩ ቜግሮቜን ለመፍታት ወቅቱን ዚሚመጥን አዋጅ በመሆኑ ዚህዝብን ዚፍትህ ሥርዓቱን ለማስፈን እንደሚያግዝ ገልጞዋል፡፡ ዚዜጎቜን ሰብአዊ እና ዲሞክራሲአዊ መብቶቜን ለማስኚበር እና ዚፍትህ ሥርዓቱን በማዘመን ወቅቱን ያዋጅ አግልግሎት ለመስጠት ሹቂቅ አዋጁ ሚናው ዹጎላ መሆኑን ዹምክር ቀት አባላት አመላክተዋል፡፡፡ በሌላ በኩል ዹምክር ቀት አባላት በበኩላ቞ውፀ ሹቂቅ አዋጁ በአተገባበር ሂደት ላይ ሊያጋጥሙ ዚሚቜሉ ቜግሮቜን ታሳቢ በማድሚግ ኚፍትህ አካላት ጋር መወያዚት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ ኚምርመራ ሂደት እና ኚዲጂታል አሰራሮቜ ጋር በተያያዘ ዜጎቜን ህገ መንግስታዊ መብትን በጠበቀ መልኩ መሆን እንዳለበት ዹምክር ቀት አባላቱ አስገንዝበውፀ በማሚሚያ ቀት ቆይተው ፍርድ ቀት ነፃ ዹሚላቾው ዜጎቜ ዚካሳ ክፍያ ሥርዓትን ለመዘርጋት በግልጜ በሹቂቅ አዋጁ ማስቀመጥ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ምክር ቀቱፀ ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅ ፀ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 አድሚጎ በሁለት ተቃውሞፀ በአብላጫ ድምጜ አጜድቋል፡፡ (በ-መኩሪያ ፈንታ)

ዚህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል --------------------- (ዜና ፓርላማ) መጋቢት 24፣ 2018 ዓ.ምፀ 6ኛው ዚኢፌዎሪ ሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በ5ኛ ዓመ
ዚህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል --------------------- (ዜና ፓርላማ) መጋቢት 24፣ 2018 ዓ.ምፀ 6ኛው ዚኢፌዎሪ ሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በ5ኛ ዓመት ዚስራ ዘመኑ 13ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል። ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና ዚማስሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ዹሕግና ፍትህ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ሪፖርት እና ዚውሳኔ ሀሳብ በንባብ እያቀሚቡ ይገኛሉ። ሹቂቅ አዋጁን ለማዳበር በርካት ባለድርሻ አካላትን፣ ዹዘርፋ ምሁራንንና ዚሥራ ኃላፊዎቜን በማሳተፍ ሰፊ ውይይት በማድሚግ ጠቃሚ ግብአት መገኘት መቻሉን ዚተኚበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ አስሚድተዋል። ምክር ቀቱ እያካሄደው ባለው መደበኛ ስብሰባው ዚቀሚበለትን ሹቂቅ አዋጅ መርምሮ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። © : HPR

new criminal procedure and evidence code Draft .pdf3.62 MB