uk
Feedback
AMAN አማን

AMAN አማን

Відкрити в Telegram
1 127
Підписники
+124 години
+37 днів
-3230 днів
Архів дописів
" ወደ አላህ መመለስ ተውበት ባይሮር ኖሮ ምን ይውጠን ነበር !? " 🎤selu

☆Anahira☆             🎀 ክፍል 29 ☆ ዛሬ የምነግራችሁን አታምኑም አቲካ ቁርዐን አኸተመች በመስጂዱ ጓደኞቿ ስጦታ ተበርክቶላት ብዙ ራሷን የምትቀይርባቸው ሁኔታዎች ተፈጥረውላታል የሴቶቹ አሚር የሆነችውም ኸልዋ ቤት መጥታ ስንጫወት አርፍደን አንድ ሃሳብ ነገረችን ከአቲካ ጋር ወደ ኒውዮርክ ስለመሄድ አቲካም ትንሽ ካቅማማች በኋላ እሺ አለች ኒውዮርክ ውስጥ የአባቷ ሁለተኛ ሚስት አለች የእንጀራ እናትን ያህል አይደለችም መውለድ ስለማትችል ብቻ ወንዶች እየፈቷት ተቸግራ አባቷ ኸሊል አግብቷት ኑሮዋን እዛ ቀልሳለች ከኸልዋም ጋር በጣም ስለሚዋደዱ የእሷንም ብቸኝነት እንደሚያስለቅቁት አያይዛ ነገረቻት እና የተስማማችውም ለዚህ ነው እነዚህን እና መሰል ሃሳቦችን እያነሳን ስንወያይ አርፍደን ኸልዋ ነገ እንደሚሄዱ ትርናገረች ፍጥነቷ እየገረመኝ ነበር አቲካ መቼም እሺ እንደማትላት እያሰብኩ <<ግን አልፈጠናችሁም? አቲካ አንቺስ ምን አሰብሽ?>> አልኳት ጭራሽ የአቲካ ሃሳብ እንደነበር ስትነግረኝ በጣም ከፋኝ ""ለምን? የጠላችን መሰለኝ ባዕድነቷን እያንፀባረቀችም እንደሆነ ተሰማኝ አላውቅም ብቻ መጥፎ ሃሳቦች በእኔ ላይ ተዥጎደጎዱ በዛ ላይ እርግዝናዬ ፈታኝ ሁኔታ ላይ ወድቋል አግዝሻለሁ ብላኝ ነው የመጣችው አሁን ግን ትታኝ ልትሄድ ነው?"" በጣም ከፋኝ ከምነግራችሁ በላይ ያለችውን ሁሉ ሳልቃወም እሺ ብዬ አለፍኩት እና ምሽት ላይ ልብሶቿን አብረን ስናስተካክል ቆየን እራትም በልተን ለመኝታ ስንሰነባበት አቲካ ወረቀቶች ላይ መፃፍ ጀመረች <<ምንድነው?>> ስላት <<የስንብት ደብዳቤ ነው>> <<ለማነው የምትፅፊው?>> <<ለሁላችሁም>> <<እሺ በቃ ፃፊ አልረብሽሽም ብያት ወጣሁ>> <<ታውቃለህ? ምንም ሳትነግረኝ ነገሮች በሙሉ እንዲህ መሆናቸው አሳዘነኝ አብረን አድገን አብረን ኖረን አንድ ቤት ተወልደን እንዲህ መራራቃችን ፣ እዚህ ከመጣች እኮ ኡሚን በራሱ ለማየት ሄዳ አታውቅም ይህን ሁሉ እንድታደርግ እንድትጠላን የሚያደርግ ምን ብናደርጋት ነው?>> ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ <<በመስለሟ ደስ ብሎኝ ሳለ ግን ሌላ ሰው መሆኗን መቀበል በቅቶኛል ኢርቫ ፣ የበፊቷን አትሮን ነው የምፈልጋት አንዳንድ ጊዜ በቶሎ መቀበሏን ቁርዐን አኽትማ አቂዳ መማሯ በራሱ በእልህ ነው የሚመስለኝ>> <<በቃ…… በቃ አንዳንድ ጊዜ የጠበቅነው ሌላ የሚገጥመን ደግሞ ፍፁም ካሰብነው ተቃራኒ ይሆንብናል ያ ማለት ደግሞ አላህ ተሳስቶ ሳይሆን የማናውቀውን ብዙ ነገር አላህ ሊያሳየን ስለሚፈልግ ነው እንደዛ ለማሰብ ብንሞክርስ?>> <<እ……አዎ ልክ ነህ ግን መልመድ ይከብዳል ብቻ አልሃምዱሊላህ ከእንቅልፍህ ላይ ረበሽኩህ አይደል?>> <<ኧረ አንቺ በራሱ በሌሊት መነሳትሽ  ታመሽ መስሎኝ ነው ደህና ከሆንሽ በቃ እንተኛ ነገ አቲካን ለመሸኘት በጠዋት መነሳት ሳይኖርብን አይቀርም>> አለኝ እሺ ብዬው ወደ አልጋ ተመለስኩ ሌሊቱም በእንደዚህ መንገድ ማለፍ ጀምሯል አትሮኖስ የአሁኗ አቲካ የሁሉንም የስንብት ደብዳቤ በመረጠቻቸው ቃላት አስፍራ ስትጨርስ ለኢነብ የምትፅፈውን ደብዳቤ መጀመር ተሳናት ቢሆንም የቻለችውን ያህል ጉንጮቿ በእንባ እየታጠቡ ትፅፍ ጀመር እንዲህ ይላል ᚜᚜᚜᚜᚜᚜᚜ከመሄዴ በፊት ላይህ ባለመቻሌ አዝናለሁ ግን በአጋጣሚዎች ሳይሆን በራሴ ነ የማዝነው የማዝነው በሃያዕ አልባው ልቤ ነው ሽሽት ምንድነው ፍርሃት ነው እንዴ? ወይም የሰዎችን ደስታ ላለመንጠቅ ነው አይደል? የእኔ ሽሽት ግን ሁለቱንም ነው አንድ በጌታዬ ፍራቻ ሁለት ደግሞ ያንተንም ህይወት በእኔ ተራ ስሜት ላለማበላሸት ኢነብ አሁን ስለምለው ነገር እንዴት ሊሆን ቻለ? እንደምትል ይገባኛል ግን እኔም ምን እንደተፈጠረ አላውቅም የማውቀው ነገር በኒሳዕ ቦታ እኔ መሆን እንደምፈልግ ብቻ ነው ስሟን ስሠማ የማላውቀው ጭካኔ እና ፀፀት ውስጥ እንደምገባ ነው ለምን አሳልፌ እንደሰጠሁህ አላውቅም ምናልባት ወረቀት ላይ እየፃፍኩት ያለውን ነገር በአካል ብነግርህ የስድብ አይነት አውርደህብኛል አዎ ስድብ ስድብ ይገባኛል ለዚህ ተግባሬ አይደለም ስድብ ምንም ይገባኛል ይህን መናገሬ ትርጉም እንደሌለው አውቃለሁ ግን ከምሄድበት ቦታ ተቀይሬ እንደምመለስ ስነግርህ ቃሌ ነው᚛᚛᚛᚛᚛᚛᚛᚛᚛ አትሮኖስ(አቲካ) ብላ ፃፈችበት ቀጥላ ደግሞ ለብቸኛ እህቷ የይቅርታ እና የሆነችውን ነገር አይን አይኗን እያየች ልትነግራት እንዳልቻለች ሁሉንም በደብዳቤው ላይ አሰፈረችው ያፈቀርኩት ወንድምሽን ነበር ግን አትዘኚብኝ ይህ እንዲሆን እኔም አልፈለግኩም᚛᚛᚛᚛᚛᚛ <<……አዎ ሁሉም ደብዳቤ ላይ ስም ፅፌያለሁ ስለዚህ ለመስጠት አትቸገሪም>> <<መርሃባ አንቺ እንዳልሽ እና በቃ እነ ኡሚን ሳትሰናበቺ ነው የምትሄጂው?>> <<ነገርኩሽ ሚኑ ብዙ አልቆይም አንድ ሶስት ወር ጊዜ ነው ስለዚህ ቶሎ እመለሳለሁ አቢን ባየው ደስ ይለኝ ነበር ግን አልሆነም ደብዳቤው በቂ ሆኖ ስለታየኝ ነው>> <<እሺ አንቺ እንዳልሽ ግን ደውዪልኝ እሺ ሶስት ወር እኮ ብዙ ነው እኔ እስከዛ እወልዳለሁ ምናምን ግን አንቺ እያለሽ ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር>> <<በቃ ቻው ወሰላሟለይኪ ስደርስ እደውልልሻለሁ>> ብላኝ ተሰነባበትን ኸልዋም እንዲሁ ወላጆቿን ተሰናብታለች ሁለቱም ሻንጣቸውን ይዘው ለፓስፖርት ማረጋገጫ  ተሰለፉ እዛም የሚጠበቅባቸውን ጨርሰው ከአይናችን ሲሰወሩ ከአየር ማረፊያው እኛም ወጥተን ወደ ቤት ጉዞ ጀመርን ድጋሚ ወደ ባዶው እና ሰው ወደ ተራበው ቤት እየሄድን ነው ከፋኝ በቃ አስጠላኝ በዚህ መሃል ነበር ስልኬ የጠራው ኡሚ ናት ድምፄን እያስተካከልኩ ሳነሳው <<አባትሽ መጥቷል>> አለቺኝ እንደተናደደች በሚያሳብቅ ልሳን ቁና ቁና እየተነፈሰች ወዲያው ስልኩ ተዘጋ <<ኡሚ ናት …………አቢ እና አባቴ ተመለሱ ነው የምትለኝ ወደ ዛ ንዳው በቃ>> አልኩት ለኢርቫ እና የሰጠቺኝን ደብዳቤዎች መጠን እያየሁ ነበር ድንገት የኢነብ ስምን ሳይ ለእሱ ከቻው ውጪ ምንም ልትፅፍለት አትችልም አልኩ በልቤ ወደ ቦርሳዬ እየከተትኳቸው        20🥰ይቀጥላል

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 سورة الطور وآصْبِِرْ لحكم ربك فااِنك بأعيننا وسبح بحمد ربك حین تقوم 48:ለጌታህ ፍርድም ታገስ።አንተ በጥበቃችን ውስጥ ነህና።ጌታህንም በምትነሳ ጊዜም ከማመስገን ጋር አወድሰው። ማክሰኞ 5/1/2019 ✨መልካም ቀን✨

አዝነን ለቀናቸው ስንዝል ጠብቀው ለጣሉን ስንፈልጋቸው ፈላጊ አጥተን ለመሰላቸው አሳቢ መስለው እጦታችንን ለሚያጎሉ ስንንገዳገድ አይተው እናሲዝ ይወድቃል ብለው ለሚቆምሩ...... ድንበራቸውን ከልለው ድንበራችን ውስጥ ዘው ለሚሉ ..... የልባችንን ስናወጋቸው ሸፈፍ አድርገው ለሚሰሙ ....  ስለመልካምነታቸው ሲነግሩን እንባ ለሚቀድማቸው ..... ለነሱ ሁሉ ልቦና ይስጥልን

ታሪክ መነሻን እንጂ መድረሻን አይወሰንም!

☆Anahira☆      🎀 ክፍል 28 ☆ እንዴት እንደተናደድኩ አታውቁም <<ማለት?>> አልኩት <<ማለትማ ደረጃ ስትወርጂ ስትወጪ አስተውለሽዋል? እንዴት እንደምትንደረደሪ ቀስ አትዪም ያንን እያየሁ አንቺ በሰላም ትውያለሽ ማለት አልችልም ስራ ስሠራ ስራ አይደለም የምሰራው የተበታተነ ሃሳብ ይዤ>> እንደዛ ሲል በትንሹም ቢሆን ተረጋጋሁ እና ተሳስቀን ምግቡ ቀርቦ በላን             ֎         ֍          ֎ አመሻሽ ላይ ለኡሚ ደወልኩላት እና አቲካ እኔ ቤት መሆኗን ጠዋት በመውጣቷ እንዳይደናገጡ ነገርኳት በዛሬው ውሎ ሁለቱ እናቶች በልጆቻቸው ተስማምተዋል የኒሳዕም እናት ከዛሬ ጀምሮ ለኒሳዕ የሚመጡ የጋብቻ ጥያቄዎችን በር ለመዝጋት ተስማምታለች ሸውዓን ሲመጣ ሁሉም ነገር ሊስተካከል እንደሚችል በራሳቸው ግን ይህን ከወሰኑ ጥሩ እንደሆነ አስበዋል ኢነብም ኒሳዕ የግሉ ትሁን እንጂ የዛሬ አመትም ቢባል ይጠብቃታል የኢሻን አዛን ሙዐዚኑ አሰምቶ እንዳበቃ ተሰገደ እና እንደተለመደው ኢነብ ወደ ቤት ይመለሳል ምክንያቱን ባያውቅም ገና ከመኪናው እንደወረደ የእህቱ እና የአትሮኖስ የነበረውን ክፍል ሽቅብ ቃኘው ሁል ጊዜም ቢሆን እሱ እና ጌታው ብቻ የሚያውቁት አንድ ትዕይንት አለ ዛሬ ግን ያ ! ነገር ያለ አይመስልም ባልተለመደ ሁኔታ መብራቱ ጠፍቶ ጨልሟል ሌላ ጊዜ ይበራ ነበር ከመብራትም አልፎ አንዳንድ ጊዜ በመስኮቱ መጋረጃ ላይ ጥላ ይታያል የአትሮኖስ ጥላ ዞማ ፀጉሯን ስታበጥር ነው ረጅም መሆኑን እና ቀልብ እንደሚሰርቅ ያወቀው በሁለት አጋጣሚ ነው አንድ በር ሳያንኳኳ ክፍላቸው የገባ ቀን ሁለት  በታካሚዋ አደጋ ከደረሰባት በኋላ ከሁለቱ አጋጣሚዎች በኋላ ሁል ጊዜም ከመስጂድ ሲመለስ ፀጉሯን ስታበጥር በመስታወቱ ላይ ባረፈው የመጋረጃ ጥላ ይታያል ይህን ነገር ሳያስበው ነው በመጀመሪያ ሰሞን ሊሰድባት በራሱ ያስባል እያለ እያለ የለመደው ይመስላል ከመናገር ይልቅ ሽቅብ ማየትን መረጠ ሱጁድ በወረደ ቁጥር ለጌታው እንዲምረው ይማፀናል እና እንደለመደውም ያወቀው ዛሬን ቅር ሲሰኝ ነው <<አስተغፊሩላህ>> አለ አይኖቹን እያሻሸ ምን <<እየሆንኩ ነው? ኢላሂ ማረኝ>> የመኪናውን ቁልፍ እና ሶስት ኪታቦችን ይዞ ወደ ውስጥ ዘለቀ እናቱ በሳሎኑ መጅሊስ ላይ ቀን ስለሰራችው ጀብድ ልትነግረው ትስተካከላለች ይህ ከመሆኑ ከሽርፍራፊ ደቂቃዎች በፊት ግን አያቱ <<ሙኒራ ቆይ ትላንት አስቀይመናታል እንዴ? ሄደች እኮ>> ብላ የአትሮኖስን መሄድ አረዳችው <<ማለት ሄደች ማለት ማናት የሄደችው?>> አለ አያቱም <<ካፊሯ ልጅ እህትህ ጋር እንደምትቆይ እና ከእንግዲህ እንደማትመለስ ሰማሁ እህትህ የተፈጠረውን ስላላወቀች ከዚህ በኋላ አብራኝ ትሁን ነው ያለችው ግን ቅር ተሰኝታብን ይሁን? የቲም ስለሆነች ውስጤ ይገላበጣል>> አለችው ለምን እንደሆነ ባያውቅም በነገረችው ቅፅበት የማያውቀው እና በድጋሚ እንዲሰማው የማይፈልገው ስሜት ተሰማው አናደደው በቃ ከፋው ጥፋ ጥፋ አሰኘው ግን ያንን ደግሞ ለማንም ማሳየት አልፈልገም ሙኒራም ልትነግረው እያሰበች <<እራት ቀርቧል>> ብትለውም የምግብ ፍላጐቱ ቀድሞውኑ ተዘግቶበት ስለሆነ ትቶ ወደ ክፍሉ ገባ ሙኒራም ነገ ይደርሳል በሚል ችላ አለችው ኢነብ ክፍሉ ከገባ በኋላ ለሴት እንደ ሴት አነባ የጮኸባት አጋጣሚ ሁሉ እንደየ አጋጣሚው መጥቶ ትውስታ አዥጎደጎደበት ትውስታ ክፉ ነው መታከም እና መዳን የማትችለውን ቁስል የማስታመምን ያህል ነው ስልኩን አውጥቶ ደወለላት ለማንሳት ትንሽ ብትዘገይም ማንሳቷ ግን አልቀረም አቅም ማጣቱን እየደበቀ <<ደግሞ በራስሽ ጥፋት ከቤት ስትወጪ አታፍሪም? ማን ጠጪ አለሽ?>> እንደለመደው ተቆጥቷት መልሷን መጠበቅ ያዘ የእሷም ድምፅ እየተዘጋጋ ነው <<እ…… አይ ለዛ ብዬ እንኳን አልነበረም ከዚህ በኋላ የሚንሃ እርግዝና አስቸጋሪ ስለሚሆን ላግዛት ይገባል ብዬ ነው እና እስከምትወልድ ድረስ እዚህ ከእሷ ጋር ለመቆየት ወስኛለሁ>> አለችው የሚለው ግራ ስለገባው <<እ……? ጥሩ ነው በቃ እኔ በዛ ጉዳይ የሄድሽ መስሎኝ ነው እንደዛ ከሆነ ጥሩ እ……ቻው>> ብሏት መልሷን ሳይጠብቅ ዘጋው እና አልጋው ላይ ተዘረረ እህቱ ጋር ናት ግን ለምን እንደከፋው በራሱ አልገባውም በታካሚዋ አደጋ ከደረሰባት ወዲህ ስራ በሚያደርሳት ሰዓት ፊት እና ኋላ ይሂዱ እንጂ በፊት መስታውት አሻግሮ እያያት መሄዱን አይክድም ስልኳ ላይ ተደፍታ አነቃቂ ንግግሮችን ትሰማለች ፈገግ ስትል ጉንጮቿ ስርጉድ የሚሉት ነገር አብሯት ፈገግ ብሎ መልሶ እስቲغፋር የሚያደርገውን ነገር ከፊቱ ማስወገድ አቃተው ሸውዓን ለሄደበት መመለሻ ጊዜ ከሁለት ሳምንትም አልፎ ሁለት ወራትን አስቃኘ በዚህ መሃል ደግሞ የኢነብም ኒሳዕን የመመኘት ስሜት በአትሮኖስ ተተክቶ መከነ ከአይኑ ሲያጣት ልቡ ደግሞ እሷን ሻተች የራሱ ስሜት ለራሱ ግራ ገባው እህቴን ልያት በሚል ሰበብ ሊያያት በሄደባቸው ቀናት ሁሉ አትሮኖስ የአሁኗ አቲካ የለችም ሊደውል ስልኩን አውጥቶ ምን እንደሚላት እና የሚደውልበት ምክንያት ያጣል ኢነብ ታሟል የታመመው ግን ልቡ ነው በነጋ በመሸ ቁጥር ለቅሶው ወደ ጌታው ሆነ ሙኒራ ለይል ለመስገድ በነቃችበት ጊዜ የሱን ክፍል ጎበኘችው መስገጃው ላይ ይንሰቀሰቃል የዚህ ሁሉ ምክንያት ደግሞ ኒሳዕ ናት ብላ ስላሰበች ያለወትሮው በምትወደው ባሏ ላይ መናደድ ጀምራለች <<ቆይ የሄድክበት ጉዳይ ከኢነብ ከልጅህ ይበልጥብሃል ጠዋት እና ማታ እያለቀሰ ነው እባክህ መጥተህ አንድ በለው>> የዚህን ያህል ነው ብሎ ሸውዓን ለመምጣት ወሰነ ከጓደኛው መርዋን ጋር ኒሳዕ ደግሞ  ከዛሬ ነገ አባቱ መጥቶ ኒካህ ያስርልናል እያለች በተስፋ ባከነች <<ቆይ ኒሳዕ ልጁ አይፈልግሽም እንዴ? ሁለት ሳምንት ታገሱኝ ብሎ ስንት ወንድ አስከልክሎሽ ሲያበቃ ቆመሽ እንድትቀሪ ነው እንዴ የሚፈልገው?………ቆይ አላህን አይፈራም?>> አለች እናቷ ነበረች ከጎረቤቷ እኩያዋ ጋር ተቀምጠው ቡና ይጠጣሉ <<እናቴ አባቱ ካልመጣ ምን ማድረግ ይችላል እስኪ እንታገስ የሚሆነውን አላህ ያውቃል>> አለቻት አሁንም ተስፋ አላት 25😭🥰 ይቀጥላል ☆ ☆ ☆ . . . . . . . . .

♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️ ኢማም ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡- አላህን ከማውሳት የሚርቅ ሰው ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በመጨረሻዋ ዓለም፣ በቀብር ውስጥ፣ በቂያማ ቀን የተጣበብ አስቸጋሪ ህይወትን  ይኖራል። ሰኞ 4/1/2019 💐የብስራት ለይል ይሁንላችሁ 💐

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 8:ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን? 9:ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም። ሰኞ 4/1/2019 ✨መልካም ቀን ተመኘሁላችሁ✨

☆Anahira☆ 🎀ክፍል 27 ☆የሆነ ልትነግረኝ ያሰበችው ነገር እንዳለ ያስታውቅ ነበር ሁለታችንም ለረጅም ምክንያት አልባ ደቂቃዎች ዝም ተባባልን እና በስተመጨረሻ አትሮኖስ ለጆሮዬ የማይታመን ነገር ተናገረች <<እስልምናን ልቀበል ነው ግን ትላንት ከነገርኩሽ ሰው ጋር እንዳታያይዢው ይህን የማደርገው በራሴ ፍላጐት እና ሃሳብ ነው እና ዛሬ መስጂድ እንሄዳለን?>> አለቺኝ እኔ መጀመሪያ ያለችውን ባለማመን አይኔን እጨፍናለሁ እገልጣለሁ <<ምነው? መሆን አልችልም እንዴ? ማለት የሚጠይቀው መስፈርት አለ?>> <<አይ ያልሽውን ባለማመን ነው ግን እርግጠኛ ነሽ አይደል? መወላወል የተጠላ ስለሆነ ወደ ነበርሽበት ላትመለሺ ማመን አለብሽ>> <<ነገርኩሽ እኮ አልመለስም እስከ መጨረሻው ለመቆየት ወስኛለሁ ማለትም እስከ ሞት ድረስ>> አላመንኩም ነበር ተነስቼ አቀፍኳት እንባ ተናነቀኝ በስተመጨረሻ አልኩ በልቤ <<ካመንሽበት ደስ ብሎኛል እና እነኡሚ አውቀዋል?>> ስላት <<አይ አልነገርኳቸውም ይህን ሃሳብ መጀመሪያ የሰማሽው አንቺ ነሽ ቅር ካላለሽ እዚህ አብሬሽ ማሳለፍ ነው የምፈልገው ከዚህ በኋላ እርግዝናሽም ከባድ ሊሆን ስለሚችል እንድረዳሽ አትፈልጊም?>> አለቺኝ እንደ እውነቱ ኢርቫንን ላለማስቸገር ነው እንጂ ቤት ብቻዬን መዋል ሰልችቶኝ ነበር ኡሚ ጋርም ልሂድ እያልኩ እሱን ማሰልቸት ከብዶኝ ነበር ደስ አለኝ <<እሺ ችግር የለውም እንደውም በጣም ደስ ይለኛል ግን ለምን ለኡሚ አልነገርሻትም?>> <<ስላልፈለግኩ አንቺ ካወቅሽ ይበቃል ለአቢ ልነግረው አስቤ ነበር ግን ተቀይሬ ቢያንስ አንዳንድ ነገሮችን ይበልጥ ካወቅኩ በኋላ ልነግረው እና ላስደስተው ፈልጌ ነው>> <<እሺ በቃ ያም ሆነ ይህ ደስ ብሎኛል ስራሽስ?>> <<ስራ ደግሞ ለአመት ረፍት ፈቃድ ጠይቄያለሁ ማለት ሃይማኖቴ ላይ በደንብ መጠንከር እፈልጋለሁ ከዛ በኋላ ወደ ስራዬ እመለሳለሁ>> <<መርሃባ በጣም ቆንጆ ሃሳብ ነው በቃ ዛሬ ወደ መስጂድ እንሄዳለን>> ተባብለን አንዳንድ የቤት ውስጥ ስራዎችን አከናወንን እስከ 04:00 ድረስ የእሷን መኝታ ክፍል ስናዘጋጅ ቆይተን 04:20 ሲል አባያ ለብሰን ወጣን በዛው በሪልስቴቱ መንደር ውስጥ ባለው መስጂድ ነበር የሄድነው ከኢማሙ ጋር እንዲያገናኙን ጠይቀን ገባን ወዲያው ሸሃዳ ይዛ ተጨማሪ ሃሳቦችን ለግሰዋት አበቃ አትሮኖስ እስልምናን ተቀበለች እንደምታዘልቀው ደግሞ አላህ ብቻ ነው የሚያውቀው ይዤላት የነበረውን አባያ ለበሰች እና ውዱዕ አደረግን ብዙ ነገሮችን አብራን እያለች ስለምታይ አላስቸገራትም እኔንም ማስተማር ትችላለች አይደለም ሌላ ደስ ብሎኝ ነበር አላህ ዱዓዬን ሰማኝ እያልኩ በውስጤ እንዴት እንዳመሰገንኩት አታውቁም ስሟ በአቢ ጥሪ ተወሰኗል አቲካ ተብላለች  ከኹጥባ በኋላ ጁምዓን በጀመዓ ሰግደን ወደ ቤት መጣን ከዛ በፊት ግን የኢማሙ ሴት ልጅ አሁን መስለሟን ስታውቅ በዛው መስጂድ ውስጥ ከአሱር እስከ መغሪብ በሴቶች በኩል እሷ እንደምታስቀራ እና ከአቂዳ እስከ ሂፍዝ እንደምታስተምራት ቃል ገባችላት በዚህም አትሮን ደስ ብሏት ነበር አትሮን በቃ አንበላት ከአሁን በኋላ አቲካ እንበላት እና አቲካ በጣም ደስ አላት ዛሬውኑ ልትጀምር እንደምትችል ነገረቻት እና ወደ ቤት ሄድን ቤት እንደ ደርሰን  ኢርቫ ደወለ <<አዚዘቲ እ……ስራ የለም እና አሁንም ኡሚ ጋር ነሽ እንዴ? ልምጣ ቤት ብቻዬን ከምሆን>> አለኝ የደስታ ሳቅ እየተናነቀኝ <<እ…… አዎ እዛው ነኝ ግን እንዳትመጣ ማለት እንድትመጣ  አልፈለግኩም ቀጥታ ወደ ቤት ሂድ>> ቅር እንዳለው በሚያስታውቅ ድምፅ <<……ኧ…… እሺ በቃ እንድገኝ ካልፈለግሽ እሺ>> አለኝ እና ዘጋው አሳዝኖኛል ግን አውቄ ነው ሙፋጃዓ ላደርገው ነው ከአትሮን ጋር ቤቱን ከሌላ ቀን በተለየ አስዋብነው ብርያኒ ሰራን ብርያኒ ማለት(የበግ ስጋ ለብቻው ከገበታ ግብዓቶች ጋር እንደሽንኩርት ፣ ድንች ፣ ካሮት ፣ ቲማቲም የመሳሰሉት ጋር አብሮ ያለ ውሃ በስሎ ሩዝ እንደዛው ተሰርቶ የሚበላበት መንገድ ነው የመካከለኛው እስያ እና በተለይ ህንድ መደበኛ ምግብ ነው) እሱን ሰርተን እና በሩን ዘግተን ጠበቅነው  የመኪናውን ድምፅ ስሠማ በመስኮት አየሁት ፊቱ የነሃሴን ሰማይ መስሏል በጣም በተሰላቸ መንፈስ የቤቱን በር ቁልፍ አውጥቶ ሲከፍተው ከውስጥ በኩል ጠበቅኩት ሲያየኝ አላመነኝም እንደተለመደው ሰላምታችን ተቃቀፍን እና <<እንዴ? እንዴት መጣሽ?>> <<ሲጀመር አልሄድኩም ነበር>> <<ኦህ ደስ ሲል እኔ እኮ ብቻዬን እንደምውል ሳስብ አልቅስ አልቅስ እያለኝ ነው የመጣሁት ደግሞ ጨክነሽ አትምጣ ማለትሽ በራሱ ከፍቶኝ ነበር>> <<እኔማ ብትሄድ እንደምታጣኝ አስቤ ነው>> ይህን ተባብለን ጫማውን እያወለቀ ነበር ሲጨርስ <<ዛሬ ስራ የለም ፣ የተጋበዝኩበትም ምሳ የለም ፣ ማለትም ካንቺ ጋር ነኝ ማለት ነው እና የሆነ ነገር አስቤያለሁ ዶክተሯ ከ6 ወር በፊት ምንም ማድረግ ይቻላል ብላን የለ?>> <<ብላለች እሱማ እኔን ደግሞ ስማኝ ያሰብከውን በሚያሳዝን ሁኔታ ሰርዘው አትሮኖስ አለች ስለዚህ…>> <<እ?…… እሺ እንደዛ ከሆነ የልዕልቷን ሃሳብ መጋፋት አይቻልም አይደል?>> <<እንደዛ አስበው ልዑል ሆይ!>> እየተፎጋገርን ወደ ሳሎን ሄድን አቲካ ተቀምጣ ስልኳን እየነካካች ነበር <<ደህና ዋልሽ አትሮኖስ>> አላት እየተቀመጠ <<ከእንግዲህ አሰላሙ አለይኪ ነው የምትላት አትሮን ሰልማለች>> አልኩት ፈገግ እያለ <<ማሻአላህ እንደዛ አትዪኝም እንዴ ፊትሽ እንደዚህ የበራው ለዛ ነዋ በር ላይ እንደዛ አናግረሺኝ……>> አፍህን ዝጋ አይነት አስተያየት አየሁት መልሶ የጀመረውን ንግግር ተወውና <<እ…… ማነው መብሩክ የእኔ ውድ የሁል ጊዜም ዱዓሽ ነበር እኮ እና እነ ኡሚም መቼስ ተደስተዋል>> <<ኧረ አልነገርናቸውም እኔ እና ሚንሃ ብቻ ነን ያሰብንበት>> አለችው ፈገግታው በትንሹ እየዳመነ <<አ…… አይ ይሁን ብትነግሯቸው ደስ ይላል አቢስ ያውቃል?>> <<እሱን ደግሞ ከሄደበት ሲመለስ ልንነግረው ነው>> <<በጣም ጥሩ ሃሳብ ሚንሃ በራሱ አጫዋች አገኘች ማለት ነው ቤት እሷን ትቶ መሄድ ሃሳብ እየሆነብኝ ነበር ምንም ጥንቃቄ የላትም>>                  15🥰 ይቀጥላል ☆ ☆ ☆

🌴የምሽት ውብ ስንቅ🌴 ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡- በአሁኑ ጊዜ ከነፍሳችን ጋር የሚደረግ ትልቅ ጂሃድ ያስፈልገናል። ምክንያቱም ልባችን ታሟል። አካላችን ከበጎነት ታክቷል። ልቦቻችን የእርስ በርስ ግጭት ውስጥ ናቸው!። እሁድ 3/1/2019 🌴የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ🌴

ሁሉም ይሄድና ለነሱ ብለክ የገደልካት ነብስ ብቻ ትቀራለች😔

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 አልሃምዱሊላህ በኸይር አነጋን በችሮታው ከተኛንበት አነቃን እሁድ 3/1/2019 ✨መልካም ቀን✨

♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️ ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለሁት ብለህ አትዘናጋ፡፡ ከጀነት የበለጠ ጥሩ ቦታ የለም፡፡ አባታችን አደም ዐ.ሰ በሷ ዉስጥ ሆነው ጭምር ፈተና አግኝቷቸዋል። በዒባዳህ ብዛትም አትጃጃል፣ ኢብሊስ ከዚያ ረጅም የዒባዳ ሕይወት በኋላ ምን እንዳጋጠመው ይታወቃል፡፡ በዕውቀት አለኝ ብለህም አትመፀደቅ፤ በልዓም  የአላህን ታላቅ ሥም ያውቅ ነበር። ነገር ግን መጨረሻ ላይ ምን እንዳጋጠመው አስተዉል። ደጋጎችን አይቻለሁ ብለህም አትጃጃል፤ ከአላህ መልዕክተኛ በላይ አላህ ዘንድ ትልቅ ደረጃ ያለው አልነበረም፤ የቅርብ ዘመዶቻቸውም ሆነ ጠላቶቻቸው አልተጠቀሙባቸውም። ቅዳሜ 2/1/2019 💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 ቁርዓን የልብ ብርሀን የሕይወታችን ብቸኛው መመሪያ ቀናችንን በቁርዓን አላህን በማውሳት እንጀምረው። ቅዳሜ 2/1/2019 ✨መልካም ቀን✨

🌴የምሽት ውብ ስንቅ🌴 ከትዳር በፊት ፍቅር የለም ብዬ የኸዲጃን ፍቅር ገደል አልከተውም… ምክንያቱ ምንም ይሁን አፍቅራ እንዳገባቻቸው አልጠራጠርም… በሪራ በሚሏት ሰሓቢት ፍቅር ተለክፎ በመዲና መንገዶች ላይ ከኋላዋ እየተከተለ…  የእንባ ቋንጣውን በመዲና አድማስ  ሲወረውር የነበረውን ሰሓባው ሙጊስ … አፍቃሪ አልነበርክም ልለው አልችልም… ቀድመው ቢለያዩና ከዚያ በኋላ ባያገባትም “ሙጊስ ለበሪራ ባለው ፍቅር፣ በሪራ ደግሞ ለሙግስ ባላት ጥላቻ አልተገረምክም ወይ” የተባለለት አፍቃሪ ነው… ያውም በረሱል አንደበት። አንድ ነገር ግን አምናለሁ… ፍቅር በስሙ የሚደረጉ ኃጥያቶችን እንደማያውቃቸውና  የአፍቃሪ መድሀኒቱም ትዳር እንደሆነ…  ማንነትህን ፣ እምነትህንና ጉዞህን የሚያመክንብህ ከሆነ በሽታ እንደሆነ… አምናለሁ። ነብይህ “ለተዋደዱ ሰዎች ከኒካህ ውጪ (አማራጭ) አላየሁም” ሲሉም… ከትዳር በፊት መዋደድ እንዳለና ኒካህ ካልታከለበት ግን የኪሳራ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ነው… አፍቅርሃል? በበር በኩል ና በቃ … በፍቅር ስም ሙድ አትያዝ! ጁሙዓ 1/1/2019 🌴የብስራት ለይል ተመኘሁ🌴

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 16:ከጌታችሁም ፀጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? ኢላሂ በየትኛውም ፀጋህ አናስተባብልም! ኢላሂ ኒዕማህን ፀጋህን የምናስተነትን የምናመሰግንበትም አድርገን ያረብ! ጁሙዓ 1/1/2019 ✨መልካም ቀን✨

🌴የምሽት ውብ ስንቅ🌴 ኢማም ኢብኑ ረጀብ አል-ሀንበሊ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡- ደጋግ ሰለፎች ከኃጢአቶቻቸው ማነስ የተነሳ ኃጢአቶቻቸውን ይቆጥሯቸው ነበረ።ሪያህ አል-ቀይሲ እንዲህ አለ፡- ከአርባ በላይ ኃጢአቶች አሉብኝ።ለእያንዳንዳቸው መቶ ሺህ ጊዜ ምህረትን ከአላህ ጠይቄያለሁ። ሀሙስ 5/13/2018 💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐

☹️
☹️

⚠️ መስከረም 1 እና የጿጉሜ በዓል — ሙስሊሙ ይጠንቀቅ! ነገ መስከረም 1 ነው። አንዳንዶችም “አዲስ ዓመት” በሚል ስም ልዩ ዝግጅትና ክብረ በዓል ያደርጋሉ። ነገር ግን ሙስሊሙ ከመከተሉ በፊት ይህ ነገር ከዲናችን ነውን? ብሎ መጠየቅ አለበት። አላህ ﷻ እንዲህ ይላል፦ ﴿إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا﴾ “በአላህ ዘንድ የወራት ቁጥር አሥራ ሁለት ወራት ነው።” 📖 አል-ተውባህ 9፥36 ይህ አያ የሚያሳየን የአላህ የተደነገገው የወራት ቁጥር 12 መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ደግሞ እንደ የዓመት ስሌት መጠቀሙ አንድ ነገር ነው፤ እንደ ዲናዊ በዓል ማክበር ግን ሌላ ነገር ነው። ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ» “በዚህ ጉዳያችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር ያስገባ የተመለሰ ነው።” 📚 ቡኻሪ 2697፣ ሙስሊም 1718 ስለዚህ ጿጉሜን ወይም መስከረም 1ን እንደ ልዩ የሃይማኖት በዓል ማክበር ሲመጣ ሙስሊሙ በጣም መጠንቀቅ አለበት። ወንድሜና እህቴ፣ የሰዎች ልማድ የዲን ማስረጃ አይደለም። “ሁሉም ያከብራል” ብለን እንዳንከተል። “አዲስ ዓመት ነው” ብለንም የዲናችንን መርህ እንዳንረሳ። ዘመን መቀየሩ ራሱ ችግር አይደለም፤ የዘመን መለወጫን የዲን በዓል አድርጎ ማክበር ነው ሙስሊሙ ሊመረምረው የሚገባው። ⚠️ ሙስሊም ሆይ! በዲንህ ነገር አትቀልድ። በሱናህ አትደራደር። የሰዎችን ልማድ ከአላህ ትእዛዝ በላይ አታድርግ። እውነተኛው ሙስሊም ሰዎችን እንደ ማስረጃ አድርጎ አይዝም “አላህና መልእክተኛው ﷺ ምን አሉ?” ብሎ ይጠይቃል ይማራል እንጅ.! اللهم ثبتنا على التوحيد والسنة، وجنبنا البدع والضلال. آمين.

🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃 Sharif Mustafa - Saba' የሩህ ቀለብ ሀሙስ 5/13/2018 ✨መልካም ቀን✨